en
Feedback
Ethio monitor

Ethio monitor

Open in Telegram
1 482
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
ፋኖ እየተጠበቀ ነው ‼ ➺ የቦረና ኦሮሞ እየጠበቀ ነው ➺ የባሌ ኦሮሞ እየጠበቀ ነው ➺ የጉጂ ኦሮሞ እየጠበቀ ነው ➺ የሸዋ ኦሮሞ እየጠበቀ ነው ➺ ጉራጌው እየጠበቀ ነው ➺ ወላይታው እየጠበቀ ነው ➺ ጋሞው እየጠበቀ ነው ➺ ሱማሌው እየጠበቀ ነው ➺ አፋሩ እየጠበቀ ነው ➺ ወዘተ : : ከእዚህ ሁሉ የወጡ ልጆች ወደፋኖ እየተቀላቀሉ ነው። ብዙዎች ብሔረሰቦች ፋኖ እየሆኑ ነው። በቅርቡ ከአማራ ወንድማቸው ጋር ትግሉን በተደራጀ መንገድ ይቀላቀሉታል። ገዢ ቡድኑ የአማራ ሕልውና አጥቂ ብቻ ሳይሆን የሌሎች ኢትዮጵያውያን ሁሉ ስጋት ሆኗል። የጋራ ጠላት ሆኗል። ይሸነፋል ‼

የጠላት አሽከር የሆኑት እነተመስገን ጥሩነህ በአማራ ሕዝብ ላይ የዘር ማጥፋት ጦርነትን ደግፈው እያስፈፀሙ ባሉበት፥ ገዢው የኦሮሙማ ልሒቅ ለሕዝቡ ተጠባባቂ ጦር እንዲደራጅ፣ እንዲሠለጥን፣ እንዲታጠቅ
የጠላት አሽከር የሆኑት እነተመስገን ጥሩነህ በአማራ ሕዝብ ላይ የዘር ማጥፋት ጦርነትን  ደግፈው እያስፈፀሙ ባሉበት፥ ገዢው የኦሮሙማ ልሒቅ ለሕዝቡ ተጠባባቂ ጦር እንዲደራጅ፣ እንዲሠለጥን፣ እንዲታጠቅ  በብርቱ እየሠራ ነው።

እንደብዐዴን   አማራን ያስገመተ ፣ ያሳነሰ፣ ያስናቀ፣ ያሰቃዬ፣ ያስጠቃ  ከቶ ማን አለ !?

የአማራ ትግል አብዮታዊ የብሄረተኝነት ትግል ነው❗️ የአማራ ህዝብ ትግልን በተመለከተ እኒህ ሁለት መሠረታዊ ሀቆች ሊታወቁ ይገባል፤ 1ኛ ) ጥያቄያችን እና የምንፈልገው ለውጥ በቅርጽም ሆነ በይዘቱ #አብዮታዊ ነው። የህልውና አደጋን የመቀልበስ እና ርትዕ ፍትህ የማረጋገጥ ጥያቄያችን አብዮታዊ ነው፤ ማለትም ከዚህ ጥያቄ አኳያ በሀገሩ ያለውን ነባራዊ ሁኔታ የማሻሻል ሳይሆን አብዮታዊ በሆነ መልኩ የመለወጥ ጥያቄ ነው። ሌላው የአማራ ህዝብ የሀገረ መንግስቱ ማህበረ ፖለቲካዊ መገለጫዎች የሆኑ መዋቅሮች፣ ተቋማት እና ዕሳቤዎች አብዮታዊ ለውጥ እንዲካሄድባቸው ይፈልጋል። ይህን ስንል ከአደጋ የመውጣት፣ አደጋ ያጋረጠውን የማስወገድ እና መሠል ሁኔታ ዳግም እንዳይፈጠር ማረጋገጥ አብዮታዊነትን ይጠይቃል። እኛ ሀገሩን የምናይበት እና አሁን ባለው ሀገር የምንታይበት አውድ የፖለቲካ ዲዛይኑ ውጤት ነው፤ ይህ መለወጥ አለበት። በአማራውና በሌሎች ብሄሮች መካከል ያለው ግንኙነት መሻሻል ሳይሆን በሙሉ መለወጥ አለበት፤ ተቃርኗዊ ዕይታ ከወለደው ጠላትነት ወደ ወዳጅነት እና አጋርነት የሚደረግ ለውጥ አብዮታዊ ነው። 🎯 እናም የአማራ ትገል አብዮታዊ ትግል ነው። 2ኛ ) የትግሉ ገዢ የሀሳብ ማዕቀፍ እንዲሁም መመሪያ በርዕዮተአለማዊ ምደባ አንጻር ብሄረተኝነት ነው። በሌላ አገላለጽ የምንመራው #በአማራ_ብሄረተኝነት ርዕዮት ነው። አማራነት በምደባ ያገኘነው ማንነት አይደለም። አማራ ነበርን፤ አማራ ነን። ይህ ስርአት የፈጠረልን ማንነት የለም፤ ይልቁኑ በማንነት የምንጠቃበትን ተረክ ፈጥሯል። እኛም የምንጠቃበትን እና እየተጠቃ ያለውን አማራነታችንን የምንሰባሰብበት፣ የምንደራጅበት እና የምንታገልበት ሀሳብ አድርገነዋል። እናም የአማራ ብሄረተኝነት በአማራነት የምናደርገው አብዮታዊ ትግል ማታገያ መሳሪያ ነው። ይህ የማይካድ ሀቅ ነው። የአማራ ህዝብ በአማራነቱ እና ስለአማራነቱ የሚያደርገው ትግል ባለበት ጊዜ ሁሉ የአማራ ብሄረተኝነትን የትግል ርዕዮቱ አድርጎ መቀጠል አለበት፤ ይቀጥላልም። በዚህ ጉዳይ በአማራ ትግል ውስጥ ያለም ሆነ ገብቶ ማገዝ የሚፈልግ ብዥታ ሳይኖረው፣ ግልጽ አቋም ሊይዝ ይገባል። በተለይ በቅርቡ የአማራን ተጋድሎ እየተቀላቀሉ ያሉ እንዲሁም ቀድሞም ለህዝቡ ተቆርቋሪ የነበሩ አሁን ደግሞ የትግሉ አካል ሆነው የተሰለፉ ጓዶች እና መሠል ሀይሎች በዚህ ላይ ስህተት እንዳይፈጽሙ ለማሳሰብ እወዳለሁ። 🎯 የአማራ ብሄርተኞች ነን፤ ትግላችን ለአብዮታዊ ለውጥ ነው። _ ድል ለአማራ ❗️ #AmharaRevolution

ለዚህ አጋርነት የተሰጠው ምላሽ የጅምላ ጭፍጨፋና ዘር ማጥፋት ነው
+2
ለዚህ አጋርነት የተሰጠው ምላሽ የጅምላ ጭፍጨፋና ዘር ማጥፋት ነው

ከአገዛዙ ጋር ያሉ የኦሮሞ አክቲቪስቶች ፣ ዳንኤል ክብረት እና የመከላከያ ሠራዊት የፕሮፖጋንዳ ዘርፎች ፡ << የአማራን ኃይሎች መከፋፈልና ልዩነታቸውን ማስፋት>>  በሚል የጀመሩት ፕሮፖጋንዳ የአገዛዙን የሽንፈትና ጭንቀት ልክ የሚመሰክር ነው። እነሱም የሚወጉት የአማራን ሕዝብ ፣ ገጥሞ የሚዋጋቸውም የአማራ ሕዝብ መሆኑን መሐል መሐል ላይ እየረሱት ተቸግረዋል። የሚፈፅሙት የጦር ወንጀልና ዘር ማጥፋት እንጂ የሚያስከብሩት ሕግ እንደሌለ፣ የሚያስታጥቁት መሣሪያ እንጂ የሚያስፈቱት ትጥቅ እንደሌለ ቢያውቁትም ለድል እንደማይበቁ አልገባቸውም!! ከአገር ያሰደዱትና ከሥራ ያገዱት ባለሀብት፣ በየማጎሪያው ያገቱት ልሒቅ በጦርነቱ አሸናፊ ለመሆን አላስቻላቸውም!! በሚጋጩ የፋኖ መሪዎች ወይም በሚገደሉ  የፋኖ አመራሮች ተስፋ አድርገው ቢጮሁም  የሚያሸንፉት የሕዝብ ትግል እንደሌለ ገና አልገባቸውም። ያፈናቀልከው ፣ የጨፈጨፍከው፣ ማዳበሪያ ከልክለህ ያስራብከው፣ የጅምላ ግድያ የፈፀምክበት አማራ፡ በወንጀልህ ልክ ሳትጠየቅ፡ በአንተ ተራ አጀንዳ መማለል እንዳቆመ ባይገባህም፡ የሕልውና የፍትሕና ርትዕ ትግሉ ደማቅ አማራዊ  ማሕተም ሆኗል !! ከብልፅግና መንደር የሚሸመት አጀንዳ የለንም ‼

▪️"ለሀገር ሉዓላዊነት እና ለሕዝብ ሰላም ነው" በሚል ማደንዘዣ ለገዢዎቹ ድሎትና ምቾት የማይተካሕ ይወት እና አካሉን የሚገብረው ወታደር የሚዋጋው እርሱን ከመሰሉ የህዝብ ልጆች፣ ከወንደሞቹ ከእህቶቹ ጋር መሆኑን ማሳመን ያስፈልጋል። ▪️ሆነ ብሎ ኃይል የማሳሳትና የመበታተን ሥራ ማካሄድ እና ያልታሰበ ደፈጣ ጥቃር ማካሄድ፤ የሚተላለፉ የቴልግራም መልዕክቶች እና ትዕዛዞ የተዛቡ፣ አዘናጊ እና ግራአግቢ እንዲሆኑ ማድረግ፤ ▪️አገዛዙ "ለምን ትሸሻላችሁ? ለምን ትክዳላችሁ?" እያለ በሰራዊቱ አባላት ላይ እየወሰደ ያለውን ግብታዊ እና አምባገነናዊ እርምጃ በማጋለጥ በሰራዊቱ ውስጥ አዛዥ እና ታዛዥ መካከል መከባበር እና መግባባት እንዳይኖር እንዲሁም ትዕዛዝ የሚቀበል ሰራዊት እንዳይኖር ማድረግ፤ አገዛዙ የሚሸችቱን ከጀርብል ሆኖ የሚረሽን ገዳይ ስኳድ እንዳለው ልብ ይሏል። ከሞላ ጎደል በእነኝኽ ስልቶች ከተራመድን ውድቀት እና ሽንፈት አፋፍ ላይ የቆመውን አገዛዝ እና ሰራዊት ድል የምናደርገበት ጊዜ ሩቅ አይሆንም። በመጨረሻም፤ ዓላማችን ሊቀመንበር ማኦ እንዳለው «ዓላማችን አንድ ነው፤ ጨቋኝ ገዢዎቻችንን ማጥፋት ነው። ግባችን አንድ ነው። ይህን ሕዝባችንን እየበላ ያለ ሥርዓት በምድራችን ዳግመኛ እንዳያቆጠቁጥ አድርገን ማጥፋት ነው። አካሄዳችን አንድ ነው፤ ገዢውን ሰይጣን ቀስ በቀስ አካሉን ቆራርጦ ማጥፋት!» ከሕዝባችን የተለየ ማንነት የለንም! መነሻችን ሕዝብ፣ መድረሻ ግባችንም ሕዝብ ነው! የምንዋደቀው ለሕዝብልችን ነጻነት ነው! ድል ለፋኖ! ድል ለአማራ!

ውድቀት እና ሽንፈት አፋፍ ላይ ያለውን አገዛዝ እና ሰራዊት ቀብር ለማፋጠን መደረግ ያለባቸው ነገሮች፦❗️ ጠላት የፈለገውን ያህል ደካማ ወይም አቅም ቢስ ቢሆንም እንኳን የትጥቅ ትግል ማድረግ ብቻውን ለድል እንደማያበቃ የታወቀ ነገር ነው። ሕዝብን አነቃቅቶ፣ ሕዝብን በደንብ ማሰለፍ እና ማስታጠቅ የሚል ፕሮግራም በእጅጉን አስፈላጊ ነው። የሚያሸነፈው ጥይት ብቻ ሳይሆን የፖለቲካ ወይም የለውጥ ፕሮግራም ነው። ታክቲካልም ይሁን እስትራቴጂካል አጋር እና ደጋፊ ኃይሎችን መፍጠር የሚችለው እና የሚያነሳሳውም ይኽው የፖለቲካ ፕሮግራም ነው። ጠንካራ እና ሕዝባዊ መሰረት ያለኽ እንድትሆን የሚረዳው የፖለቲካ ፕሮግራም ነው። ይኽው የፖለቲካ ፕሮግራም ለሕዝብ ይደርስ ዘንድ በተለያዩ የሚዲያ አማራጮች ሊተላለፍ እና በጽሑፍ ሊሰራጭ ይገባል። ያንጊዜ ዓላማህ ለብዙኃኑ ተደራሽ ይሆናል፤ ድልህም ቅርብ ይሆናል። የጠላትን ወታደር ማርኮ ፕሮግራምን አስታጥቆ መልሶ ወደ ጠላት ካምፕ መላክም ያስፈልጋል፤ ከወታደራዊ ፕሮግራም ይልቅ ፖለቲካዊ ፕሮግራም ነው ወሳኙ፤ ከወታደራዊ ትግል በተጨማሪ ወሳኙ ነገር የፖለቲካ ፕሮግራም እና ዓላማ ነው። የሚያሸንፈው ይኽው አስተሳሰብና አቋም ነው። ሁሉም ነገር በወታደራዊ ዓይን ብቻ ከታየ ነገሮች እንደታሰበው አይሆኑም። ስለሆነም፤ እነኝኽ ፖለቲካዊ ፕሮግራም እና ዓላማ በደንብ ይስመርባቸው እያለን፤ የጠላትን ቀብር ወደሚያፋጥኑት ወታደራዊ ስልቶች እንገባለን። ▪️የሕዝብን ልብ ማሸነፍ እና ሁለንተናዊ ድጋፍ ለማግኘት መሞከር፤ እንደ ቬተናም የሽምቅ ተዋጊዎች የክብር መሃላው "ሕዝብን ማክበር፣ ሕዝብን መረዳት እና ለሕዝብ መቆም" የሚል መሆን አለበት።የሕዝብን ብሶት እና ችግር በማንሳት፤ የአገዛዙን በደል እና ግፍ ለሕዝብ በማጋለጥ ሕዝብን መቀሰቅስ እና ከጎን ማሰለፍ ቀዳሚው ስልት ነው። ▪️የጠላት ሰራዊት በየትኛውም ቦታ ሲንቀሳቀስ መረጃውን ማጋራት፤ በሰራዊቱና በአገዛዙ ተቋም ውስጥ ወኪል አስርጎ በማስገባት የጠላትን እቅዶችን እና ሚስጥሮችን ቀድሞ ማወቅ።  የጠላት የመረጃ ክፍል ጉርሻ በሚከፈላቸው ወኪሎች በኩል የተዛባ መረጃ እንዲደርሰው ማድረግ፤ ▪️ለጠላት ቅዥት የሆነ የረቀቀ እና የላቀ የመረጃ መረብ መዘርጋት፤ ቁርጠኛ ተዋጊ እና መሪዎችን መፍጠር፤ ▪️ከችሎታ ይልቅ በግለሰብ ታማኘነት መስፈርት የተደራጀው ጠላት ያለበትን የአደረጃጅት ችግር እና መደበላለቅ በአግባቡ መጠቀም፤  ጠላት የአንድዮሽ እዝ የሌለው (መከላከያ፣ ፖሊስ፣ አድማብተና እና ሚሊሻ) የሚል ወጥነት የጎደለው ጣት ለመቀሳሰር እና ለመደባላለቅ የተጋለጠ በመሆኑ ይህን ክፈትት በአግባቡ መጠቀም፤ ▪️የጠላትን ወረዳ ዙሪያውን በመቆጣጠር ስንቅ እና ትጥቅ እንዳይደርሰው በማድረግ በርሃብ፣ በመድኅኒት እና በንጽሕን አቅርቦት ችግር እንዲሰቃይ በማድረግ በቀላሉ ድል መምታት፤ ▪️ቀንና ሌሊት ማጥቃት፣ በስነ-ልቦነ ጦርነት ብልጫ መውሰድ፣ አቅርቦትና የእርዳታ ጦር እንዳይደርስ ማድረግ፤ ▪️ሐሰተኛ ማጥቃት በመሰንዘር ጥይት ማስጨረስ፣ ሌሊት ፈንጅ ማጥመድ እና ማንቆ ቦታ ላይ ጥቃት መሰንዘር፤ ▪️ጠላት ውስጥ ቦርቡሩ እና ሰርጎ በመግባት አስቀድሞ መረጃዎችን በማግኘት ጥቃት ማድረግ፣ የማይገጥም ጥይትና ጠመንጃ እንዲታደል ማድረግ፣ የፈዘዘ መከላከል የሽንፈት ምንጭ በመሆኑ ሰራዊቱ ራሱን እንዳይከላከል እና እንዲጠቃ ማድረግ፤ ስንቅ እና ትጥቅ ለሰራዊቱ በስዓቱ እንዳይደርስ ማድረግ፣ ለውጊያ ተነሳስቶ የመጣን የጠላት ጦር ቀድሞ ከቦታው በመሸሽ እንል በመሰወር ሞራሉ እንዲቀዘቅዝ እና እንዲዘናጋ ማድረግ፤ ▪️ሕዝባዊ የሆነው የፋኖ ጦርነት ምስኪኑን የአገዛዙን ወታደር ለማጥፋት ሳይሆን ምስኪኑን ወታደር በምስኪን ወገኖቹ ላይ እንዲተኩስ ያስገደደውን ሰው-በላ አገዛዝ ለማስወገድ መሆኑን እንዲያውቀው ሰፊ የቅስቀሳ ሥራ መሥራት፤ ▪️ፖለቲከኞች ሥልጣናቸውን ለማራዘም ሲሉ ከሚጠብቀው ሕዝብ ጋር እያጋደሉት መሆኑን ሠራዊቱ እንዲያውቀው ከፍተኛ፣ እጅግ ከፍተኛ የቅስቀሳ ሥራ መሠራት፤ የአውሬው የጦር አዛዦች ከሚመሩት ጦር ጋር በመንፈስ እንዲለያዩ ማድረግ፤ ▪️በጦርነት የሚማረኩ ወታደሮች፣ መኮንኖች፣ ቁስለኞች፣ ተገቢው እንክብካቤ ሊደረግላቸው፣ በፍቅርና በወንድማዊነት መያዝ፤ ይህ የጠላትን ወታደር የመዋጋት ሞራል ይቀንሳል፣ ይህም ብዙ የጠላት ሰራዊት አሁን እያደረገ እንዳለው በውድም ይሁን በግድ እየካደ በገፍ ወደ ሕዝባዊው የፋኖ ጦር እንዲቀላቀል ያደርጋል። ▪️የፋኖ ጦርነት ሁሉን አካታች፣ ሁሉን አቃፊ፣ ሁሉን ቻይ፣ ታጋሽ፣ እና ለዓላማ በፀኑ ቆራጥ፣ እና ጨዋ (ዲሲፕሊን በተላበሱ) ጓዶች የሚመራ መሆን አለበት፡፡ በሕዝባዊ ጦርነት መሪና ተመሪ የየራሳቸው ሚና ቢኖራቸውም፣ የአዛዥና የታዛዥ ግንኙነት የባርያና የጌታ ግንኙነት ፈፅሞ ሊሆን አይችልም። እያንዳንዱ የሕዝባዊ ጦር አባል የየራሱ ነፃነት ሊጠበቅለት ይገባል፤ እንዳሻው እንዲሠማራ፣ አጠቃላዩን ዓላማ እስካወቀ ድረስ ያሻውን እርምጃ እንዲወስድ flexibility and freedom ሊሰጠው ይገባል። ▪️ከቤታቸው ተጠራርተው ወጥተው በእጃቸው ላይ ባላቸው መሣሪያ በአውሬው አገዛዝ ላይ ጥቃት የሚሰነዝሩ ሲቪል ሰዎችም የሕዝባዊው ጦር አለኝታ ናቸው። አምስት ስድስት ሆነው ተመካክረው፣ ብቻውን በሚዘዋወር የአውሬው ወታደር ላይ የደፈጣ ጥቃት የሚሰነዝሩ ዜጎችም የሕዘባዊው ጦር ጀግኖች ናቸው። ▪️የአውሬው ሠራዊት እንዳሻኝ ልጋልባችሁ ሲላቸው አደብ የሚያስገዙት፣ ገደል-ግባ የሚሉት፣ መብቴን አላስነካም፤ ብለው የሚተናነቁትም የሕዝባዊው የፋኖ ጦር ኩራቶች ናቸው። ▪️አገዛዙ ካደራጃቸው ሚሊሺያዎች፣ ክፍለጦሮች፣ የፖሊስ ሠራዊቶች፣ የፀጥታና የፖለቲካ ተቋሞች ከድተው ሕዝባዊውን የፋኖ ጦር የሚቀላቀሉ ሁሉ ለፋኖ ጦር ዋልታና ማገር ናቸው። ▪️ሕዝባዊውን የፋኖን ጦር በቻሉት ሁሉ የሚደግፉ፣ ወራሪውን የአውሬውን ጦር መፈናፈኛ የሚያሳጡ የታጠቁ ሽፍቶች የሕዝባዊው ጦር መከታና ጋሻዎች ናቸው። ▪️አገዛዙ ካሰለፈው ጦር ጋር በዓላማ፣ በፖለቲካ፣ በውግንና መቃቃር፣ መለያየት አለበት። ከሕዝቡ ጋር ሆድና ጀርባ መደረግ፣ መነጣጠል፣ ቂም በቀል ያረገዘ ሕዝብ መበራከት አለበት። አገዛዙ እርስበርሱ መተራመስ፣ መባላት፣ መጠራጠር፣ መነካከስ እና መለያየት አለበት። ▪️አገዛዙ አረመኔያዊ እርምጃ በሠላማዊ ሰዎች ላይ በወሰደ ቁጥር አውሬያዊነቱ ለሕዝቡ ግለጽ ይሆናል። አገዛዙ የገበሬውን ማሳ ባቃጠለ ቁጥር፤ ንብረቱን በዘረፈ ቁጥር አውሬያዊ ማንነቱ ለኅብረተሰቡ ግልጽ ይሆናል። አገዛዙ ተዋጊውን ከሠላማዊው ሰው መለየት እንዳይችል በተደረገ ቁጥር አውሬያዊ ስብዕናው ለሕዝቡ ግልጽ እየወጣ ይመጣል። ▪️የአጒዙ ሹማምንትና የጦር አዛዦች የተቀናጣ ሕይወት በየጦር ሜዳው ተሰልፎ ከሚዋጋውና ሕይወቱን ከሚገብረው፣ አካሉን ከሚያጎድለው የደሃ ልጅ አኗኗር ጋር ምን ያህል የተለያዩ እንደሆኑ ተደጋጋሚ ቅስቀሳ፣ ማጋለጥና ሰፊ ዘመቻ ማካሄድ ያስፈልጋል። ▪️የጦር መኮንኖች ውድ የመኖሪያ ቤቶች፣ በውድ ትምህርት ቤት የሚማሩ ልጆች፣ የሚጎርፍላቸው ጥቅም፣ የሚሰለፉበት ከጥቃት የራቀ የጦር ሰፈር ሁሉ ለወታደሩ እንዲያውቀውና ቅሬታ እንዲያድርበት ማድረግ ያስፈልጋል።

"The Merawi massacre is one of the deadliest episodes in Amhara since the fighting started" Š The Guardian

ባለፉት 36 ሰዓታት የአማራ አውደ ውጊያ መረጃዎች ፤ 1) ጎጃም ► በጎጃም ዕዝ የቀኝ ጌታ ዮፍታሄ ንጉሴ ክፍለጦር በአምበር የተድላ ጓሉ ብርጌድና በንጉስ ተክለሀይማኖት ብርጌድ የየቦቅላ የአባይ ሻለቃ ቅንጅት አምበር በሚገኘው የፋሽስት አገዛዙ ሰራዊት ላይ እርምጃ ተወስዶ ከ55 በላይ የአገዛዙ ሠራዊት ተደምስሷል። ቁጥራቸው ያልተለየም ቁስለኛ ሆነዋል። በአምበር ጫካ መሽጎ የተቀመጠው የብርሀኑ ጁላ ዙፋን ጠባቂ ሰራዊት ስለተደመሰሰ ከደብረ ማርቆስ ሌላ ሀይል ተተክቷል። ► በጎጃም ደብረ ወርቅ በነበልባሉ ፋኖ በተደረገ የደፈጣ ጥቃት በ2 ኦራል መኪና ሲጓዝ የነበረ የአገዛዙ ሰራዊት ተደምስሷል ። ► እዚያው በጎጃም ቁጭና ወይንማ አካባቢዎች በተደረጉ ውግያዎች በቁጥር ያልታወቁ የአገዛዙ ወራሪ ጦርና ሚሊሻዎች ተገድለዋል። የቡድንና የነፍስወከፍ መሳሪያዎችም በአማራ ጦር ተማርከዋል:: ► በጎጃም አገው ምድር አብዛኛው ቦታ የብልፅግና ወታደሮች፣ ፖሊስ እና ሚሊሻ በየቤተ ክርስቲያኑ እየዞሩና እያስፈራሩ ግብር ክፈሉ ካልከፈላችሁ "ፅንፈኛውን ፋኖን" ትደግፋላችሁ እርምጃ እንወስዳለን እያሉ ሲያስፈራሩ መዋላቸውን ኢትዮ 251 ሚዲያ ዘግባለች። ► በምዕራብ ጎጃም በጅጋ ከተማ የአድማ ብተና አባልት በከተማው የሚገኘውን ወጣት እያፈኑ ገንዘብ እየጠየቁ እንደሆነና በየቤቱ እየገቡ እየዘረፉ እንደሆነ ታውቋል።  እስከአሁንም ደምበጫ በርና ደጋዳሞት በር በሚባልት ሰፈሮች ላይ ፍተሻ እናደርጋለን በማለት ወርቅ እና ሞባይሎችን መዝረፋቸውን ሰዎችን አፍነው በመውሰድም በጎን ለቤተሰቦቻቸው "ብር ክፍሉና እናስለቅቅላችሁ" እያሉ እንዳሉ የደረሰን መረጃ ያስረዳል። 2) ጎንደር፤ ► በደቡብ ጎንደር በደራና በእስቴ ወረዳዎች ሠራዊት በወራሪው የብልጽግና ጦር ላይ ባደረሱት ማጥቃት በ6 መኪና ሲጓዝ የነበረ የጠላት ሰራዊት ከበባ ፈፅመው ከ40 በላይ ሙት ሲደረግ ከ60 በላይ ቁስለኛ ሆኗል። ብዛት ያለው ኃይል መማረኩን የግንባሩ ከፍተኛ አዛዥ ሻለቃ ቢራራ ደምሴ ተናግሯል። ► ተጨማሪ ከሃሙስት አቅጣጫ ሲመጣ የነበረ ጠላትም በደራ ግንባር በሚንቀሳቀሰው የጣና ገላውዲዮስ የፋኖ ሰራዊት ተደምስሷል! 3) ወሎ ፤ ► በደቡብ ወሎ መካነ ሰላም የቤተ አምኃራ ፋኖ በፈጸመፈው መብረቃዊ ጥቃት በርካታ ጠላት ሲረግፍ ወደ 56 የሚሆነውን ቁስለኛ በካሶኒ ጭኖ ወጥቷል። ► በሌላ መረጃ ወሎ ወግዲ የቤተ አምኃራ ፋኖ በወራሪው ላይ ከባድ ምት አድርሰው በቁጥር ያልታወቀ አድር ባይ ሚሊሻ ሲገደል የጦር መሳሪያዎች ተማርከዋል፣ አንድ ኦራልና አንድ ካሶኒ መኪና ወድሟል። ► ደቡብ ወሎ ለጋንቦ ወረዳ በገነቴ ከተማ የመሸገው የአገዛዙ ጦር እርስ በእርሱ ተታኩሷል። በከተማዋ ፈረጅ ጎራ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ ካምፕ ውስጥ የሚገኘው የብርሃኑ ጁላ ጦር በትናንትናው ዕለት ባደረገው የእርስ በእርስ ተኩስ ቁጥራቸው ያልተለየ የአገዛዙ ወታደሮች ሙት እና ቁስለኛ ሆነዋል። የተታኮሱበት ምክንያት ዋና መነሻው በአገዛዙ ተስፋ የቆረጡ ወታደሮች ከድተው ከካምፕ ለመውጣት ሲሞክሩ ፤ ሰራዊቱ በሁለት ጎራ ተከፍሎ መውጣት አትችሉም እና እንወጣለን በሚል የተኩስ እሩምታ ከፍተዋል ። ► በተያያዘ በገነቴ ከተማ ፖሊስ እና ሚሊሻ ለሰላሳ ደቂቃ ያክል በህዝብ ላይ የተኩስ እሩምታ ከፍቶ የነበረ ሲሆን ተኩሱ ጋብ ካለ በኋላ የግለሰብ መኖሪያ ቤት በመግባት ‹ፋኖ ደብቃችኃል› በሚል ሰበብ ዝርፊያ ፈፅመዋል። 4) ሸዋ፤ ► በሸዋ መርሐቤቴ አለም ከተማ በተጣለ የድሮን ጥቃት አርበኞች 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ላይ ጥቃት የደረሰ ሲሆን፤  ቁጥራቸው ያልታወቀ ተማሪዎች ተገድለዋል:: ► በሸዋ በፋኖ አሰግድ መሪነት ምስረታው ይፋ የሆነውን የሸዋ ፋኖ ዕዝ አንቀበልም ያሉትና በፋኖ መከታው የሚመሩ ብርጌዶች ሌላ ዕዝ መመስረታቸውን አስታውቀዋል። ► መርሀቤቴ በአካባቢው 7 አስታራቂ ሽምግሌዎችን የአገዛዙ ወታደሮች አፍነው ወደ ደብረብርሃን በመውሰድ ባህር ሃይል ግቢ ውስጥ ሲገርፉና ሲያሰቃዩቸው እንዳደሩ ታውቋል። ከታፈኑት ውስጥም ከ70 አመት በላይ የሚሆኑ ሲገኙበት ከነዚህ ውስጥ 1) አቶ ላቀ ሰሙ 2) መምህር ዋጋዬ  የሚባሉ ይገኙበታል። ከሽማግሌዎቹ በተጨማሪም በርካታ ወጣቶችም መታፈሳቸው ሲታወቅ ሽማግሌዎቹን ጨምሮ ከደብረብርሃን ወደ ሸዋሮቢት ማረሚያ ቤት ለመውሰድ እንደታሰበ ታውቋል። ድል ለአማራ ጦር ሠራዊት !! ውድቀት ለዘር አጥፊ ፋሽስቶች !!

ለስምንት ወራት ባካሔደው የዘር ማጥፋት ጦርነት ወደር የለሽ ኪሣራ የተከናነበው ዘር አጥፊው አገዛዝ፥ ተስፋው የአማራ ኃይሎች እርስበርስ ግጭት መሆኑን  ይፋ አድርጓል። ባለፉት ወራቶች ሁሉ ለወረራ የላከው ሠራዊት እየከዳው ሕዝባዊ ጦሩን ሲቀላቀል፣ የአገዛዙን አረመኔዎች ደምስሶ ወደ ፋኖ ሲገባ፣ ሙሉ ሻምበልና ሻለቃ ጦር አገዛዙን ትቶ ወደአማራ ኃይል ሲገባ፣ ኤሊት ጦር እያለ የተመፃደቀበት ጦር ሲወድምበት፣ አማራ ናችሁ ብሎ በአሥርሺህዎች ሠራዊት በማጎሪያዎች አጭቆ እያሰቃዬ ያለው አገዛዝ  "መከላከያ" ተብዬ ነው ዛሬ ፋኖዎች እርስበርስ ተጣሉ ብሎ ያርበደበዱትን ጀግኖች በስም የሚያወድስ ትርኪምርኪ የለቀለቀው።

አማራ ብሮድካስቲንግ ሴንተር  (Abc Tv) የአማራን ህዝብ ድጋፍ  ጠየቀ የካቲት 1 2016 ዓ/ም ላለፉት 8 ወራት በአማራ ህዝብ ስም የተቋቋመ እና ዋነኛ ትኩረቱን ለአማራ ህዝብ አድርጎ እየሰራ የሚገኘው የአማራ ብሮድካስቲንግ ሴንተር ስርጭቱን  ከጀመረ ግዜ አንስቶ በርካታ ስራዎቹን ለህዝቡ ማድረሱን የመስራች ቦርድ ሊቀመንበር የሆኑት ዶ/ር አብርሃም መለሰ ገልጸዋል። ኤቢሲ ለአማራ ህዝብ ተመስርቶ እያለ የአማራ ህዝብን ድጋፍ አጥቶ መዘጋት እንደሌለበት የገለጹት ዶክተር አብርሃም እስካሁን የተቻለውን ሁሉ ተደርጓል ከአሁን በኋላ ኤቢሲ የማስቀጠል ግዴታ የህዝቡ መሆን አለበት ብለዋል:: በርካታ ስራዎችን የሰራው ኤቢሲ የአማራ ህዝብ በሚገባው መልኩ እንዳልደገፈው የገለጹት ረ/ፕ ትንግርቱ ገብረጻቅድ ከመደገፍ ይልቅ መገፋት እንዳስተዋሉ ገልጸዋል። ኤቢሲ ለአማራ ህዝብ የቆመ የቴሌቭዥን ጣቢያ በመሆኑ ሁሉም አማራ ሊደግፈው እንደሚገባ አጽኖት ሰጥተው ገልጸዋልተናግረዋል።  በኤቢሲ ቴሌቭዥን የቴክኒክል ክፍል ሃላፊ በመሆኑ እያገለገሉ የሚገኙ አቶ ዳግም እንደገለጹት  ኤቢሲን የመሰረቱት አማራዎች በርካታ ዋጋ መክፈላቸውን ያስታወሱ ሲሆን ሚዲያው የአማራ ህዝብ ድምጽ ሁኖ እንዲቀጥል ሁሉም የበኩልን አስተዋጾ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል።  ‹የአማራ ህዝብ ተቋም መመስረት አይችልም › በሚል በጠላቶቹ ወቀሳ ሲቀርብበት የነበረው የአማራ ህዝብ የተመሰረተለትን ተቋም ሊደግፍ እንደሚገባ ተገልጿል። በተለይም በአማራ ስም የተመሰረቱ አደረጃጀቶች ቅድሚያ ሰጥተው ኤቢሲን ሊደግፉት እንደሚገባ ተነግሯል። በሰራቸው ስራዎችን ለአማራ ህዝብ እንደቆመ ያሳየ የመገናኛ ብዙሃን መሆኑን እያወቁ ኤቢሲ ስራውን እንዲያቆም የስም ማጥፋት ዘመቻ የሚያደርጉ አካላት እና የገንዘብ ድጋፍ እንዳያገኝ የተለያዩ ዘመቻዎችን የሚያደርጉ አካላት ከመጥፎ ስራቸው እንዲታቀቡ ተጠይቋል።      https://gofund.me/e224aaa6

ጦርነቱ በአማራ ወረዳዎች እና ከተሞች እስከቀጠለ ድረስ ጠላት በደስታ ያስቀጥለዋል። ባሩድ የሚያጥናቸው መንደሮች የአንተ ናቸው ። ቦንብ የሚመርዛቸው ቀዬዎች የአንተ ናቸው። የሚፈርሱ መሠረተ ልማቶች፣  የሚዘጉ ቢዝነሶች፣ የሚሰቃየው ሕዝብህ የአንተ ነው። ይሔ ለጠላት ደስታ ነው። ሊያጠፋህ ለሚፈልግ አገዛዝ እንደሕዝብ ድሕነትን የሚያባብስ ፣ ሰዎችን የሚበላ ሒደት መቀጠሉ እሰየው ያስብለዋል። ስለሆነም የወታደራዊ እና ፖለቲካዊ ሥራዎችን አመቻችቶ አውደ ውጊያውን ከሕዝብህ ጫንቃ እና ቀዬ ማራቅ ቁልፍ ጉዳይ ነው። ያ እስካልሆነ ድረስ እያነቀ የሚልካቸው ወጣቶች አያጣም፣ ተበድሮም የሚተኩሰው አያጣምና በአንተ ቀዬ ያደርገዋል።  ነፃ ቀጠናዎችን መፍጠር የሚቻለው  የውጊያ ሜዳው ሲለወጥ ነው።ስለሆነም ጦርነቱን ከአማራ ቀዬዎች ማስወጣት ቁልፍ ሥራ ሊሆን የግድ ነው !!

⓺ ከውጫዊ ተፅዕኖ ነፃ መሆን ይገባል፤ በሕልውና ትግሉ ላይ የውጫዊ አካላት ተፅዕኖ ይኖራል፣ አለ። ውጫዊ አካላት ሲባል ከወታደራዊ ትግል ውጭ ያሉ የአገር ውስጥና የውጭ አገር እንዲሁም የሌላ ሶስተኛ አካል ተፅዕኖ ማለት ነው። እነዚህ አካላት የአላማ ተጋሪዎትም ሊሆኑ ይችላሉ፣ የአላማ ጠላፊዎችም ሊሆኑ ይችላሉ። የአላማ ተጋሪዎች ቢሆኑም ሚናቸው ወታደራዊ አይደለም። የእነዚህ አካላት ተፅዕኖ በቀጥታና በተዘዋዋሪ የሚገለፅ ነው። በወታደራዊ አደረጃጀት ፣ በወታደራዊ አመራር ሰጪነት፣ በሪሶርስ ምደባ ፣ በአካሔድና አሠራር ወዘተ ሊገለፅ ይችላል። መጀመሪያ ሚናን ለይቶ ማስቀመጥ ይገባል። ወታደራዊና ፖለቲካዊ አመራር ያለው በረሃ ነው። ሌላው ከሆነ የዚህ ደጋፊ ነው። በሚድያ ይደግፋል፣ በዲፕሎማሲ ይደግፋል፣ በገንዘብ ይደግፋል፣ በእውቀትና ሰነድ አቅርቦት ሊደግፍ ይችላል። በቀጥታ ትግሉን በመቀላቀልም የትግሉ አካል መሆን ይችላል። ከውጭ ተቀምጦ ግን ትግሉን በዚህ አውጣው በዚህ አውርደው ማለት የለበትም። ውጫዊ ኃይል ሊሠራ የሚችለው ባለበት ነው። ውጭ አገር ከሆነ በውጭ አገር የሚድያ ፣ የዲፕሎማሲ፣ የገንዘብ እንዲሁም የቴክኖሎጂና የእውቀት አስተዋጽኦ ሊያደርግ ይችላል። ጣልቃ ገብነትን ማስቆም ያስፈልጋል። ጣልቃ ገብነቱ ግለሰቦችን በመያዝ፣ የሆነውን ታጋይ ቡድን በማታለል፣ አጠቃላይ ሒደቱን ልወስንላችሁ በማለት ወዘተ ይገለፃል። ይሔ ታጋዩን ደጅ ተመልካችና ጥገኛ ያደርገዋል። መተማመንን ይጎዳል፣ ለሠርጎ ገብ አመለካከቶችና የቡድን ፍላጎቶች በማጋለጥ ትግሉን ያኮላሻል። ⓻ የትግል አንድነት እና ማዕከላዊ ኮማንድ የትግሉ አንኳር ሼል ነው፤     በሕልውና ትግል ውስጥ ለተሠለፈ ኃይል የትኛውም መከፋፈልን የሚያስከትል ልዩነት የሕልውና አደጋ ተደርጎ መታየት አለበት። የአሠራር ልዩነት በምክክርና ክርክር በውስጠ-ዲሞክራሲ የሚፈታ ነው። ከዚያ ያለፈው እና በተለይ የትግሉን አንድነት የሚጎዳ አካሔድ አፍራሽ፣ ፀረ-አማራና ፀረ-ዲሞክራሲያዊ ነው። የአላማ አንድነትን በጥብቅ ማረጋገጥ ዋናው ነው !! የአደረጃጀት አንድነትን አሁን በተጀመረው ልክ ቶሎ ወታደራዊ የአደረጃጀትና ኮማንድ አንድነትን ማረጋገጥ ይገባል። በአደረጃጀት ፣ በኦፕሬሽን ፣ በሪሶርስና ሕዝብ ግንኙነት  "ወታደራዊ ሉዓላዊነት" የሚሠማቸው የታጠቁ ቡድኖች መኖር የአማራ ትግል አንድነት ስጋት ናቸው። ስለሆነም ወደዕዞች ምስረታ ያደገው የአደረጃጀት ሼል ወጥ ወደሆነ ወታደራዊ ኮማንድ ማደግ አለበት። ይሔንን ኮማንድ የሚመራው ፖለቲካ እና ፖለቲካዊ አመራርም በፍጥነት መመስረት አለበት።  ማዕከል የሌለው አደረጃጀት መቅረት የሚችለው ወታደራዊም ሆነ ፖለቲካዊ ትግሉ አባት ሲኖረው ነው። አባት የሌለው አደረጃጀት አባት እንደሌላቸው ልጆች የተበታተነና አንድነት የሌለው ይሆናል። አፈንጋጭነት ከሕልውና ታጋይ አይጠበቅም። ለመወያየት ለመመካከር አለመፍቀድ ፀረ-ዲሞክራሲያዊነት ነው። መከፋፈል እና የብቻ ጉዞ የሕልውና አደጋ ከተጋረጠበት ሕዝብ አይጠበቅም። ⓼ ከድል ፈንጠዝያ መውጣት ያስፈልጋል፤ ትግሉ በሆነ ግንባር ፡ የሆኑ የአገዛዙ ወታደሮች ላይ በሚገኝ ድልና ሽንፈት የሚወሰን አይደለም።  ሩቅ ተጓዥ በአጭር ድል አይፈነጥዝም፣ በሆነ ፈተና አይቆምም።  ጊዜያዊ ሙቀትና ቅዝቃዜ የሚፈትነው ቁመና ሊኖር አይገባም። የአገዛዙን ሠራዊት መመከትና ማስቆም በራሱ የመጨረሻ ግብና ፈንጠዝያ ምንጭ አይደለም። አገዛዙን ማሸነፍም የሕልውና ጉዟችን ሩብ መንገድ እንጂ ሕልውናችን የሚረጋገጠው በበለጠው የፖለቲካ መድረክ ነው። እርካታ የሚባል ነገር ትግል ያስቆማል፣ አደገኛ ነው !! ይሔ ትግል ሰው እየተከፈለበት ያለ ነው። በአውደ-ውጊያ ብቻ ሳይሆን በእየእሥር ቤቱ እና በተለያዩ ቀጠናዎች ጠላት ሰው እያስከፈለ ነው። ይሔንን እያሰቡ መጓዝ ትግሉ ለድል እስኪበቃ ለቡረቃና ለፈንጠዝያ ጊዜ የለም። እሱ ከዘላቂ ድል በኋላ የሚደርስ ነው። ➈ አጋሮችን ማፍራት ትልቁ ተልዕኮ መሆን አለበት፤ የያዝነው ትግል የሕልውና ጥቃት የተከፈተ ስለመሆኑ ብዙዎች ኢትዮጵያዊያን ያምናሉ። በእኛ ልክ ቢሆንም ባይሆንም በአገዛዙ የጥቃት ሰለባ የሆኑ ብዙ ናቸው። ስለሆነም አጋሮችን ለመፍጠር ምቹ ሁኔታ አለ። ወታደራዊም ፖለቲካዊም አጋሮችን መፍጠር በእጅጉ አስፈላጊ ነው። ለዚያ የሚመጥን የራስን ፖለቲካዊ እና ወታደራዊ ቁመና ማስተካከል ቀዳሚው የቤት ሼል ነው። ቁመናህ መስተካከሉ በራሱ የሚፈጥራቸው አጋሮች አሉና !! ከዚያ በመለስ ለወታደራዊ እና ፖለቲካዊ ትብብር አብረው የሚሰለፉ አካላትን ማግባባት ማግኘት መተባበር በእጅጉ ወሳኝ ነው። አጋሮችን ያላበጀ ትግል ሩቅ አይሔድም ቢሔድም የዘገዬ ሼል ይሆናል። ስለሆነም ይሔንን አላማ አድርጎ ለመስራት መነሳት ተገቢ ነው። ➉ ጦርነቱ ከአማራ መውጣት አለበት፤ ጦርነቱ በአማራ ወረዳዎች እና ከተሞች እስከቀጠለ ድረስ ጠላት በደስታ ያስቀጥለዋል። ባሩድ የሚያጥናቸው መንደሮች የአንተ ናቸው ። ቦንብ የሚመርዛቸው ቀዬዎች የአንተ ናቸው። የሚፈርሱ መሠረተ ልማቶች፣  የሚዘጉ ቢዝነሶች፣ የሚሰቃየው ሕዝብህ የአንተ ነው። ይሔ ለጠላት ደስታ ነው። ሊያጠፋህ ለሚፈልግ አገዛዝ እንደሕዝብ ድሕነትን የሚያባብስ ፣ ሰዎችን የሚበላ ሒደት መቀጠሉ እሰየው ያስብለዋል። ስለሆነም የወታደራዊ እና ፖለቲካዊ ሥራዎችን አመቻችቶ አውደ ውጊያውን ከሕዝብህ ጫንቃ እና ቀዬ ማራቅ ቁልፍ ጉዳይ ነው። ያ እስኬልሆነ ድረስ እያነቀ የሚልካቸው ወጣቶች አያጣም፣ ተበድሮም የሚተኩሰው አያጣምና በአንተ ቀዬ ያደርገዋል።  ነፃ ቀጠናዎችን መፍጠር የሚቻለው  የውጊያ ሜዳው ሲለወጥ ነው። ስለሆነም ጦርነቱን ከአማራ ቀዬዎች ማስወጣት ቁልፍ ሼል ሊሆን የግድ ነው !!

መልዕክት ለአማራ ሠራዊት መሪዎች፤ በፋኖ አመራርነት ውስጥ ያሉ ጓዶች በከፍተኛ ጥንቃቄና ብስለት ስሜት መሥራት አለባቸው!! ➀ ፖለቲካ ወታደራዊ ትግሉን ሊመራ የግድ ነው፤ ፖለቲካዊነት የአመራር ሚና ነው። ትግሉ ፖለቲካዊ ግብ የያዘ ነው። ያ ፖለቲካዊ ግብ በወታደራዊ ትግል እንዲካሔድ አስገድዷል። ስለሆነም በተለይ አመራሩ ፖለቲካዊ ግብንና አላማን ለማሳካት እየሠራ መሆኑን መገንዘብ ተገቢ ነው። ወታደራዊ አካሔዱ የፖለቲካ ማሳኪያ መሣሪያ ነው። ጠበንጃውን የሚያዘው የፖለቲካ ግብ ነው። ስለሆነም ፖለቲካዊ አላማንና ግብን የሚመራ ጠንካራ አደረጃጀት ተጠናክሮ መውጣት አለበት። ➁  ዲሞክራሲያዊ አሠራሮች ጥብቅ እስቶቹ ሊሆኑ ይገባል፤   ከዲሞክራሲያዊ አሠራርና አካሔድ የተፋታ አመራር ለዲሞክራሲያዊ ትግል አይመጥንም። አፈናን፣ ጭቆናን፣ አምባገነናዊነትን ለመታገል በዱር በገደሉ ዋጋ የሚከፍል ታጋይ ዲሞክራሲያዊ አሠራርን ካልተከተለ ከትግሉም ከፋኖነትም ጋር ይቃረናል።  ለላቀ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት የሚታገል ታጋይ ከአሁኑ በሚያደርገው ትግል ዲሞክራሲያዊነትን ሊለማመድ የግድ ነው። የተልዕኮ መለኪያ መርሆዎችና እምነቶች የታጋዩ መነጋገሪያ ሆነው ልዩነቶችና አለመግቤባቶች የሚፈቱበት ዲሞክራሲያዊ አሠራር ሊኖረው ይገባል። ያ ካልሆነ ልዩነትን በማጎሪያ ቤት እንደሚፈቱት ገዢዎች ይሆናል። በውስጣዊ አሠራሩ ፀረ-ዲሞክራሲያዊነትን የሚከተል አደረጃጀትና አመራር ፡ ትግሉ ለአማራ ዲሞክራሲን ሊያጎናፅፍ አይችልም። ➂ ፍትሐዊነት  እና ሰብዓዊነት ማተቡ ይሁን፤ የሚያታግለን ፍትሕ ማጣት ነው። የሚያታግለን ሰብዓዊነት ያጣ ጨካኝ የዘር ማጥፋት አዋጅ ነው። ለፍትሕ የሚታገል ታጋይ ፍትሐዊ መሆን አለበት። በአሠራሩና በአመራሩ ፍትሐዊነትን ሊመራበት ይገባል። ፍትሐዊ ያልሆነ ታጋይ የፍትሕ ጠበቃ ሊሆን አይችልም። ቢያሸንፍም ፍትሐዊነትን ሊያሰፍን አይችልም።  የሰብዓዊነት እሴት የሌለው ታጋይ ለሰብዓዊ ክብር መታገል ይቸግረዋል። በሰብዓዊነት ላይ የተከፈተ አገዛዛዊ ጥቃት በረሃ ያስገባው ታጋይ እምነቱና ትግሉ ለአማራ የፍትሕና ሰብዓዊ ክብር መጠበቅ በመሆኑ የሚያዳብረው እሴቱ መሆን አለበት። ➃ መሪዎች የሚፈጠሩት በትግል ነው፤   ራሱን የበቃ የጨረሰ መሪ አድርጎ የሚያስብ አመራር ካለ የመማርና የማደግ እድሉን የዘጋ ነው። ላለፉት ሰባት ወራቶች በረሃ እያደረ፣ በአማራ ወጣቶች ህይወት ላይ ውሳኔ እየወሰነ ፣ እያደራጀ፣ እያሰለጠነ ፣ ጦርነት እየመራ ፣ አንዳንዴ እየቀናው ሌላ ጊዜ እየተፈተነ የሚወጣ አመራር የነገ ትልቅ መሪ ይሆናል። ያለ ፈተና ተዘጋጅቶና በቅቶ የሚገኝ መሪ የለም። ሁሌም ለመማማር ሁሌም ለመሻሻል የሚተጋ አመራር ነገ ሕዝብን ሠራዊትን ይመራል። በጎም ሆኑ መጥፎ የትግል ገጠመኞች ከሰው ጋር ብቻ ተያይዘው አታጋዮች የሚብጠለጠሉበት ሊሆን አይገባም። አንድም እንደክስተት ጉዳዩን ለብቻ መገምገም ሁለትም ኄላፊነት የነበረበትን አመራር ክፍተቶች ማለየትና እርምት ማስቀመጥ ይገባል። ይሔ ሒደት መሪዎች ይወልዳል። የመጀመሪያ መሪ ወይም ቀድሞ የነበረ እስከፍፃሜው የሚደርስ ተደርጎ ሊታይ አይገባም። የተሻለ መሪ የበለጠ አታጋይ ሲገኝ ወደፊት ይመጣል። ከፍተኛ መስዋዕትነት በሚጠይቅ ትግል ውስጥ እኖሬለሁ ከማለት ይልቅ እኔ አልፌ ድል ለሕዝብ ይደርሳል ማለትን ይጠይቃል። መሪ የመፍጠር በጎ ፍላጎትና ድጋፍ ሁሌም በእጅጉ አስፈላጊ ነው። ➄ ከራስ ጥቅም(Ego) የወጣ ጓዳዊነት ያስፈልጋል፤ ፍክክር ፣ እኔ እበልጥ እኔ እበልጥ፣ መጠላለፍ፣ እኔ  ካልመራሁ ማለት የትግል እንቅፋት ነው። ፀረ-ዲሞክራሲያዊ በመሆኑ ብቻ ሳይሆን ከራስ በላይ ለሆኑ የሕዝብ ጥቅምና መብቶች ለቆመ ታጋይ የማይገባ ነው። ዲሞክራሲያዊ እና ሰብዓዊ ከሆነ በእርግጥም በዚህ መሠል የራስ ማንገስ ሚና ውስጥ አይገኝም። ጓዳዊነት የሌለው ታጋይ ሕዝባዊነት የለውም። አጠገቡ ካለው ታጋይና ጓድ ጋር ዲሞክራሲያዊ ግንኙነት የሌለው ታጋይ ፣ ራሱን ዋጋ ከሚከፍለው ታጋይ በላይ የሚመለከት አመራርና ታጋይ ለሕዝብ ጥቅም ሊሠራ አይመጥንም። ለመሞት የወጣ ታጋይ ለመንገስ ከሠራ አላማው የሕዝብ መበደልና መጨፍጨፍ አይደለም ማለት ነው። ከሕዝቡ አላማዎች ይልቅ የግል ዝናው የሚያስጨንቀው አመራር ሥፍራው የሕልውና ትግል አይደለም። ይቀጥላል

ትግራይ እና የፕሪቶሪያ ስምምነት፤ "የፕሪቶሪያ ስምምነት ተጨማሪ የሰው ሕይወት እንዳያልፍ ማድረግ አስችሏል" የሚለው የትግራይ አመራር  አነጋገር በከፊል ስህተት ነው። የአብይ አሕመድና የብርሃኑ ጁላ አገዛዝ በፕሪቶሪያ ያደረገው፥  "ተኩሶ ከመግደል"  ወደ "ሳይተኩሱ መግደል" ነው የቀየረው። ከጦርነት ማግስት የተፈጠረው ሁኔታ አገዛዙ የትግራይን ሕዝብ በርሃብና በሽታ  "ሳይተኩስ መግደል" (Killing without Murder) የሚችልበትን ሁኔታ ነው ያመቻቸው ‼ የአለም ዘር ማጥፋት ፕሮጀክቶች ሁሉ፡ እንዲጠፋ የፈለጉትን ሕዝብ ገድለው እንደማይጨርሱት ሲያምኑ፥  "ሳይተኩሱ መግደልን" የሚያረጋግጡ የበሽታ እና ርሃብ ጥቃቶችን ተግብረዋል። ጤና ተቋማት የሚወድሙት ፣ እርሻ የሚራቆተው፣ ትምህርት የሚቋረጠው፣ ሌላም ሌላም ለዚሁ ነው። እርግጥ ነው ወያኔ በአማራ ላይ ያላደረገው ነገር አልገጠመውም። ግን የዘር ማጥፋት ግፎችን የመሩበት፣ የፈፀሙበት፣ እየፈፀሙበት ያሉት የኦሮሞ ልሒቃን ስለመሆናቸው መቀበል አይፈልግም። የአማራውን ቅራኔ የተጠቀመው አብይ ሆኖ ሳለ ፥ አማራን የበደለውም ወደራስ መከላከል ያስገባው ወያኔ ሆኖ ሳለ፥  ወያኔ ግን  የአማራ ልሒቅ አብይን ተጠቀመ በማለት ስቷል። አማራ ከወያኔ የተዋጋው የአብይን አገዛዝ ስለተቀበለ ይመስለዋል። እርግጥ እንደገና የትግራይን ቅራኔ ለአማራ መምቻ ሊጠቀም መሆኑን፣ የትግራይን ቅራኔ ለኤርትራ መምቻ ሊጠቀም መሆኑን ዘግይተው የተረዱ አልጠፉም !! በመጀመሪያው ጦርነት የሆነውም ይህ ነበር። እናም አብይ የሚተኩስ ወታደር ወደትግራይ ስላላከ ትግሬዎችን መግደል አቁሟል ማለት ትልቅ ስህተት ነው !! He is killing you without Murder !! በአማራም ይቀጥለዋል !! ስለሆነም ከአማራ ጋር ያደጋችሁበትን ፀበኛነት ተውትና ይሔንን አገዛዝ ለማስወገድ ተነሱ !!

ያራዘመውን የአስቸኳይ ጭፍጨፋ ጊዜ አዋጅ ተከትሎ የተፈጠረበትን የጦረኛነት ገፅታ ለመሸፈን የሚውተረተረው ዘር አጥፊ አገዛዝ  የሚሠራውን የውይይት ድራማ አፈርፍረህ ብላው በሉት!! ይሔንን የጠነባ አገዛዝ እንደመስሰዋለን !! ይልቅስ ስለድሕረ-ብልፅግና እያሰብን እንታገል!! ዘር አጥፊው የኦሮሙማ ገዢ ልሒቅ ተፈጥሯዊ ሞቱን ሞቷል‼

የዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ  ብዙዎቹ ቤተሰቦች መርአዊ የሚኖሩ ናቸው። የመርአዊን ዘር ማጥፋት ጭፍጨፋ የፈፀመው አገዛዙ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለማራዘም የፓርላማ  ስብሰባ ሊያደርግ ሲያስብ ቀድሞ  ደሳለኝን አሠረው። አገዛዙ በዚህ ልክ የወረደ አረመኔ ነው !!

Genocidal war ምን እንደሆነ ማወቅ የሚፈልግ  ማጀቴና መርአዊ ላይ የተፈፀሙትን ጉዳዮች ይመልከት።

Silencing dissent with drones and military campaigns: The Ominous Escalation of Abiy Ahmed’s Genocidal War on Amhara region  February 3, 2024 Aster Michael  In a recent move, Prime Minister Abiy Ahmed has extended the state of emergency by four months, escalating what appears to be a disturbing war aimed at creating a state of terror among the Amhara population. The tactics employed are deeply troubling, ranging from indiscriminate drone attacks on civilians to shelling residential areas with heavy weapons. Reports indicate door-to-door searches and extrajudicial public executions of civilians, all part of a broader strategy of psychological warfare to suppress opposition and resistance to Abiy Ahmed’s autocratic and ethno-fascist government. The gravity of the situation cannot be understated, as the Prime Minister seems to have chosen a path of violence over dialogue. The extension of the state of emergency raises concerns about the further erosion of civil liberties and human rights in the region. The international community must take note of these alarming developments and act accordingly to prevent a humanitarian crisis. It is crucial to remind Prime Minister Abiy Ahmed that a political or military victory cannot be achieved by causing immense harm to the Amhara civilians. His autocratic and ethno-fascist regime’s actions have led to the loss of countless lives and sown seeds of fear and discord among the population. The Amhara people including all peace loving Ethiopians, both within the country and in the diaspora, are uniting to resist the existential threats posed by the government. The international community must step in to support the Amhara community and condemn the delusional genocidal war of terror waged against them. The recent extension of the state of emergency and the reported atrocities demand a swift and coordinated response to prevent further escalation and ensure the protection of innocent lives. As we witness the Amhara people’s struggle under Abiy Ahmed’s tyrannical regime, it is imperative for global leaders, human rights organizations, and the broader international community to join forces in condemning the violence and advocating for a peaceful resolution to the crisis. Editor’s note : Views in the article do not necessarily reflect the views of borkena.com