1 482
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
1 482
ብልጽግና እግረኛ ሰራዊት መጨረሱ ታወቀ!
**
የመረጃ ምንጮች እንደሚናገሩት የብልጽግና እግረኛ ሰራዊት አልቋል፡፡ አሁን ባለው አቅም ከሁለት ሳምንት የዘለለ ሊዋጋ የሚችል እግረኛ ሰራዊት የለም፡፡ በብልጽግና ግምገማ መሰረት አዲስ ምልምል አሰልጥኖ ለማድረስ ጊዜ የለም፡፡ ኢኮኖሚም የለም፡፡ ስለዚህ ለሚሊሻውና አድማ ብተናው ከፍተኛ ገንዘብ በመመደብ ለማዋጋት ነው እየተሞከረ ያለው፡፡ በተጓዳኝም በሽምግልና ስም እየሞከሩ ናቸው፡፡ የሆነ ሆኖ ወታደራዊ ብቻ ሳይሆን የኢኮኖሚና የፖለቲካ ውድቀቱ አገዛዙን በአፍ ጢሙ እየደፋው ይገኛል፡፡
--
Dr misganaw
1 482
Fano leaders make calls to the regime army and security forces to join and surrender to the Amhara popular forces in the coming 45 days!.
በአገዛዙ ውስጥ የሚገኙ የመከላከያ ፣ የፖሊስ፣ የደሕንነት፣ እና መሠል ታጣቂዎች እስከ ታሕሳስ 30/ 2016 የአማራ ሕዝባዊ ሠራዊትን እንዲቀላቀሉ እና እጅ እንዲሠጡ ጥሪ ቀርቧል።
1 482
የአማራ ፋኖ በወሎ ዕዝ ምስረታ ምክንያቶች ፤
የአማራ ህዝብን ህልውናን እና የሀገሪቱን አንድነት እየተፈታተነ ያለውን ፈሪና አረመኔያዊ ስርዓት ከመሰረቱ ነቅሎ ለመጣል ከታች በተዘረዘሩት ምክኒያቶች የአማራ ፋኖ ወሎ ዕዝ በመመስረት ትግሉ የሚጠይቀውን የአደረጃጀት የአመራርና የማስፈጸም ብቃት ማሳደግ አስፈልጓል።
1) የትግሉ ግብ በማደጉ፡- የአማራ ህዝብ ጥያቄ ሲጀምር አስተዳደራዊና ፖለቲካዊ የነበሩ ሲሆን ጥያቄዎችን በሰላማዊ መንገድ ለማስመለስ የሞከረ ቢሆንም ምላሽ ከማግኝት ይልቅ በተቃራኒው ዘር ማጥፋት ነበር የታወጀበት ስሆንም ጥያቄዎቹ መልስ ማግኘት የሚችሉት በስርዓት ለውጥ ደረጃ ወደ ሚደረግ ትግል በማደጉ፡፡
2) የትግሉ ደረጃ በከፍተኛ ሁኔታ በማደጉ ፡- በጥቂቶች የተጀመረዉ ትግል መላዉ አማራን ከማነቃነቅ አልፎ በኢትዮጵያ ጉዳይ የሚያገባቸዉን ሁሉንም ማህበረሰቦች ወደ ማሳተፍ በማደግ ትግሉ የአደጋ ጊዜ መዉጫ ትግል መሆኑን አዉቀዉ በተስፋ የሚጠብቁት በመሆኑ እና ይህንን የህዝብ ንቅናቄ መሸከም የሚችል አደረጀጄት፣ አመራርና የመፈፀም አቅም ማሳደግ አስገዳጅ ስለሆነ፡፡
ከፊታችን የሚጠብቀንን ሀገራዊ ሃላፊነት በሚገባ መወጣት ያስችለን ዘንድ ከወታደራዊ ኃይሉ በትይዩ የሲቪል አስተዳደሩን መሸከም የሚችል ኃይል ማዘጋጀት ምቹ ሁኔታ መፍጠር ስለሚያሰፈልግ፡፡
3) የትግሉን ጊዜ ማሳጠር በማስፈለጉ ፡- ትግሉ በተራዘመ ቁጥር ይህ ኃላፊነት የማይሰማዉ ስርአት በሀገሪቱ አንድነት እና በማህበረሰቦች መካከል የሚፈጠረዉ አለመተማመን አደጋ ስለሚጨምር ይህን ለመቀነስ ይቻል ዘንድ በተደራጀና በተቀናጀ አካሄድ ትግሉን ማሳጠር አስፈላጊ በመሆኑ፡፡
የሌሎች ብሔሮች ወይም ነገዶች በትግሉ የመሳተፍ ፍላጎትና ጥያቄ እየጨመረ በመምጣቱ ለዚህም ምቹ ሁኔታን መፍጠር አስፈላጊ በመሆኑ፡፡
4) ትግሉ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ መድረሱ ፡- ይህ መደራጃዉን ፍርሀት ያደረገ አዉዳሚ ስርአት በወሳኝ መልኩ ጦርነቱን ተሸንፏል ብለን እናምናለን፡፡ ለዚህም ተስፋ በቆረጠ ስሜት በምክርቤት ጭምር የሀገሪቱን ግዙፍ ተቋማትና ፕሮጀክቶች በመሸጥና በማቆም ለመዋጋት መወሰኑ እንደ ማስረጃ መውሰድ ይቻላል ፡፡ ይሁንና በወታራዊ አውደ ውጊያ ማሳካት ያልቻለዉን ህልም በሌሎች አዉደ ዉጊያዎች ለማካካስ ርብርብ እያደረገ ይገኛል፡፡
ለአብነት ፋኖን ከህዝቡ ለመነጠል ይረዳኛል ያለዉን ፦
⁼ አንደኛ ለመንግሰት ተጠሪ የሆነ ቀማኛና ዘራፊ ቡድን በፋኖ ስም በማደራጀት
⁼ ሁለተኛ ከፍተኛ መጠን ያለዉ ገንዘብ በመመደብ በትግሉ ዉስጥ የሚሳተፉ ግለሰቦችና ቡድኖችን በጥቅም በመደለል
⁼ ሶስተኛ በድርድር ስም የስልጣን ፍላጎት ያላቸዉንና የትግሉ እድገት ጋር አብሮ ማደግ ያልቻሉትን ግለሰቦች በመሸንገል
⁼ አራተኛ የህዝባችንን የመሰረተ ልማት አቅርቦት፣ የሸቀጥ ዝዉዉርን፣ የትምህርትና የጤና አገልግሎት አቅርቦትን፣ የግብርና ቴክኖሎጂ አቅርቦትን ወዘተ… በማስተጓጎል ህዝቡ እንዲማረርና ከትግሉ እንዲነጠል ለማደረግ የሞት ሽረት ርበርብ እያደረገ ይገኛል፡፡
ስለሆነም የትግሉን አደረጃት፣ አመራርና የመፈፀም አቅም በማሳደግ ሊፈጠር የሚችል የትግል ክፍተትን በመሙላት ስርአቱን በአጭር ጊዜ ውስጥ እስከ ወዳኛዉ ማስወገድ በማሰፈለጉ፡፡
5) አለማቀፉ ማህበረሰብ የትግሉን ምንነት፣ አስፈላጊነትና አደረጃጀት የበለጠ በሚረዳዉ ቅርፅና መልክ ማደራጀት አስፈላጊ ሆሞ በመገኘቱ፡፡
በእነዚህና በሌሎች ተያያዥ ምክንያቶች ዕዙ ሊመሰረት ግድ ሁኗል፡፡
ስለሆነም እኛ በመላው የወሎ ምድር በተለያየ አደረጃጀት እና ቅርጽ የምንቀሳቀስ የፋኖ ሃይሎች ተገናኝተን ባደረግነው ታላቅ ጉባኤ ከትብብር ወደ አንድነት በመሳደግ ዕዙን የመሰረትን መሆኑን ለተከበረው የአማራ ህዝብ ፣ ለኢትዮጵያውያን፣ በመላው ዓለም ለምትገኙ የትግሉ ደጋፊዎችና የትግል አጋሮቻችን ስናበስራችሁ በታላቅ ደስታ ነው፡፡
በዚህ መሰረት ፤
1ኛ.የዕዙ ስያሜ - የአማራ ፋኖ በወሎ ዕዝ
2ኛ.የዕዙ አደረጃትና ሃላፊነት
የዕዙ ዋና አዛዥ - ፋኖ ኮ/ል ፈንታው ሙሃባው
የዕዙ ም/አዛዥ - ፋኖ ምሬ ወዳጆ
የዕዙ አስተዳደር - ፋኖ አለምነው መብራቱ
የዕዙ ሎጅሰቲክ አዛዥ -ፋኖ ኮ/ል ሞገስ ዘገየ
የዕዙ የፖለቲካ ዘርፍ ሃላፊ - ፋኖ ሻፊ ሃብታሙ
ሆነው በጉባኤው በአብላጫ ድምጽ መመረጣቸውን እየገለጽን ትግሉ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ መድረሱን ማስገንዘብ እንወዳለን።
1 482
በአንድ ዕዝ ስር ካለው የአማራ ማህበራዊ ሚዲያ ሰራዊት የተሰጠ መግለጫ‼️
ለወገን ኃይል ሽፋን ለመስጠት ከኅዳር 23 ጀምሮ የአማራ ክልል ዋና ዋና መንገዶች በህዝባዊ ዘመቻ እንደተዘጉ እንዳሉ ይታወቃል፤ ይህም በርካታ ድሎችን ያለምንም ወይም በቀላል መስዋዕትነት ማሳካት ተችሏል።
እነዚህ መንገዶች "ለጥቂት ጊዜ ተከፍተው መልሰው ይዘጉ" የሚል ሃሳብ ኖሮ ነበር። ነገር ግን ይህ ሃሳብ ከወገን ኃይል ይሁንታ ማግኘት ስለነበረበት ንግግሮችን አድርገን የነበረ ሲሆን ተዘግቶ እንዲቆይ የጋራ ስምምነት ላይ ተደርሷል።
እኛ ሳናቅማማና ወልፈት ሳንል የትግል ሜዳው ላይ ያሉ ፋኖዎቻችን ትዕዛዝ ፈጻሚ ነን፤ መላው የአማራ ሕዝብ፣ እንዲሁም የማህበራዊ ሚዲያ ሰራዊቱም ለዚህ ተፈፃሚነት እንዲረባረብ ይሁን።
1 482
#እብናት
ከጉና በጌምድር ወደ እብናት(መና መቀጣዋ) መስመር እጅግ አስደማሚ ድል ተመዝግቧል።
እስካሁን የተረጋገጠ 384 ሙት፤ በርካታ ቁስለኛና ምርኮ ሆኗል።
ከፍተኛ ማዕረግ ያላቸው ሁለት መኮንኖችን ጨምሮ ጉዳት ያስተናገደው የብልፅግና ሰራዊት ተበታትኖ ይገኛል።
1 482
አስቸኳይ!
በላስታ አውራጃ ኩልመስክ አካባቢ የፋኖዎችን በትር መቋቋም ያቃታው ወራሪ የጠላት ጦር በዛሬው እለት ማውሬ እስጢፋኖስ በሚባለው ጥንታዊ የዋሻ ውስጥ ቤተክርስቲያን ለማፍረስ እና ጠፈላማይ በሚባሉ አካባቢዎች በደረሱ ሠብሎች ላይ እና በአርሶ አደር መኖሪያ ቤቶች ላይ ፋኖዎች በማይንቀሳቀሱበት አካባቢ ከባድ መሳሪያ መድፍና ሞርታር እየተኮሰ ሲሆን በከፋተኛ ደረጃ ሰብሎችን እያወደመ ይገኛል።
ለተጨማሪ ጥፋት ከድልብና ከጋሸና መስመር ተጨማሪ የጠላት ጦር እየተንቀሳቀሰ ሲሆን ህዝቡ ተጨማሪ ጥንቃቄ እንዲያደርግ ጥሪ እናስተላልፋለን።
ከዚህ በተጨማሪም የአካባቢው ማህበረሰብ በተደጋጋሚ በዚህ ወራሪ የሥርዓቱ ጠባቂ ወታደር የሚደርስበትን ዘርፈ ብዙ እንግልት ዝርፊያ እና ግድያ በመማረር ብንታገለም ባንታገልም መገደላችን እና መዋረዳችን ስለማይቀር ታግለን ነፃ መውጣት ይሻለናል በማለት በከፍተኛ መጠን ፋኖን እየተቀላቀለ ይገኛል።
ለጊዜው በወራሪው ከፍተኛ ውድመት እየደረሰ ቢሆንም ትግሉን ግን በፍጥነት ህዝባዊ እያደረገው እንደሆነ ለመረዳት ይቻላል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ በህዝብ ጠሉ የኦነግ ጦር አማካኝነት በህዝቡ ጉዳት እንደደረሰ መረጃ የደረሰው የላስታ አውራጃ ጄ/ል አሳምነው ፅጌ ፋኖ በህዝቡና በሠብሉ ላይ እየደረሰ ያለውን ጉዳት ለመቀነስና ጠላትን ለመቅበር ስልታዊ የማጥቃት እንቅስቃሴ ለማድረግ ይገደዳል።
በዚህም ጨካኙ አገዛዝ የድሮን ጥቃት ሊፈፅም ስለሚችል የዛሬው ቀን ቅዳሜ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በገበያ አማካኝነት ወገን ህዝብ በብዛት እንዳትሰባሰቡ፣ እንዳትንቀሳቀሱ እናሳስባለን።
ከዚህ በተጨማሪ ማንኛውም ተሽከርካሪ በየትኛውም አቅጣጫ ምንም አይነት እንቅስቃሴ እንዳያደርግ ይመከራል።
በአዲሱ ደርቤ
1 482
የአማራ ተጋድሎ .. ❗️
🎯 የአማራ አብዮታዊ የብሄረተኝነት ተጋድሎ የአማራ ህልውናን በጸና መሠረት ላይ የሚያረጋግጥ የብሄር ግንባታ እና የስርአተ ማህበር እንዲሁም አስተዳደር ለውጥን ማንበርን አላማው ያደረገ ነው።
🎯 ተጋድሎው ረጂም ጉዞ፣ ፈታኝ መንገድ እና ከብርቱ ጠላቶች ጋር በተለያየ መልኩ የሚደረግ በመሆኑ በትዕግሥት፣ በጽናት እና በማስተዋል ልንጓዝ ይገባል።
#AmharaRevolution
1 482
ሰበር የድል ዜናዎች!
ከቀናት በፊት ታላቁ "ዘመቻ ጃዉሳ" በምስራቅ አማራ ፋኖ መታወጁ ይታወሳል።
በዚህም ምክንያት አሸባሪው አገዛዝ "አሉ በተባሉ ጀነራሎች" በመመራት ዘመቻው በቶሎ እንዲቀለበስ አንድ ዕዝ (6 ክፍለ ጦር ) እና 1 ኮር (3 ክፍለ ጦር) በዘጠኝ አቅጣጫ አስገብቶ ነበር።
3ቱ ክፍለ ጦር መነሻ ያደረገው ራያ ቆቦ፣ ጮቢ እና ላስታ መገጠያ ሲሆን አንዷ ክፍለ ጦር መነሻዋን አምዳባ አድርጋ መዳረሻዋን ከተኩለሽ እስከ ቀያፈር ለማድረግ አስባ ነበር።
ሌላኛዋ ክፍለ ጦር በገደባ በኩል አድርጋ በሲቃባ በኩል አጋዋቻባ ለመውጣት ብታስብም ገደባ ማሪያም ላይ በምስራቅ አማራ ፋኖዎች ደፈጣ ጥቃት ገደባ ማሪያምን ማለፍ ሳትችል አልቃለች።
ሌላኛዉ በዋን አድርጎ፤ አረፋ ታች ታቹን፤ በአራዱም እና እራክሴ በኩል፤ ወደ ቀጭን ጎሊናን ተሻግሮ፤ በሮቢት አናት ላይ ወጥቶ፤ ከበቅሎ ማነቂያ መነሻዉን ካደረገዉ ወራሪ ጋር ለመገናኘት ቢያስብም ያሠበው ሳይሳካ በአራዱም ዙሪያ መጀሎ ላይ ድባቅ ተመትቷል።
መጀሎ ላይ 8 የተማረከ ሲሆን ብዙዉ ተደምስሷል፤ ቀሪዉ ወደ አቦሬ ሜዳ ሸሽቶ እርሻ ለእርሻ ተበትኗል።
ይህ 3 ክፍለ ጦር መነሻዉ ቆቦ ዙሪያ ሲሆን
ሌላኛዉ 3 ክፍለ ጦር የተነሳው ከግዳን ወረዳ ወይም ሙጃ ነው።
ሃሳቡ ከራያ ቆቦ ከተነሳዉ ወራሪ ጋር ተገናኝቶ ዘመቻ ጃዉሳን መመከት የነበረ ቢሆንም ሁሉም ድባቅ ተመትቷል።
መነሻዉን ሙጃ ያደረገው ወራሪ በአቦየ ጋራ፣ በቅሎ ማነቂያ እና ሸማፈጅ ግሚሱ ወደ ላኬ ገሚሱ ደግሞ ወደ ድኖ ከሮቢት ከመጣዉ ጋር ለመገናኝት እና "መሃል አስገብቸ ልምታ" ብሎ ቢያስብም በላኬ በኩል የገባዉ 1 ሻለቃ ወራሪ በምስራቅ አማራ ፋኖ ተደምስሷል።
የወገን ጦር ለጦር እስትራቴጅ የሆነዉን ቦታ በቅሎ ማነቂያን፣ አቦየጋሪያን እና ወዳችን ተቆጣጥሯል።
ድኖ ወርዶ የገባዉ ወራሪ በቅርቡ ከወልድያ ማረሚያ ቤት የወጣዉ ታላቁ ጦረኛ "ቆጥረህ ጫን" በሚመራዉ ጦር አሳሩን እያየ ነዉ።
ሌላኛዉ ወራሪ የገባዉ በቃሊም በኩል ሲሆን ይህ የብርሃኑ ጁላ ግሪሳ ዙሪያዉን ተከቦ እጅ እንዲሰጥ እየተጠየቀ ነው።
አዎ እየመጣን ነው!!
1 482
ፋኖን ከህዝብ መነጠል በሚል የጅል ሀሳብ ወደ ሽብር ድርጊት የተሸጋገሩት የብልፅግና ጀኔራሎች ባህርዳር ከተማ ላይ ቦንብ ሲያስወረውሩ ውለዋል።
ትላንት አመሻሽ ደግሞ ከባህርዳር ከተማ ወጣ ብሎ በሞጣ አቅጣጫ ወደ ደሴ እና አዲስ አበባ በሚወስደው አውራ ጎዳና ላይ የሚገኝ ድልድይ በፈንጂ አፍርሰውታል።
ድልድይ በማፍረስና ህፃናት ላይ ቦምብ በማዝነብ ፋኖን ልታሸንፉት ወይም ልታስቆሙት አትችሉም!!
1 482
#አማራዬ ያፈራው የጦር ጄነራል!
ምሬ ወዳጆ የአማራ ተጋድሎ አምጦ የወለደው ምርጥ ጀኔራል ነው። ከ2 ዓመት በፊት እና አሁን ላይ ለሚዲያዎች የሰጣቸውን ቃለ መጠይቆች ለተመለከተ ሰው ምሬ በአመራር ብቃቱ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየበሰለ መምጣቱን መገንዘብ ይችላል።
ምስራቅ አማራ ፋኖ የሚፈፅማቸው ኢ-ተገማችና የማይታመኑ የሚመስሉ ኦፕሬሽኖች ለዚህ ማሳያ ናቸው። 700 ገደማ አባላቱን ከብልፅግና መንጋጋ ፈልቅቆ የሚያወጣ ጦር የገነባ ጀግና ጀኔራል - ምሬ ወዳጆ!
ምስራቅ አማራ ፋኖ በወልዲያ ከተማ የሰራው ኦፕሬሽን ከሞሳዱ operation Entebbe, ከኮለምቢያው Operacion Jaque የሚስተካከል፤ ከቺቺኑ the Moscow theatre hostage crisis, ከአሜሪካው Operations Eagle Claw .... የላቀ በመሆኑ የታላቁ ታሪካችን አካል ሆኖ ይቀጥላል!
/ምስጋናው ዘ ግዮን/
ድል ለፋኖ‼️
1 482
ሰበር
ጃማ ደጎሎ የብልፅግና መከላከያ ለሁለት ተከፍሎ ከ1 ሰዓት ጀምሮ እስከ 3 ሰዓት ከባድ ውጊያ ነበር፤ በርካታ የሰራዊቱ አባላት በእርስ በርስ ውጊያው አልቀዋል። አሁን አንደኛው ቡድን በፋኖ ሽፋን እየተሰጠው በሰላም ፋኖን በይፋ ተቀላቅሏል።
ፋኖ ይችላል!
1 482
ኦሮሚያን ስናዋልድ የአማራ ደም መፍሰሱ ግድ ነው።
ሌንጮ ባቲ ሪያድ ለሚኖሩ ኦሮሞ ተወላጆች የተናገረው
"ኦሮሚያ የምትባል ሀገርን በማዋለድ ላይ ነን በወሊድ ጊዜ ደም መፍሰስ ግድ ነው፡፡ እናም ትኩረታችን ለሚፈሰው የአማራ ደም ሳይሆን ለሚወለደው የኦሮሞ ልጅ ወይም ለምትወለደው ኦሮሚያ ነው፡፡ ይሄ መቼም የማናገኘው የመጨረሻ እድላችን ነው፡፡ ጊዜ ለመግዛት በመላው ኢትዮጵያ ጭፍጨፋ ግድያ በየቀኑ አጀንዳ መስጠታችንን አጠናክረን እንቀጥልበታለን፡፡ ምክንያቱም ደም ሳይፈስ የተመሰረተ ሀገር የለም፡፡ በመላው ሀገሪቱ የተወሰዱ ብቻ ሳይሆን ኦሮሚያ ለምትባል መመስረት አስፈላጊ ናቸው የተባሉ ቦታዎች ሁሉ ወደ ታላቋ ኦሮሚያ ይጠቃለላሉ፡፡ ይህን ለማድረግ የቤት ስራችንን ሰርተን ጨርሰናል፡፡ በአፋር በኩል የተጀመረ ፕሮጀክት አለ፡፡ እሱንም በድል እናጠናቅቃለን የሰሜኑ ፊውዳል እርስ በእርሱ እንዲገዳደል አድርገነዋል፡፡"
ሞዐ ሚዲያ እንደዘገበው!
1 482
አማራን በርሃብ እና በህክምና እጦት
በአማራ ክልል በዋግኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞንና በሰሜን ጎንደር ዞን የተከሰተው ድርቅ ባስከተለው የጤና ችግር የ40 ያህል ሰዎች ሕይወት ማለፉን ከአካባቢዎቹ ባለሥልጣናት መስማቱን ጠቅሶ ዶይቸቨለ ዘግቧል፡፡
ከዋግኽምራ ዞን አበርገሌ ወረዳ፣ ከስድስት ቀበሌዎች 10 ሺህ ሕዝብ በድርቁ ሳቢያ ተፈናቅሏል መባሉን ዘገባው ጠቅሷል።
በዞኑ በጠቅላላው ደሞ፣ በ26 ቀበሌዎች በተከሰተው ድርቅ ከ180 ሺህ በላይ ነዋሪዎች እርዳታ ጠባቂ እንደኾኑ ዞኑ መግለጡንንም ዘገባው አመልክቷል።
በሰሜን ጎንደር ዞንም፣ 30 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች በድርቁ ጉዳት ደርሶባቸዋል ተብሏል።
1 482
አማራውን:-
ሰላሙን ነጥቀው ስለ ሰላም ይሰብኩታል። እየገደሉት በመገዳደል ለውጥ አይመጣም ይሉታል። ጦር አዝምተው ጦርነት ኋላቀርነት እንደሆነ ይደሰኩሩለታል። በጅምላ እያፈናቀሉ ስለመረጋጋት ይሰብኩታል።
እኛም እንናገር ካድሬ እንዲደናገር:-
ትውልዱ ጭቆናን እንዲቀበል በእምነት ስም፣ በኢንቨስተር ማዕረግ፣ በምሁር ካባ ድለላ የጀመራችሁ ሁሉ ቁርጣችሁን እወቁ - ይህንን ትውልድ አታሸንፉትም!
1 482
በሰሜን ጎንደር ቀጠና ጫርቢጣ ልይ የአገዛዙ ሰራዊት ከባድ ውድቀት አጋጥሞታል፡፡ ከ600 በላይ የሰራዊቱ አባላት ከጥቅም ውጭ ተደርገዋል፡፡ በርካታ ምርኮም ተገኝቷል፡፡
ከግንባር ተገርፎ ሮጦ ያመለጠው ይህ ሰራዊት ዳባት ላይ ህዝቡን ሮንድ አልወጣችሁም፣ ፋኖን ትደግፋላችሁ በሚል አረጋዊያንን እና ህጻናትን እያሰቃየ፣ የገንዘብ ቅጣት እየጣለ ህዝቡን እያንገላታ ይገኛል፡፡
መርሳ ከተማ አቅራቢያ ጉባላ ጊዮርጊስ የተባለ ስፍራ ላይ በድሮን ጥቃት ወደ 30 የሚደርሱ ንጹሀን ተጨፍጭፈዋል፡፡
አብይ በአንድ ጊዜ 10 ስልኮችን ዋትስአፕ መጥለፍ የሚችል ሶፍትዌር ያለው ቴክኖሎጅ ገዝቷል፡፡ በአገር ውስጥ ሲም አለመጠቀም ነው፡፡
@Dr Misganaw Andualem
1 482
የአፈና መረጃ
የኢትዮ ኒውስ ጋዜጠኛ በላይ ማናዬ አሁን ምሽት ላይ በመንግሥት የፀጥታ ሰዎች መወሰዱን የስራ ባልደረባው ጋዜጠኛ Belete Kassa አሳውቆናል።
