ፈለገ ጥበባት +++
Open in Telegram
+++የቀደምት ኢትዮጵያውያን ስልጣኔን ማሳየት እንዲሁም ገዳማት እና አድባራትን ማሳወቅ፡፡+++ የተረሱ አድባራትና ገዳማትን ማስታወስ ፤የ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያንን ጥበብ እውቀትን በምንችለው ሁሉ መመርመር የአባቶቻችን ልጆች በመሆን ትላንት በዛሬ እና በነገ ውስጥ ማስቀጠል ማስቻል ነው።
Show more7 163
Subscribers
-524 hours
-267 days
-7330 days
Posts Archive
7 163
ከታቦር ቀጥሎ ሳይንትን ጨርሶ ወደ ቦረና መግቢያ ላይ ሊባኖስ፣ ደማስቆ፣ አርሞንኤም፣ ደብር ፋራን፣ በስተ ሰሜን በኩል ኮሬብ &ቃዴስ ደብረ ፍጌህ& ቂሣርያ& ቢታኒያ& ጋዛ & ጎልጎታ& ፌልስጥኤም ወዘተ ተብለው ተሰይመዋል፡፡ ይኸውም መታሰቢያነቱ ለ12 ነገደ እስራኤል እንደሆነ ይነገራል፡፡ ተድባበ ማርያም ከአክሱም ቀጥላ ሁለተኛዋ መናብርተ ጽዩን ናት፡፡ በሥርዓቱም መስረት የአክሱም ጽዮን አስተዳደሪ ንቡር ዕድ የተደባበ ማርያም አሰተዳደሪ ፓትርያርክ የመርጡለ ማርያም አስተዳደሪ ርዕስ ርዑሳን የጣና ቂርቆስ አስተዳደሪ ሊቀ ካህናት በመባል ይጠራሉ፡፡ ከቀዳሚዊ ምኒልክ ጀምሮ በየዘመኑም ለሚነግሱት ነገስታት ቅብዐ መንግስቱን በመቀባት ሁሉም የየራሳቸው ድርሻ ሲኖራቸው 1ኛ የአክሱም ንቡረ ዕድ ከቀዳሚ ምኒልክ ጀምሮ በተያያዘው መሠረት ማንኛውም ንጉስ ሲነግስ ከስራት ንግስ በኋላ ዘውዱን በክብር ከራሱ ላይ ያቀዳጃል፡፡ በዚህም ሃይልና ጸጋ ይቀዳጃል
#2ኛ የተድባበ ማርያም ፓትርያርክ በትረ መንግስቱን ህለተ ወርቁን ጠላትህን በእጅህ ጭብጥ በእግርህ እርግጥ አድርገህ ግዛ ብሎ በቀኝ እጅ ያሲይዘዋል፡፡ በዚህ እውነተኛ ፍርድ ፍረደበት የእዚአብሔርን ህግ ጠብቅነት የተበላሸውን አድስበት የታደሰውን አጽናበት አመፀኞችን ቅጣበት ፍቃዶኞችን ሹምበት በዚህ ሁሉ አምላካችንን አገልግልበት ብሎ ይሾመዋል፡፡
በዚህም ጸጋ መንፈስ ቅዱስ ሃይል ይሆነዋል
#3ኛ የመርጡለማርያም ርዕስ ርዑሳን ልብስ መንግስቱን ያለብሰዋል፡፡
#4ኛ የጣና ቂርቆስ ሊቀ ካህናት ቅብዐ መንግስቱን ይቀባዋል፡፡ ይህ ሁሉ ስርዓት የሚደርሰው 40 ቀን ለስርዓተ ንግስ የተወሰነው ከብሉይና ከሐዲስ ኪዳን የተውጣጣው ፀሎትና መሥዋዕት ካረገ በኋላ ነው፡፡
ታላቁ እውነት እዚህ ላይ ነው ኢትዮጵያ ከ እስራኤል ተላልፎ የተሰጣትን ክብረ እና በረከት ከ 1966 በኋላ በአብዮታዊ ዲሞክራሲ በሚል የፖለቲካ ሂደት ከስርአቷ የወጣ መንገድ ጀመረች ።
ከዚያም ጊዜ ወዲህ ኢትዮጵያ በታሪኳ ገጥሞት የማያወቀውን ወረደት እያስተናገደች ነው።
ጽዮን ከ እስራኤል ስትወጣ እስራኤላውያን እስራኤልን አጧት ግፍ መከራ ሞት ስቃዮ መሰደድ ሆነ እጣፈንታቸው ኢትዮጵያም የጥንት የእስራኤላወያኑ እጣ ፈንታ ደርሷታል።
ታድያ ብዙሃኑ አስራኤልን ሙሴ እንደታደገው ሁሉ ኢትዮጵያን የሚታደጋት ንጉስ ይመጣል እየተባለ በእጂጉ ይነገራል የሚመጣጣበት ጊዜ ሁሉ ተወስኖ የሚነገር ትንቢት ሰምተናል።
ይህ ነገረ ትንቢት ለህዝብ ይፋ የወጣበት የራሱ የሆነ በርካታ ምክንያቶች ቢኖሩም ላልተገባ አላማ በ ቤተክርስቲያኒቱ ስም ሲነገር እንሰማለን ።
በእርግት ከሰባ ነገስት የዘር ሃረጉ የሚመዘዝ ንጉስ በኢትዮጵያ እንደሚነግስ ቢነገርም ሰወች ራሳቸው በተረዱት መልኩ ሃሳቦን ሲጠመዝዙ ይታያል። በመሰረታዊነት ስለ ንጉሱ የሚናገው ታላቅ የትንቢት መጻህፍ ጣና ቂርቆስ ያለ ቢሆንም ይህ የሚሆነው የኢትዮጵያ ሰወች ከተመለሱ ንስሃ ከገቡ ታላቁ ንጉስ እንደሚነግስ ይናገራል ሌላው ጊዜው በዚህ የሚል ግን የለውም ..ካልተመለሱስ ነው ጥያቄው ?
ይህ ታላቅ መጻህፍ የኢትዮጵያ ሃይማኖት የአለም ሃይማኖት ሁሉ እንደሚሆን ይናገራል እንጂ ብዙሀኑ እንደሚሉት በጊዜና በቦታ የተገደበ እንዳልሆነ መረዳት ያስፈልጋል።
በእነዚህ አራት መናብርተ ጽዮን ያልነገሰ ንጉስ ጠላት አጥፍቶ፣ አገር አስፍቶ &በሀይማኖት ፀንቶ ሊኖር አይችልም፡፡ እነዚህ በአሉበት ከነገሰ ግን ሀገር ለመጠበቅ ሁሉን ነገር ለማድረግ ይቻለዋል፡፡ ይህውም ከቀዳማዊ ምኒልክ ሲያያዝ መጥቶ እስከ ግርማዊ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ድረስ በነዚህ 4 መናብርተ ጽዮን ግርማዊነታቸው ነግሰው 43 ዘመን በክብረ እና በሞገስ ገዝተዋል፡፡ ግርማዊነታቸው ሲነግሱ የነበሩት የእርስ አድባራት ወገዳማት አሰተዳደሪ ለግርማዊ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ሰይፈ መንግስትና ህለተ ወርቅ ያስጨበጡና ያስታጠቁ ፓትርያርክ አፈወርቅ ይባሉ ነበር፡፡ ከላይ በርእሱ ለመግለጽ እንደተሞከረው ዘመን ኦሪት አለፈና በክርስቶስ ልደት ዘመን ሐዲስ እንደተተካ በ337 ዓ.ም በቅዱሳን ነገስታት አብረሃ አጽበሃ ዘመን በ ጥያቄ ጭምር ተድባበ ጽዮን የሚለው የምሳሌ ስም አልፎ በአማናዊነት ድንግል ስም ተድባበ ማርያም ተባለች፡፡ ነገስታቱ አብርሃ አጽብሃም የኦሪታዊት ተድባበ ማርያምን ክብር ከፍ በማድርግ ለስርዓተ ቁርባንና ለሐዲስ ኪዳን ለተዋህዶ ሐይማኖት መሰረት ትሆናቸው ዘንድ 318 መዘመራን ካህናትና ዲያቆናት ከካህናተ ኦሪቱ ጋር ያለውን ሐዲስ ኪዳን የሚያስተምሩ መምህራን ተክለው ከቀዳሚው ምኒልክ ዘመን በሚልጥ ክብር አክብራው እንበረምን ህዝበ ቀደስ አሰኝተው በፍሬምናጦስ አባ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን ሥልጣን አጽንተው የተደባበ ማርያም ክብር እስከ አሁን ድረስ የቆየውን ማዕረግ የመሰረቱ እነሱ ናቸው፡፡ በአብረሃ ወአጽብሃ ዘመን መንግስት የነበረው ፓትርያርክ መርሐ ጽዮን ይባል ነበር፡፡
ታዲያ እኒህ ቀደምት የኢትዮጵያ ጥንታዊ ገዳማት ለ ሶስት ሺ አመታት ነገስታቱ ሲነግሱ ቅብዕ መንግስት የሚያገኙበት ታላቅ ሚስጥር የሚገለጥበት ቦታ ነው ። እኒህ ገናና ቦታወች ወደ ፊት በታላቅ ክብር የሚገለጡበት የራሳቸው መንገድ ይኖራል ነገስታቱ መኳንቱ ሹማምንቱ በእኒህ የኢትዮጵያ የሚስጥር ቦታወች በመገኘት መንግስቱ እንዲጸና እግዘብሔርን የሚለምኑበት ታላቅ ገዳም ነው።
#ቅርሳቅርስ በተድበማርያም
የበግ ምስልና የተቁለመለመ የበግ ቀንድ ያለበት መስቀል በዚያ ይገኛል፡፡ የዚህ መስቀል ብርሀን የሚያስገርምና ዓይንን የሚያንፀባርቅ ሲሆን ከምን አይነት ማእድን እንደተሰራ አይታወቅም፡፡ ከጥንታዊያን ነገስታትም መካከል ዐፄ ካሌብ ወደ ደቡብ አረቢያ የናግራንን ክርስቲያኖች ለመርዳት ሲዘምቱ ፓትርያርክ ዘሙሴ እሱም የኦየሩሳሌምን ገዳም ያቀናና በመጨረሻም በአባ ጴንጠሌዎን ገዳም ገብቶ ያረፈ አባት ጋር ዘምተው ድል አድርገው ሲመለሱ ይዘው የሄዱትን ጋሻ በስዕለት ለተድባባ ማርያም አስገብተውት በቦታው ይገኛል፡፡ እንዲሁም የእብራይጥ ሲኖዶስና የአረማይክ ቅዳሴ እግዚእ በቦታው ላይ ይገኛል፡፡
#1ኛ ብራና መጻህፍት በዚህ ገዳም ከ1000 ያላነሱ የብራና ጥንታዊያን መጸህፍት ይገኛሉ እነዚህም መጻህፍት ክፊሎቹ በጥንታዊት የአክሱም ዘመን መንግስት የተጻፈ ሲሆኑ ሌሎቹ ደግም በመካከለኛ ዘመን የተጻፉ ናቸው፡፡
#2ኛ በአረማክ ቋንቋ የተጻፉ የስሌዳ መጻህፍት በአረበኛና በግእዝ የተጻፉ መጻህፍት ወንጌል ዘወርቅ እየተባለ የሚጠራ ትልቅ የወርቅ ጉብ፦ጉብታ ያለበት የወንጌል መጽሀፍ ቅድስ &ሉቃስ እንዳሳላት የሚነገርላት የቅድስት ድንግል ማርያም ስዕለ አድህኖ ባለ 3 ተከፍች የገበታ ስእልና ጥንታዊና ስነ ጥበባዊ ቅርሶች ይገኛሉ፡፡ መስቀል በተድባበ ማርያም በርካታ ጥንታዊ የእጅና የመጾር መስቀል ይገኛሉ ከእነዚህም መካከል የመጀመሪያው የኢትዮጵያዊ ጳጳስ የቀደሰበት የእጅ መስቀል የመጥመቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ መስቀል የዕጨጊ ዮሐንስ በትረ ሆሳዕና እና የእጅ መስቀል የአቡነ አኖሪዎስ የእጅ መስቀል የአቡነ ቄርሎስ የእጅ መስቀልና ሌሎች ከወርቅ የተሰሩ ጥንታውያን መስቀሎች ናቸው፡፡ ስእርተ ሀና የድንግል ማርያም እናት የቅድስት ሀና ጸጉር በገዳሙ ይገኛል ይህ ጸጉር የተቀመጠበት የሽክላ ገንቦ እጅግ ጥንታዊና በስነ ጥበባዊ ይዘቱ የሚያስገርም ትእይነት ይፈጥራል፡፡ አጽመ ቅዱሳን ከአጽም ቅዱሳን መካከል ሄሮድስ የጨፈጨፋቸው ህጻናት ዓጽም በክፊል እንዲሁም የቅዱስ ጊዩርጊስ አወራ ጣት በአጠቃላይ የ28 ሰማእታት ዓጽም የሚገኝ ሲሆን
7 163
ከቀዳማዊ ምኒልክ እስከ አፄ ኃይለ ሥላሴ ድረስ በቅብዓ ነገሥት ከብረው ለነገሡ ደጋግ ነገሥታት ኃይለ
እግዚአብሔርን የሚያገኙባቸው በርካታ የአሸናፊነት ሚስጥር የንጉስነት ክብር የሚገለጥበት ጥንታዊያን ቅዱሳት መካናት ከሆኑት ከ፬ቱ ጥንታዊያን መናብርተ ጽዮን መካከል አንዷ ናት።
አገር እንደ አገር ለመቀጠል በእወቀት በእምነትና በአመክንዩ የተዋጀ ማህበረሰብ መፈጠር ተቀዳሚ ሚና ነው።
እውነትን ፍለጋ ከያለንበት ተሰባስብን የተዳፈነን ታሪክ ከተዳፈነበት የተሰወረን እውነት ከተሰወረበት ልንገልጥ ተነስተናል .... ኢትዩጵያ እውነተኛ ማንነቱ ወደ ተዋቀረበት ስፍራ እንጓዝ ዘንድ አብራችሁ ተከተሉኝ።
ከደብረ ሮሀ ላሊበላ ተነስተን ግማደ መስቀሉ ካረፈባት ግሸን ማርያም ብንጓዝ ወረሂመኖን ተሳልመህ አምሐራ ሳይቷ ተድባበ ማርያምን ይዘን በቦረናና ወግዴ ርዕሰ አድባራትን ቃኝተን ከለላ ጥንታዊውን ጋስጫ ጊዮርጊስን ጎብኝተን ወረኢሉና ጃማን አብያተ ክርስቲያናትን አይተን እስከ የጁ ብንጓዝ ወሎ የተገነጣጠለ ሳይሆን እንደ ሰንሰለት የተያያዘ የተጋመደ ከኢትዮጵያ መዝገበ ሚስጥር ቦታወች ዋናው ያልተነገረ የሚስጥርና ታርክ ባለቤት ነው!
ከደሴ 228 ኪ.ሜ ከወረዳዉ ሳይንት ከተማ አጅባር በስተሰሜን ምስራቅ 25 ኪ/ሜ ርቀት ላይ በ11° 06′ 87″ ከምድር ወገብ ሰሜንና 30° 45′ 20″ ምስራቅ ጅ.ፒ. ኤስ ከባህር ጠለል ወለል
በላይ 8,458 ጫማ ላይ እገኛለሁ...፡፡
ለአለማቀፍ የታሪክ ምሁራን የምርምር አይነ የእውነት መንገድ ጠቋሚ የ ኢትዮጵያ እጣ ፈንታ የተወሰነባት አምሳለ ገነት ድንቅ ምድር ።
ታሪክ ሃይማኖት ስርአት ትውፊት አምልኮ ለኢትዮጵውያን የለገሰች ኦሪትን ተቀብላ ለ ሐዲስ ያስተላለፈች የኢትዮጵያ ቀደምት አውደ ምህረት ።
ደብሯ ዙሪያዋ ገደል ሆና በግራና ቀኝ በጉንዳና ገዳማይ ጅረቶች እንዲሁም በሽሎ ወንዝ ታጅባ የምትገኝ ዉብ የታሪክ አምባ ነች፡፡ አምባዉ ለመዉጣት 12 በሮች አሉት፡፡ ፊትበር፣ ቦካ፣ ገተም፣ ሞገራ ግራኝ፣ ታሪኳ፣ የዘንጌ፣ አሳስት፣ አጎና፣ አምጣ ፈረሴን፣ አህያ መደብለያ እና ጌለት በሮች መግባት ይቻላል
#ተድባበ_ማርያም_ቤተክርስቲያን
የጥንታዊት ርዕሰ አድባራት ወገዳማት ተድባበ ማርያም ፡፡
በኢትጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በደቡብ ወሎ ሀገረ ስብከት በአማሐራ ሳይንት ወረዳ የምትገኘው ጥንታዊት ርእሰ አድባራት ወገዳማት ተደባበ ማርያም የተመሰረተችው በዘመነ ብሎይ በፈቃደ እግዚአብሔር በቃዳማዊ ምኒልክ ዘመነ መንግስት 982 ዓመተ ዓለም ተመስርታለች፡፡ በመፅሐፈ ሱባኤ ዘአማኑኤል ካልእ ገጽ 2)6 ላይ እንደተጻፈው ሌዋዊያን ካህናት ከእስራኤል በአዛሪያስ መሪነት የጁን አልፈው ከዛሪዋ አማሐራ ሳይንት ደረሱ፡፡ 12 በር ባለው ተራራ ላይ ለእግዚብሔር ቤተ መቅደስ ከሰሩ በኋላ ግማሾቹ ደብር ደባብ እንበላት አሉ አዛርያስ እና የዳዊት የወንድም ልጆች ሳቤቅ ይህቺማ የኢየሩሳሌም የዳዊት መታሰቢያ ከተማ ትሆን ዘንድ ተድባበ ጽዮን እንበላት ብለው እንደሰየሟት ይነገራል፡፡ በዘመነ ሐዲስ ክርስትና ሲስፋፋ አማሮች ተድባበ ጽዮን የሚለውን ስያሚ እንዲቀይሩ የአክሱም ነገስታት አሰገደዷቸው ነገስታቱም አብረሃ ወአጽበሃ ተድባብ ጽዮንን ተድባበ ማርያም ብለው ሰየሙ፡፡ ትርጓሜውም ለእግዚአብሔር የተመረጠ ከፍተኛ ቦታ ማለት ነው፡፡
ርዕስ አድባራት ወገዳማት ተድባበ ማርያም በብሉይ ኪዳን ስለመመስረቷ ምስክር የሚሆኑ አንዳንድ የኦሪት ሥረዓቶች ሲከናወኑ ይስተዋላሉ ታቦታቱ በበሚነግሱበት ወቅት በምስራቅ ያሉ ምዕመናን ነዋያተ ቅዱሳቱን ይዘው በምዕራብ ካህናት ተሰልፈው በሰሜን ያሉ ምዕመናን መጋረጃን ይዘው በደቡብ ያሉ ምዕመናን ጎራዴውንና ካሰማውን ይዘው መንቀሳቀሳቸው በኦሪት ዚሁልቁ ፪፣፫-፬ ያለውን የኦሪት ሥርዓት ያመለክታል በሐዲስ ኪዳንም ቢሆን ክርስትና በ34 ዓ.ም በኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ከተሰበከ በኋላ እና ሚስጢራተ ቤተክርስቲያን የጌታችን የመዳሐኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት ማክበር ጥምቀትንና መሰዋዕተ ወንጌል መፈፀም የጀመሩት ወንድምማማቾቹ ደጋግ ነገስታት አብረሃ ወአጽብሃ በ330 ዓ.ም አካባቢ ነው፡፡ በዚህም ተድባበ ማርያም እነዚህን የሐዲስ ኪዳን ሥርዓቶች በመፈፀም ቀዳሚዋ ናት፡፡ በብሉይ ዘመን መስዋዕተ ኦሪት ከተሰዋባቸው መካከል አክሱም ጽዮን& ተድባበ ጽዮን የዛሬዋ ተድባበ ማርያም& መርጡለ ማርያም &ጣና ቂርቆስ ይጠቀሳሉ፡፡ ቀዳማዊ ምኒሊክ ከአባቱ ከንጉሡ ከሰሎሞን መንግስት ተቀብሎ ከኢየሩሳሌም ወደ ኢትዮጵያ ሲመጣ 4 መናብርት ጽዮን ይዞ መጥቶ ነበር፡፡
1. የአክሱም ጽዮን ንቡረ ዕድ
2. የተድባበ ማርያም ፓትርያርክ
3. የመርጡለ ማርያም ርዕሰ ርዑሳን
4. የጣና ቂርቆስ ሊቀ ካህናት ናቸው፡፡
3ስቱ በእመቤታችን ምሳሌ በጽዮን ስም አራተኛው የሊቀ ካህናቱ ታቦት ቅዱስ ሚካኤል ነው፡፡
ታድያ ታላቁ ሚስጥር ያለው እዚህ ላይ ነው በእግዚአብሔር ፈቃድ ጽዩን ከ እስራኤል ስትወጣ ሌዋውያኑ ጭምር ከአስራሁለቱ ነገደ እስራኤል ከ ያይቆብ ዘር የወጣው በእመቤታችን በኩል የክርስቶስ የዘሩ ሃረግ ከሆነው የዳዊት ልጂ ሰሎሞን የሰሎሞን ልጂ ሚኒሊክ ጸጋ ነገስትን ወርሶ ከ አምስቱ ሚስጥራዊ ውርሶች ጋር ወደ ኢትዮጵያ መጣ።
ጽዩን ከመንበሯ ተነስታለችና ያኔ ጸጋ ከ እስራኤል ለቀቀ ህዝቡም በአለም ተበታተኑ በአህዛብም ግዞትም ወደቁ ።
ያኔ ንግስናው ወደ ኢትዮጵያ ዞር ስርአተ አምልኮም የኦሪት የክህነት አገልግሎቱም የሌዋውያን የንግስና ስርአቱም የነገደ እስራኤልን ሆነ ።
ቀዳማዊ ምኒልክን ተከትለው ወደ ኢትዮጵያ የመጡ 12.000 መሣፍንትና መኳንንት ወይዛዝርት 1.500 በተግባረ ዕድ የሰለጠኑ የወርቅና የብር፣ የብረትና የመዳብ፣ እንዲሁም የነሐስ አንጥረኞች አዋቂዎች ጠቢባን ፀበርተ ዕፀውና ወቀርተ አዕባን ናቸው፡፡ እነዚህ ኢትዮጵያ ገብተው በየክፍለ ሀገሩ ሥራቸውን ሲጀምሩ አክሱም ጽዮን ትግራይ ላይ ስትቀር የዳዊት የወንድም ልጅ ሳቤቅ የሰሎሞን አጎት ከመጀመሪያው ፓትርያርክ አዛሪያስ ጋር ተከዜን ተሻግሮ አምሐራ ሳይንት ደረሰ፡፡ የአሁኗ ተድባበ ማርያም ካለችበት ላይ ሲደርስ ቤተ እግዚአብሔር መሥራት ጀመረ፡፡ ቦታዋንም በሀገሩ ስም ገሊላ ብሎ ጠራት፡፡ ፓትርያርክ አዛሪያስ ደስ አለውና ስሙን በቡራኬ አፀደቀለት፡፡ ለዚህችውም ተድባበ ጽዮን ቤተ መቅደሱን ሰርቶ ሲጨርስ ከሌዋውያኑም ከካህናቱም ከፍሎ መስዋተ ኦሪት የሚሰው ካህናትና ሌዋውያንንም ሾመ፡፡ መስፍኑ ሳቤቅ ቤተልሄማዊም በገፀ ንጉስ በወርቅ ወንበር የሚቀመጥ ነበር፡፡ ከዚህ ላይ ገሊላ ብሎ ከሰየመ በኋላ አገሮቹን አሻግሮ እያየ በሀገሩ ምሳሌ ይሰማቸው ጀመር፡፡ ደብረ ዘይት፣ ኬብሮን አሁን ከቀን ብዛት የተነሳ ህዝቡ ኬብሮንን ከሚኖር ይለዋል ይኽውም ከተድባበ ማርያም አባ በር ወደ ምስራቅ ያለውን መግቢያ ነው፡፡ ወደ ቀኝ በኩል ተመልከተና እያሪኮ ትባል አለ ከቀን ብዛት ግን ሕዝቡ እያሪኮን አራሆ ይሏታል ቀጥሎ ኢየሩሳሌም ቀጥሎ ሎዛ ከዚህ ከሎዛ በላይ ታቦር አለው ይኸውም በአፄ በዕደ ማርያም ዘመን መግስት የተነሱት የቅኔ ፈጣሪዎች እነ ዮሐንስ ገብላአዊ፣ እነ ሠምራ አብ፣ እነ ወልደ ገብርኤል እነ ደቅ እስጢፋ የነበሩበት ነው፡፡
7 163
እውነት ሲዳፈን ሃሰተኞች ይበረክታሉ እንዲሉ!
የኢትዮጵያ መከራዋ የመጣው ከመቸ ጀምሮ ነው?
መቸስ ነጻ ትወጣለች ?
የተዳፈነው የሰሎሞናዊ ስረወ መንግስትና የዘር ሃረጉ?
ይመጣል ስለ ሚባለው ንጉስ ...... ስለ እውነት እንናገራለን በእውነትም እንመሰክራለን ይህ አማን በአማን የ እውነት መንገድ ነውና በእውነት ተዋጁ ታላቁ ሚስጥእ የሚገለጥበት ጊዜ በዩቲቪ ቻናል ይጠብቁን!
7 163
ከደቂቃወች በኋላ ተስምቶ ስለ ማይታወቀው ስለ መመጸኛዋ ከተማ አስደናቂ ትንቢታዊ ታሪክ ይዠላችሁ እቀርባለሁ !
በዩቲቪ ቻናሌ ጠብቁኝ!
7 163
የዚህ ዘመን የመማጸኛዋ ከተማ
የመማጸኛዋ ከተማ በሚል ርእስ እጂግ አስደናቂ ሚስጥር የሚገለጥበት ፕሮግራም በዩቲቪ ቻናል ይተብቁን !
7 163
"ታላቁ የቀለም ቀንድ ወላዴ አእላፍ ሊቀ ሊቃውንት የድጓው ፈጣሪ የኔታ ነብየ ልዑል ከዚህ ዓለም ሰሞኑን ያረፉት ገቢረ ታምራቱ በእለተ ርፍታቸው የተከወነ ድንቅ አባት ናቸው።
በ1924 በ ላስታ አካባቢ ብልብላ ጊዮርጊስ የተወለዱት ታላቁ ሊቅ ከልጂነታቸው ጀምሮ ትንቢት የተነገረላቸው ታላቅ አባት ሲሆን የየኔታ ጥበቡም የ የቀለም ልጃቸው ናቸው ።
ታላቁ የቤተ ክርስቲያን ማኅቶት የኔታ ነብየ ልዑል ዘመናቸውን በንጽሕና በድንግልና ተወስነው ወንበር ዘርግተው ጉባኤ አስፍተው ረጅም ዓመታትን በማስተማር ለቤተ ክርስቲያን አያሌ አይናማ ምሁራንን ያስገኙ ወላዴ ሊቃውንት የብዙ ዓይነ ንሥር አእዋፍ ደቀ መዛሙርት መጠለያ የቤተ ክርስቲያን ዋርካ ነበሩ ።
ተሀራሚው ባሕታዊው እና ፍጹም ጸሎተኛው የኔታ ነብየ ልዑል በእርግና ዘመናቸው እንኳን ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ ለሀገር ለቤተ ክርስቲያን ሲጸልዩ የነበሩ የበረከት የጸሎት የፈውስ የእንባ አባት የሰኔ ግባ ጊዮርጊስ ማኅተም ነበሩ ።
ስርዓተ ቀብራቸው በጎንደር ክፍለ ሀገር በስማዳ ወረዳ ሰኔ አግባ ቅዱስ ጊዮርጊስ ደብር ሰኔ 25 /10 /2014 ተፈፅሟል።
በጸጋ መንፈስ ቅዱስ አብረው ለጸሎት ከሚቆሙት አራቱ ደገኛ የኢትዮጵያ አይን አባቶቻችን የመጨረሻው ሰው ሰሞኑን አረፉ !
ግን ስርዓተ ቀብራቸው በቤተክርስቲያን ስርዓት ተከናውኖ ከተፈጸመ በኃላ እንግዳ ነገር ተከሰተ ።እንደምትመለከቱት ለቀብር የሄደው ሰው እዚያው በቆመበት "የረጋ ደም "እና "ውሃ "የሚመስል ፈሳሽ ታየ ።
ይህን ሊቃውንቱ ሲገልጹ አንድም የአባታችን ክብር እግዘብሔር ሲገልጥ ነው ሌላው ግን ምድር ያሳለፈችው መከራና ወደ ፊት የሚመጣባትን የጭንቅ ዘመን የሚገልጥ ነው ለዚህም ምስክሩ የቅዱስ ሙሴ ታርክ አባ ዩሐንስ ዘጸይልም በአቡነ አብየ እግዚእ ገድል የመሳሰሉት በሃጥያት ምክኒያት መቅስፈት በምድሪቱ ላይ ሲታዘዝ የሚከሰት ምልክት ነው።
አባቶቻችን የሰው ልጂ ወደ ልቡ እንዲመለስ ፈጣሪውን ከማሳዘን ይልቅ በንስሃን ተመልሶ ምህርት በምድር ላይ እንዲወርድ ያሳስባሉ ።
የአባቶቻችን በረከት ይደርብን!*
ይህ ፈለገ ጥበባት ነው ያላችሁን ሃሳብ አስተያየት ጥቆማ @Nabuti 21 ላይ አድርሱኝ።
7 163
"ታቹን ከበጌምድር፣ደብሩ ጊዮርጊስ፣ቦታው ሰኔግባ፤
በደጋጎች መሄድ፣ እንኳን ሰው መሬቱ፣ የደም እንባ አነባ፤ "
ያለንበት ጊዜ እጂግ በጣም አስደንጋጭ ነው የአለም ምስቅልቅሏ የሃሳውያኑ ብዛት የመጥፊያችን ማጥፊያወቻችን መብዛት የእርስ በርስ ጥላቻ አሰቃቂ ሞት መሰደድ ርሃብ ስቃይ የምድራችን እድል ፈንታዋ ሁኗል።
ሰሞኑን አንድ አስደናቂ ነገር በአገራችን ተፈጥራል በአንድ ታላቅ አባት እረፈት ወሃው ወደ ደም ተቀይሯል።
ይህም የዩሀንስ ራዕይ 16 ላይ ሶስተኛው ጽዋውን በወንዞችና በውኋ ምንጮች ውስጥ አፈሰሰ እነረሱም ደም ሆኑ ያለው ትንቢት እየተፈጸመ ይሆንን የሚል ስጋት ውስጥ ጥሏል።
የኢትዮጵያ መከራዋ እየበዛ ሲሄድ በዚህ ጥቂት አመታት ስለ ኢትዮጵያ የሚጸልዩ አምርረው የሚያለቅሱ የተላከ ማእትን የሚያስታግሱ በረከትንም የሚለምኑ በጸጋቸው ህሙማንን የሚፈውሱ የዘመናችን አቡነ ተክለሃይማኖቶች የእነ አባ ጳውሊና የእነ አባ መቃርስን ፍኖት የተከተሉ አራት አበይት የኢትዮጵያ አይኞችን አጠናል።
በእርግጥ አኗኗራቸው በህቡዕ አሰራራቸውም በሚስጥሩ ኑሮአቸውን በብትውና ስላሳለፉ አለሙ ባያውቃቸውም እነርሱ ግን በእግዚአብሔር ዘንድ ሞገስ ያገኙ እኛ ባንጠቀምባቸውም የዘመናችን አብሪ ኮከብ የነበሩ ህያው የመነፈስ ወንድማማቾች ናቸው።
የታላላቅ አባቶቻችንን አስደናቂ የዘመኑ ተጋድሎአቸው እና ጸጋ እግዚአብሔር ዛሬም በምድራችን ላይ የመላቸው ሰወች እንዳሉ ለመ መስከር ሆነ ተጋድሎአቸውን ለመናገር ዛሬ ጊዜው ነውና በህይወተ ስጋ እያሉ ያልተገለጸ ድንቅ ማንነታቸው ዛሬ በአጸደ ነፍስ ነፍስ ሁነዋልና እንመሰክራለን።
አንድ አባት ከጥቂት አመታት በፊት በዚህ ዘመን በደቡብ ጎንደር ዙሪያ በብቃት ደረጃ የሚገኙ ለሃገር የሚጸልዩ ተራርቀው እየኖሩ ነገር ግን እረስ በ፦እርሳቸው በመንፈስ የሚገናኙ አራት አባቶችን እንዳሉ ነግረውኝ ነበር እነሱም የኔታ ኃይለ ሚካኤል ዘመካነ ኢሱስ(አስቴ)፤የኔታ ተዘራ ዘወርቅ አምባ (በለሳ)፤የኔታ ጥበቡ ዘዛራ ሚካኤል(ደራ) እና የኔታ ነብየ ልዑል ዘሰኔ ግባ ጊዮርጊስ(ስማዳ) ናቸው ብለውኝ ነበር እኒህ አባቶች .....
በመንፈስ የተሳሰሩ እኒህ ጸጋ የመላቸው መምህራን ስለ ወደፊቱ ሲናገሩ የ ነብያትን ጸጋ እንደ ወንጌል ሰባኪነታቸው ሃወርያት የዚህን አለም ኑሮ በመካድ በመንኩስና መናራቸው ሰማይትም ሁነዋል።
እኒህ የዘመናችን አብሮ ኮከቦች የአወደ ምህረት ጭብጨባ ያላደነቆራቸው ጸጋቸውን ፈልጎ ለሄደ እንጂ እንዲሁ በግብዝነት ራሳቸውን የማይገልጡ።
ሁሉን እያወቁ እንደ አላዋቂ ራሳቸውን ቀብረው ና ሸሽገው ከእግዚአብሔር ጋር የሚነጋገሩ ትጉህ የኢትዮጵያ ረኞች ነቀሩ።
ከእኒህ የመንፈስ ጓደኛሞች ቀድመው ያረፉት የበለሳው አንበሳ ሊቁ ነብይ ወሃዋርያ አባ ተዘራ ካሳ(ሃይለ ማርያም ካሳ) ሲሆኑ...... ስለ ኢትዮጵያ ከሚጸልዩ ከታላላቅ ታዋቂ የግዜያችን ባህታዊ አባቶች ውስጥ አንዱ ሲሆኑ።
እጂግ በጣም ደግ ሩሩህ የተወደዱ ጸጋ የመላባቻው ታላቅ ያለፈውን የሚያወቁ የወደፊቱን በ ጸጋ ትንቢት የሚረዱ በእግዚአብሔር ጸጋ እና ፈቃድ የሚናገሩ ታለቅ ባህታዊ ሲሆኑ። በዚህ በእኛ ዘመን በጸጋ እግዘብሔር ህሙሞንን እንደ ሃዋርያት በሚያስደንቅ ሁኔታ የሚፈውሱ ሃጥያትን የሚያስተሰርዩ ታላቅ አባት የተወለዱት በሰሜን ጎንደር ዞን ሚካኤል ደበር አካባቢ ምጎ ስላሴ ላምባልጋ ከተባለ ጎጥ ከአባታቸው ከአቶ ካሳ ከእናታቸው ከወ/ሮ ማለፊያ ዘውዴ የካቲት 12 በ1928 ዓ.ም ተወለዱ በልጂነታቸው ብዙ ገቢረ ታምራት የተደረገላቸው በዚህ ዘመን እንስሳትና አራዊት የሚታዘዙላቸው ከተሰወሩ አባቶች ጋር የሚነጋገሩ እርሳቸውም የሚሰወሩ በደመና ተጭነው የሚንቀሳቀሱ ታላቅ የጸሎት የብትህወና አባት ሲሆን ይህን ና ስለ ተሰወሩ ቤተ መቅደሶች በርካታ አስደናቂ ሚስጥር የተናገሩትን በሌላ ጊዜ ይዠላችሁ እመለሳለሁ። እኒህ አባት ከ ያሉበት ለጸሎት በመንፈስ ቅዱስ አብረው ከሚቆሙ አራቱ ባህታዊያን አንዱ ነበሩ በ መጋቢት 19 2011 አረፉ ።
ሌላው ታላቅ አባት የኔታ ሃይለ ሚካኤል ዘእስቴ ሲሆን ታላቅ የጸሎት አባት ከመንፈሰ ወንድሞቻቸው ጋር ሁነው በጸጋ ከያሉበት አብረው ለጸሎት የሚቆሙ ድንቅ አባታችን ነበሩ።
ሌላው ሊቁ እና የኢትየጵያ አይን የኔታ ጥበቡ ታየ
ወላዴ አዕላፍ የኔታ ጥበቡ ታዬ የተወለዱት መስከረም 17 ከአቶ ታዬ ውቡ እና ከወ/ሮ የሻረግ በለጠ (እሟሆይ) በደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት በደራ ወረዳ ቁላላ መስቀለ ኢየሱስ ከምትባል አጥቢያ እንደሆነ ይነገራል። በ1933 ዓ.ም ከአቡነ ይስሐቅ ዲቁናን እና ታኀሳስ 29 ቀን በ1967 ዓ.ም ደግሞ ከመምህር ገብረ ማርያም ምንኩስናን እንደተቀበሉም ይገለጻል፡፡ በ1967 በጥር ወር ጎንደር ቅዱስ ሚካኤል ከብጹዕ አቡነ እንደርያስ ቅስና ተቀብለዋል። ማስተማር የጀመሩት ግን በ1930 ዓ.ም ነው።
በከበረች ጸሎታቸው ሃገራችንን ከተቃጣ መዓት ከታዘዘ መቅሰፍት ከሚሰውሩ አባቶቻችን አንዱ ናቸው የኔታ። ዛራ ሚካኤል ሄዶ ሥጋዊም መንፈሳዊም ሕይወቱን የሚያስተካክል ጸሎተ ማርያም ከየኔታ የተቀበለ መቼም የተደረገለትን ያውቀዋል።
የኔታ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን ገብረሔር የሆኑን በርካታ ሊቃውንት ያፈሩ ወላዴ አዕላፍ አበ ሊቃውንት ለሃገራችን ብቻቸውን እልፍ አእላፍ ምሁር ያፈሩ መካነ አእምሮ (ዩኒቨርሲቲ) ነበሩ። በርካታ ሰባኪያነ ወንጌል፣ የጉባኤ ቤት መምህራን፣ የገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎችንና ሊቃነ ጳጳሳትን ያፈሩት የኔታ ለምዕመናን ልጆቻቸው ደግሞ በርካቶች ላይ የተተበተበውን ቋጠሮ የፈቱ መጠለያ ጥግ ነበሩ የኔታ።
አንጋፋው ሊቅ የዛራው ዋርካ መልአከ ምሕረት ወለደ አእላፍ የኔታ ጥበቡ ታዬ ካስተማሯቸው ውስጥ፦ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ መርቆሬዎስ፣ ብፁዕ አቡነ ኤልሣዕ፣ ብፁዕ አቡነ እንድርያስ፣ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ፣ ብፁዕ አቡነ በርናባስ እና ሌሎችም ከ9 በላይ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ከሊቃውንት ደግሞ መምህር ባሕታዊ ኪዳነ ማርያም፣ ሊቀ ሊቃውንት አባ ዕዝራ ሐዲስ፣ ሊቀ ሊቃውንት ትሕትና እና ሌሎችም በመላ ሃገሪቱ አንቱ የተባሉ ቁጥራቸው በውል የማይታወቅ በርካታ አንጋፋ ሊቃውንት ይጠቀሳሉ። እነዚህ ያስተማሯቸው ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን የኔታን “የፍቅር የትሕታና፣ የጸሎት፣ የትሕርምት ሰው ታላቅ አባትና መምህር “ በማለት ይጠሯቸዋል።
በርካታ ሊቃነ ጳጳሳትንና ሊቃውንትን በሃይማኖት የወለዱት ወላዴ አዕላፍ፣ ሊቁ እና ባሕታዊው የኔታ ጥበቡ ታዬ ሥራቸው ከአእላፍ የሚበልጥ ክቡር አባት ናቸው እልታይ ልታይ ሳይሉ እጂግ አስደናቂ ገቢረ ታምራትን በጸጋ የሚያደርጉ በርካቶችን ከ አለም ፈተና በጸሎተ ማርያም ያዳኑ አባት ነበሩ።
በጸጋ ለአገራቸው በመንፈስ ከያሉበት ቁመው በጋራ ጸሎት ከሚያደረሱት ደገኛ አይነ ኢትዮጵያ ሊቅ አንዱ ነበሩ በቅርብ በአካለ ስጋ የተለዩን አባታችን ናቸው።
ሌላው ሰሞኑን እጂግ ያስደነቀና በአለም ያሉ ኢትዮጵያውያንን ያስገረመ የእግዘብሔር ታምር በምድሪቱ ላይ ታይቷል።
በጸሎት አበረው በመንፈስ የሚቆሙ ደገኛ ሊቃውንተ ቤተክርስትያን ከአራቱ ደገኛ አባት ሰሞኑን ያረፉት ሊቁ ባህታዊው የኔታ ነብየ ልዑል ይባ ላባላሉ።
7 163
ዪቲቪ መከታተል ለማትችሉ ፈለገ ጥበባውያን ወሃው ወደ ደም የተቀየረበትን ሚስጥር እና ተሰምቶ የማይታወቅ የዘመኑ የአባቶቻችን ተጋድሎ በጹሑፍ ይዠላችሁ እቀርባለሁ
ጠብቁኝ!
