merkatotube
Open in Telegram
Important Ethiopian and international news. If you have tips/ጥቆማ @merkatotube_bot We are open 24/7
Show more9 376
Subscribers
-224 hours
-387 days
-11130 days
Posts Archive
9 376
ይህ ተደጋጋሚ ክስተት የዜጎች በሕይወት የመኖር፣ ከቦታ ቦታ ተንቀሳቅሶ የመሥራት፣ የአካል እና የንብረት ደኅንነታቸው፣ የሃይማኖት እና የእምነት ነፃነት ስጋት ላይ ከመጣሉ በሻገር “የዜጎችን ሁለንተናዊ ደኅንነትን የመጠበቅ እና የማስጠበቅ ግዴታ ያለባቸውን አካላት በሙሉ በምድርም ሆነ በሰማይ ተጠያቂ የሚያደርግ ጉዳይ ነው” ብሏል።
@merkatotube @merkatotube_bot
9 376
ጄኔራል አብዱልፈታህ አልቡርሃን የሚመሩት ኃይል የፈጥኖ ደራሽ ኃይልን ካለፈው ዓመት ታኅሣሥ ጀምሮ ሲፋለም ቆይቷል። ጂቡቲ በተደረገው ጉባኤ አብዱልፈታህ አልቡርሃን ተገኝተዋል። የኢጋድ መሪዎች ፈጥኖ ደራሽ ኃይሉን ከሚመሩት ጄኔራል ሐምዳን ደጋሎ ጋር በስልክ መነጋገራቸውም ተመላክቷል።
@merkatotube @merkatotube_bot
9 376
አምባሳደር ተሾመ፤ ከአማራ ክልል የሚነሳው የአካባቢ ይገባኛል ጥያቄ እና የኤርትራ ሠራዊት በድንበር አካባቢ እያደረገ ያለው እንቅስቃሴ በትግራይ ክልል እና በፌደራል መንግሥት መካከል ያለውን መተማመን “ሊሸራርፍ” እንደሚችልም ገልጸዋል።
@merkatotube @merkatotube_bot
9 376
ስማቸውን እንዲጠቀስ ያልፈለጉ ሌላ የአጣዬ ከተማ ነዋሪ ሕይወታቸውን ያጡት “ሁለት ጠና ያሉ ሴት የባጃጁ ተሳፋሪዎች” መሆናቸውን ገልጸዋል። ሦስተኛው የከተማዋ ነዋሪ በበኩሉ “ቁጥራቸውን ይሄን ያህል ማለት አይቻልም። አሁንም በከተማዋ ውስጥ የተኩስ ልውውጡ ስላልቆመ እንኳን ቁጥሩን ለማወቅ ይቅር እና እነማን እንደሞቱም ለመለየት አዳጋች ነው” ሲል የሟቾቹን ቁጥር በአሃዝ ለማስቀመጥ አንደሚያስቸግር ተናግሯል።
@merkatotube @merkatotube_bot
9 376
አቶ ታዬ ደንደአ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ከሥልጣናቸው የተሰናበቱት በአገሪቱ ያለው ጦርነት እንዲቆም ጥሪ በማቅረባቸው እንጂ ሌላ ምክንያት እንደሌለ ለቢቢሲ ተናገሩ።
@merkatotube @merkatotube_bot
9 376
የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታ የሆኑት አቶ ታዬ ደንደአ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ደብዳቤ ከሥልጣን መነሳታቸውን የሚገልጽ ደብዳቤ እንደደረሳቸው አስታወቁ።
@merkatotube @merkatotube_bot
9 376
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች በአገልግጋዮች፣ በምእመናን እና በአብያተ ክርስቲያንት ላይ እየተፈጸመ ያለው ድርጊት በምድርም በሰማይም የሚያሰጠይቅ ነው አለ።
@merkatotube @merkatotube_bot
9 376
በአማራ ክልል፣ ሰሜን ሸዋ ዞን፣ አጣዬ ከተማ ከትላንት እሁድ ረፋድ ጀምሮ በመከላከያ ሠራዊት እና በታጣዊዎች መካከል በተደረገ የተኩስ ልውውጥ የሰዎች ሕይወት ማለፉን ነዋሪዎች ተናገሩ።
@merkatotube @merkatotube_bot
9 376
በአማራ ክልል ከመንግሥት ጋር ውጊያ ላይ ያለው የፋኖ ኃይል በአንድ ዕዝ ሥር አለመሆኑ መንግሥት ከኃይሉ ጋር ለሚደረግ “ንግግርም ሆነ ድርድር” አመቺ እንዳልሆነ የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር ተሾመ ቶጋ ተናገሩ።
@merkatotube @merkatotube_bot
9 376
የሐማስ ወታደራዊ ክንፍ የሆነው የአል-ቃሳም ብርጌድ ቃል አቀባይ በእስራኤል-ጋዛ ጦርነት ጎልተው ከወጡት መካከል አንዱ ነው። “አቡ ኡቤይዳ” በመባል የሚታወቀው ግለሰብ በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ የቡድኑን መልዕክት በበይነ መረብ ሲያሰራጭ ደጋግሞ ይታያል።
@merkatotube @merkatotube_bot
9 376
ስለ ታንዛኒያ ምክንትል ፕሬዝዳንት ፊሊፕ ምፓንጎ የጤና ሁኔታ ሐሰተኛ መረጃ በማሰራጨት የተጠረጠሩ የማኅበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ላይ በአገሪቱ መሪዎች ምርመራ እየተደረገ እንደሆነ ተገለጸ።
@merkatotube @merkatotube_bot
9 376
በገጠራማዋ ቻይና የነበረውን የኤድስ ወረርሽኝ ያጋለጡት እና ለግዞት የተዳረጉት ቻይናዊቷ ዶክተር ጋኦ ያኦጄ በ95 ዓመታቸው አረፉ።
ከአውሮፓውያኑ 2009 ጀምሮ ለስደት የተዳረጉት ዶክተር ጋኦ በኒውዮርክ ህይወታቸው ማለፉን ጓደኛቸው አስታውቀዋል።
@merkatotube @merkatotube_bot
9 376
በስፔን ላ ሊጋ ግራናዳ ከአትሌቲክ ቢልባዎ የሚያደርጉት ጨዋታ የአንድ ተመልካች ሕይወት በማለፉ ምክንያት ተቋርጧል።
በኑዌቮ ሎስ ካርሜኔስ ስታድየም የነበረው የላ ሊጋ ጨዋታ ሰኞ ዕለት ከተቋረጠበት እንደሚቀጥል ተሰምቷል።
@merkatotube @merkatotube_bot
9 376
ለሁለት ዓመት የዘለቀውን ደም አፋሳሽ ጦርነት ማክተሙን ተከትሎ አርሶ አደሮች ወደ እርሻቸው ቢመለሱም በድርቅ ምክንያት ለከፋ የምግብ እጥረት ተዳርገዋል።
እርጅና እና መከራ የተፈራረቀባቸው አርሶ አደር ገብረመድኅን ገብረማርያምን ቢቢሲ ያገኛቸው በደጃፋቸው ከተቀመጠ ያልተወቃ ትንሽ የባቄላ ክምር ፊት ተቀምጠው ሲቆዝሙ ነው።
በአካባቢያቸው ያጋጠመውም ድርቅ ምን ያህል የከፋ እንደሆነም ሲናገሩ በሐዘን ነው።
@merkatotube @merkatotube_bot
9 376
በቁጥር 200 የሚሆኑና ከዩኬ ጎን ተሰልፈው ታሊባንን ሲፋለሙ የነበሩ የአፍጋኒስታን ልዩ ኃይል ወታደሮች ‘ዩኬ ክህደት ፈጸመችብን’ ሲሉ ቅሬታ አቀረቡ።
@merkatotube @merkatotube_bot
9 376
በሱዳን እየተፋለሙ ያሉት ኃይሎች የተኩስ አቁም ስምምነቱን እንደሚያከብሩ መስማማታቸውን ኢጋድ ገለጸ።
የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት (IGAD) እሑድ እንዳስታወቀው እዚህ ስምምነት ላይ የተደረሰው በጂቡቲ በተደረገ የአባላት አገራት ስብሰባ ነው።
@merkatotube @merkatotube_bot
9 376
እስራኤል በጋዛ ላይ አጠናክራ የቀጠለችው የማያባራ የቦምብ ጥቃት የተኩስ አቁም ስምምነት ዕድሉን እያጠበበው ነው ሲሉ የኳታር ጠቅላይ ሚኒስትር ተናገሩ።
ሼክ መሀመድ ቢን አብዱልራህማን አል ታኒ በዶሃ ጉባኤ ላይ እንደተናገሩት ኳታር ሁለቱ ወገኖች የተኩስ አቁም እንዲያደርጉ ግፊት ማድረጓን ትቀጥላለች።
@merkatotube @merkatotube_bot
9 376
በሱዳኗ መዲና ካርቱም በእርዳታ መኪኖች ላይ ‘‘ሆን ተብሎ በተፈጸመ ጥቃት’ ሁለት ሰዎች መገደላቸውን አለም አቀፉ ቀይ መስቀል አስታወቀ።
በዚህ ጥቃት ከሟቾቹም በተጨማሪ ሰባት ሰዎችም መቁሰላቸው ተነግሯል።
@merkatotube @merkatotube_bot
9 376
በኢትዮጵያ ውስጥ በተለይ ለሕጻናት እና ለታዳጊዎች የሚሆኑ መጽሐፍትን የሚቀርቡ ቤተ መጽሐፍትን በገጠሩ ውስጥ ብቻ ሳይሆን በከተሞች ማግኘት አዳጋች ነው። ከዚህ አንጻር ሕጻናት የማንበብ ልማዳቸውን ለማዳበር ያለባቸውን ችግር የተገነዘበችው መምህርት ኤልሳቤጥ፣ በእራሷ ጥረት በአንድ የገጠር መንደር ውስጥ ለሕጻንት የሚሆን ቤተ መጽሐፍትን ከፍታለች።
@merkatotube @merkatotube_bot
9 376
‘የጠፉ መጽሐፍት አዳኙ’ ኤልያስ ሜክሲኮን እስከ ወዲያኛው ይሰናበታት ይሆን?
ኤልያስ ገብረማሪያም ንባብ በሚያዘወትሩ አዲስ አበቤዎች ዘንድ የሚታወቅ ስም ነው። ዋቢ ሸበሌ ሆቴልን አለፍ እንዳሉ ነጠላ ጫማ የተጫማ ባለ‘ድሬድ’ ፀጉር ጎልማሳ ከተመለከቱ እሱ ኤልያስ ነው።
“ሜክሲኮ አምደ መጻሕፍት” ሲል የሰየማት እና ባለ አስራ አንድ ወለሉን ሸበሌ ሆቴልን ሽቅብ የምትመለከተው የመጽሐፍት መደብሩ ላለፉት አስር ዓመታት ከሜክሲኮ መልኮች አንዷ ነበረች።
ኤልያስ ጋር ተፈልጎ የማይገኝ የድሮ መጽሐፍ አለመኖሩን ቢቢሲ ያነጋገራቸው ደንበኞቹ ይገልጻሉ። ከአገርኛ የሥነ ጽሑፍ ሥራችዎች እስከ ብሉይ (classical) የሩሲያ ልቦለዶች ድረስ ከኤሊያስ መደርደሪያ ላይ አይታጡም። ከዘመን አይሽሬዎቹ የኩራዝ አሳታሚ ውጤቶች እስከ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬስ የአካዳሚ መጽሐፍትም ይገኛሉ።
የማስታወቂያ ሰሌዳ ተጎራብታ የምትገኘው መደብር የመጽሐፍ መሸጫ ብቻ አልነበረችም። “ሜክሲኮ አምደ መጽሐፍት” ከዘመድ ወዳጅ ጋር መገናኛ፣ አዳዲስ ሰው መተዋወቂያም ጭምር ነበረች።
@merkatotube @merkatotube_bot
