en
Feedback
Ethio monitor

Ethio monitor

Open in Telegram
1 482
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
#Amhara #Merawi በአማራ ክልል ፤ በየጊዜው በተለያዩ አካባቢዎች ላይ በመንግሥት የፀጥታ ኃይል መከላከያ እና በ " ፋኖ " ታጣቂ ኃይሎች መካከል ግጭቶች ይደረጋሉ። በእነዚህ ግጭቶችም በሁለቱም በኩል ከሚሞተው የግጭቱ ተካፋይ ባለፈ ንፁሃን ሰዎች ሰለባ እየሆኑ እንዳለ በተደጋጋሚ ተገልጿል። ምንም እንኳን #መንግሥት ፤ " ከእውነታው ያፈነገጠ እና ሚዛናዊነት የጎደለው " ብሎ ቢያጣጥለውም የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮኒሽን  (#ኢሰመኮ) ይፋ አድርጎት በነበረው ሪፖርት በክልሉ ፦ - የአንድ ዓመት ከሰባት ወር #ሕፃንን ጨምሮ በርካታ ሲቪል ሰዎች በድሮን መገደላቸው / የአካል ጉዳት እንደደረሰባቸው። - በከባድ መሣሪያ ድብደባ ምክንያት #ሲቪል_ሰዎች ላይ የሞትና የአካል ጉዳት መድረሱ። - በመንግሥት የጸጥታ ኃይል አባላት #ከሕግ_ውጪ የሆኑ ግድያዎች እንደሚፈፀሙ። - ከዚህ ቀደም ግጭቶች በተካሄደባቸው አካባቢዎች የመንግሥት የጸጥታ አካላት በመንገድ ላይ ወይም ቤት ለቤት ፍተሻ በማድረግ ከያዟቸው በርካታ ሲቪል ሰዎች ውስጥ ፦ ➡" ፋኖን ትደግፋላችሁ " ➡" ለፋኖ መረጃ ትሰጣላችሁ " ➡" መሣሪያ አምጡ " ➡ " የተኩስ ድምጽ ስለተሰማበት አቅጣጫ መረጃ ስጡ " በሚልና ይህንን በመሰሉ ምክንያቶች ከሕግ ውጭ የሆኑ በርካታ #ግድያዎች መፈጸማቸውን በይፋ ማሳወቁ አይዘነጋም። ከሰሞኑን ዳግሞ በሰሜን ጎጃም ዞን መርዓዊ ከተማ በመከላከያ ሠራዊት እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል፣ ሰኞ ጥር 20/2016 ዓ/ም የነበረውን ውጊያ ተከትሎ በርካታ ሰዎች መገደላቸው ተሰምቷል። አንድ የአካባቢው ነዋሪ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ገለጻ ፤ በሰሞኑ ተኩስ እሳቸው የሚያውቋቸው ብቻ 15 ወጣቶች መገደላቸውን ተናግረዋል። ከዚህም ባለፈ ግን ፤ " የሟቾቹን ቁጥር በዚህ ወቅት ለመግለጽ መሞከር የጥቃቱን አድማስ ያሳንዋል እንጂ አይገለጸውም" ብለዋል። እኚሁ ነዋሪ በግፍ የተገደሉ ንጹሐን ሰዎችን ቁጥር በሂደት እንጂ አሁን ሁሉንም ማወቅ እንደማይቻል ገልጸው ፤ " የዚህ ህዝብ ጭፋጨፋ ግን መቼ ነው የሚያበቃው? " ሲሉ ጠይቀዋል። በሌላ በኩል ለቢቢሲ አማርኛው አገልግሎት ቃላቸውን የሰጡ ነዋሪዎች፣ የሆስፒታል ሰዎችና የአይን እማኞች በከተማው ከ50 በላይ ሰዎች መገደላቸውን ተናግረዋል። አብዛኞቹ ነዋሪዎች ግድያው የተፈጸመው በቤታቸው እና በመንገድ ላይ በተገኙ ሰላማዊ ሰዎች ላይ መሆኑን ተናግረዋል። አንድ የህክምና ባለሙያ 13ት ሰዎች ከአስፓልት ዳር መገደላቸውን እንደሚያውቁ ተናግረው በአጠቃላይ በከተማዋ በዚያ ዕለት 85 ሰዎች መገደላቸውን አመልክተዋል። አንድ የአይን እማኝ በርካታ ቀብሮች ላይ መገኘታቸውን ጠቅሰው የሟቾችን ቁጥር " ከ100 በላይ ነው " ብለዋል። ጥቃቱ በተፈጸመ ማግስት ጠዋት ላይ 48 አስከሬን መቆጠራቸውን ተናግረው ፤ " ከማርዘነብ ሆቴል እስከ በረድ ወንዝ ድረስ ግራ እና ቀኝ አስከሬን ብቻ ነበር " ብለዋል። የሟቾችን ቁጥር 115 ገደማ የሚያደርሱ አንድ የዐይን እማኝ ደግሞ መከላከያ ከተማዋን ከተቆጣጠረ በኋላ ስታዲየም እና ጤና ጣቢያ በተባሉ ሰፈሮች " ከ6 ዓመት ህጻን እስከ 75 ዓመት አዛውንት " ድረስ ግድያ ተፈጽሟል ብለዋል። የሆስፒታል ሠራተኛ የሆኑት የዐይን እማኝ በከተማዋ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የ6 ወር ነፍሰ ጡርን ጨምሮ 25 ሰዎች ቆስለው መጥተው " የተረፈ የለም " ሲሉ ገልጸዋል። " 24ቱ ሆስፒታል የመጡት ሞተው ነው። አንዲት የ6 ወር ነፍሰ ጡር ሴት ከነ ነፍሷ መጥታ ሆስፒታል እንደደረሰች አርፋለች። አጠቃላይ 25 ነበር የመጡት " ብለዋል። ቃላቸውን የሰጡ ነዋሪዎች ፤ #በመርዓዊ_አስተዳደር ህንጻ ውስጥ በነበሩት የመከላከያ ሰራዊት አባላት ላይ የፋኖ ታጣቂዎች ሰኞ ጠዋት ድንገተኛ ጥቃት ፈፀመው እንደነበርና ለዚህ ምላሽ " የበቀል እርምጃ " በመወሰዱ ነው ለበርካታ ሰዎች ግድያ ምክንያት የሆነው ብለዋል። ሾለ ግድያው ምን ምላሽ እንዳለቸው ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ ያቀረበላቸው የአማራ ክልል ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ  መንገሻ ፈንታው (ዶ/ር)፣ " ስብሰባ ላይ ነኝ መልሸ ልደውል " ብለዋል። መንገሻ (ዶ/ር) ይህን ያሉት እንዲያብራሩ የተፈለገውን ጥያቄ በዝርዝር ከሰሙ በኋላ ሲሆን፣ በድጋሚም ስልክ ሲደወል ስልክ ለማንሳት ፈቃደኛ አልሆኑም። እንዲሁም፣ " እባክዎ ስልክዎን ያንሱና በኮሚዩኒኬሽን በኩል ያለውን የመርዓዊ ጉዳይ ማብራሪያ በመስጠት ኃላፊነትዎን ይወጡ " የሚል የፅሑፍ መልዕክት (SMS) ቢላክላቸውም ምላሽ ሳይሰጡ ቀርተዋል። በተጨማሪ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፦ * የክልሉ የኮሚዩኒኬሽን ምክትል፣ * የክልሉና የሰሜን ጎጃም ዞን ኮማንድ ፖስት፣ * የክልሉ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ስለጉዳዩ ምን ምላሽ እንዳለቸው ለማወቅ እና ሃሳባቸውን ለማካተት ስልክ ቢደውልም ለማንሳት ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ሀሳባቸውን ማካተት አልተቻለም። የኢትዮጵያ ሰብዓዊ ኮሚሽን ( #ኢሰመኮ ) ምክትል ኮሚሽነር ራኬብ መሰለ ፤ " መረጃው ደርሶናል (የመርዓዊ ጉዳይ) ። እያረጋገጥን ነው " ብለዋል። አክለው ፣ "የጸጥታ ጉዳይ ስለሆነ ትንሽ መንቀሳቀስና መረጃ መሰብሰብ አስቸጋሪ ሊሆን ስለሚችል ሊዘገይ ይችላል። ግን እያጣራን ነው" ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጠዋል። @tikvahethiopia

ሰው በላው አገዛዝ  የአማራ ወጣትንና ወንድን እንዲጠፈጭፍ ከላከው ወራሪ ፀረ-ሕዝብ ሠራዊት ውስጥ ከኦነግ ሠራዊት፣ የኦሮሚያ ልዩ ኃይልና ፖሊስ፣ ኦሮሚያ ሚሊሻ የተውጣጡት በተለይ ያገኙትን ወንድ እንዲጨፈጭፉ ልዩ ተልዕኮ የተሰጣቸው ናቸው። ሰው በቁሙ ዐይን አውጥተዋል፣ የወንዶችን ብልት ሰልበዋል፤ ያልፈፀሙት ግፍ የለም። በአንዳንድ ቦታ የሚፈፀመውን ግፍ በማየት የአማራ ወታደሮች በኦሮሞ ወታደሮች ላይ ተኩስ በመክፈት  መተው ፋኖን ተቀላቅለዋል። ኢትዮጵያ የአገር መከላከያ ሠራዊት የላትም። ያላት አረመኔ ወራሪና ዘር አጥፊ ሠራዊት ነው !! ይሔ ሠራዊት በመንግስት ለውጥ ተበትኖ አመራሮቹ ለፍርድ የሚቀርቡበት ሁኔታ የግድ ይፈጠራል። ዘር ማጥፋትን  ወታደር ይፈፅመው ዶክተር ተጠያቂነት አይቀርም !!

"ከ18 አመት በላይ ያለህ ወጣት በሙሉ ትግላችንን እንድትቀላቀል ጥሪ አቀርብልሀለው" ፋኖ ምሬ ወዳጆ
"ከ18 አመት በላይ ያለህ ወጣት በሙሉ ትግላችንን እንድትቀላቀል ጥሪ አቀርብልሀለው" ፋኖ ምሬ ወዳጆ

ኦሮሚያ መንገድ ዝግ ነው። የኢ-መደበኛ ታጣቂው አንጃ ከአገዛዙ ጋር እየተዋጋ ነው።  እና አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለምን እንደማይታወጅ ገብቶሃል⁉ ይሔ እኮ በእነተመስገን ጥሩነህና ብናልፍ አንዷለም ጭንቅላት ሊመረመርና ሊጠረጠር አይችልም!! አንጎላቸው ተሽጧልና !!

ስጋት ከሚሆኑበት በታች አውርደን ለቀማ ላይ ነን ያለው አገዛዝ የአፈና ጊዜያቱን በማራዘም የጅምላ ግድያና እሥራት ወቅቶች አራዝሟል። አስቸኳይ ጊዜ አዋጅን ለአምስት አመታት የቀጠለው አገዛዙ ሁነኛ የአፈና መሣሪያ አድርጎታል።

የአማራ ትግል ምንድን ነው!? የአማራ ትግል የሕልውና እና የፍትሕ ትግል ነው። እጅግ በጣም በአጭሩ ለማስቀመጥ ተከታዮቹ አንኳር ጉዳዮች ያሉት ነው። 1) ትግሉን የሕልውና ትግል የሚያደርገው የሕልውናውን የሚፈታተኑ ጥቃቶች እየተፈፀሙበት ስለሆነ ነው። 📍 ከሥርዓተ-መንግስቱ የሚመነጩ የሕልውና ጥቃቶች አሉበት። 📍 ከአገሪቱ ሕገመንግስትና ሌሎች ፖሊሲዎች የሚመነጩ የሕልውና ጥቃቶች አሉበት። 📍 በሰብዓዊ ጭፍጨፋ የተደቀነ የሕልውና አደጋ አለበት 📍ከማሕበራዊ ባሕላዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች የሚመነጩ የሕልውና ጥቃቶች አሉበት። እነዚህ ሰፊና ዝርዝር መገለጫዎችና ገፅታዎች ያሏቸው የአማራ ትግል መሠረቶች ናቸው። ብዙ ጊዜ የሚነሱ ዝርዝር ጥያቄዎች ሁሉ ከእነዚህ ማዕቀፎች የሚመነጩ ናቸው። እነዚህን ማስቆም፣ ማስተካከል ፣ ማረም የአማራ ሕልውና ትግል አንኳር ትኩረት ነው። ይሔንን የማድረግ ጉዳይ በሰላማዊ ፖለቲካዊ አግባብ ስላልተቻለ ትግሉ ወታደራዊ አማራጭን ይዞ ተነስቷል። ፍፃሜው ፖለቲካዊ መሆኑ የግድ ነው!! 2) ሌላኛው የአማራ ትግል የፍትሕ ጥያቄ ትግል ነው። ከላይ በጥቅል በተቀመጡ የሕልውና ጥቃት ምንጮች ስር የተፈፀሙ የሕልውና ጥቃቶችና የጥቃት ምንጮች ፍትሕ ያስፈልጋቸዋል። 📍 አንዱ የዕርምት ፍትህ [Retrospective justice] ነው። በዕርምት ፍትህ አውድ ዋነኛ እና የመጀመሪያው ጥያቄ በተለያዬ መጠን በአለምአቀፍ የመብት እና ግዴታ መስፈሪያ ለተፈጸሙ የወንጀል ድርጊቶች በፍርድ ቤት የሚሰጥ ብያኔ ነው። የአማራ የሕልውና ትግል ይሔንን የማረጋገጥ ትግል ነው። 📍 ርትዕ ፍትህ [Prospective or Restorative justice] ይህ የፍትህ ጥያቄ በዋናነት መጪውን ጊዜ ለአማራው ሰላማዊ እና ጤናማዊ ማድረግን ያለመ ነው። ለተፈፀሙ በደሎች እውቅና ሰጥቶ የተጎዳውን መካስ እና ማረም አስፈላጊ ነው። ሌላኛው ሥራ ለሕልውና ጥቃት ምንጭ የሆኑ ፖለቲካዊና መዋቅራዊ ጉዳዮች መታረም አለባቸው። ትግሉ የሕልውና ጥቃት ምንጮችን እርማት መስጠት ባልቻለበት የሕልውና አደጋውን መቀልበስ አይችልም፤ ፍትሕ ተሰጠ ማለት አይቻልም። ከዚህ አኳያ የርትዕ ፍትህ የማምጣቱ የመጀመሪያው አጀንዳ እውነት አፈላላጊ አካል አቋቁሞ ተልዕኮ መስጠት ነው። 📍 አዲስ የህግ እና የፖለቲካ ስርአት መፍጠር ቀጣዩ ወሳኝ ምዕራፍ ነው። በኢትዮጵያ ለአማራም ሆነ ለሌሎች ቀጣዩ የህግ እና የፖለቲካ ስርአት ምን መሆን አለበት የሚለው ወሳኝ ነው ። የአማራ ህዝብ ዳግም ወደ ህልውና አደጋ የማይገባበት፣ ህልውናው እንዲሁም እንደ ህዝብ ያሉት መብቶች የሚረጋገጡበት እና ፍላጎቶቹን በዲሞክራሲያዊ መልኩ ታግሎ የሚያሳካበት የህግ እና የፖለቲካ ማዕቀፍ ሊኖረው ይገባል። ይሔ የሌሎች ኢትዮጵያውያንን ፍላጎቶች ያካተተና የጋራ አገራዊ ራዕይን ለማስቀመጥ ከመግባባት ጋር የሚያያዝ ነው። ይሔ የአማራ ብሔርተኝነት እና ብሔራዊ ትግል መሠረት ነው !!

photo content

#ታፍነዋል የህ/ተ/ም/ቤት አባሉ ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ዛሬ ጥር 22 ቀን 2016 ዓ.ም ምሽት 3 ሰዓት በግፈኞች ታፍነው ተወስደዋል!!
#ታፍነዋል የህ/ተ/ም/ቤት አባሉ ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ዛሬ ጥር 22 ቀን 2016 ዓ.ም ምሽት 3 ሰዓት በግፈኞች ታፍነው ተወስደዋል!!

አንዳንድ ነገሮች፤ ► የአፋር ርዕሰ መስተዳድር እና የድሬዳዋ ከንቲባ በስራቸው ላይ አይደሉም!! ►በኦሮሚያ አመፆችና ገደቦች ቀጥለዋል ► ፋኖ ሶስተኛውን ወታደራዊ ዕዝ እውን አድርጓል!! ► የብልፅግና አገዛዝ እንደሲሪላንካው አገዛዝ የነዳጅ መኪና አታምጡ፤ የግል መኪና አቁሙ፣ እያለ ነው። በቀጣይ ከቤታችሁ ሥሩ ይለናል። ► ኢትዮጵያውያን፥ በአብይ ቡድን  በ8.6 ሚሊዮን ዶላር የተገዛው የFAO ሽልማት ውርደትና ሀፍረት አከናነበን እያሉ ነው። ► ብዐዴን/ብልፅግና በተሳካ ሁኔታ ከማዕከላዊ መንግስት ተራግፎ ጥቂት አድርባይ ጥቅመኞች ቀርተዋል። ► ግብፅ ፣ ኤርትራ፣ ሱማሊያ... ኩዌት፣ ኳታርና ቱርክ በጋራ የተሠለፉበት የቀይ ባሕርና ወደብ  ነገር  የ4ኪሎውን አገዛዝ አስደንግጧል። ► በዩጋንዳ የኢጋድን ስብሰባ አሻፈረኝ ያለው የኦሮሞ ብልፅግና እባካችሁ ሰብስቡኝ እያለ ነው። ► በሱማሊያ የፀረ-ኦሮሞ ንቅናቄ አይሏል። እና የብልፅግና ጉዟችን አላማረበትም ወይ⁉

ቲክቶክ ላይ የምትውሉ ወይም መዋል የምትፈልጉ አማራውያን፥ የተሻለ content እንዴት መፍጠር ይቻላል የሚለውን በደንብ አጢኑት። የግድ ፖለቲካ ማውራት የለባችሁም! የግድ ልብስ እየቀያየራችሁ እስክስታ መደነክም የለባችሁም። creative ሁኑ !! የአማራ ሴት መሆንሽን አሳያቸው!! የምትናገሪውና የምታስተላልፊው መልዕክት የምትሸጪው ሀሳብ ያለሽ እንጂ ጭንና ከንፈር ለማስጎብኘት አትድከሚ!! የአማራ እናቶች እየተጠቁ ፣ የአማራ ሴቶች እየተደፈሩ፣ የአማራ ልጃገረዶች ከትምህርት ገበታ ተነቅለው፣ የአማራ ሴት ታዳጊዎች ወላጆቻቸውንና ወንድሞቻቸውን በፋሽስቱ ጦርነት እየተነጠቁ አንቺ በእስክስታ መነኹለል የለብሽም!! እንደምታስቢያቸው ተናገሪ እንጂ !! የሆነ ሀሳብ በመሸጥ ገንዘብም መስራት ወገናችሁንም ማገዝ ትችላላችሁ።

#ኦሮሚያ የእግዚአብሔርን ቤት አነደዱት!!
+2
#ኦሮሚያ የእግዚአብሔርን ቤት አነደዱት!!

"አማራ የሚድነው አሁን ብቻ ነው። አንድ እርምጃ ወደኋላ ከሔድን እንወድቃለን!! አሁን ከወደቅን አንነሳም!!" ዘመነ

የምስራቅ አማራ ፋኖ ዕዝ የተመዘገቡ አስደናቂ ጀብዶች‼️ ነግቷል ሸጋ ሁኖ💪💪 ጦርነቱ እደቀጠለነው ። ተኩለሽ ላይ ተከባ የነበረችዉ 1ሻለቃ የጥላት ሃይል እጅ አልሰጥም በማለቷ በነበልባሉ ምስራቅ አማራ ፋኖ ዕዝ ዞብል አምባ ብርጌድ (ብረቱ) እርምጃ እየተወሰደባት ነው። የሚገርም ድልም እያስመዘገብን እንገኛለን። እጅግ አስቸጋሪ የሆነችዋ በራያ ቆቦ ወረዳና በግዳን ወረዳ መካከል ላይ ከተኩለሽ በትንሽ ርቀት ላይ የምት ገኝ ቦታ ወዳች ከተማን ንጋት ላይ የተቆጣጠረው ምስራቅ አማራ ፋኖ በረህኛዉ ብርጌድ (ቆጥረህ ጫን) አሁን በዚህ ስአት የግዳን ወረዳ ሙጃ ከተማን ለመቆጣጠር የከተማዋን ዙሪያዋን ከቦ ጥላትን እያስቆጠረ እያስጫነዉ ይገኛል። ይህም ብርጌድ በታላቁ ጦረኛ በቅርብ ወልድያ ማሪሚያ ቤትን ከእስር ያስወጣው ቆጥረህ ጫን የሚመራ ነው። ኩልመስክን የተቆጣጠረዉ አድማሱን በማስፋት ወደፊት በሚሄድ ከባህዳር ወልድያ ያለዉን ዋናዉን መንገድ ለመቁረጥ አመሻሹን ሽር ጉድ እያልን ነው። ምስራቅ አማራ ፋኖ ዕዝ ታጠቅ ብርጌድ (ወልጊዉ) አምባሰል ቀጠናን ቆርጦ ይዞታል። ከደሴ ወልድያ ቆቦ ዋናዉ አዉራ ጎደና ተቆርጦ በምስራቅ አማራ ፋኖ የተዘጋበት ጥላት በአፋር አሳጊታ ጭፍራ ሃራ ለመግባት ቢሞክርም የምስራቅ አማራ ፋኖ ባለሽርጡ ብርጌድ በእንዲርስ ጉድሌ (ሞርተ) የሚመራዉ ጦር ሃረርቲ ላይ የሳት ነደድ ሁኖ እያቃጠለው ነው። የምስራቅ አማራ ፋኖ ተወርዋሪወቹ ብርጌዶች አሳምነዉ ብርጌድ ( የምድር ድሮን) ሃውጃኖ ብርጌድ ( ጀቱ) ካላኮርማ ብርጌድ (ዙ 23) ተወርዋሪ እና ማርሽ ቀያሪ በመባል ይታወቃሉ። እንደየ አስፈላጊነቱ በማንኛዉም ቀጠና ሰብርው እየገቡ ድል በድል ሆነዋል። ተኩለሽ እና አካባቢው ነፃ ለማውጣት ባደረገው ከፍተኛ ተጋድሎ ጀግናው የምስራቅ አማራ ፋኖ ዕዝ አራት ከባድ የአገዛዙን (አለቃው መንደር፣ ሲንካአምባን፣ ገደባን፣ ወይዘሮአምባን) ምሽግ ድርምስምሱን በማውጣት ሰባብሮ ጠላት ሰፍሮባቸው የነበሩ በርካታ ቦታዎችን መቆጣጠር ችለዋል። አራቱም ብርጌዶች በጥምረት ባደረጉት ተጋድሎ ጠላት አይቀጡ ቅጣት ተቀጥቶ እየፈረጠጠ ይገኛል ሲል የዞብል አምባ ብርጌድ ም/አዛዝ ፋኖ ዋሲሁን ጫኔ መረጃ አድርሰውናል።

ደፋር ከሆንክ አንብብ! የኦሮሞ ልሂቃን እነጃዋርን ጨምሮ በጠቅላይ ሚኒስትሩ መሪነት አማራን በፍጥነት ትጥቅ እናስፈታ ካልሆነ ለስልጣናችን አደጋ ይሆናል ሲሉ መከሩ። ለዚህም አይነተኛ ጥቅም ይሰጠናል ብለው ያሰቡት የፕሪቶሪያው ስምምነት እንዲሳካ ወተወቱ። ድርድሩ ለህወሓትም ጥቅም ይሰጥ ነበርና በሁለቱም ተፋላሚ ሀይሎች በኩል በደስታ ተቀባይነት አገኘ። በምዕራባውያንም ዘንድ ይፈለግ ነበርና የፕሪቶሪያው ስምምነት ተካሔደ። ይህንን ስምምነት ተከትሎ አብይ አህመድ የአማራ ታጣቂዎችን በአንድ ወር ውስጥ ትጥቅ አስፈትቼ የፕሪቶሪያውን ስምምነት ሙሉለሙሉ እንድተገብር ድጋፍ አድርጉልኝ ሲል አሜሪካኖቹንና አውሮፓዎቹን ተማጸነ። የትግራይ ሀይሎችም ይህንን ማድረጉ ጠቃሚ ስለመሆኑ ምስክርነታቸውን ለአሜሪካኖቹና አውሮፓውያኑ ሰጡ። ጠቅላይ ሚኒስትሩም ይህንን እንዳደርግ ከፈቀዳችሁልኝ ተፈናቃዮችን በአንድ ወር ውስጥ ወደቄያቸው እመልሳለሁ፣ ወልቃይትና ራያን መልሼ ወደ ትግራይ አሰሰተዳደር አካልላለሁ ሲል ቃል ገባ። ከዛም አልፎ ፋኖን ከአስወገድን በኋላ የኤርትራን አምባገነን መንግስት ለመገርሰስም አቅም ይሰጠኛልና የፋኖ መወገድ ለቀጠናው ሰላም አይነተኛ ጥቅም አለው ሲል አግባባ። ልብ አድርጉ! አብይ አህመድና እነጃዋር በአማራ ላይ ጦርነት መክፈት የፈለጉበት ዋነኛ ምክንያት ፕሪቶሪያን በተጨባጭ ለመተግበር አልነበረም። የፕሪቶሪያ መተጎበር ያኔም ሆነ ዛሬ ላይ ጉዳያቸው አልነበረም። የነሱ ፍላጎት ለስልጣናችን ተቀናቃኝ ነው ያሉትን አማራን መስበር ነበር።  በዚህ ረገድ እንኳን እነአብይ ህውሃቶችን ማታለል ባይችሉም አውሮፓና አሜሪካን በሚገባ አታለዋል። ጦርነቱ ቀላል operation የሚጠይቅና በፍጥነት የሚደረግ መሆኑንን ደጋግመው በመግለጽ የነዚህን ሀገራት ይሁንታ አገኙ። ሆኖም ግን አውሮፓውያኑም ሆነ አሜሪካኖቹ የገንዘብ ድጋፍ የሚደረግልህ ቃል የገባኸውን በአንድ ወር ውስጥ ከተገበርክ ብቻ ነው አሉት። አብይ አህመድ እንደውም አስራ አምስት ቀን ብቻ ይበቃኛል ሲል ተናገረ። ልዩ ሀይሉን አፈረሰ። ግርማ የሺጥላን አስገደለ። ከዛ በህግ ማስከበር ስም በአማራ ህዝብ ላይ ጦርነትን አወጀ።  ከዛ ከባዱን የዘር ፍጅት በአማራ ህዝብ ላይ ያለአንዳች ከልካይ ማካሄድ ጀመረ። ሳምንት፣ አስራምስት ቀን እያለ አንድ ወር አለፈው። ጦርነቱ አብይ እንደገመተው ብቻ ሳይሆን መላው አለም እንደገመተው ሳይሆን ቀረ። አብይ አልቻለም። ደወሉለት። ለሳምንት ያህል ስልክ ማንሳት አልፈለገም። ከዛ እነማይክ ሐመር ተላኩ። ምንድነው እየተፈጠረ ያለው ሲሉ ጠየቁ። አብይ አህመድ ተሸነፍኩ አላለም። በአንጻሩ የክልሉ መንግስት ከድቶኝ ከፋኖ ጋር ተሰልፏል አላቸው። እና ምን ይሻላል አሉት? አስቸኳይ ግዜ አውጄ ሙሉለሙሉ የክልሉን መዋቅር አፍርሼ ላደራጅ ስድስት ወር ብቻ ፍቀዱልኝ ሲል እግራቸው ላይ ተዘረረ። እንዳለውም አደረገ። ፍጅቱን ቀጠለበት፣ ድሮን፣ ከባድ መሳሪያ...አለኝ የሚለውን ሁሉ ተጠቀመ። ወይ ፍንክች አማራ! ስድስት ወር እንዳይደርስ የለምና ይሔው ደረሰ። ጦርነቱ ሲጀመር በክልሉ የነበረው በቀላሉ የታጠቀ የፋኖ ሀይል ቁጥሩ ከሰላሳ እስከ አርባ ሺ ብቻ ይገመት እንደነበረ ከወደ ምዕራቡ ያሉ የሚስጥር ሰነዶች ያስረዳሉ። ዛሬስ? በከፍተኛ ደረጃ የተደራጀ፣ የሰለጠነና የታጠቀው የፋኖ ቁጥር ብቻ ወደ አንድ ሚሊዮን መጠጋቱን እነዚሁ ጥብቅ የደህንነት ሪፖርቶች ያሳያሉ። ይህ ቁጥር ቀላል መሳሪያ የታጠቀውና ጦርነት ማድረግ የሚችል አቅም የፈጠረውን አብዛኛውን የአማራ ህዝብ ቁጥር አይጨምርም።  እናስ? Jeffrey Feltman የሚከተለውን አሉ፦ Those committed to Ethiopia’s stability need to work together, to identify the tools that can help persuade Abiy to throw himself into a genuine, inclusive political process with the same gusto he used to transform the Addis Ababa cityscape with construction and park projects. በአጭሩ ሲተረጎም..."የኢትዮጵያን ሰላም ማየት የሚፈልግ አካል ሁሉ አብይ አህመድ ዛፍ እና ፓርክ ለመንከባከብ እንደሚፍጨረጨረው ሁሉ አቅሙን አውቆ ለእውነተኛ የፖለቲካ ለውጥ እንዲዘጋጅ ሊመከር አልያም ሊገደድ ይገባል" አሉ። አሜሪካና አውሮፓውያኑ በአብይ አህመድ ተስፋ ቆረጡ። ከዚህ በኋላ መቀላመዱን ትተህ አርፈህ ተቀምጠህ ተደራደር በፋኖ ተሸንፈሃል ሲሉ በድፍረት ተናገሩ።  ካልሆነ የራሳችንን እርምጃ ለመውሰድ እንገደዳለን አሉ። ነወር ጌጡ አብይ አህመድስ? "ከዚህ ውርደት አውጡኝ፣ ሸምግሉኝ" ሲል ድጋሚ በምዕራባውያኑ እግር ላይ ተደፋ። ፋኖስ? ጀግኖቹ ያልጨረሱት የቤት ስራ ላይ ናቸው። ስራቸውን አውቀውታል። ጠላትንም አውቀውታል። ድሉ አይቀሬ መሆኑ ገብቷቸዋል። ሳይታክቱ ይሰለጥናሉ፣ ሳይታክቱ ይዋጋሉ፣ ሳይታክቱ ድል ያደርጋሉ። መጪው ዘመን የፋኖ ትንሳኤ መሆኑ ገብቷቸዋል። መጪው ዘመን የአማራ ትንሳኤ መሆኑን አውቀዋል። መጪው ዘመን የኢትዮጵያ ትንሣኤ የመሆንም እድል አለው ብለው አምነዋል። ድል ለተገፋዋ ወገኔ!

"ነገር መበላሸቱን እያወቁ ለመወሰን የተቸገሩ አሉ" ነበር ያለው ታዬ ደንደአ!! ወስን  አዴፓ !! ወስን ሱማሌ!! ወስን አፋር!! ወስን ሲዳሞ : ወስን !! መላላክ በቃኝ በል!! አገዛዙ ይሔን አገር መቀመቅ ሲከታት ደግፈህ ቆመህ የነበርክ መባል ያዋርዳል!! የታዬ ደንደአን እና ስዩም መስፍንን መንገድ ተከተል !! የፀጥታ ሠራዊት አባላት ታሕሳስ 30 እንዳይረሳ!! እስከዚያው ሹልክ እያልክ ወገንህን ተቀላቀል!!

አብይ አሕመድ ሁሉንም ሚኒስትሮች እና ባለስልጣናት  ከውጭ ጉዞ ካላገደ ሔደው ማለቃቸው ነው። በነገራችን ላይ በርከት ያሉ የአማራ ሹመኛ ነን የሚሉ ተላላኪዎች ከአገር እንዳይወጡ ታግደዋል። ከአገር ውጭ የሚመጡ የሥራ ጉዞዎች እየተሠረዙ ነው። በደም የጨቀየው እጅህ ይከፍልሃል!! መቃብርህ ቅርብ ነው !!

የዋግኸምራ ወታደራዊ መኮንኖች ከወገናቸው መጨፍጨፍ በርሃብ ማለቅ በላይ መላላክና ሆድ የገዛቸው ግብዞች ናቸው። #አንረሳውም!!
የዋግኸምራ ወታደራዊ መኮንኖች ከወገናቸው መጨፍጨፍ በርሃብ ማለቅ በላይ መላላክና ሆድ የገዛቸው ግብዞች ናቸው። #አንረሳውም!!

የአገዛዙን ዲስኩር እርሳው!! ከዛሬ 6 ወር ይልቅ ዛሬ የበለጠ ወጣትና ሕዝብ ትግል ገብቷል ከዛሬ 6ወር ይልቅ ዛሬ ከፍተኛ የመሣሪያ ትጥቅ በሕዝባችን እጅ ነው!! ድላችን አይቀሬ ነው !!

የአገዛዙ ሠራዊት  ዋነኛው የፋሽስታዊው አገዛዝ ሰለባ ሆኗል። ይሔ ሠራዊት በየክልሉ እየዞረ ወገኑን እንዲወጋ እየተደረገ በሕዝቡ ፍፁም የተጠላ ሆኗል። የከፋው ነገር ግን ሠራዊቱ ፍፁም ራሱን የጣለ እና  መሠረታዊ አቅርቦት እንኳ የማይሰጠው ተደርጎ እንዲሞት ተፈርዶበታል። በጎጃም አማኑኤል የተማረኩ 73 ወታደሮች የእግር ካልሲያቸው ሳይቀር ቀምሎ ተገኝቷል። ይሔ አገዛዝ የኢትዮጵያ ጠላት ነው ሲባል በብዙ መልኩ ነው !! ለዚህ አገዛዝ የሚታዘዝ ሠራዊት ሊኖር አይገባም‼ ታሕሳስ 30 ድረስ ወደአማራ ሕዝባዊ ጦር መቀላቀልና ትጥቅን ማስረከብ ተገቢ ነው ‼

የአገዛዙ ሠራዊት አባላት እስከ ታሕሳስ  30 የአማራ ሕዝባዊ ሠራዊትን እንዲቀላቀሉ የቀረበውን ጥሪ ተከትሎ 230 ኮማንዶዎች ፋኖን ተቀላቅለዋል 📍