en
Feedback
📚 የኛ_ግጥም 📚

📚 የኛ_ግጥም 📚

Open in Telegram

Show more
Ethiopia4 030The category is not specified
6 604
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
#በዚህችም_ቀኑብኝ!? ----------------------------- ህይወትን ልመራት ባለኝ ተደስቼ፡ አንድ ሁለት ስል ልበላ ሰርቼ፡ አርሸ አለስልሸ ዘሬንም ዘርቼ፡ በቅሎልኝ አርሜ ሰብስቤ ወቅቼ፡ ለቅሜ አበጥሬ አስጥቼም አዝርቼ፡ ወፍጮ ቤት ወስጄ አልሜ አስፈጭቼ፡ ቤት ባፈራው እቃ ልጋግር አቡክቼ፡ ማገዶ ቆስቁሸ ምጣዱን አስምቼ፡ ሰምቶልኝ ጋግሬ ልበላው አውጥቼ፡ አሁን ካሁን ስለው ርቦኝ ጓጉቼ፡ በሰለ አልበሰለ ብዬ ቢወጣልኝ፡ በላሁ ልል እንጀራ ችግሬ ሊያልፍልኝ፡ እስኪ ተመልከቱ ምን ማድረግ አለብኝ፡ መበያ ነው ብለው አፈር በተኑብኝ፡ አጅብ የሰው ነገር በዚህችም ቀኑብኝ!!! #ይገርማል.......!! #semir aklu @getamiyan

የክፍትሽ ብዛት የበደልሽ ጥጉ ማንም የማይተካው ማይገጥም ወጉ፤ ከከፍታ በላይ ከልቤ ጫፍ ጥጉ ከነፍሴ አስበልጬ ስወድሽ ስወድሽ፤ አንች ግን ከሌላ ተዛምደሽ ተገኘሽ ባንቺ መራቅ መሄድ መከፍቴን ሲያውቀው፤ አይኔም የእምባ ናዳ ጎርፉን አዘነበው፤ ባንቺ መራቅ መሄድ አእዋፍ አዝነዋል፤ አንበርም በሰማይ አንታይ ብለዋል ባንቺ መራቅ መሄድ ጨረቃም በሽቃለች ከበፊት ውበትዋ አሁን ደብዝዛለች፤ ባንች መራቅ መሄድ ፀሀይም በሽቃለች ከበፊት ጉልበቷ አሁን ጠንክራለች፤ እሷ ካለችበት አልበርድም ብላለች አሁን ግን ያዘነው ትልቁ ሰማይ ነው ያንችን መራቅ መሔድ መከፋቴን ሲያዉቀዉ ፤ እኔን ያሳርፈኝ ትልቁን እምባውን ዝናቡን ሲጥል ነው። Semir aklu✍ @getamiyan

sticker.webp0.32 KB

#ድኩም_ምርጫ ሰው ሲኖረው እንጂ ፥ ነብስ ሲዘ'ራበት ብቻውን ኦና ነው ፥ተክል እና ዳገት ሰው ነው ያገር ጥንሱ ሰው ነው ያገር ዳሱ ሀገር የት ይቆማል ፥ ሰብ እያፈረሱ ? ብዬሽ እንዳልነበር ብል በልቶት ጭንቅላት አልቅት ጎጠኝነት ፥ ተጣብቶን ለቅጣት ማዘን ተጠይፈን ከገቢሩ ዘለል ፥ አዳም ላወረሰን ፥ የሰውነት ቅንጣት ከሰው ሰው መረጥን ከጣትም ልዩ ጣት !! ፐ !!! #ም_ይ_ም_ና #አብርሃም_ተክሉ ጳጉሜ / 4/ 2013 ከምሽቱ 3:00 አዲስ አበባ @Abrham_teklu

ባልቀረ ቅንጣት ዘሩን ውጦ ፥ ጨቅላ የሚያፈልቀው ከመቼ ወዲያ ነው የሴት ልጅ አከላት ፥ በመስጠት ያለቀው ? በ90 አመቱ ፥ ስጋው ተሸብሽቦ ፥ ዘሩ ያላረጠው ከመቼስ ወዲያ ነው የወንድ ልጅ መቅኔ ለሴት በማደግደግ ፥ ወዙ የሟጠጠው ? ከመቼስ ጀምሮ የጥንዶች ፍንጠዛ ፥ መሬት የከበዳት ? እንዲያውም ተመቻት አፈር ባፈር ዝላይ ፥ ኩርማኗን ይዞታ ፥ ለቤት አስወደዳት አንቺ እንካ....በመደብ እንቺ እንካ...በቁሙ እንቺ እንካ ቀን በቀን እንቺ እንካ በሌቱ ለሰው ልጅ ፣ ለእፅዋት ፣ ላዋፍ ፣ ለአራዊቱ የመጀባበቱ ስንክሳር ቢበዛው አልጋቤት ቢወደድ... ምግብ እና መጠጥ ፥ ሰማይ ቢንተራስም እቀምስ ላለው ጃል ...ኑሮ ባያቀምስም ፍቅር እርካሽ ነው... ከመዋደድ በቀር ፥ ወረት አይዳብስም ዝም ብሎ መዋደድ ከሚወዱት መክረም ፣ በፍቅር መታከም በውድ መታረም ፣ እድሜን ማነባበር ዘር ሀረግ መከመር እንዲያ ነበር አዳም ፥ መሆን የሚገባው !!! ስራውን ወጥሮ እሾሁን ላጣሪው ፥ መተው እንዲረባው ። እርሻውን መረሽረሽ ከብቶቹን ማስባባት ሚስቱን ማቀማጠል ለዶሮዎች ጥሬ... ለፍየሎች ቅጠል ጭድና ገለባ ... ለቡሬ እና መጋል ካዳረሰ ኋላ መልካም ሚስቱን አቅፎ ፥ ሰውነቷን ማጋል ውሀ...ውሀ እያሉ ፥ ተጣምሮ መጠማት አካል አወዳጅቶ ፥ በገላ መቃዳት ፥ በገላ መጠጣት ተያይዞ መርካት... ለታመኑት መውጣት እንዲህ ነበር መልኩ እድሜና ክራሞት አያዉቁን ፈትፍቶ ... አያውቁት ከመሞት ። ✍ አብርሃም ተክሉ @Abrham_teklu

ዜና እረፍት ! ክብርት ዶ/ር አበበች ጎበና ከዚህ አለም በሞት ተለዩ፡፡ እናታችን ክብርት ዶክተር አበበች ጎበና በቅርቡ በኮቪድ-19 ተይዘው በቅዱስ ጳውሎስ ሆሰፒታል በጽኑ ህሙማን ክፍል ውስጥ ገብተ
ዜና እረፍት ! ክብርት ዶ/ር አበበች ጎበና ከዚህ አለም በሞት ተለዩ፡፡ እናታችን ክብርት ዶክተር አበበች ጎበና በቅርቡ በኮቪድ-19 ተይዘው በቅዱስ ጳውሎስ ሆሰፒታል በጽኑ ህሙማን ክፍል ውስጥ ገብተው እንደነበር መግለፁ ይታወሳል። ዛሬ ጠዋት በተወለዱ በ85 ዓመታቸው ከዚህ አለም በሞት ተለይተዋል፡፡ ምንጭ፦ አበበች ጎበና የህፃናት ክብካቤ እና ልማት ማህበር @tikvahethiopia

ወደው አይስቁ የውልሽ..... አንቺዬ በታዳሚያን ፊት ፥ አንዱ ወግ አዋቂ ዲስኩር ሲሰካካ እራሱን ኮርኩሮ ፥ አንቺም እንድትስቂ አላውቃት አታውቀኝ የነቀዘ ሰብል ፥ መች እኔን ሊደንቀኝ ከሁሉም አጣላኝ ፥ አምላክ ሊታረቀኝ ብሎ ክትክት አለ...በሳቁም ገደለኝ ። በኔና በሱ ቤት ድንግል ጎልማሳ አገር ፥ በእድሜዋ ማምሻ በደባ ተደፍራ ወልዳ ታርፍ ዘንዳ አምሮቷ እያደገ ሽታ እየነቀሰ ፥ በህዝብ እየሰፋ ተስፋ ተገዝግዞ ፥ ሰበዙ ሲለፋ ቀዩ ሰው ሲጠቁር ጥቁሩ ሰው ሲከፋ እንደ ሁሉ አገርሽ እንደ እንደልቡ ሁሉ እንደሞላለት የጭንቅን አቀበት በመታበይ ጉልበት ለመውጣት ማሰቡ ፥ በራሱ ይደንቃል ድሮስ ሹማምንቷ የልመና ስንዴ ፥ መቼ በልቶ ያውቃል ? አብርሃም ተክሉ @Abr_sh @getem @getem

#አንቺ እና ግጥም ....(ሚካኤል አስጨናቂ) ልማዴ እንዲህ ነው ... ከጀምበር መግለጥ ጋር አንቺንና ግጥምን ስንቅ ነው 'ምውለው። . #ግጥም ያስጠላኛል! አንድ ሀሳብ ለመግለፅ መዞር ዙሪያ ጥምጥም ቃላት ማሰካካት ... ምኑም እኮ አይጥምም። እወድሻለሁ ለማለት መመሰል በፀሀይ... ማሞገስ ጨረቃ እዬዬ ማለት ነው ... ማውረድ ልቅሶ ሲቃ በቃ ! . #ግጥም! ለመግለጥ ቁንጅናን ... ሰውን ማድረግ መልዐክ...ማጋነን ...መጨመር መወጠር.. .መቆለል ... ቅኔያት መከመር ከዚህ ሁሉ ስቃይ ቁንጅናዋን ነግሮ ወደድኩሽ እያሉ በዝርው መናገር አይቀልም ማሳጠር? ስከርቭን ጠምጥሞ ጠቢብ ነኝ እያሉ ጉራ ከመቸርቸር? እያልኩ አስባለሁ ... . አንቺም እንደዚያው ነሽ ! እንደ ግጥም ሁሉ በኔ ትጠያለሽ ሁሉንም አልወድም ያንቺን ነገራቶች ጨዋታና ሳቅሽ እንዲሁም ቃላቶች መስማት ይቀፈኛል የድምፅሽን መውጣት ቅብጥብጥ ዓመልሽ ይመስለኛል መዓት ጠጉርሽ ዞማ ቢሆን ቢመስል ፀሀዳ ከብዶኛል እንደ እዳ! . ይብላኝልሽ ላንቺ ቁንጅና በሚሉት ሰንሰለት ለታሰርሽ ራስን በመውደድ ኩራት ለተጠመድሽ እንጂ እኔ ሳይገርመኝ የውበትሽ ግርማ ጠልቼሽ አለሁኝ ታምራለች ከሚሉኝ ሰዎች ሳልስማማ ። . እያልኩኝ ቢሆንም ... እንደዚህ ባስብም... ግጥምን እየጠላሁ መግጠም ግን አልተውም። . አንቺም እንደዛው ነሽ ቅኔ ነሽ ወርቅ ያለሽ ጠላኋት እያልኩኝ.. . አደባባይ መሀል ቆሜ ብፎክርም አንቺን ላለማሰብ ሞልቶልኝ አያውቅም። . #ግጥምና አንቺ አንቺ እና ግጥም የልክፍት ጥርቅም አቃጣይ ተብለው እጅን ለመሰብሰብ ማባያም ተብለው ደርሶ ለመንገብገብ እንደማይመቹት ... አዋዜ ፣ ሰናፍጭ ... ዳጣ አይነት ናችሁ አቃጣይ ቢሆንም ቅመም ነው ፍቅራችሁ ጠልቼ አልጠላችሁ! @getamiyan @getamiyan @getamiyan #Mikael aschenaki

#እምነተ_ቢስ_አማኝ ህላዌ ለራቀው መኖር ለናፈቀው ለምስኪኑ ልቤ እምነት ባልኩት ካባ ማፍቀሬን ሸሽጌ በለይል መቆሚያ እንባ ተሰንጌ አንቺን ብጠይቀው ደጁ ተንበርክኬ እምነት ለጎደለኝ ለእምነተ ቢስ አማኝ ይኸው አንቺን ሰቶ ጀሊል ራሱን ቀማኝ ለምን አይሉት እንዴት የሁሉ ባለቤት ሁሉም ይሁን ካለ እሱ ከፈቀደው አሚን ባይ ነው እንጂ የለም የሚያግደው ግና እሱ እንደነገረን ያኔ ትላንትና ሴጣን ነበር ስሩ ነብስያው ሳይሸፍት ሳይሽት ለወንበሩ ያኔ ዝም ያላለ ሰይጣን ሲሰየጥን ለወንበር ሽኩቻ እኔን ዝም ይላል ወይ ስገዛ አንቺን ብቻ እንጃ በዚ በኩል ፍቅር በዚያ በኩል ፍርሀት ነብሴን ሲሰንጋት አመልጣለው ብዬ ደሞ ከሱ ቅጣት ካንቺ ጋር መጣላት አንቺን ላለመጣት ጀሊሉን መሰዋት ልኩን ለመለካት መለኪያውን መሳት እፀድቃለው ሲሉ እኩነኔ መግባት ሆነና ተግባሬ ላንቺ ተገዝቼ ዙፋኑን ባሳጣው የሰራው እኔነት ጀሊሉን አስቆጣው ለካ "ጀሊሉ ሲቆጣ ብትርን አይቆርጥም ያደርገዋል እንጂ ነገርን እንዳይጥም" ይኸው ኑሮ እየወበራ ነብስ እየቃተተ ልክ ነው ይለኛል ልኩን እየሳተ ድሮም በነተበ እርምጃ እደርሳለው ባልኩት እግሬን ሳምነው ነበር መንገዴን የሳትኩት ✍ @Tufaw_muhe @getamiyan @getamiyan @getamiyan

...... #ትንሳኤ ....... መድኔ....ስለኔ አከላቱ ደምቷል፣ የበደሌ ሸማ በሞቱ ተገፏል፣ እነሆ ...ተነስቶ ለዘላላም ነግቷል ። ፨፨፨ ሀጢያተኛው እኔ... ከነ ግሳንግሴ የጥፋቴ ጋሪ ፥ ከብዶ ለፈረሱ ሳያወላክፈኝ..... ፊዳ ሆኖ እርሱ በእድፋም ገላ ፥ ክንዱን መንተራሴ ሞቴን ቢሞትልኝ ፥ነፃ ወጣች ነብሴ። #ክበር _ተመስገን!! ✍ #አብርሀም_ተክሉ ( #መርዕድ) @Getamiyan @getamiyan

#__ቁዝም.... የዘመን መገለጥ ...የጀምበር ወጋግታ እኩል አይታይም ለእኩል ስጋ ለባሽ ...እኩል ባንድ ቦታ ። እያረፋፈደ የሚገለጥ ሰማይ ሰው እያጋደመ ፥ ሰው እያፋረደ ጨክኖ መጨከን የተለማመደ የቀደመው ነቅቶ ፥ የተኛ እያረደ ነጋ...ነጋ ...ባዩ ሽመሉን ወልውሎ ፥ በነጋው ወረደ ። ወ ረ ደ መአቱ ክንትው ....አለ ስንቱ ሺ ዘመን ቢኖሩ ... ነገ መሰወሩ ያለመገመቱ የትላንትና እሾ ዛሬም መዋጋቱ ለነገ ጠባሳ ሽንቁር ማበጀቱ ክ ፋ ቱ ይገርማል !!! በንዲህ ያለ ግዜ መላ ቅጡን ባጣ ፅልመት ያው....ፅልመት ነው ተገባም ....ተወጣ ሁሉን ይጋርዳል ከነጭ ጥርስ ኋላ የውሸት ቅጥልጥል ፥ በሌት ይገመዳል እውነት የሚመስል ተቀፅላ ሀሰት ፥ ሴረኛው ይወልዳል የተወለደም ዘር ባድርባይ እንኮኮ ፥ ተንፈላሶ ያድጋል ቀመሩ ያልገባው ልቡ የታወረ ኗሪ እንደ ደረጃው ለእግሩ ጧፍ ያነዳል ጉርሱን ቶሎ ጎርሶ ... ፍንጥቅ ላምባ ደፍኖ ፥ ትልቅ ሌት ይለምዳል እንዲ ነው ክፉ ቀን ይሄ ነው ጨለማ ይህ ነው ሰንካላ እድል እግር እየነሳ ፥ ክራንቹን የሚያድል ስጋ የሚያተላ ... ወገን የሚያጋድል ይህ ነው እርኩስ ወራት ይህ ነው ብላሽ እድል ምንም ማለት ማቃት ምንም ማድረግ መሳን ብዙ ጉድ ባለበት ... ባሰቡት ያነዳል ዳሩ ቀን ሲጎድል ቀን ሲጥል ቀን እንጂ ከፈጣሪ በቀር ፥ መች ሰው ይማለዳል ? የት ችሎስ ይፈርዳል !!! #አብርሀም_ተክሉ @Abrham_teklu @getamiyan @getamiyan

# ነብስ_ይማር . አትጠብቁ ከቶ፣ ቀጠሮ አትያዙ ለዋይታ ለልቅሶ ካፈር እስክገባ ጉዱጓዴ ተምሶ! : በፊቴ አፍስሱልኝ የወዳጅ እንባውን ባንገቴ አጥልቁልኝ ጉንጉን አበባውን፣ ፡ ብርሃን ሲያኮበኩብ ፅልመት ሲያንዣብብ፣ ቀኔን ነጥቆኝ ሊሮጥ ሌቱ ሲንደረደር ነብስ ይማር ነው እንጂ አትበሉኝ ደና 'ደር! የ'ድሜ ሽኝት ሐውልት የለት ተለት ሞቴ የመቃብር ላይ ፁፍ ጥቅስ ናት ህይወቴ!! -----------------------//----------------------- ( በርናባስ ከበደ ) @getamiyan

ቅ ና ት ! (( በአበባው መላኩ)) ======©====== . ፍቅሬን ሜዳ ላይ ጥላ ስትከዳኝ አይቻታለሁ እንደገፋችኝ ትገፋ እያልኩ እረግማታለሁ። ~ ዘወትር ሙሾ ታላዝን የዕንባ ማዕበል ይጠባት ደስታዬን እንዳጨለመች ደስታዋ ይጨልምባት ሺህ እጥፍ ትጨድ አበሳ ለዘራችብኝ ጥፋት። ~ እያልኩ እረግማታለሁ። … የኮራችበትን ገላ መብረቅ ያንድደው በቁጣ በላይዋ ዲን ይውረድባት ጥጋት መሸሻ ትጣ። ~ እያልኩ እረግማታለሁ። … የምድር የቀላይ ጥፋት በላይዋ ይውረድ ኩነኔ ኑሮዋን ሲዖል ያድርገው ስቃይዋን ያሳየኝ በዓይኔ። እንደከዳችኝ ትከዳ የኔ ያለችው ይሽሻት ቀላዋጭ ዓይኗን ያፍርጠው ከውካዋ እግሯን ያልምሻት። ~ እያልኩ እረግማታለሁ ። … ክንዷ በመጅ ይሰበር ሌላ ያቀፈችበት አባጨጓሬ ይሙላው ፍራሹ የተኛችበት። ~ እያልኩ እረግማታለሁ። … የሌላ ሆና ብትከዳኝ አይጠሉ ጠልቻታለሁ ስለማተቤ ብጠየቅ በዓለም ላይ ካለ የምሻው የረገምኳትን እላለሁ ሌላም እርካታ የለኝ እሷን አምጡልኝ እላለሁ። ~ ጥላቻዬና ፍቅሬ ናት እርግማኔና በረከቴ ያለሷ ሕይወት የሌለኝ ያሳበደችኝ ቅ ና ቴ ። @getamiyan