cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ፍቅሬን በግጥም

https://t.me/joinchat/AAAAAExXHV9q9Kpd_QG1hA

Show more
The country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
Advertising posts
9 948
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

#አይኔን አይንሽ ስለሚያምር ላደንቅልሽ ስጥር የጥርስሽ ፈገግታ አይኖቼን ቢረታ አይኖችሽን ትቼ ለጥርሶችሽ ሞቼ እድንቄ ሳልጨርስ ጸጉርሽ ሲተራመስ ቢነካካው ፊቴን ወደድኩት ዞማውን ወደድኩት ጸጉርሽን ጉንበስ ስል ቀና ሚጣል አጣውና ካንቺ ውበት ዝና ይሄን ሁሉ ውበት አንቺን ያየውበት ቢገርሙኝ አይኖቼ ያንቺን ውበት ትቼ አይኔን አደነኩት ያየውን ሲወደው ዛሬ ገና አየውት*** 😉😉😉 @yefikir1 @yefikir1
Show all...
​​ : : ፡ ፡ ❤️በጣም የሚዋደዱ ባልና ሚስት ድንገት በማይታወቅ ምክንያት በማሃላቸው ባለመግባባት የተነሳ ግጭት ይፈጠራል... ባል ይናደድና ይደበድባታል፤ ሚስት በጣም ታዝንና ታለቅሳለች ባል ትቷት ወደ መኝታ ቤት ይገባና ይተኛል፤ ሚስት ትንሽ ካሰበች በኋላ ወደ መኝታ ቤት ገብታ ትተኛለች፤ ሲነጋ ባል ከተኛበት ሲነቃ በጣም ደንግጦ ስቅስቅ እያለ ማልቀስ ይጀምራል...ሚስት ጥቅልል ብላበት አቅፋው ተኝታ ነበር፤ ለቅሶውን ሰምታ ትነቃለች እንዲም ትለዋለች እንዳስለቀስከኝ አስለቀስኩ ብድሬን መለስኩ ብላ እየሳቀች ሳመችው.... እሱም በጣም ተደስቶ አቅፎ ሳማት.....እሳትን በውሃ እንጂ በእሳት አታጠፋውምና።......... GOOD NIGHT😴 GOOD NIGHT😴 GOOD NIGHT😴 https://t.me/yefikir1 @yefikir1 @yefikir1
Show all...
በናፍቆት ተይዤ ሲደክም ጉልበቴ 😔 ደሞ ይባስ ብሎ ታሰረ አንደበቴ🙁 ስብር ያለ ለታ ስሜም እንደቅስሜ😔 እፅናናለው ሳይሽ እንኳንስ ተስሜ😘 ብክንክን ስል አደብ ሲያሳጣኝ🥺 ትዝታሽ ደርሶ ከጭንቅ አወጣኝ😍 አወይ መታደል አወይ መገፋት 💏 ከሞት ያስጥላል እንኳን ከዕንቅፋት 🖤 ሀኪሜ ነሽ መዳኒቴ 🤎 @yefikir1 @yefikir1 @yefikir1 ❤️❤️❤️❤️❤️❤️
Show all...
*አልችልም* ( ፍቅሬን በግጥም ) ፡ የፅጌን ማህሌት የዳዊቱን ደግም፣ ልሰማ ማልጄ ቤተስኪያን ብሄድም፣ አምላኬን ልወድስ እልፍ ብፈልግም፣ ፡ እኔ ግን አልችልም፣ ፡ ውርጩ ምን ቢወርጭ ነጠላ አጣፍቼ፣ ከመቅደሱ ቆሜ አይኖቼን ዘግቼ፣ ላመሰግን ብዬ ቃል ካፌ አውጥቼ፣ ስምሽን እንዳልጠራ ዝም አልኩኝ ፈርቼ፣ ፡ ፀሎቱ እንዲሰምር አሜን ሲል ምዕመን፣ በጉልበቱ ሲወድቅ ሲሰብር አንገቱን፣ በቃሉ ሲቀጣው ደንዳውን ልቡን፣ በምክር ሲጎሽም የምድር ስጋውን፣ ፡ እኔ ግን አልችልም፣ ካንቺ ሌላ እንዳስብ ሺ ምክንያት ባገኝም፣ አንቺን አለማሰብ ሀሳብ አይመስለኝም፣ ፡ ፈጣሪ ይመስገን ሲሉ መሪ ጌታ፣ ለኛ ይመስለኛል የህዝቡ ዕልልታ፣ በአንድ ልንኖር የተጋባን ለታ፣ ፡ አይ እኔ ምስኪኑ፣ ካንቺ ጋር ሆነና ልቤ ቃልኪዳኑ፣ በስምሽ ተሳስሮ ድምፄ ወ ልሳኑ፣ ከቤተስኪያን ቆሟል ስጋዬ በድኑ፣ ፡ ከአትሮኖሱ ቆሞ ቀሲሱን ባየውም፣ አይኔን ለአፍታ እንኳ ዳሩ ባልከድነውም፣ እውነት አልሻለሁ ምንም አላየሁም፣ ፡ እኔ ግን አልችልም፣ ፡ የቃሉን መገኛ ከያዝኩት ደብተሬ ላሰፍረው ፈልጌ፣ ስምሽን እፅፋለሁ ከመስመሩ ግርጌ፣ ፡ አሁን ምን ይለኛል የሰማና ያየ፣ የኔ አንቺን ማፍቀር ከፍቅር ተለየ፣ ፡ እኔ ግን አልችልም፣ ካንቺ ሌላ እንዳስብ ሺ ምክንያት ባገኝም፣ አንቺን አለማሰብ ሀሳብ አይመስለኝም፣ ፡ ፡ አልችልም፡፡ እውይ ፍቅር @yefikir1 @yefikir1 @yefikir1 ❤️❤️❤️❤️❤️❤️
Show all...
poetries Matiyas berza ፈዋሹ ቁስለኛ ሐምራዊ ደመና ለበሰ ሰማዩ ቁልቁል ሲተረተር የግርዶሽ ኪዳኑ፤ ወደ ላይ ሲወጣ የሥቃይ ተማጽኖ የደሙ እንፋሎት ጠፈር ላይ ደምኖ ከብርሃን ዕልፍኝ አልፎ እስኪገባ ጸባኦት እስኪደርስ ከራስ ቅሉ ካባ እሪታ ጩኸቱ ቅናቱ ብርታቱ እስኪቆም ትንፋሹ ወጣ ገሠገሠ አካሉ ካለበት ሰማየ ሰማያት አልፎ እየጣሰ፤ ማን ካህን ይቆማል በጌቴሴማኒ ምን ትርጉም ሊያመጣ የኃያላን ወኔ ማን ቀምሶ ይኖራል ከጽዋው ጠብታ ትንፋሽ ትነሣለች ከሰውነት ገብታ። እሱማ እሱ ግን ይሄን ሁሉ ችሎ ዕርጉም እስከሚባል ዕርግማን ላይ ሆኖ ያሰማል ሰቆቃ ከሰው ዝቅ ብሎ። ___ ማርከን ዜማ @Markengeta@markenzema_bot ◁ ▷ @markenzema_bot ◁ ✟መልካም ፋሲካ✟ △Join Us△
Show all...
💚192
👍238
​​​​​​🚶የድሀ ልጅ ፍቅር 🧡 🌹ክፍል ስድስት 🌹 🌼በእውነተኛ የህይወት ታሪክ ላይ የተመሰረተ🌼 እኔና ሜላት በስልክ ስናወራ ቆይተን ነገ ቤተስብን አስፈቅደሽ እናጠናለን ብያት ስልኩ ተዘጋ። ስልኩን እንደዘጋሁት ሌላ ስልክ ተደወለልኝ የማላውቀው ስልክ ነበር ዝም አልኩት። ደግሞ ተደወለልኝ ግራ ገባኝ ከሜላት ውጪ ይሄንን ስልክ ማንም አያውቀውም... በሶስተኛው አነሳሁት በር ላይ ነኝ ውጣ የሚል ጎርናና ድምፅ.. ማን ልበል ስለው ውጣ! ብሎኝ ስልኩን ዘጋው። ደነገጥሁ! ለእናቴ ሳልነግር መጣሁ ብዬ ወደ ውጪ ወጣሁ አንድ ግብዳ ሰውዬ በር ላይ ቆሞ አገኘሁት። አቤት ማን ልበል? አልኩት.. ና! አለኝ ቆጣ ብሎ ተጠጋሁት ስልክህን! አለኝ.. አልሰጥም አልኩት ! አምጣ !! ብሎ ጮኸ ሰጠሁት 'ስማ ከዚህ በኃላ ከሜላት ጋ እንዳላይህ ካየሁህ ግን ከምድርገፀ ነው የማጠፋህ' አለኝ። ወዲያው ከፊት ለፊት የመኪና መብራት በረጅሙ በራ ወደኛ ተጠጋ። የመኪናው መብራት አይኔን እየወጋኝም ቢሆን የግዴን አየሁት... የሜላት ወንድም ነበር መኪናው ውስጥ የነበረው። አጠገቤ የነበረውም ግብዳ አስፈሪ ሰውዬ ካስጠነቀቀኝ በኃላ መኪናው ውስጥ ገብተው ሄዱ። ሜላት የሰጠችኝ ስልክ አዲስ ሴም ነበር ግን ከስልኳ ውስጥ ነበር ስልክ ቁጥሩን የወሰዱት በስልክ እንደምንገናኝና ትምህርት ቤትም አብረን እንደምንውል፣ ቤተክርስትያን እንደምንገናኝም፣ በደንብ ያውቃሉ። ምክንያቱም በቅርብ እርቀት ይከታታሉን ስለነበር። በጣም አዘንኩ ትንሽ በር ላይ ከቆምኩ በኃላ ወደ ቤት ገባሁ ለእናቴ ሁሉንም ነገር ነገርኳት። በቃ ይቺ አመት እስክትጠናቀቅ ድረስ አብራችሁ አትሁኑ አለችኝ ግን እንዴት አድርጌ... አንድ ቀን ጠዋት ተነስቼ ቤተክርስቲያን ደርሼ ስመጣ የስራ ማስታወቂያ ለማንበብ ጠጋ ብዬ ቆምኩ ድንገት አይኔ ተወርውሮ አንድ ስራ ላይ አረፈ እነ ሜላት ሰፈር ካሴት(cd)ፊልም ማከራየት የወር ደሞዝ 150 ብር ይላል ደስ አለኝ ወዲያው ሄጄ ተነጋገርኩ ስራ ስላልነበረኝ እዛ ተቀጠርኩ። ስልክ ቤት ሄጄ ለሜላት ነገርኳት ደስ አላት ፊልም ለመክራየት እየመጣች እንደምንገናኝ ተነጋገርን። እቤት ሄጄ ለእናቴ ሁሉንም ነገርኳት ግን ክፍያው በቂ አይደለም ጫማ ብጠርግ በቀን ከ150 ብር በላይ አገኛለው ብቻ ትንሽ ጊዜ ልየው ብዬ አሰብኩኝ። እናቴ ደስ ያለህን አድርግ አለችኝ። ስራ ጀመርኩ.. ከሜላትም ጋ መገናኝት ጀመርን ስናፍቃት መጥታ አይታኝ በአይን አውርተን እንለያያለን። እኔም ከቀጠረኝ ሰዉዬጋ ተነጋግሬ በር ላይ ጫማ መጥረግ ጀመርኩ። ታናሽ ወንድሜ ፊልም ማከራየት ጀመረ። እንደምንም ብለን ሁለት ወር ክረምት እየተገፋ ነው እኔም የአቅሜን እየሰራሁ ጫማ እየጠረግሁ ጎን ለጎን የሞባይል ካርድ ማስቲካ ሌሎች ትናንሽ ነገሮችን እየሸጥሁ ነው። እናቴ የሰው ቤት እንጅራ መጋገርና ልብስ ማጠብ ትታ ሆቴል አንሶላ ማጠብና አልጋ ማስተካከል ትሰራለች። ባለቻት ሰአት ደግሞ ሽንኩርት ቃሪያ ድንች ትቸረችራለች ተመስገን አሁን ነገሮች እየተስተካከሉ ነው። ሁለት ወር ክረምት አለፈ የኢንትራንስ ውጤት ሊመጣ ነው ውጤቱ ምን እንደሚሆን አይታወቅም ብቻ አሪፍ ውጤት አምጥቼ እንደማልፍ እርግጠኛ ነኝ ከፈጣሪ ጋር !. ሜላቴም እንድታልፍ ፀሎቴ ነው! ብቻ መድረሱ አይቀር የኢንትራንስ ፈተና መጣ ሲባል እኔም ሜላትም ተያይዘን ውጤት ለመቀበል ሄድን። ውጤትም ተቀበልን ግን ............... ✍🏼ይቀጥላል........... ▬▬▬🌺🌺🌺🌺🌺🌺ክፍል7 ከ100👍 like በኋላ ይቀጥላል በቶሎ እንዲቀጥል like እና share አድርጉልን እናመሠግናለን🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺▬▬ @yefikir1 @yefikir1 :¨·.·¨: ❀ ·. ┈┈••◉❖◉●••┈ይ 🀄️ላ🀄️ሉ
Show all...
💚107
👍218
የደም ሙሽራ ገጣሚ ማቲያስ በርዛ ዓለም ነበር የተሳለችው ከክርስቶስ ጀርባ በጅራፍ ብዕር አብም ቢሆን ዓለምን ያየው በልጁ ነው በእጆቹ ቀዳዳ በጣር ጩኸቱ ጭንቅ በደሙ ፍልቅልቅ፤ የመስቀል ዘንግ ተገልድሞ በትከሻው ጻዕር አልተለየው እስከ ነብሱ ትግል እስከ መጨረሻው አንተን የወለደች ማሕጸን ብለው እንዳልመረቁ ሸላቾች ዶትለው የስላቅ ሳቅ ሳቁ ለራሱ የሾህ አክሊል ተጎነጎነ ሰው በዘይት ሲወዛ እሱ በደም ሸገነ ዙፋን ክብሩ የሆነ የመላዕክት ዜማ ጌጡ አካሉ ለግቦ ቁስሎቹ በዘገር ሲፈርጡ የሕይወት ቃል የወጣበት አንደበቱ ለጣር ሲከፈቱ ደዌያንን የፈወሱ እጆች ዓይንን የፈጠሩ በደረቀ እንጨት ለሥቃይ ሲወጠሩ የለበቁ ሽራብ ሥጋውን ይዞ ሢነሳ ዐጥንቱ እስኪገለጥ ቁርበቱ ሲሳሳ አንቺ ዓለም አንቺ ዓለም ያኔ ባንቺ ሲዞር ያልሰጠሽው ቦታ ዛሬ ፈቀድሽለት ያን ዲብ ጎልጎታ። በገፍ የተከተለው ሆሳዕና ብሎ በጀማ የመጣው አገር አጠቃሎ ይሰቀል ይሰቀል ምንም ባላረገ ሕሙማንን በታደገ። ፀሐይ ምን ይዋጣት በቀትር ጨለመች ፊቱ አልቆመችም ከዕርቃኑ ሸሸች የጨለማ በርኖስ ሥጋውን ሸፈነ ጻዕር ሲፈራረቅ ድምጹ ታፈነ ማቀቀ ደቀቀ ላመ እስከ ነብሱ ስቅታ ታመመ ዓይኑ ፍቅርን አለቀሱ ጣሩ ተማጸነ ለጉዳቱ ትቶ ላመፃችን ለመነ የሱ መስቀል ይለያል በደም ተጨማልቋል። አንተ የክርስቶስ አባት በኤሎሄ የተጠራህ በዕንባው ሰዓት የቀረህ ወዴት ነው ወዴት ሄደህ? ምድርን በውኃ ሰዶምን በእሳት ቁጣህ አይደለም ወይ ያኔ የገረሰሳት? ታዲያ አንድያህ ታናሽ የሌለው የሰው ልጆች ክፋት ለሞት ሲያቀዋልለው. sʜᴀʀᴇ◈sʜᴀʀᴇ◈sʜᴀʀᴇ ማርከን ዜማ @Markengeta@markenzema_bot ◁ ▷ @markenzema_bot ◁ ✟መልካም ፋሲካ✟ △Join Us△
Show all...
💚59
👍63
👍 1.1K
አዳዲስ የፕሮቴስታንት መዝሙሮች ለማግኘት ከታች ያለውን የቴሌግራም ቻናል ይቀላቀላሉ https://t.me/joinchat/S2wsmZMSQp3vcGxp https://t.me/joinchat/S2wsmZMSQp3vcGxp
Show all...
☞♥✔★ #Elehun_Film's ቁምነገር እና ሳቅን ያዘለሉ ልብን የሚያፅናኑ ቁምነገር ያላቸው አዝናኝና አስተማሪ #አጫጭር_ፊልሞችን #በቅርብ_ቀን #Coming_Soon ቻናሉን በመቀላቀል ይመዝገቡ👇 https://t.me/joinchat/9xJjv1by4EI2ZTFk https://t.me/joinchat/9xJjv1by4EI2ZTFk
Show all...