ግጥም ከሁኔታ
ሰላም ሰላም ይሄ የግጥም ስፍራ ነው ስሜት በሚገልፁ ቃላት ተጭነው ከሚፀፉ ግጥሞች በተጨማሪ #ለprofile_ለwallpaper ስራ ጀምረናል our link @freepoems Inbox @Tumaybot advert our channel Share our posts and we are happy #ግጥም_ከሁኔታ
Show moreThe country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
326
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
- Subscribers
- Post coverage
- ER - engagement ratio
Data loading in progress...
Subscriber growth rate
Data loading in progress...
እሷን ማግኘት እያለ በቀንዱ
ተዋት ይሉኛል ምንም ሳይረዱ
ምርጫዬ አሳጥረው ስሜቴን በከንቱ
የታሰረው ልቤን በእጃቸው ሊፈቱ
እንኳንስ ልተዋት ባላያትም ጭሱ
እንኳንስ በውኔ ህልሜ ላይ በራሱ
ህልምም አይመጣልኝ እሷ የሌለችበት
ታሸንፈኛለኝ ምኗ ላይ ችዬበት
ተዋት የምትሉኝ መሞከር ደክሞኛል
እሷን ከመተው ራሴን ይቀለኛል
ርእስ_እንዴት ብዬ
Alisen
🖌
❣
🕳
ጨለማ ከሆነው ባልነካቺው ጀምበር
ብቻዬን ስራመድ ለራሴ ስናገር
ስንቱን ስነካካ እንዳልኖር በልኬ
ቁስሉን እየኖረ አይድንም ታሪኬ
አልቅሶ የማያቆም አይኔ ቀኑ ደረሰ
ዛሬም እያመመው እምባው ተጨረሰ
እምባው ቢጨረስም ማልቀስ አላቆመም
ለውስጥ ቢያለቅስ እንኳን ብዙም አልቀጠለም
ፀሀይ ከመታቺው ብረቱ ይሞቃል
ትዝታ ሲነካ ልቤም ይቃጠላል
የሚሆነው ሳያጣ በእጁ እያነሰ
ክብሩ በሰው ወሬ ሄዶ ከረከሰ
በትላንቱ ታስሮ ትዝታ እያፈሰ
አለው ለሚል ወዳጅ ታይቶ እየጨሰ
በጨለማው ግና አገኘው መፍትሄ
ከሄደበት እግሯ ይከተል እልሄ
ከመንገዴ ወለል አለኝ ምስሏ
ታየቺኝ ከመድረክ በሙሉ ስራዋ
ሰው የለም የሚያይልኝ ይሄን
እያሙ አይግደሉኝ ይመልሱት ክብሬን
የሚያባብል የለም ወይም የሚያባብስ
እጮሃለሁ እነጂ ንዴቴ እስኪነፍስ
ራሴን ስጥል ሳለቅስ በሃዘኔ
ሰው አይጠፋም አያጣኝም እኔን
የጨለመ ታሪክ ከውስጤ ታቅፎ
አታውጣው የሚል ህግ በእጇ ተፅፎ
ኖርኩኝ ህጉን ሳከብር ለምኔ
አምባው ከጨረሰ የሚያለቅሰው አይኔ
ለውስጥ ያለቀስኩት ተከማችቶ ዛሬ
ከጨለማ ስጓዝ ተከፈተ በሬ
በራሷ ህግ ካሰረቺው ቦታ
ልቤ ነፃ ሆነ ዛሬኮ ተፈታ
በማይታይ ምንም በድቅድቅ ጨለማ
መካሪ ሳይኖር ልቤ ጀሮ አውጥቶ የሚጠቅመው ሰማ
ካስተኛቺው እንቅልፍ ከህልሙ ባነነ
መድሀኒት ሳይፈልግ በጨለማው ዳነ
ምንም ከማይታይ እጅግ ከጨለማው
የልቤ ጨለማ አምስሎ ያቆመው
ጀምበር ላልነካው እጅግ ላመስግነው
ጀምበር ለነካቺው ልቤን ለበደለው
ስንት እንዳላለፈ ለማየትም በቃው
በቀን ተኝቼ በጨለማ ነቃው
በምሽቱ ስሄድ በሃሳብ እይታ
ከማይታይ ቦታ ሰው ታየኝ በማታ
ርእስ_ሰው ታየኝ በማታ
Alisen
🖌
💭
*
*
*
እጅሽ ይሄ አይገባውም
ቀን ወጣልኝ ሲል ሊያመሰግን
አግኝቶ ቀልሎበት ልቤ ሲደነድን
ስለ ሌላ ማየቱ ስለ ሌላ ማሰቡ
በራቀኝ ልቦናው በራቀብኝ ቀልቡ
ብቻዬ አልቆምኩኝ እያለች ከጎኔ
ምን ነበር የጋረደው እንዳያይሽ አይኔ
አልጠፋም መኖርሽ በግዜው በዝቶበት
ሳያመዛዝን ኮርቶ ነገሮች ቀልሎበት
ለማያውቀው ዋጋው ፍቅር መግበሽው
ብቸኛ ባልሆነው እኔ አለው ብለሽው
ልቤ ግን እውር ነው አያይም ሲበዛ
ጭንቅላቴ ድንቁርናው አያስብ እንደዛ
ከላይ የወረደች እርግብ የመኖሩ ደስታ
የከበረ ፍቅር ስትሰጠው ከልቧ አውጥታ
ስታቅፊው በክንድሽ ያልታየው አይኔ ግን
ንቆ ጉዳዩ እንዳልሆነ በሌላ ሊባንን
የእጁን ያላገኘው እጅሽ ደርቆ
በበረደሽ ኣንቺ የኔ ገላ ሞቆ
የእጁን ያላገኘው ልብሽ እርቦት
የኔ ልብ ግን ጠግቦ ያንቺ ልብ መግቦት
የእጁን ያላገኘው እግርሽ ደክሞት
ቤቴ ሲመላለስ መራመድ አቅስሎት
የእጁን ያላገኘው እውነትም ህሊናሽ
ክብር በሰጠ እጁ ተንቆ እንደ ትንሽ
ስንቴ ልትቋቋም ልትችለው የኔ ነገር
ሰጥታ ለማታገኘው የሚፈለግ ፍቅር
በርሮ ባረፈበት እግሯ በኔ ህይወት
ያኔ ኮርቶ ልቤ አሁን በናፍቆት እስኪሞት
በሄድሽበት መንገድ በጎ እንዲያጋጥምሽ
ብቻዬን እላለው የት ሂጄ ላገኝሽ
✍Alisen... @Alek18
╔════✿💌♡💌✿═════╗
☞ join & share ☜
☞ @POEM_CHANNAL☜
╚════❀💌♡💌❀═════╝
ጣጣዬ ብዬሽ ነበር የምጨነቅላት
አንዲች ጠርታኛለች ዛሬ እሷን ላገኛት
ነገ እሷን ጣጣዬ እንኳን ብላት
ትላንት የኖረቺኝ በፍፁም አልረሳት
ከነገ ወዲያ ደሞ ኣንቺን ሳገኝሽ
ሌላ አወጣልሻለው ምንም አይጭነቅሽ
መቀመጫ ከሌለው ስፍራ ቆሜ
መቀመጫ የምፈልግ እጅግ ተዳክሜ
መቀመጫ ቦታ አግኝቼ ቁጭ አልኩኝ
እዛ ነው ያላቹት ከሄድኩ እኮ ቆየሁኝ 😁
✍ Alisen
ትላንትና
አንድ ግሮሶሪ እየጠጣው ትላንት
እየሞቀኝ በሄደበት ሰዓት
ጭፈራ ቤት ከቅርቡ ወደ አለው
ወስውሶኝ ጭፈራው ወደዛ እገባለው
ከሴቶቹ መሀል በጣም ትታያለች
አይቼ አልተወኳትም ተመችታኛለች
እንጨፍር ብያት ሞቅ ብሎኛል እኔ
ማውራቱ ጀምረን ቢሆንም በቅኔ
ተመቸኋት እኔም ከጎኔ አልራቀችም
ለማምሸት መረጠች ንቅንቅ አላለችም
ትጠጣለች እስዋ እኔን አላየችም
ምን ይምጣ አይምጣ ምንም አይጨንቃትም
የሌለ ሰክሬ እሷም ስክር ብላ
መሄድ አቅጧት ከእጄ ተጥላ
ስነሳ ጥዋት በማለውቀው ቤት
ውብ ከሆነች ልጅ ተኝቼ አረፍኩት
Join for @freepoems
💜🖊 Alisen
@Alek18
እጠብቅሻለው
ተቀይመሽኛል አቃለው አቃለው
ናፍቆት ተሸክሜ እንነበርኩ አለው
ያን ያህል ጥምረት በትንሽ ቀናቶች
ያለያዩን እነዛ ሁለት መንገዶች
ጠፋኝ የት ላገኝሽ ከየት ልፈልግሽ
መውደዴ እያወቅሽ ያሳለፍነው ትተሽ
ግን አልይዝልሽም ጥለሺኝ ብትሄጂም
አንቺን ለመመለስ ቀን ለኔ ቢመሽም
ምንም ቢፈጠርም ተስፋዬ ገና ነው
ትመጪ እንደሆን በህልሜ አይሻለው
በትዝታ ፍሰት ከውስጡ እስቃለው
ተስፋዩ ገና ነው እጠብቅሻለው
join For @Freepoems
💛🖋 Alisen
@Alek18
ደስታም ሀዘን የኔ ጓደኞቼ
አንዱን መርጠው ሁለቱም የሚያዩ አይኖቼ
ምርጫ ቢያደርጉም መሬት ላይ የሌለ
መጨፈን አይቻል ህይወት ከቀጠለ
ማማረር እና ማመስገን ለክፈዉኝ
አንዴ ከደስታ አንዴ ከሀዘን ጥለውኝ
ማማረር ሲጠፋ ማመስገን ከኔ ጋር
የተሰጠኝ ጠጋ በደስታ ሳከብር
ማመስገን ሳበዛ ያ ማማረር የሚባል
የጎደለኝ አሳይቶ አሳብዶኝ ሁሌ በኔ ይስቃል
መጋፈጥ ወይም መሸሽ ሁለቱም መንገዶች
የሚያስተምሩኝ ነገር በግዜ ቀናቶች
ያጠነክሩኛል ሁሌ እንድ በርታ
በዚ አለም ያለ ትልቁ እውነታ
ቀላል የማናየው በርቀት እይታ
ግዜ ያህል የልም ትልቅ ስጦታ
እኔ እኖራለሁ እስከ እለተ ሞቴ
ሁሌ ከማይጠፋ ትልቁ ፀሎቴ
የምወዳቸው ሰዎች ከኔ ዘንድ እንዲኖሩ
ሳያማርሩ በአላቸው ጠጋ ሁሌም እንዲኮሩ
በበለጠ ደሞ ለታላቋ የምወዳት እናቴ
ከፍቷት እንዳልሰማ እስከ እለተ ሞቴ
ርእስ_ኑሮዬ የምለው
🖌
ALISEN
@Alek18