en
Feedback
📚 የኛ_ግጥም 📚

📚 የኛ_ግጥም 📚

Open in Telegram

Show more
Ethiopia4 030The category is not specified
6 604
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
እርቀሽ ሔደሻል የአዕዋፍ አለቃ የሠላም ምልክት እርግብ ሆይ ብረሪ እስቲ ዝሪ ህይወት ዳሩ ምን አግኝተሽ በምን ላይ ልትበሪ የቱን ሰላም አይተሽ ምንስ ልታበስሪ አልታይም ብለሽ ዕርቀሽ ሄደሻል ባንቺ ክንፎች ፋንታ ፅልመት ተክተሻል ቤተልሄም ሰለሞን @Getamiyan

°°°°° ፊርማ °°°°°° ©ሲራክ ያልፈካው አበባ ሲቀጠፍ ለዝና፣ ለለማኝ ይሰጣል ያልታደለው መና። .... @Getamiyan @getamiyan

#የመዳፍ_ላይ_እድፍ ~~~~ ©#ሲራክ ~~~~~ . በሀሰት ድባብ ፀዳል ከአይናችን አንደበት የእምባ ፀበል ደርቋል ደግሞም ወዲህ ማዶ.... የግንባር ስር ደዌ ኮርቶ ተንፀባርቋል በውብ መቃ ብዕር በህብረ ቀለም ወዙ አሉን የሀቅ አለም ከማጣት ልቦና ከመገኘት ጓዙ በመሸከፍ ወኔ በጮራነት ልሳን ሰፍረው ያልፈዘዙ ከእጓላዊት ሸራፋ እቅፍ ከአባትነት የሰማይ ግፍ ከማስመሰል ተውኔት ጥንስስ ከልማዳት ድግግም ዳስ እነሆ ክቡድ ቃል በራስህ መካከል ላይነሳ ወድቋል በስንፍና መርፌ ለተጣፈው ሱሪህ ሳትሰጠው መባ እዮሃ አበባ እዮሃ እዮሃ እዮሃ አበባ ዘመንህ ተወልዷል አሜኑን ተውና ወየው ብለህ ግባ እዮሃ ለአንተ ነው.... እነሆ ይሰበር የቀን ሰባራ ጣት እነሆ ተስፋችን በቀኙ ይንጋላት ምድር ገጿ ነትቦ በደም ስትጣጠብ ከሰማይ አክናፋት ስርየት ሲታቀብ አሜን ይሁን ላንተ ለእኔ ግን ወየው ነው ፈጣሪ ሚበዛው ምልኪ ሲረክስ ነው እምነት ሲጎል ነው... ለአንተ ነኝ ባዩ ሰው አልጋህ ላይ ተጋድሞ ከመሬት ምትተኛው ወየው ልበል እንጂ እኔማ ምን ቀረኝ እኛማ ምን ቀረን ካለ መድረስ ቀረን የትም ወድቀን ወድቀን የሸከፍነው ሀሳብ እያወላገደን /°°°°°°° #ሲራክ @siraaq °°°°\ /______~~~~~~________\ @Getamiyan @geyamiyan

✍ ሎሬት ፀጋዬ ገ/መድን @Abrham_teklu @Abrham_teklu

ሙሾ ላመለጠ ወጣትነት ------------------------------- ሳይደምን ይዘንባል ይዶፋል ከደጃፌ ግርጌ፥ የሕይወት ጎርፍ ያልፋል፤ የክንፌ ርጋፊ አንድ የላባ ነዶ ያካሌ ቅራፊ የቀረ ተጎርዶ ተጠርጎ ሲወሰድ ፥ በጥሞና እያየሁ ይሄው ቁጭ ብያለሁ፤ ሲጋልብ በፊቴ፥ ይህ የውሃ ሰጋር ጀምበሬን አየኋት ተጥርጋ ስትሄድ፥ ከሰርዲን ጣሳ ጋር የልጅነት ቅርሴ ድዴ ያባረራት፥ ያች የወተት ጥርሴ ካሮጌ ቆርኪ ጋር፥ አብራ ተቀላቅላ ባረፋ ተከባ፥ በጎርፍ ጀርባ ታዝላ ስትሄድ እያየሁ ይሄው ቁጭ ብያለሁ፤ የመጀመሪያዋ፥ የጉንጬ ላይ ቡግር የመጨረሻዋ የራሴ ላይ ጠጉር ከሳር ከትቢያው ጋር፥ እንደተቃቀፉ በጎርፉ ጀርባ ላይ፥ እንደተንሳፈፉ እንደዋዛ ሲያልፉ በጥሞና እያየሁ ይሄው ቁጭ ብያለሁ። ------------------------------ ✍ በዕውቀቱ ስዩም @getamiyan @getamiyan

የወ.ዘ.ተ. ግጥም (ልዑል ሀይሌ) የዓይነቶች ዝርዝር የቀለማት ዝርዝር የኹነቶች ዝርዝር ገልጠው! ገልጠው! ገልጠው! እስከመጨረሻ መዝለቅ ሲያቅታቸው፤ ይኸው ታዘቢልኝ! ወ.ዘ.ተ. ሚለው ነው ላላወቁት ዕውቀት ከሰው ማምለጫቸው። . ይኸው ታዘቢልኝ! ያፍቃሪ ውዳሴ መች ዘመን ይዘልቃል፤ ትዳር ላይ ይረሳል ወ.ዘ.ተ. በሚለው በሰነፍ ሰዎች ቃል። . እኔም በስንፍና በዳተኝነቴ ፍቅርን ከማረክሰው፤ ዕድሜዬን 'ገልጣለሁ የልቤን ውዳሴ ዘመን ማይጨርሰው። . ይኸው ታዘቢልኝ! የጥበብ ሰው ሁሉ ቀለሙን በጥብጦ ቃል እያሰመረ፤ ሊገልጥሽ ይጥራል የራሱን ስንፍና ባንቺ እያኖረ። . እውነታው እንዲህ ነው... ወ.ዘ.ተ. በሚሉት በመቀጠያ ቃል፤ ሊገልጥሽ ሚደክም ደራሲው ገጣሚው ስላንቺ ምን ያውቃል?፤ . ሰዓሊው ወ.ዘ.ተ. 'ሚል ስዕል ሸራ ላይም ሳለ፤ ልፋ ቢለው እንጂ ከቀለማት መሃል ያንቺ እውነት የታለ?፤ . እኔንም ታዘቢኝ! ወ.ዘ.ተ. የሚል ቃል ምን 'ካፌ ባይወጣ፤ ዘርዝሬ ያልጨረስኩት ብዙ እውነት አለኝ ዘመናት ታገሺኝ ከልቤ እስኪወጣ። . ነዳጅ ነው ወይ?! እህእ! ፲፩-፪-፪፳፻፰፩ ዓ.ም. @getaniyan @getamiyan @getamiyan

(በላይ በቀለ ወያ) በበእውቄ ስታይል . . ስሚ! እኔ በዚህ ሀገር ፤ብዙ ብሰቃይም በወዲህ ዘረኛ ፣ በወዲህ ኮሮና ፣ በወዲያ መሀይም ዱላ ድንጋይ ክላሽ ፣ ሜንጫ የፈላ ውሃ ፣ ከበውኝ ብታይም ዘጠኝ ሞት በሬ ላይ ፣ ሲያኳኳ ቢገኝም ለትውልድ የሚተርፍ ፣ መፅሐፍ ሳላሳትም አንዱን ግባ ብዬ ፣ ለሞት በር አልከፍትም አልሞትም ።።።። ስሚ ወደ ሳቅ ሳልለውጥ ፣ የምስኪኑን እንባ እንደዶክተር አብይ ፣ ግራ ሳላጋባ ለጨለመበት ህዝብ ፣ ብርሐን ሳላነጥፍ ስቄ ሚያሳይ ፎቶ ፣ ፌስቡክ ላይ ሳለጥፍ😂 ሚለብሰው ላጣ ህዝብ ፣ ሳላለብስ ፀጋ ከኋላ ሺህ ገዳይ ፣ ከፊቴ ሺህ መንጋ ደብድቦ ቀጥቅጦ ፣ ሰቅሎ ቢጥለኝም አፈር ልሼ እንደ እባብ እነሳለሁ እንጂ ፣ አፈር አይበላኝም አልሞትም! ።።። ስሚ ህንፃ በህንፃ ላይ ፣ ገንብቼ ሳልከምር ፖለቲከኞች ጋር ፣ ቁማሬን ሳልቆምር ያባይ ግድብ ሞልቶ ፣ አምፖሌን ሳልቀጥል በአሜሪካን ላይ ፣ ማእቀቤን ሳልጥል ወደብ ሳላስመልስ ፣ ገንጣይ ሳልገነጥል ያሳደደኝ ሁሉ ፣ አይቶኝ ሳይፈረጥጥ ሀያላን ላይ ሳልዝት ፣ ግብፅን ሳልቆነጥጥ ለምስኪኖች ሳልቆም ፣ ለደሀው ሳልወግን ቢራ ውድ ሆኖብኝ ጉበት ጨጓራዬ ፣ በአረቄ ቢበግን አልሞትም እኔ ግን ።።። ስሚ ፎቶ ባሳጥብም ፣ ልብሴን አቆሽሼ ግዙፍ ነኝ በሚል ፊት ፣ ብታይም አንሼ ሀገር እንደ ሀገር ፣ አንድ ሆና እንድትቀጥል ፣ አቅለ ቢስ መስዬ እልፍ አእላፍ ጎልያድን ፣ በአንዲት ጠጠር ጥዬ ልኩን ሳላሳውቅ ፣አቅሜን ሳላስቃኘው ያልታወቀ ኋይል የሚሉትን አካል ፣ በአካል ሳላገኘው አጣኋትኝ ብዬ ፣ ብትገድዪኝ አልሞትም እኖራለሁ በቃ ካንቺ ተለይቶ ፣ መኖር ቢያዳግትም አልሞትም @getamiyan

...... #አንጣር ~~ #ባንጣር .... ሜሮን ተቀብቶ በትረ ሰለሞኑን ፥ በደም ለታደለ በትውልዶች መሀል .... የተንከባለለ አልጋ ወራሽ እና ፥ አልጋ አፍራሽ ልጅ አለ ። የተገናኙለት.... እነኝህ ሁለቱ ሁሌም ጦርነት ነው ...ሁሌም አተካራ ማር ከሬት ያመራል ... ከደጋፊ ውጪ ...ለሚሰየም ጭፍራ ። በተንቆጠቆጠው በወርቁ ድንክ አልጋ በዘመነ ዙፋን... ቤተ-ንጉስ ጣራ በስተስር ላደረ ፥ ብቻ የሚበራ ልክነት ቦታ እንጂ ፥ ስልጣን እና ተራ ፍፁም እውነት የለም !!! ፍፁም ድንቅ ስራ !!! ወራጅ ነው ህፀፁ ...በቀን የሚጠራ ። ✍ አብርሀም_ተክሉ ( መርዕድ ) @Abrham_teklu @Abrham_teklu @getamiyan

#አባይ ! (ሚካኤል አስጨናቂ) ።።።።።።። #ምድራዊ ወተት ፥ የኤዴን ደምግባት የኢትዮጵያ ካስማ ፥:የፍጥረታት በዓት የሀገር ንጥር ቅቤ ፥ የሚያወዛ ቅባት የቁጭት ማረፊያ የህብር ማሳያ ለምን መፍሰስ ብቻ ፥ ክንፍ አውጥቶ መብረር? ተግ ብለህ ላፍታ አንዴ እንማከር ብለንህ አልነበር ? ይኸው ሰምተኸናል.. . ጆሮውን አውሰህ ፥ ከጉዞህ ታቅበህ የእናትህ ምልጃ ፥ ልመናዋን ሰምተህ .. ንሳ እንካ መልዕክት! የወላጅ ተማፅኖ.. . ባዕድ ቤት አትክረም ፥ ዳሳችን ደምኖ አረፍ ብለህ ስራ.. . የጎጆዋችን ፀሊም ፥ ተገፎልን ይብራ። እንካ እውነት ንሳ.. .. ጠቦት በጓን እረድ.. . ስለ ቤትህ ካሳ እኛም በደልህን ... እንደ አምናው ሁሉ ፥ ዘንድሮም አናውሳ ። ይሽከርከር ሞተሩ.. . ይዘምር ሀገሩ ... ተነቅሎ ይቀንጭር ፥ የድህነት ስሩ ። ተንጣለል በሜዳህ ፥ ተዘርግተህ ክረም ተኮትኩቶ ይክሰም ፥ ያለመቻል አረም ። በል እንዲያ በል እንዲያ... አብረን እንበል እስክስ ፥ እንደልቅ ዳንኪራ እንደ ሀገርህ እንቅጥቅጥ ፥ የጎዣም ጭፈራ እስክስ በል ደክር ፥ ወንድ ሆነህ አቅራራ ሀሞትህ ይጋጋል ፥ በበላይ ፉክራ ። በል እንዲያ ... በል እንዲያ ዝናር አደግድገህ ፥ ውጣ ከገበያ በቅጥር መንደሩ... ያለ አንዳች ከልካይ ፥ በጎፈሬህ ክርክም ተንጎማለልበት ማማር ሀገር ላይ ነው ፥ አይደለም በስደት። @getamiyan @getamiyan @getamiyan

የኔ ዘመን አቅሙ የተረታ መተንፈስም የደከመው በጅምር የቀረ ሀሳብ የገደለው አስቦ እያደረ አስቦ ሚውለው የዘመኑ ልጅ ነኝ ዘመኔ ይሄ ነው ያለሁበት ዘመን የቆምኩበት ቦታ ወጣት የሱሥ ጣት ነው አቅሙ የተረታ ወጣት የነብር ጣት ለዘመኔ አይሰራም ስሙን ብንሰጠውም ተግባሩ አይስማማም የኔ ዘመን ማለት......... በብርጭቆ መሃል እራሱን ሚፈልግ በመጠጡ መሀል ወደ ሠማይ እ'ሚያርግ አየር ላይ ሚንሳፈፍ ድፍረት የተሞላው ከብዙ መሀከል አብዛኛዉ እንዲ ነው በየጥጋጥጉ በስርቻው መሀል በጫት ተከልሎ ወገን ይታየኛል ምክንያት እየሰጠሁ ምክንያት እየነፈኩ ሀሣቤን ሣልዘጋ ሌላ ሃሳብ ከፈትኩ መንፈሴን ሰብስቤ ባይኔ ስመለከት ካለሁበት ማዶ ወዲያው ተመለከትኩ አፍላና ምስኪኑ ወጣቱ ተማግዶ ደግሞ ተሻገርኩኝ......... ያሠብኩትን ሀሣብ ደግሜ ሳልዘጋ ከሀሳቤ ሙግት ብቻዬን ላወጋ አውጥቼ ላወርደው አውርጄ ላወጣው የኔ ዘመን ትውልዶቼ....... በጭሱ መሀከል በክብ ተቀምጠዋል ዛሬም እንደትላት ሊውሉ አስበዋል የቀን መፈራረቅ ቁብ አልሰጣቸውም መንጋቱ መምሸቱ አልታወሳቸውም ቀን ማለት ለነሱ መንጋቱ መምሸቱ ተፈጥሮ ብቻ ነው ይሄ ነው እውነቱ የዕድሜዬ ባለጋራ እኩዮቼ ናቸው በተስፋ መቁረጥ ውስጥ ተቀምጠው ሣያቸው የቀረኝ የምለው የኔ ትንሽ ተስፋ ከሀሳቤ መሀል ከመቅፅበት ጠፋ ጉልበታቸው ሰንፎ በጣም ደካክመዋል የተነጠቁትን ያጡትንም ተስፋ ፍለጋ ይዘዋል ከሀሳቤ መሀል አንድ ሃሣብ ተነሣ ረቂቁ ተስፋ ፈንቅሎ ሲነሣ ረቂቁ ተስፋ ከጫቶቹ መሀል ረቂቁ ተስፋ ከመጠጡ መሀል ረቂቁ ተስፋ ከክለቡ መሀል ረቂቁ ተስፋ ከስካሩ መሀል ምክንያት እየሰጠሁ ምክንያት እየነፈኩ ሐሳቤን ሣልዘጋ ሌላ ሀሳብ ከፈትኩ ከመቼ ወዲህ ነው ...... ረቂቁ ተስፋ ከጫት የሚገኘው ረቂቁ ተስፋ ክለብ ጭፈራ ቤት መቼ ነው የታየው ረቂቁን ተስፋ መጠጥ የከለለው ረቂቁን ተስፋ ስካር የሸፈነው ሽፋኑ ተገልጦ መቼ ነው ምናየው ያልታደለው ትውልድ በሚያምረው ገፅታ በጫት በመጠጡ በጭስ የተረታ ኑሮ ሲያስቸግረው ችግር ሲፈትነው የታሰረበት ውል አልፈታም ሲለው መፍትሄ ፍለጋ ወደ ሱስ ያመራል አልችልም በማለት ህልሙን ያጨልማል የሱሱ መገኛው ጓደኛው ይሆናል ዞርኩኝ ተመለከትኩ እጅ ሰጥቶአል ወኔ ወጣት ተሸንፎ ስምም ተሰጥቶታል የሚባል ወመኔ የኔ ዘመን ትውልድ..... ፊቱና ገፅታው ጭራሽ አልተከፋም የሚያምረው ብርሀን ዛሬም ላይ አለጠፋም ነገር ግን ነገር ግን...... ፊቱ ላይ ሚታየው ያልጠፋው ብርሀን የውሸት ማስመሠል ነው የውስጡን ቃጠሎ ሀቁን ደብቆ ነው የተስፋ ማጣቱን የምሬት እንባውን የሠለቸው ኑሮን የታረዘ ነብሱን ቀን ከሌት ሚባክን የታፈነ ድምፁን ሀሉንም ሸፋፍኖት ደብቆ ነው እንጂ ከጫት ከሲጋራው በድንገት ነበረ የሆነው ወዳጂ ቤተልሄም ሰለሞን @Getamiyan @getamiyan

የሁለት ዓለም ስካር ❖ ምነዋ እቴዋ . . . ደካማ ገበሬ እንዳቆመው ክምር ካሉበት ተነስቶ ከራስ ላይ መቀነስ፣ 'ያልጠበቁት ደስታን' እጨብጠው ብሎ ደርሶ ተቀላቅሎ እያደሩ ማነስ፤? አየር ጋር መነስነስ . . . መኩነስነስ . . .መዳነስ . . .! ምነዋ . . .ምነዋ. . .?! ትከርሚ ይመስል፥ትቀሪ ይመስል እላይ ላይ መታየት፣ ገለባ ገላሽን . . .! አንድ የክብሪት እሳት . . . ጫፍሽን ቢነካው ወድቆ ለመጋየት። ምነዋ . . .?ምነዋ ተቻኮልሽ?! ለመጉደል ተቻኩለሽ . . . ረሳሽው ደብሩን፥ዘነጋሽ አድባሩን አንቺው አንቺን ስትዪ . . . ችላ አልሽው ነገሩን? በያንዳንዱ ሰው ውስጥ ንቁ የ'ብደት ጽዋ . . .! በስውር መኖሩን፤! እንደምን አጠፋሽ . . . የፍጥረት ምሥጢሩን የምሥጢር አገሩን?! - ይኼው . . . ይኼው የኔው ነቃ . . .!! አገረሸ ወጣ ጀመረኝ ወፈፍታው፣ ብቅ ቀረብ አለ የመንፈስ እፍታው፤ የስካር ከፍታው . . .!! ፉት አለው ጨለጠው ልቤ ማእበሉን ሞገደ መጠጡን፣ ንፋሱን ዳቦ አርጎ በላው ሰውነቴ ያዘ መነጥነጡን . . .!! አዎ . . . አዎ ባይጎላብኝ እኔም ዛር አለብኝ። አለብኝ ክፉ ዛር . . . የሚያንዘረዝረኝ የሚያቀነዝረኝ የሚመነዝረኝ . . .!!! ካመድ ብንንን አድርጎ ጉም የሚሰውረኝ፤ የቃል ቅኔ ድንጋይ የሚያስወረውረኝ። አለብኝ ክፉ ዛር . . .! አፌን ከፈትኩ በቃ ምድር ታነውረኝ። - ሰማይ ተሰንጥቆ ቢያወርደውም ዶፉን፣ አያጨቀየውም የሕይወት ደጅ ደፉን። አንድ እውነት አለ . . .! ይኸውም፦የሴት ኩራት የወጣት ዝሙት የመንግሥት ትእቢት ቢታጠብ አይጠራም፤አይጠፋም፤አይቀርም፤ ሰው ለትልቅ ጉዳይ ዓለም ላይ አይኖርም!!! በቃሉ ሙሉ (ዘባህር ዳር) @getamiyan @getamiyan @getamiyan