School Of Mali
Open in Telegram
Its a channel opened by the Administration of the school to Provide Necessary Information for the School Community.
Show more592
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
እንኳን ደሰ አለን ደሰ አላችሁ ሰኩል ኦፍ ማሊ በዙሪያችን ከሚገኙት 8 የግልና የመንግሰት ትምህርት ቤቶች መካከል በጥያቄና መልስ ውድድር ዛሬ እንደወትሮ አንደኛ በመወጣት ተሸላሚ ሆኗል እንኳን ደሰ አለን እንኳን ደሰ አላችሁ!!!ታህሳስ 2016 ዓም
ለሰርቢስ ተጠቃሚዎች በሙሉ
በ14/01/2016 ዓ.ም የሰርቢስ አገልገሎት እንደምንጀምር ማሳወቃችን ይታወቃል::ሆኖም የሚቀጥለው ሳምንት በባዕላት ምክንያት ትምህርት የማይኖርበት ቀናት በመኖራቸው የመሰከረም የትራንስፖርት ክፍያን ወደ ጥቅምት በማዞር በ28/01/2016 የትምህርት ቤቱ የሰርቢሰ አገልግሎት የምንጀምር መሆኑን በአክብሮት እንገልፃለን።
።።።።።።።።ለውድ ስኩል ኦፍ ማሊ ወላጆች/ህጋዊ አሳዳጊዎች ።።።።።።።።።።።
የ2016ዓ.ም የትምህርት ዘመን ሰኞ፣ መስከረም 7፣2016 ዓ.ም ይጀመራል። ትምህርቱም የሚሰጠው የመጀመሪያ ሳምንት ግማሽ ቀን ይሆናል። ስለዚህ ወላጆች ይህን አውቃችሁ ልጆቻችሁን ከመስከረም 7፣2016ዓ.ም ጀምሮ ወደ ትምህርት ቤት እንድትልኩ ስንል እናስታውቃለን።
በመጀመሪያ የከበረ ሰላምታችንን እያቀረብን ለወላጆች/ሕጋዊ አሳዳጊዎች በተለይም አዲስ ለሆኑት የሚከተሉትን ነጥቦች ማስገንዘብ እንወዳለን፡፡
# ሁሉም የት/ቤታችን ተማሪዎች የት/ቤቱ ባጅ ያለበትን ሹራብ፣ እጅ ሙሉ ሸሚዝ፣ ሱሪ ጉልበት ድረስ መሰብሰብ የሚችል እና ለሴቶች ቀሚስ ከጉልበት በታች ዩኒፎርም መልበስ አለባቸው ፡፡ ካለ ት/ቤቱ ዩኒፎርም የሚመጣን ተማሪ ወደ ት/ቤቱ ቅጥር ግቢ የማናስገባ መሆናችንን እናሳውቃለን፡፡
# ወንዶች ተማሪዎች ፀጉራቸው እኩል ሆኖ ባጭሩ መቆረጥ (መስተካከል) አለባቸው፣ ሴቶች ተማሪዎች ደግሞ ሹሩባ/ ቁጥርጥር መሠራት አለባቸው።
# ማንኛውንም አይነት ጌጣጌጥ ( አምባር፣ ተንጠልጣይ ጉትቻዎች፣ የአንገት ሃብሎች እና የመሳሰሉትን) እና ኤሌክትሮኒክስ ( ሞባይል፣ ስማርት የእጅ ሰዓት፣ አይ ፓድ እና የመሳሰሉትን) ይዘው መምጣት ፈፅሞ የተከለከለ ነው።
# ተማሪዎች ወደ ት/ቤት ሲመጡ በቂ ምግብ መያዝ አለባቸው፡፡ እባክዎ በምሳ ዕቃዎቹ ላይ የተማሪዎቹ ስም መለጠፉን ያረጋግጡልን፡፡
# ወላጆች /ሕጋዊአሳዳጊዎች ተማሪዎች በቂ የሆነ የትምህርት መሣሪያዎች እንዳለው/ላት/ላቸው እርግጠኛ መሆን አለባቸው፡፡
# ተማሪዎች ወደ ት/ቤቱ በሰዓቱ መምጣት አለባቸው፡፡ልብ ይበሉ የት/ቤቱ በር ከጥዋቱ 1፡00 ጀምሮ ክፍት ሲሆን ትምህርቱ 2፡00 ላይ ጀምሮ 9: 30ሰዓት ላይ ያበቃል፡፡ በመጀመሪያ ሳምንት 2:00 ጀምሮ 6:00 ሰዓት ያበቃል
# ወላጆች /ሕጋዊአሳዳጊዎች ልጃቸውን/ልጆቻቸውን ለመወሰድ ሲመጡ የት/ቤቱን የተማሪዎችን መታወቂያ ካርድ የግድ መያዝ አለባቸው፡፡ መታወቂያውንም በር ላይም ለመምህራን ለአስተዳዳር ሰራተኞች /ለጥበቃሠራተኞች ማሳየት አለባቸው፡፡ ካለ ት/ቤቱ መታወቂያ ተማሪዎች እንዲወጡ አይፈቀድላቸውም፡፡
ስኩል ኦፍ ማሊ እስተዳደር
፨፨፨ማስታወቂያ ለወላጆች በሙሉ፨፨፨፨
ትምህርት ቤታችን ያስፈተናቸውን የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች በከፍተኛ ውጤት ወደ7ኛ ክፍል ማሳለፍችን ይታወቃል ሆኖም ምዝገባ የሚከናውንው በ27/11/2015 እና በ28 /11/2015 ብቻ መሆኑን አውቃችሁ እንድታስምዘግቡ እያሳሰብን ከተቀምጠው ቀን ውጪ የሚማጣ ተማሪን ትምህርት ቤቱ ሃላፊነቱን የማይወስድ መሆኑን እንገልፃለን::
