en
Feedback
Books world

Books world

Open in Telegram

... የአባቶች ልብ ለልጆች፥ የልጆች ልብ ለአባቶች ተሰጥቷል!... "...አዕምሮ ያላቸውን ሰዎች መረጠ በህዝቡ ላይም አለቆች አደረጋቸው።" ዘፀአት መልካም ምንባብ...

Show more
1 341
Subscribers
+124 hours
-17 days
-2230 days
Posts Archive
የሀይልዬ ስኒ ናታ! እትዬ የሺ በቀን ቢያንስ ሁለቴ ቡና ያፈላሉ:: የጊቢው ሰው ይሰበሰባል:: በተለይ የማታዋ የትዬ የሺ ቡና መሰባሰቢያችን: የቀኑን ሸክም ማራገፊያችን: የሳቅ ጨዋታችን ምንጭ: የሀዘናችን መርሻ: መደገፊያ ትከሻችን ነው:: ለዚያውም  ምንም የማይጎድልበት ቡና ... ዕጣኑ ጉዝጏዙ ቡና ቁርሱ የሳቸው "አፈር በበላሁ" መስተንግዶ... ታዲያ ቡናው ደርሶ በየስኒው ሲቀዳ: የጠጣው ሰው ሁሉ ስኒውን ሲመልስ... "የትኛው ነው ያንተ ስኒ?" "ይሄ ያንቺ ነው ? ቆይ እሷ ያለ ስኳር ነው የምትጠጣው.." “አዪ ተቀላቀለ ቆይ ይታጠብ".. እዚህ ሁሉ ውስጥ የማትገባ : አንድ የማትቀየጥ: ሌላም ሰው የማይጠጣባት እጄታ ያላት ስኒ አለች:: ሁልጊዜም ስለሚገርመኝ: አንድ ቀን እትዬ የሺ ይቺ ስኒ የማን ናት? አልኳቸው:: በእጃቸው ከፍ አድርገው ስኒዋን ያዙ እና "ይቺ? ይህቺ የሀይልዬ ስኒ ናታ! " አሉኝ:: ስኒዋን እያዩ በሐሳብ ጭልጥ አሉ:: ፈገግም ይላሉ: አይናቸው እንባም ቀሯል:: ከአመታት በፊት ያረፉት ባለቤታቸው ጋሽ ሐይሌ:: ጋሽ ሐይሌ አልፈዋል: ስንያቸው ግን አለች:: በየቤታን ቡና ሲፈላ : ሁልጊዜም ተጨማሪ ስኒዎች አሉ። ከሚጠጣው ሰው ቁጥር በላይ.. ለካስ... ከእኛ ጋር የሌሉትን ለማስታወስ፣ ድንገት የሚመጣ እንግዳን በመናፈቅ.. የራቁንንም በልባችን ለማቅረብ ኖሯል::

>>> «ማን ... ማን ልበል?» ተንቀጠቀጠ። «አይ የሰው ነገር? ምነው እንዲህ ልብህ ጨከነ የኔ ልጅ? ... ለጌትዬ? ... ለጓደኛህ? ለአብሮ አደግህ? ... ምነው አንተዬ? ቢሞትም ይሄው ነበር! እርሙን በልተህ በዚያው ትጠፋ ነበር! አበስኩ ገበርኩ! ...» እያለቀሱ ሳይሆን አይቀርም። «እማምዬ ... ኧረ እንደዚህ አይደለም! ኧረ አልገባዎትም! በፍፁም በዚህ መልክ ሊያስቡ አይገባም! የኔና የጌትዬን ፍቅር ያውቁ የለም?» የሚለውን አጣ። «እኔማ ብዬ ነበር! ጌትዬ አንድ ነገር ቢሆን የሚደርስለት እሱ ነው እል ነበር። አንተ ግን ሌላ ሆንክ... ተወው ልጄ ድሮም ባዳነት ይኸው ነው! ስግነት ባይኖርህ ነው!» አሉ። እያለቀሱ ነው። «እውነቴን ነው እማምዬ! አባባ ይሙት ይሄው አንድ ወር ሆነኝ ከአዲስ አበባ ውጭ ነኝ! ለፊልድ ሥራ ወጥቼ ጋምቤላ ነኝ። ገና ትናንት ነው ጌትዬ በመኪና አደጋ እንዲህ መሆኑን የሰማሁት። አውሮፕላን ካገኘሁ ዛሬ ከሰዓት በኋላ እመጣለሁ ...» ምክንያት አላጣም። «እስቲ ይሁን ... ይሁን ... እኔ ግን እንዲህም አትመስለኝ ነበር! ... በል ተወው...» ተቀይመዋል በጣም ተከፍተዋል። «አልሰማሁ ሆኖ እንጂ ጌትዬ መታመሙን ሰምቼ ይህን ያህል ጊዜ መቆየት የምችል ሰው አይደለሁም። ... እውነት እማመይ! እንደምንም ብዬ ዛሬውኑ እደርሳለሁ ...» መፍጠን አለበት። ለምሳ ሲወጣ ሁለት ኪሎ ሙዝ አንጠልጥሎ ወደ ጓደኛው መብረር አለበት። መዘግየት የለበትም። የሚችለው ሁለት ኪሎ ሙዝ መግዛትና ፈጥኖ ወደ ታማሚ ጓደኛው መድረስ ብቻ ነው። «እሱማ ስምህን እየጠራ ሲቃዥ ነው የሰነበተው... 'ጓደኛዬ የክፉ ቀኔ' እያለ ሲለፈልፍ ይቆይና 'ናልኝ... ማር አማረኝ አልሰኝ' እያለ ይጣራል። ምኑ ቅጡ። አንተም ጠፋህ ... እሱም ማር እንዳማረው ቀረ። ለበሽተኛ የሚሆን ንፁህ ማር በማንኪያ እንኳን የሚሰጠኝ ለክፉ ቀን የሚሆን ሰው ጠፋ። ተወውማ የኔን ጉድ ... ማሩ ይቅር ባይሆን እንደማር የሚወድህ የልጅነት ጓደኛው አንተ...» ንግግራቸው ተቆራረጠ። «እውነት እማምዬ ዛሬውኑ እመጣለሁ። መርካቶ አካባቢ ማር የመሸጥ ታዋቂ ነጋዴ ሰው አውቃለሁ። እሱ ጋ እወስድዎታለሁ ... በጥሩ ዋጋ ይሸጥልዎታል።» በደሉን ለማቃለል መለፍለፍ ጀመረ። «አይ አንተ ... ደ'ሞ የዘንድሮ ማር ምኑንም ምኑንም እየጨመሩበት ተበላሽቶ የለ! ... ሙዝ እኮ ነው በማር ሚዛን ስናስለካ የኖርነው ... ጌትዬን ደግሞ ታውቀዋለህ ሙዝ አይስማማውም። የመንደር ሰው መታመሙን ሰምቶ ይዞለት የመጣው ሙዝ አንዷን ቢቀምስ ሲያስመልሰው አደረ። ቢቸግር እኮ ነው! ... ከሙዝ የተቀላቀለ የመርካቶ ማር ይስማማው ብለህ ነው?» የተጨነቀ ድምጽ። «እሱ... አዎ... ንፁህ ማር ካልሆነ... » መቀጠል አልቻለም። እሳቸው ቀጠሉ። «ይልቅ ልጄ ... ጋምቤላ ንፁህ ማር አለ ሲሉ ሰምቻለሁ። አንድ ሁለት ኪሎ አምጣለት።» ፈጥኖ መመለስ አልቻለም። «ነገርኩህ እንዳታበዛው! ሁለት ኪሎ ይበቃል ... ብቻ ማስቸገር እንዳይሆን! መቼም አንተ ነህ ብዬ ነው። ፍቅራችሁን ስለማውቅ ነው "እማምዬ" እያልህ ስትጠራኝ እኮ ራሱን አምጬ የወለድኩትን ጌትዬን ነው የምትመስለኝ። ... ንፁሁን መርጠህ ...» ስልኩ ተቋረጠ። ጓደኛው ሁለት ኪሎ የጋምቤላ ማር እንጂ ሁለት ኪሎ ሙዝ አይመጥነውም። መልስ አዳኝ እና ሌሎች አጫጭር ልብ-ወለዶች

ማር Vs ሙዝ አንተነህ ይግዛው ከሰማ ሰነባብቷል። አልሞላለት ብሎ እንጂ ወሬው ከ'ሱ ከደረሰ ቀናት ተቆጥረዋል። የልጅነት ጓደኛው በመኪና አደጋ ተጎድቶ አልጋ ላይ መዋሉን ከሰማ ሰነባብቷል። አብሮ አደግ ጓደኛው ጌትዬ መታመሙን ሰምቷል። ይወደዋል። እንደሚወደውም በተግባር አሳይቶታል። ጌትዬ ከሥራ ተፈናቅሎ አንገቱን በደፋባቸው ቀናት ከጎኑ ሆኖ አለሁልህ ብሎታል። ዛሬ ግን መውደዱን ፈጥኖ በተግባር ማሳየት አልቻለም። ይህን ማድረግ ባለመቻሉ ራሱን ጠላ። አቅጣጫዋን ስታ በጓደኛው ላይ የወጣችው ክልፍልፍ መኪና ወደ እርሱ አቅጣጫ ብትመጣ ተመኘ። ጓደኛው ከተገጨ ከሦስት ቀናት በኋላ ወሬውን ከሰው ሰማ። የእውነቱን አዘነ። ጓደኛውን ከጎዳና ላይ አፋፍሰው ወደ ሆስፒታል ከወሰዱት አዛኝ ሰዎች መካከል እሱ የለበትም። ከሥራ የተፈናቀለ፣ አደጋ ደርሶበት በደም አበላ የጨቀየ ልጃቸውን ሕይወት ለማዳን ተበዳድረው ወደ ሆስፒታል የወሰዱት እናቱ ናቸው። ማንም ሳይረዳቸው፣ ዘመድ ጓደኛ ሳያግዛቸው። ታማሚ ጓደኛውን እየተመላለሱ የጠየቁት ሌሎች ጓደኞቹና ዘመዶቹ ናቸው። እሱ ዘግይቶ ነው ሁሉንም የሰማው። ዘግይቶ እንደ መስማቱ መፍጠን ነበረበት። ግን አልቻለም። 'እወድሃለሁ' የሚለውን ጓደኛውን አርፍዶ መጠየቅ አስፈራው። በደለኛነት አባከነው። «ምን ይለኛል? እንዲህ ቆይቼ ልጠይቀው ስሄድ ምን ይሰማዋል?» እያለ ነጋ ጠባ ማሰብ ያዘ። ምን ማድረግ እንዳለበት ሲያስብ አሁንም ዘገየ። ቀኑ ሲጨምር በደሉም እየጨመረ መምጣቱ ተሰማው። «ያለኝን ይበለኝ እንጂ ከዚህ በኋላስ መዘግየት የለብኝም» ብሎ ተነሳ። ተነስቶ ግን አልሄደም። «ምን ይዤ ነው የምሄደው?» አለ። ደመወዙን አሟጦ ጨርሷል። የሚያበድረው አጥቶ ለቀናት ባዝኗል። ጌትዬ ሆስፒታል አልጋ ላይ ተንጋሎ ጣራው ላይ እሱን ጓደኛውን ሲፈልግ ይታየዋል። ሰውነቱን የሚጠግን ሁነኛ ምግብ አምሮት የድሃ እናቱን አቅም በማየት ዝል ሲል ይታየዋል። የተሰበረ አጥንት የሚጠግን ጥሩ ምግብ ይዞለት ሊሄድ አስቦ ነበር። ግን በቂ ገንዘብ የለውም። ኪሎ ሙዝ ከመግዛት የሚያልፍ ገንዘብ የለውም። ቢሆንም ግን ወደ ጓደኛው መሄድ አለበት። ያገኘውን ይዞ ከፊቱ መቆም ይገባዋል። አሳፋሪ ቢሆንም መሄድ እንዳለበት አምኗል። እንኳን የሚወደው ጓደኛውን፣ ጓደኝነታቸውን የሚያውቁትን እናቱን ዓይን ማየት ቢያሳፍረውም መሄድ አለበት። ዛሬን ሊያልፋት አልፈቀደም። ዛሬ ጠዋት ቆርጦ ነው ከቤቱ የወጣው። በምሳ ሰዓት ከቢሮ ወጥቶ ሙዝ ገዝቶ ወደ ጓደኛው ይሄዳል። ይቅርታውን ይቀበላል። ምሳ ሰዓት ላይ ወደ ታማሚ ጓደኛው ለመሄድ እያሰበ ቁርስ ሰዓት ላይ ስልኩ ጮኸ። «ምነው ልጄ? ... የአንተና የጌትዬ ነገር እንዲህ ሆኖ ቀረ? ... የናንተ ጓደኝነት መጨረሻው ይሄ ነው?» የተቆራረጠ ድምጽ። የባልቴት፣ የታማሚ ጓደኛው የጌትዬ እናት ድምጽ። .....

የቴያትር አዳናቂ ቅጥረኞች በጥንት ጊዜ ከሌሎች ደራሲያን ሁሉ ፀሐፊ ተውኔቶች የተደራሲውን (የቴያትር ተመልካቹን) ስሜት ለማነሣሣት የተለያየ መጠቀሚያ ዘዴ ነበራቸው። የተውኔት ፀሐፊውና ደጋፊዎቹ ተውኔቱን ተወዳጅና ያማረ ለማስመሰል የተውኔት አዳናቂ ቅጥረኞችን (Claque) ይከራያሉ። ይህ ዓይነቱ ዘዴ በፈረንሣይ አገር በ1820 ወይም ከዚያ በኋላ እንደተጀመረ ይገመታል። ታዲያ አንድን ቴያትር ወይም ተውኔት እጅግ በጣም ግሩም በማስመሰል እንዲወደድና ብዙ ሕዝብ እንዲመለከተው ለማድረግ የሚሠማሩት እነኝህ ቅጥር የተውኔት አዳናቂዎች የሚከተለው የሥራ ክፍፍልና ሥያሜ ነበራቸው። 1. Commssaires → ተውኔቱን አስቀድመው በቃላቸው በማጥናት በተመልካቹ ሕዝብ መሀል ጥሩውን ክፍል የሚገልፁ፤ 2. Rieurs → ተውኔቱ በመድረክ ቀርቦ በሕዝብ እየታየ ሣለ፣ በተመልካቹ መሀል ሆነው በቴያትሩ ውስጥ ለሚቀርቡ ቀልዶች፣ ሞቅ ያለ ሣቅ የሚሥቁ፤ 3. Pleureurs → አስፈላጊ በሆነ ቦታ ላይ የሚያለቅሱ ቅጥር ሴቶች፤ 4. Chatouillurs → በልዩ ልዩ ዘዴ ተመልካቹ በታሪኩ እንዲጓጓና አድናቆት እንዲሰማው የሚገፋፉ፣ በጭብጨባው አርአያ ሆነው ለአድናቆት የሚያነሳሱ፤ 5. Bleseurs → ቴያትሩ ታይቶ ሲያበቃ "ቢስ!" ወይም "ይደገም" የሚል ጥያቄ በልዩ ልዩ ድምፅ (በፉጨት፣ በቃል) እየጮሁ የሚያሰሙና ተመልካቹ ቴያትሩን ወድዶት እንዲመጣ የአድናቆት ድባብ የሚፈጥሩ ቅጥር ጀሌዎች ናቸው። ታዲያ! በዚሁ ጥበብ የተካኑት እነኝሁ ቅጥር አዳናቂ ሙያተኞች ለተከራያቸው ቴያትር ቤት ሁሉ የሚያገለግሉ ከመሆናቸውም በላይ እንደየሥራ ድርሻቸው የሚከፈላቸው የኪራይ አበልም የተለያየ ነበር። ጣዝማ - አስደናቂው የደራሲያን ሕይወት ንጉሤ አየለ እና ደጀኔ ጥላሁን

እ ሚ ታ ያ ደግ ሰው ዕድሜአቸው የጠና ባልቴትን፡ «እንደምን ዐደሩ እማማ? ጊዜ ይኼዳል ጊዜ ይመጣል፤ ወርዱና ቁመቱ አንድ አይነት ለኾነ ቀን የተለያየ ስም እየሰጠነው "ዛሬ ሰኞ ነው፣ ነገ ደሞ ሌላ ቀን" የምንለው ነገር አልገባኝም። እስኪ፣ "ዐለፈ" ከተባለውና "ይመጣል" ብለን ከምንጠብቀው እያጣቀሱ ምክር ይለግሡኝ» አላቸው። እማማም፡ «አይ አንተ! ተጎንብሶ የሚኼድ ሰው ኹሉ ጥበብ ያለው እየመሰለህ እኮ ነው ዕዳ የገባኸው። የማድባት መልኩም እኮ መጎንበስ ነው፤ እና ምርምርህ እንዳይርቅብህ። ለጨዋታችን ግን፣ እኔ እንደምታየኝ እያረፍኹ ነው የምኼደው፤ የመሮጥ መጨረሻው ቀስ ማለት ነው። ድሮ ድሮ በየመንገዱ ኹሉ አየኹ፣ ተገኘኹ ለማለት ክንብንቤን አውልቄ እቆም ነበር። አኹን ግን እንቅልፍ እንደወሰዳት ዐይን ተሸፍኜ ነው ዝም የምለው። እንግዲህ "እንቅልፍ" የምንለው ማረፍ በመሸፈን ውስጥ እንጂ በመገለጥ ውስጥ አይደለም። ደሞ ዜናው ብዙ በኾነ ዓለም ስንቱን አይተህ ታልፋለህ? እና እኔም ብዙ ጉድ ያመጣብኝ፣ ወገቤን የሰበረብኝ፣ ለመዝመሜ ምክንያት የኾነው አናቴ ላይ የተሸከምኹት እንስራ አልነበረም፤ ራሴ ላይ የተለጠፈው ብዙ የሚሰማው ጆሮ እንጂ። አኹን ይህ ጆሮ ብልኅ ሆኖ ነገርን መርጦ ቢቀበል መች እንዲህ እሳት እንደነካው ላስቲክ እጨማተር ነበር!» አሉት። ያ ደግ ሰው የእማማን የቆዳ ሽብሽብ ፍዝዝ ብሎ እየተመለከተ፣ «እውነት ግን ሰውን የሚያስረጀው ሰምቶ የሚይዘው ነገር መኾን አለበት። ሙቀት እየነደደበት ምጣድ እንደሚሰማ፣ ሰው ግሎ መቃጠሉ በጆሮው በኩል በሚቆሰቆሱት አቃጣይ ቃላት ሊኾን ይችላል» አለ። ግርባብ ያ ደግ ሰው ፍቃዱ አየልኝ

አንድሬ ማልሮ (1901 - 1976) የልቦለድ ደራሲ፣ የኪነ ጥበብ ፈላስፋ እና የማይበገር ታጋይ ነበር። በጉርምስናው ዘመን ወደ ካምቦዲያ ተጓዘ። እዚያም ለመቶዎች ዓመታት ጫካ ውጧቸው ጠፍተው የነበሩ የጥንት ቤተ መቅደሶችና ከተሞች እየተፈለጉ እየተገኙ ነበር። ማልሮ በግሉ እዚህ ፍለጋ ውስጥ ገብቶ የአርኪኦሎጂ ቁፈሮ አካሂዶ ከቤተ መቅደስ የተለያዩ ሀውልቶችና የቅርስ እቃዎችን አገኘ። በአርኪኦሎጂ ቁፋሮ የተገኘ ንብረት ሁሉ የመንግሥት ነው አለና አገሩ ገባ። አንድሬ ማልሮ ወደ ቻይና ሄደ። በ1927 የቻይና አብዮት ሲካሄድ በቅርብ አጥንቶና በድርጊት ተሳትፎ (L Condition Humaine) "የሰው ልጅ ሁኔታ" የተባለውን ታላቅ ልቦለድ ጻፈ። ፍልስፍናና ድርጊት በደራሲውም በገፀ ባህርያቱም ውስጥ ተወራራሽ ናቸው። የስፓኝ እርስ በርስ ጦርነት ተነሳ። ማልሮ ወደዚያ ዘመተ፣ ፋሺስቶችን ሊወጋ። እንደ ማልሮ አይነቶቹን ጦረኞች የአገር ድንበር አይወስናቸውም። የሪፐብሊካኑ ወገን አየር ኃይል ውስጥ አዛዥ ሆኖ ተዋጋ። በ1940 ተማረከና ታሰረ። አመለጠ። የስፓኝ ሪፐብሊካዊ ወገን ድል ሆነ። ማልሮ ወደ አገሩ ተመልሶ የነፃይቱ ፍራንስ  ጦር ኃይል ውስጥ አዛዥ ሆኖ ጦርነቱ ቀጠለ። ማልሮ ሩቅ ምስራቅን ስለሚወዳትና ስለሚያውቃት የዤኔራል ደጎል ልዩ መልእክተኛ እየሆነ ተመላልሶበታል። ከ1958 - 1968 ማልሮ በፕሬዝዳንት ደጎል መንግሥት ውስጥ የባህል ጉዳይ ሚኒስትር ሆኖ ለውቢቱ ፍራንስ ባህል ትልቅ የግንባታ አስተዋፅኦ አድርጓል። በየክፍለ ሀገሩ የባህል ተቋማትና ሙዚየሞች አስከፍቷል። (Les Voix du Silence) "የዝምታ ድምፆች" የሚል ትልቅ መጽሐፍ ውስጥ ለዘመኑ ሰዎች ስነ ጥበብ በስፋትና በጥልቀት ተንትኖላቸው ዓይናቸውን ከፍቶላቸው የልባቸውን አድርሶላቸዋል። ስብሀት ገ/እግዚአብሄር እነሆ ጀግና

photo content

እመ መከራ ኢትዮጵያ እመ መከራ የግዜር መመራመሪያው የስቃይ ቤተ-ሙከራ መውደቅማ ነበር ያባት እንደ ያሬድ እስከ ሰባት እንደ በላ ብላቴና የእንክርዳድ ሙልሙል እንጎቻ የትውልዴ እጣ ፈንታ መውደቅ፣መውደቅ፣መውደቅ ብቻ! በእውቀቱ ስዩም

የስልጣኔ መነሻ ፍርሀት እንጂ ጀግንነት አይደለም። መስጠም የማይፈራ ሰው የዋናን ጥበብ አይፈለስፍም በውቀቱ ስዩም

photo content

የላይበራሪው ጥቅስ ዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው ኮንግረስ ላይበራሪ ከግድግዳው ላይ ከተነቀሱት ጥቅሶች ውስጥ አንዱ እንዲህ ይላል፡ ‘BOOKS MUST FOLLOW SCIENES AND NOT SCIENCES B
የላይበራሪው ጥቅስ ዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው ኮንግረስ ላይበራሪ ከግድግዳው ላይ ከተነቀሱት ጥቅሶች ውስጥ አንዱ እንዲህ ይላል፡ ‘BOOKS MUST FOLLOW SCIENES AND NOT SCIENCES BOOKS’ በእንግሊዝኛ ሰዋሰው ህግ ትክክል የማይመስል ያልተለመደ ጥቅስ በመሆኑ ለተወሰኑ ደቂቃዎች ለመረዳት ግራ ተጋብቼ ቆየሁና ኮምፒተሬን ከፍቼ መልዕክቱን እንዲያስረዳኝ ጠየቁት፡፡ አባባሉ የእንግሊዛዊው ፈላስፋ ፈራንሲስ ቤከን መሆኑንና ለማለት የተፈለገው በመጻህፍት የተጻፈው እውቀትና መረጃ ሁሉ የመጨረሻ አለመሆኑን ይልቁንም በአዲስ ግኝት፣ ዕውቀት፣ መረጃ ሊዳብር ሊሻሻል የሚገባ በመሆኑ ቤተ መጻህፍት የተከማቹ መጻህፍት ሁሉ ለእርማት ክፍትና ዝግጁ መሆን አለባቸው ለማለት ነው አለና ላይበረሪው ለማስተላለፍ የፈለገው መልዕክት ‹ዕውቀት የማያቋርጥ ዕድገት ነው› የሚለውን ነው፡፡ ቀጠለና ሳይንስ ማለት በህክምና፣ በአስተዳደር፣ በህግ፣ በአመራረትና በመሳሰሉት ያለንን መረዳት የሚያካትት ነው፡፡ የተጻፈና የታተመ ሁሉ የእውቅትና የመረዳት መጨረሻና መደምደሚያ አይደለም፡፡ ሊለወጥ ሊሻሻል ሊታረም ይገባዋል ለማለት ነው ብሎ የድመድማል፡፡ እኔም እሰማማለሁ፤ የእግዚአብሔርን ቃል ከያዘው መጽሐፍ ቅዱስ በቀር! አለማየሁ እሼቴ

የላይበራሪው ጥቅስ ዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው ኮንግረስ ላይበራሪ ከግድግዳው ላይ ከተነቀሱት ጥቅሶች ውስጥ አንዱ እንዲህ ይላል፡ ‘BOOKS MUST FOLLOW SCIENES AND NOT SCIENCES BOOKS’ በእንግሊዝኛ ሰዋሰው ህግ ትክክል የማይመስል ያልተለመደ ጥቅስ በመሆኑ ለተወሰኑ ደቂቃዎች ለመረዳት ግራ ተጋብቼ ቆየሁና ኮምፒተሬን ከፍቼ መልዕክቱን እንዲያስረዳኝ ጠየቁት፡፡ አባባሉ የእንግሊዛዊው ፈላስፋ ፈራንሲስ ቤከን መሆኑንና ለማለት የተፈለገው በመጻህፍት የተጻፈው እውቀትና መረጃ ሁሉ የመጨረሻ አለመሆኑን ይልቁንም በአዲስ ግኝት፣ ዕውቀት፣ መረጃ ሊዳብር ሊሻሻል የሚገባ በመሆኑ ቤተ መጻህፍት የተከማቹ መጻህፍት ሁሉ ለእርማት ክፍትና ዝግጁ መሆን አለባቸው ለማለት ነው አለና ላይበረሪው ለማስተላለፍ የፈለገው መልዕክት ‹ዕውቀት የማያቋርጥ ዕድገት ነው› የሚለውን ነው፡፡ ቀጠለና ሳይንስ ማለት በህክምና፣ በአስተዳደር፣ በህግ፣ በአመራረትና በመሳሰሉት ያለንን መረዳት የሚያካትት ነው፡፡ የተጻፈና የታተመ ሁሉ የእውቅትና የመረዳት መጨረሻና መደምደሚያ አይደለም፡፡ ሊለወጥ ሊሻሻል ሊታረም ይገባዋል ለማለት ነው ብሎ የድመድማል፡፡ እኔም እሰማማለሁ፤ የእግዚአብሔርን ቃል ከያዘው መጽሐፍ ቅዱስ በቀር! አለማየሁ እሼቴ

ይህ በምስሉ ላይ በቆሻሻ መኪና ሲደፋ የምናየው ለማዳበሪያነት የተዘጋጀ 24 ሚሊዮን የተፈጨ ዶላር ሲሆን ፡ ከላይ የቆሻሻ ክምር መስሎ የሚታየው ደግሞ ለወራት የተከማቸ በመቶ ሚሊዮን የሚገመት ዶላር ነው ። ........... የተፈጨ ሚሊዮን ዶላሮችን እየተመገቡ የሚያድጉት የኒው ኦርሊያንስ አትክልቶች በአሜሪካን ውስጥ በየቀኑ በብዙ ሚሊየን የሚቆጠር ዶላር ከዝውውር ውጭ እንዲሆን ይደረጋል ። .... እነዚህ በእርጅና ወይም በሌሎች ምክንያቶች አገልግሎት መስጠት የሚያቆሙ ብሮች በየእለቱ እየተሰበሰቡ ፡ ከፍተኛ ቁጥጥር እና በካሜራ በሚጠበቅ ክፍል ውስጥ ቁጥራቸው እየተመዘገበ ፡ ለዚሁ ተብሎ በተዘጋጀ የወረቀት መፍጫ ማሽን ውስጥ ገብተው እንዲፈጩ ይደረግና ፡ በየአራት ቀኑ በቆሻሻ ማንሻ መኪና እየተጫኑ ይወሰዳሉ ። ............ ከጥቅም ውጭ ናቸው ብለው ገንዘቦችን በየእለቱ ከሚያስወግዱት ባንኮች መሃከልም የኒው ኦርሊያንስ ፌዴራል ባንክ አንዱ ነው ። ይህ ባንክ በደንበኞቹ አማካኝነት በሚደረጉ የገንዘብ ዝውውሮች በእጁ ከሚገቡት ገንዘቦች መሃከል ፡ በየቀኑ ስድስት ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ያስወግዳል ። በነዚህ በተለያዩ ባንኮች ከአገልግሎት ውጭ በሚደረጉት ገንዘቦች ምትክም ፡ በዩናይትድ ስቴትስ በየአመቱ 8 ቢሊዮን የሚሆን የዶላር ኖት ይታተማል ። ......... የገንዘብ ኖት ሲታተም እንደ ምንዛሪ መጠኑ የአገልግሎት ዘመኑም ይገመታል ። በዚህም መሰረት የአንድ ዶላር ኖት ሲሰራ ለ21 ወራት እንዲያገለግል ታስቦ ሲሆን ፡ የመቶ ዶላር ኖት ደግሞ እስከ ሰባት አመት በዝውውር ውስጥ እንደሚቆይ ይገመታል ። እናም እነዚህ ከጊዜ ብዛት ያረጁ ወይም በላያቸው ላይ የተጻፈባቸው የተቀደዱ ፡ የብር ኖቶች ከላይ ባልነው መሰረት በሚገባ ከተፈጩ በኋላ በከተማው ዳርቻ ወደሚገኙ የእርሻ ቦታዎች ይላካሉ ። ............. ሳይመን መናሽ ኒው ኦርሊያንስ ውስጥ በሚገኝ grow on የሚባል የግብርና ምርቶችን የሚያመርት ድርጅት መስራች ነው ። ሳይመን ስለሚያመርቱት አትክልቶች ሲናገር ፡ እኛ የምናለማው ሚሊዮን ዶላሮችን ተመግቦ ፡ በተፈጥሮ ማዳበሪያ ያደጉ አትክልቶችን ነው ። ስለሆነም ምርቶቻችን በአካባቢው ነዋሪዎች ዘንድ ይወደዳሉ ፡ ሲል በቀልድ መልክ ተናግሯል ። 75 ፐርሰንቱ ከጥጥ የሚሰራው ይህ የዶላር ኖት ፡ በሚገባ ተፈጭቶ ከአፈር ጋር ሲቀላቀል ለተክሎች የሚስማማ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ይሆናል ። ዋሲሁን ተስፋየ

photo content
+3

bewketu(1).mp35.02 KB

bewketu.mp32.74 KB

"ዓይን የሐሳብ ምንጭ ነው.." ሰላም ገብሩ ራስን ያለመግዛት: ፈተና ድሮ ድሮ : ከዝሙትጋር: ከሱስ ጋር: ከምግብ ጋር ነበር .. የዘመኑ ግን መልኩ ሌላ ነው:: በእጃችን ይዘን የምንዞረው... Something that quietly controls what we see, what we hear, what we think, what we say and even how we want to be seen and accepted. That temptation is our phone. ስልክ እጃችን ላይ ሳይኖር ከሰው ጋር ለመነጋገር እንኳ አልቻልንም : ምግብ ቀርቦ ፎቶ ካላነሳን መብላት ተስኖናል: ከቤታችን ስንወጣ : ሳናሳይ እንዴት?! ቤተመቅደስም አስገብተነዋል:: ስልካችን ላይ እንኳ መሰልጠን ያቃተን እንዴት ነው? በቀደም የኔታ: "ኸረ ተዉ ምእመናን ዓይን እኮ የሐሳብ ምንጭ ነው" ያሉት ትዝ አለኝ:: How did we get here?.... How? we should pause and ask what it has taken from us? our attention, our silence, our relationships and most importantly our communion with God. Oh Christ help us! Teach us to be present again. አለምን መናቅ የተባለ : እንግዲህ በራስ ላይ : በምኞት ልይ መሰልጠን ይኾን? እንደምን ያለ ጥበብ ነው? We used to fear being controlled by addictions. Today… many of us carry our addiction in our pocket.

"ብዙዎቻችን እንደጨርቅ ብንጠመዘዝ ከውስጣችን ተንጠባጥቦ የሚወጣው ፈረንጅና ፈረንጅ ነኬዎች በምላሳቸው፣ በድርሳኖቻቸውና በማባበያ ሙርጣቸው በአንጎላችን የዘሩት ባርነታችን ነው።” መረቅ አዳም ረታ

+1
marxism_unmasked.pdf1.09 MB

#MoE ትምህርት ሚኒስቴር የ2018 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ዙሪያ ከደቂቃዎች በኋላ መግለጫ ይሰጣል። ሙሉ መረጃውን ከታች ባለው ቻናል መከታተል ትችላላችሁ:: @Ethiopian_Dig
#MoE ትምህርት ሚኒስቴር የ2018 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ዙሪያ ከደቂቃዎች በኋላ መግለጫ ይሰጣል። ሙሉ መረጃውን ከታች ባለው ቻናል መከታተል ትችላላችሁ:: @Ethiopian_Digital_Library @Ethiopian_Digital_Library