en
Feedback
📚 የኛ_ግጥም 📚

📚 የኛ_ግጥም 📚

Open in Telegram

Show more
Ethiopia4 030The category is not specified
6 604
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
"ደግ አይበረክትም" ፡ ፡ ©(አበባው መላኩ) ፡ እስከ:ማዕዜኑ ..እስከ፡ማዕዜኑ አነብር:ውስተ:ልብየ:ትካዘ ዐሊውየ:ሕገ:ወትዕዛዘ: ማርያም:ኩነኒ:መናዝዘ። አቤል: በፀጋ : ርቆ ፣ በየዋህነት:ከመጠቀበት ፣ ቃዬል:በንፍገት:ከብሮ ፣ መቀመቅ:ከወረደበት፣ የዕጓለ መሕያው: ታሪክ ፣ ሲጀመር : የጠቆረበት . እንውረድ:ብሎት:ወንድሙን ፣ እስትንፋሱን:የነጠቀበት ፣ ኃዘና ፣ ስምዒ:ወብካያ ፣ ለሃገሪትነ:ኢትዮጵያ ። የሞት:ታሪክ:ሊዘከር በአዝማናት:ማሀል:ሊነገር የመጀመሪያው:መልአክ ፣ ታሪኩን:ሲፅፈው:እንደዚህ:ነበር። .... ክልዔቱ: አኃው: መንገደ:ቀላይ :ወረዱ፣ እኒህ:ሁለት:ወንድሞች:ወደ:አዘቅት:የሄዱ፣ አንደኛው:ሟች:ሊሆን:ገዳይ:ሊሆን:አንዱ፣ አሃዱ:ተመይጠ፣ ወኢተመይጠ አሃዱ ፣ አንደኛው ሲመለስ ሁለተኛው እዚያው የቀረ፣ ውረድ እንውረድ ያለው ወንድሙ ገድሎት ነበረ። ከዚህ የቀን፡ጎደሎ፡ነው ፣ ከዚህ፡ክህደት፡በኋላ፣ ከተራራው፡አናትና፡ ከግርጌ፡በቆመው፡ማሀል፡ መተማመኑ፡የላላ። የአዳም፡የልጅ፡ልጅ፡ሁሉ ፡ምን፡ቢጀግን፡ምን፡ ቢያቅራራ፣ ምን፡ደግ፡ንግርት፡ቢያስነግር ፣ ምን፡ በማዕረግ፡ቢጠራ ፣ ይገሉኝ፡ይሆን፡እያለ፡ነው ፣ ውረድ፡ሲሉት፡ የሚፈራ ። እናም፡መውረድ፡ሞቱ፡ነው፡ አንዴ፡ደርቡን፡ ከወጣ ፣ ውረድ፡ሲባል፡በመውረዱ፡ነው ፣ ወንድሙ፡ ሕይወቱን፡ያጣ። በርግጥ፡ለምን፡ይወርዳል፡ መውረድስ፡ማንን፡ ጠቀመ ? የወረደውን፡መግደሉ፡ለዘላለሙ፡ካልቆመ ! @getamiyan @getamiyan @getamiyan

( በላይ በቀለ ወያ ) . "በኔ መንገድ ካልሔድክ መንገድህ ገደል ነው" ፣ ማለት የሚከጅል "እንደኔ ካላሰብክ ማሰብ አትችልም" ፣ ሊል የሚዳዳው ጅል በህይወት መንገድ ላይ... እንደራሴ ስጓዝ ፣ ነፍሴ ምትሞግተው ስንት ገደል አለ "ድልድይህ ነኝ" የሚል ፣ መሻገር ሲያቅተው፡፡ @Getamiyan @getamiyan

እንግዲህ ይግረምሽ ፥ አይቀርም ማለቁ ለዚህ ነበር ድሮም ፥ ጉሮሮሽ መድረቁ ጥሬ ቆርጥሞ አደር.... ሲተልም ለሩቁ ሲቆርጥ ቆራጥ ነው...ጦብያዊ ለሀቁ ። ✍ አብርሀም ተክሉ ( መርዕድ) @Abrham
እንግዲህ ይግረምሽ ፥ አይቀርም ማለቁ ለዚህ ነበር ድሮም ፥ ጉሮሮሽ መድረቁ ጥሬ ቆርጥሞ አደር.... ሲተልም ለሩቁ ሲቆርጥ ቆራጥ ነው...ጦብያዊ ለሀቁ ። ✍ አብርሀም ተክሉ ( መርዕድ) @Abrham_teklu

[ሔለን ወንድሙ] ✍@Helen_wd ከእናት ሆድ አልቅሶ ፤ በእልልታ ሲወጣ ምድርን ሲቀላቀል የዚህን ዐለም ጣጣ ለመኖር ሲዋጅር ትንፋሽ ለማቆየት አንዴ ራሱን ሸጦ ምድርን ሊኖርባት አፈር ለሚገባው አፈር መስሎ ሲቀር ለእፎይታ ሲዳክር ለመሞት የሚኖር 100ም ሆነ 50 : የእድሜ አሀዝ ቆጥሮ እፎይ ሳይል ላንዴ እየኖረ ግሮ ነፍሱ በዚያ ስታልፍ...... ዋይ!! ይባልለታል አልቅሶ እንዳልወጣ ስለምን ተወለድኩ ብሎ እንዳልመጣ ::::::: ዋይ! ከንቱዋ አለም ማን ይሆን ዘላቂ ለሞት አየኖርን ሆንን አላዋቂ፡፡ ✍@Helen_wd @Getamiyan @getamiyan

ምን ያደርግልኛል ??? ገልጠሽ ስላየሁት እጄ የነበረን ...በሩቅ ለማተርኩት ምን ያደርግልኛል ያንን እቶን ገላ... በቆፈኔ ወራት...ለብርዴ ካልሞቅኩት ??? ቁር መስመር አልፎ ቁርጥማቴ ሆኖ...አጥንቴን ሲያኝከኝ አንድ አካሌ ርቀሽ አልጋው አንድ ጎኔን ...ለብቻዬ ሲያከኝ አለሁልህ ማለት ...በሌለሽበቱ ኮምፒውተሩን አብራ ፥ ብሎ መጎትጎቱ በይነ መረቡ ላይ... የተገላለጠ.... ምስልሽ መነዛቱ ምን ያደርግልኛል ??? እዚህ ጋ እንድትነካኝ .... ከመቼውም በላይ ከመጓጓት አልፎ ፥ ግለትህ ናፍቆኛል እስከግዜው ድረስ ... በምስለ ቅጂው ላይ ፥ ጅስምህ ይታየኛል ከሰው የሸሸኩት ያንተ ብቻም ስጋ ላንተው ተጠብቆ ፥ አምሮበት ይገኛል ። አየኸው.... ብሎ መሸናገል በገዛ ጣቶችሽ ፥ እያመላከትሽኝ ስሜቴን ማባበል ደብሎ እንደ ሌጣ ፥ለብቻ መታገል ካንቺ ጋ ፋፍሞ ፥ ተናጠል መፈንገል ምን ያደርግልኛል ??? ✍ አብርሀም_ተክሉ ( መርዕድ ) @Abrham_teklu @Abrham_teklu @Getamiyan @getamiyan

የድሌ ቀን ------------- ባልነዘረ ክራር ባልተነፋ እምቢልታ፣ ባልተመታ ታምቡር ባልጮኸ ጡሩንባ፣ አካሌ ሲደንስ እስክስታ ሲመታ። በሌለ ሙዚቃ ብለው ለሚስቁ፣ የድል ቀን ሲመጣ፣ "ሹ.ክ.ሹ.ክ.ታ" እንኳ ቅኝት መሆኑን ባወቁ። =========== የ"10" ሣንቲም እውነት በወንድወሠን ካሣ @getamiyan

።።።። ዋ! ።።።። (በረከት በላይነህ) አይኔ ወደደሽ ስልሽ፣ አይኑን አጥፋው ብለሽ ገባሽ አሉ ስለት ምኞትሽ ሰመረ አይኖቼ ጠፉልሽ ይኸው አንደዘበት። ግን መች ተውሻለው በልቤ ብሩህ አይን ዛሬም አይሻለው። ደሞ አንደዚ ስልሽ አትወጅኝምና ልቡንም አጥፋልኝ ብለሽ ትሳይና ፀሎት ያልቅብሻል እሞትብሽና። @getamiyan @getamiyan @getamiyan

የማርያም ካህን ነኝ!!!!!! ሩጩ ያልጠገብኩ፤ ገና ብላቴና፤ በአባቶቼ ቀለም ፤ ጎጆዬ የቆመ፤ መንገዴ የፀና፤ የማርያም ካህን ነኝ፤ ጠግቤ የማድር ፤ እመ ብርሃን ብዬ፤ በስሟ ጥፍጥና። የአሮንን ጥምጣም፤ የያሬድን ዜማ፤ክህነት ተሸክሜ፤ ማህሌት የምሰሙን፤ ደብር የማቀና፤ በገሞራው ዋድላ፤ በተክሌ ዝማሜ፤ በውዳሴ ማርያም፤ በአንቀፀ ብርሃን፤ ይሽራል ህመሜ። ሸጋው ልጅነቴን፤ ይህ ለጋ ዘመኔን ፤ ሰአሊነ እያልኩኝ፤ የምገብርላት፤ በባዶ እግሬ ሩጩ፤ በውዳሴ ቅኔ የምዘምርላት፤ የጦቢያ ባለርስት፤ ማርያም ናት ማርያም ናት። ((( ጃ ኖ ))) @getamiyan @getamiyan @getamiyan

የፍቅር ፍልስፍና ! ( ገ/ክርስቶስ ደስታ ) .. ጅረቶች ከወንዞች ጋር የሙጥኝ ብለው ተጣምረው፤ ወንዞችም ውቅያኖስ አቅፈው.. የሰማየ ሰማያት ንፋስ ፥ ጣፋጭ ስሜት ሲዋሃደው፤ ተመልከችው ! ከቶ አንድም ነገር.. ባለም ላይ ያለአቻ ያለጓደኛ፤ ሆኖ አይገኝም ብቸኛ። በውስጠ ምስጢር ህላዌው ይጣመራል ሁሉም በውል፤ በአንድ መንፈስ በአንድ ቃና ስጋና ደሙን ሲያዋውል። እኔና አንቺስ ምናለበት ፤ አንድ ብንሆን ብናውቅበት!? እንደመሶብ ከግጣሙ ፤ ተራሮች ሰማይ ሲስሙ፤ ዕይው ጣዕሙን ! ደግሞም የፍቅር ጡር ጣጣ፤ ሴቴ አበባ ያለወንዱ፥አበባነቷ ቅጥ ሲያጣ፤ ወንዴ አበባም ያለሴቷ፥በፀሐይ ሐሩር ሲቀጣ፤ ዕይው ቆንጂት ዕይውማ ፤ ልቦና ፍቅር ሲጠማ። የፀሐይ ብርሀን ጠዋት፥የመሬትን ከንፈር ሲስም፤ በሙቀት እየዳበሰ ፈገግታዋን ሲያለመልም፤ ለዛው ሲፈካ ሲተም። የጨረቃ ጨረር ሞገድ፥የባህርን ራቁት ገላ፤ በምሽት የዕንቅልፍ ሰዐት፥ይደበዝዛል እያጠላ። ስለዚህም አስተውይው፥እኔን ሁኝ አንቺን ልሁን፤ በደም ስርሽ ደሜ ይፍሰስ፥በደም ስሬ ደምሽ ይሁን! አንድ እንሁን !! @getamiyan @getamiyan @getamiyan

ዘመንህ ዘመኔ አፍ ብቻ ቢሆንም ብታምንም ባታምንም አንድ ታሪክ ላውራህ ፣ ጆሮ ስጠኝ ልጄ እንዲህ እንደዛሬው ፣ ኦና ሳይሆን ደጄ እኔው የተከልኩት በለጋነት እድሜው የተንከባከብኩት አድጎ ልክ እንደ አድባር ፣ ሲታይ የነበረ ቅርንጫፉ ሰፍቶ ፣ ግንዱ የወፈረ እዚህ እበሬ ላይ ፣ አንድ ዛፍ ነበረ። ።።። እናምልህ ልጄ እንዲህ እንደዛሬው ፣ ቆሌያችን ሳይርቀን ወበቅ ሳይወብቀን ፣ ድርቅ ሳያደርቀን ንፁ አየር ፍለጋ ፣ ዛፍ ያለበት ሳንሔድ ፣ ቤታችንን ለቀን እዚህ እበሬ ላይ አንድ ችግኝ ነበር ፣ አድጎ የሆነ አድባር ይህንን ዛፍ አይተው እዚ ነው መሸፈት ይል ነበረ ቋምጦ ፣ ምድረ ነፃ ግንባር። ።። እንዲህ እንደዛሬ የወፎች ዝማሬ በሰው ልጆች ጩኸት ፣ ሳይጠፋ ተውጦ ሁሉም ላዚም ሳይል ፣ ማይኩን ጨብጦ ምስኪን ጆሯችንን ፣ የነጠላ ዜማ ፣ዋይታ ሳይጠልዘው እኔና እናትህ ከዛፍ የተቀዳ የወፍ ዜማ ነበር ፣ ምንገባበዘው። ።። እንዲህ እንደዛሬው ዩንበርስቲ በዝቶ ትምህርት ተስፋፍቶ ምሁር ነኝ ባይ ሁላ ፣ እውቀት የቸገረው ከመሆኑ በፊት እዚህ ዛፍ ስር ነበር ፣ ፊደል ሚቆጠረው። ።። እናምልህ ልጄ እንዲህ እንደዛሬው ፣ ፅድቃችን ሳይርቀን ወበቅ ሳይወብቀን ፣ ድርቅ ሳያደርቀን ንፁ አየር ፍለጋ ዛፍ ያለበት ሳንሔድ ፣ ቤታችንን ለቀን አንድ ዛፍ ነበረ ቅርንጫፉ ሰፍቶ ፣ ግንዱ የወፈረ ቅጠሉ የበዛ ፣ ጥላ የሚሰጠኝ እንጃ ብቻ አንድ ቀን ፣ ምን እንዳቀበጠኝ ዛፉ የሚጥለው ጭራሮና ፍሬ ፣ ጣሪያዬ ላይ ወድቆ ፣እያስደነገጠኝ አላስተኛ ብሎ ፣ ስለበጠበጠኝ ቅርንጫፉን ልቆርጥ ፣ ግንዱን መውጣት ጀመርኩ ፣ አንድ ቀን በምሬት ቅርንጫፍ ላይ ሳልደር ድንገት ዛፉ አዳልጦኝ ፣ ወደኩ ወደመሬት። ።።። መቼም ሰው ነኝና ስድስቴ ወድቄ ሰባቴ መነሳት ፣ እንደ ትል አልታደልኩ ዛፉ አንዴ ጣለኝ ፣ ሰባቴ ተሰበርኩ ተሰብሬ አልቀረሁ መታከሚያ ባጣ ዛፉን አስቆርጬ ፣ ሽጬው በሱ ታከምኩ። ።።። እናምልህ ልጄ ዛፉን የገዛኝ ሰው ፣ ጣውላ ቤት ነበረው ካላጣው ቁሳቁስ ፣ ሞያ ሳይቸግረው ባለ ጊዜ ሁሉ እንዲቀመጥበት ፣ በ"ተራበ"ተራ እኔ በሸጥኩት ዛፍ ፣ ግዙፍ ዙፋን ሰራ። የሰራውን ዙፋን ቤተ መንግስት ወስዶ ፣ በስልጣን ለወጠው ፀሐይ መንግስት ሁሉ እዛ ዙፋን ላይ ነው ፣ ህዝቡን ለማቃጠል ፣ ታግሎ ሚቀመጠው። ።።። እናምልህ ልጄ ችግኝ ተክዬ ፣ ግዙፍ ዛፍ አሳደኩ ከዛፍ ላይ ወድቄ ፣ ዛፌን ሽጬ ታከምኩ እኔ ግን ጥላ አጣሁ ፣ ኦና ሆነ ደጄ ለመዳን ዛፍ ስሸጥ ፣ ህመም ገዛው በጄ ከግዜር ፀሐይና ከፀሐይ መንግስታት ፣ ልጠለል የት ሔጄ? ከሁለቱም ፀሐይ ለመዳን ዛፍ ትከል ፣ ዛፍ ጥላ ነው ልጄ። ዛፍ ትንፋሽ ነው ልጄ ዛፍ ዜማ ነው ልጄ ዛፍ ህይወት ነው ልጄ ዛፍ ዙፋን ነው ልጄ ።።።። #አረንጓዴ አሻራ @Getamiyan

#_ት_ዕ_ዝ_ብ_ት በበግ ቅዬ ጋጣ... ቀንድ ከሌላቸው ፥ መሀል የተገኘ ባጋዘን ቅርፅ ራስ ፥ ጌጡ በተቀኘ የሳጥናኤል ጭፍራ ፥ መችና ተሰኘ ? ይማስናል እንጂ ስምሪቱ መሀል ፥ ግርምት እንዳልታዬ ዘውድ ጫነ ብሎ ፥ የዋህ በግነቱ ፥ መች ከርሞ ጨቀዬ ? ተቀጥላ ... ተደራቢ ... ተለጣፊ ... የስም ርቢ ... ምግባረ ቃል ፥ እንጥልጥሎሽ አሉባልታ....... ስሚስሞሽ በበግ እምነት ፥ ይታለፋል ከበጎች ቤት ፥ በበግ መሀል ። በእኩልነት.. በሁዳድ መስክ ፥ ያለ ከልካይ ነጭ ፣ ጥቁር ፣ ቦሀና ፣ ቀይ ግጦሹ #ወጥ' ! ፥ ጥላው ሰማይ ሆኖ ያድራል ፥ ባንድ ጋጣ ሆንተብሎ ለትንኮላ ከበግ ራስ ፥ ቀንድ አይወጣ ። ነገር ግን ሲጠጋው.... በግ እንኳን አያልፍም ፥ የመላሸቅ ደዌ ጆሮው ላይ ሲፈጫጭ...ጥል እንደ ሸውሸዌ ያኔ ...ገራገሩ ቀለም ፣ ቀንድ ፣ ልሳን ፥ ስላይደል ሽብሩ ፤ አንዴ ጭንቅላቱ ፥ ለጠብ ካዘገመ ተንደርድሮ ሄዶ የሚተመትመው ፥ በግ ቢያጣ የቆመ ዘረ በግ ቢቀን'ን ...ፍቅርን እያለመ ካገኘው ሲማታ. . . ይኖራል ራሱን #እ_የ_ቸ_መ_ቸ_መ ። #አብርሀም_ተክሉ ( #መርዕድ) @Abrham_teklu @getamiyan @getamiyan @getamiyan

ኩርኩም ----------- እልፍ ኩርኩሞችን የቀመሱ ራሶች፣ ዳሳሽ እጆች እንጂ አይሹም ትራሶች። ============ 📙 "የወንድ ምጥ" ✍ ይስማዕከ ወርቁ @Getamiyan @getamiyan

. ተ ረ ት ተ ረ ት . ----------------------------- ተረት ተረት የላም በረት አንድ ሰው ነበረ በሀብቱ የከበረ ውልደቱም እድገቱም የሆነ አሜሪካ ባለው ነገር ሁሉ ጭራሽ የማይረካ ሲሞላለት ሆዱ 'ሀምበርገሩን' በልቶ 'ጋዴሚት' ይለዋል አልጋው ላይ ተኝቶ። ተረት ተረት ... አንድ ሰው ነበረ በጣም የተማረ በቃኝን የማያውቅ የጣልያን ተወላጅ ሁሌም ለአዲስ ነገር ጠዋት ማታ 'ሚባጅ 'ፒዛና ፓስታውን' ጥርግርግ አድርጎ ይተኛል ጥሩ እንቅልፍ 'ባፋንኩሎ' ብሎ። ተረት ተረት ... አንድ ሰው ነበረ ህልሙ የሰመረ ጀርመን ነው ሀገሩ 'ምርጥ ዘር' ነው ዘሩ 'ቮግ ቮረስቱን' በልቶ ሞልቶለት አዱኛ 'ሻይሰ' ብሎ ነው ሁሌም የሚተኛ። ተረት ተረት ... አንድ ሰው ነበረ የተመራመረ ጃፓን ተወለደ በሮቦት አደገ ቀን ሲሰራ ውሎ ሩዙን ቀቅሎ 'ሱሺ' ጠግቦ በልቶ 'ባጋይሮ' ብሎ ያነጋል ተኝቶ። ተረት ተረት ... አንድ ሰው ነበረ አጥቶ የተቸገረ ኢትዮጵያ ተወልዶ ኢትዮጵያ ያደገ ኩራት ነው 'ራቱ ዛሬም ሆነ ነገ ቢጠግብም ባይጠግብም ቆሎውን ቆርጥሞ 'ተመስገን' ይለዋል መደብ ላይ ተጋድሞ። ተረት ተረት ... እግዜር ከመንበሩ ወደ ምድር ወርዶ ይጎበኝ ነበረ በየቤቱ ሄዶ ከእነኚያ ከአራቱ ቆዳቸው ከነጣ ከየአንደበታቸው መልካም ነገር ቢያጣ ጥቁሩ ሲያመሰግን የፈለገው ሞልቶ ያጎደለባቸው አንድ የሆነ ነገር እንዳለ ገምቶ ሊጨምርላቸው ነጮቹጋ ሄደ አበሻውን ትቶ። ተረቴን መልሱ አፌን በዳቦ አብሱ። ------------------------------- ✍ በሜሮን ጌትነት @Getamiyan @getamiyan

ሕ ይ ወ ት -------------- ምንድነው ሰበቡ፤ ለምንድነው አልኩኝ ለምን ምክንያት፣ ይህ ዓለም መኖሩ አዱኛ ሕይወት፣ ህፃን መወለዱ አርጅቶ ሊሞት። ለምንድነው አልኩኝ: ለምን ምክንያት፤ ማን ያውቃል እንዳለው ለቋጥኝስ ቋንቋ፣ ዛፍ ለሚቆረጥ ዛፍ እንዳይቆም ጠበቃ። ማን ያውቃል፣ የመስቀል ወፍና የአደይ አበባ፣ ቀጠሮ እንዳላቸው መስከረም ሲጠባ፤ ማን ያውቃል፣ ማን ይፈትልለታል ልብሱን ለድንጋይ፤ ሰው ሳይዘራ ሳይተክል አያመርትምና፣ ሄዋን ሳትኖር አዳም ልጅ አይወልድምና። ምክንያቱን ይሻል ለሚታየው ሁሉ፣ እንዲያው ለግብር ይውጣ ለወጉ ላመሉ። ሠቅራጥስ አፍላጦን ሙሴና ዳዊት፣ ያለም ፈላስፋዎች ያለም ነቢያት። የትናንቶቹና የትናንቱ በስቲያ፣ የዚያ የዚህ ወዲያ፣ ወዲያ ወዲያ ወዲያ። ልቤ ተስፋን ቆርጧል እናንተን አይቼ፣ ግና ሁሉ ሲሞት ልብ ይሞታል መቼ። ስህተት ነው መሰለኝ ሰበቡን መሻት፣ "ለምንድነው" ማለት "ለምን ምክንያት"፣ ለምንድነው አንበል "ለ"ን እንግደፋት። ታዲያ ዓለም ምንድናት፣ ምንድናት ሕይወት፣ የሆነችው በዛ፣ ይህ ነች አንላት። ራሴም፣ጥያቄዬም የሕይወት ደቂቃ፣ የሕይወት ኬክሮስ ነን አለቀ በቃ። ከንቱ ነው ወዳጄ መተርጎም ማተት፣ "ይህ ቢሆን ይህ ሆነ" "ስለዚህ" ማለት። መልሳችን ዝም ሊሆን፣ ላናውቀው አንልፋ፣ ከዝም ለበለጠው ራሳችን ይደፋ። ግሩም ነው አንበል ከንቱ ነው አንበል፣ ድንቅ ነው አንበል አንበል ነው ቆንጆ፤ መፍርህ ነው አንበል መርዕድ መደንግፅ፤ ላንቃ እስኪሰነጠቅ፣ ምላስ እስኪነቃ፣ የሚባለው ሁሉ ቢደመር ላይበቃ። ግሩም ነው አንበል፣ ድንቅ ነው አንበል። አጥጋቢ አይደለም ያውም ዝም እንኳን፣ ጋን ሲታጣ ጊዜ ምንቸት ጋን ይሁን፣ እንዲያው እንደመም ቃል ፍሬ ላይሆን። ካፋችን አይውጣ ሕይወት አትርከስ፣ አለዚያ አይቻልም የህሊና ክስ። ============= 📙 "የግጥም ጉባዔ" ✍ ከመንግሥቱ ለማ 1950 ዓ.ም. ---------------------------- @getamiyan @getamiyan

አትፅናኝ ።።።።።። ሞትን አንመልሰዉ፣ እናውቃለን አይሸሽ ስንት ጥፍራም ኀዘን አይተናል መሰለሽ! ስንት ጥፍራም ኀዘን፣ እንደማቀይር አምነን ስንት ጥፍራም ኀዘን፣ እንደማይቀር አምነሽ፤ ዳሩ ታውቂዋለሽ። ፣ አቀጣጡ ክፋት፤ አመጣጡ ም‘ፃት፤ ግን ከሄደው ሁሉ፣ ከተመላለሰዉ ምን ይባላል ይኼ፣ ባንቺ የደረሰዉ?! ምን ይባላል ይኼ? አንቺስ ምን ልትባይ? እኩይ ነዉ እታለም፣ ሽንገላ እንደ ሥራይ። ፣ በእድፋም ጥፍሩ፣ ቧጦሽ ጥፍራም ኀዘን መፅናናት መመኘት፣ ምንድነዉ መማፀን? ምንድን ነዉ ዕንባ አባሽ? ምንድን ነዉ ማገገም? ዕንባሽን ማድረቂያ፣ አልሰጥሽም ማ‘ረም። እሪ በይ! ቢል በይ! ኩርምት በይ–ዋኔ! ላንቺ መፅናናትን፣ አልመኝም እኔ። ወይኔ በይ! ወዮ በይ! ተይ አልልም ጭራሽ፤ አለመፅናናት ነዉ፣ አንቺን የሚያፅናናሽ! ፣ የሚገርም አይነት ጽሑፍ፣ ለዛውም የግጥም ጽሑፍ ማንበብ እንዲህ ከፍ ያደርጋል ለካ! ፣ #መዘክር_ግርማ (ወደ መንገድ ሰዎች: 2010 ዓ·ም) @getamiyan @getamiyan @getamiyan

በላይ በቀለ ወያ እኔን ብትመርጡኝ ፣ ለሚመጣው ምርጫ አፄ ሚኒሊክን ፣ ገድዬ በሜንጫ አወርደዋለሁኝ ፣ ከፍ አርጎ እንዳስከፋን ከመቶ አመት ቀላይ ፣ ከኖረበት ዙፋን😂😂 ።።። እኔን ብትመርጡኝ ፣ ለሚመጣው ምርጫ ለጠጪዎች ውስኪ ፣ ለቃሚዎች በርጫ ለእግርኳስ ክለቦች ፣ ለእያንዳንዱ ዋንጫ ለፈረሶች ፍጥነት ፣ ለአህዮች እርግጫ በነፃ አድላለሁ። ።።። በሚመጣው ምርጫ ፣ እኔን ብትመርጡኝ ድምፃዊ ሳትሆኑ ፣ ድምፅ ብትሰጡኝ አንድ ዜማ ሰሪ ፣ አንድ ጊልዶ ካሳ😂 አንዲት ውብ ኮረዳ ፣ አንድ ውብ ጎረምሳ😂 አንድ ካሜራ ማን ፣ አንድ የባህል ቡድን ፣ ክሊፕ የሚሰሩ ወይም ዘመናዊ ፣ ዳንስ የሚጨፍሩ አስቀምጣለሁኝ ፣ በየ አንድ ሜትሩ😂 (ግጥሙን ለኔ ተውት😂) ።።። ለሚመጣው ምርጫ ፣ እኔን ብትመርጡ በዘር በሀይማኖት ፣ ምትቦጣቦጡ ሰላም ያልገባችሁ ፣ ለፀብ የምትሮጡ ከኪሴ መድቤ ፣ ከፍተኛ ባጀት ጠብመንጃ ገጀራ ፣ ታንክና የጦር ጀት ከሆነ ቦታ ጋር ፣ ለጦር ሜዳ ምቹ በነፃ አድላለሁ ፣ እንዲዋጣላቹ😂! ።።። ለሚመጣው ምርጫ ፣ ብትመርጡኝ እኔን በምስራቅ ፣ በደቡብ ፣ በምእራብ ፣ በሰሜን ላሉ ህዝቦች ሁሉ ፣ አንዳች ሳላዳላ ቀስት የፈላ ውሃ ፣ ክላሽና ዱላ ለተጠቃሚዎች ፣ በነፃ አድላለሁ ለእያንዳንዱ ቤት ፣ ቤት ቁጥር አንስቼ ፣ ክልል እሰጣለሁ😂 ።።።። ለሚመጣው ምርጫ እኔን ብትመርጡኝ ፣ ሔዋኔና አዳሜ አልጋ ቤት በነፃ አድላችኃለሁ ፣ ቅዳሜ ቅዳሜ😂 ።።። ለሚመጣው ምርጫ ፣ እኔን ብትመርጡ ላመት ባል ላመትባል ነጭ የጤፍ እንጀራ ፣ ጥብሱ ዶሮ ወጡ ጥሬ ስጋ ቁርጡ ጠላው እና ጠጁም በቴሌቭዥን መስኮት ፣ አይታችሁ አትጎመጁም ሁሉንም በቤታችሁ ታገኙታላቹ ምርጫ በሌለበት ምርጫችሁ እኔ ነኝ ፣ ምረጡኝ ባካቹ😂 ።።። ሁሉ እንደ ፈቀደው ሁሉ እንደወደደው ሚኖርባት ሀገር መኖር ብትፈልጉ ፣ ምረጡኝ በሞቴ አፄ ሚኒሊክ ነው ፣ ምርጫ ምልክቴ😂 @Getamiyan @geyamiyan

🙏🙏🙏 ....... አጣብቂኝ .............................🙏🙏🙏 @Abrham_teklu @getamiyan @getamiyan

[ሔለን ወንድሙ] ✍@Helen_wd የጊዜ የዘመን ጣር የአለም ስቃይ ሽብር የምድሯ እንባ ዥረት ለቅሶ ላይመልሰው ያልታሰበ እዳ አምሳሉን ጨረሰው ፡፡፡ .............. የመልሱ መባቻ አንድነትን ትቶ መሆን ነው ለብቻ ሞት መቁጠሪያ ሆኖ አሀዝ እስኪታጣ እንደ ቅጠል ረግፎ መኖር ሲሆን እጣ ዘመን ደም አልቅሶ.... የአካሉን ፈሳሽ በእንባ ቢጨርሰው ይህን ቀን ይን ጊዜ ደርሶ ላይመልሰው ከንፈር ብቻ መምጠጥ ምን ያረጋል ለሰው ተቃቅፎ በማልቀስ ከአፈር ላይመልሰው ብቻ..... መሆን ነው ለብቻ ጊዜ ጊዜን ሽሮ እስኪያልቅ ፍራቻ 😷😷😷 ✍✍@Helen_wd @Getamiyan @getamiyan