ፈለገ ጥበባት +++
Open in Telegram
+++የቀደምት ኢትዮጵያውያን ስልጣኔን ማሳየት እንዲሁም ገዳማት እና አድባራትን ማሳወቅ፡፡+++ የተረሱ አድባራትና ገዳማትን ማስታወስ ፤የ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያንን ጥበብ እውቀትን በምንችለው ሁሉ መመርመር የአባቶቻችን ልጆች በመሆን ትላንት በዛሬ እና በነገ ውስጥ ማስቀጠል ማስቻል ነው።
Show more7 163
Subscribers
-524 hours
-267 days
-7330 days
Posts Archive
7 163
ወዳጀ ተጨንቀሃልን ?
እየመጣ ላለው ነገር መዘጋጀቱ የአባት ነው
ጨለማው ድቅድቅ ነው መከራውም ጽኑ ነው
እግዚአብሔር ፀሐይ ሊያወጣህ ነውና
በአለህበት ጸንተህ ኑር !
ንቁም በበህላዌነ !
7 163
ባለ ቆብ ሚስማሮች !
ዛሬ መድኃኔ ዓለም ነው::ቀኑም በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ነገረ ቅንዋት ይነገርበታል።ቅንዋት መድኃኔ ዓለም ለሁላችን ቤዛ ሊሆን የተቸነከረባቸው ችንካሮች(ሚስማሮች) ናቸው። ዛሬ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መድኃኔዓለምን መስላ እርሱን ተከትላ በእነዚህ ባለቆብ ችንካሮች ተቸንክራለች።
ችንካሮቹ መነቀላቸው አይቀርም። ለጊዜው ግን ሕመሙ ከባድ ነው።ሚስማሮቹ ባለቆብ ናቸውና። የቤተ ክርስቲያንን እግሮቿን ቸንክረው እያደሟት ነው።
ለቤተ ክርስቲያን ዛሬ ስቅለት ነው። ስቅለት ደግሞ የትንሣኤ ጎረቤት ነው።ለንጊኖስም የዘረኝነት ዘገሩን ነጥቆ ጎኗን እየወጋት ነው። ከባለቆብ ሚስማሮች ጋር።ዛሬ የፍርድ ፀሐይ ጨልሟል። ስቅለት ነዋ!
ነገ ግን በእርግጥ ትሣኤ አለ። ትንሣኤ ብቻ አይደለም እርገትም አለ !!
ባለቆብ ሚስማሮች
7 163
አንተ ሰው አሁንም እያነቀላፋህ ነውን?
ብዙሃኑ ተጨንቋል ፣እኔ ግን በ ጹኑ መከራው ውስጥ የሚታየኝ ተስፋ ያስደስተኛል።
አንዳንዶቹ ቤተክርስቲያን ተከፈለች ይላሉ፤ እኔ ግን ቤተክርስትያን ራሷን እያጠራች እንደገና እየተሰራች ነው እላለሁ።
እየፈረሰን የሚመስለቸው አሉ እግዘብሔር ግን እየሰራን ነው ፤
ብዙሃኑ ጨለማ ከቦናል ይሉኛል፤ እኔ ደግሞ በጨለማው ውስጥ ከፍ ብሎ ያለው ብርሃን ይታየኛል።
አንባቢ ሆይ አስተውል!
ይህ ጊዜ ..
የሽንጋይ አንደበቶች ግብረ ፈርኦናውያን ነገስታት የታወቁበት ፤
ከመጋረጃ በሻገር የሚደረገው ጥፋት አድራጊወቹ በፊት ለፊት የተገለጠበት ፤
አምሳለ ፈሪሳውያን ማንነታቸው የተለየበት፤
የሊቃነ ጳጳሳት ጽናት እና አንድነትን ያጠነከር፤
ምዕመናንን የሚያሰባስብ የአላውያን ነገስታትን ሴራ የገለጠ ፤
ግፈኞችን በሹመት ያዋረደ በሽልማት ያኮሰመነ ጊዜ ነው.....
ወዳጀ ሆይ ምን ይታይሃል.....ይህ ነብዩ የዕንባቆም ትንቢት የሚፈጸመት ጊዜ ነው ።
ሚጨነቁት የኢትዮጵያ ድንኮኖችን፤ የሚሰነጠቁ የምድያም መጋረጃወች ህያው ምስክር ይሆናሉ።
አንተ ሰው የት ነህ ....
ኢትዮጵያ ድንኳኖቹ ሲነቀጠቀጡ ለምን በል?
የተመረጡት ሲስቱ ወዮ ለእኔ በል፤
የአበው እንባ ሲፈስ ዘመኑ ዘመንን ሊወልድ እንደሆን ተረዳ ፤
አንተ ንጹህ ካልህንክ መከራው በአንተ ላይ ያልፋል አንተ ከነጻህ በመከራው ላይ ታልፋለህ...፤
አንተ የዋህ በእውነቱ አንተ ራስህ እሳቱን ለማጥፋት ከመከራው ለማምለጥ የቤተክርስቲያን ጥፋት ላለማየት እንደምትሻ ሁሉ እግዚአብሔር እሳቱን ያጠፋልህ ዘንድ መከራውንም ያስታግሰው ዘንድ አይፈልግምን?
ነገር ግን የሱን ቀን፤ የሚያስነሳውን ሰው እየጠበቀ ነው፤ ያኔ ከፊቱ የሚቆም አመሳለ ሃና ወቀያፋ ፈሪሳውያን ሁሉ ይረዳሉ ይንቀጠቀጥማሉ ...
አንተ ግን ከዚህም የባሰ ለአይንም ለልብም እንግዳ መከራ ይመጣብሃልና ዘመኑ በአንተ ላይ እንዳያልፍ ባለህበት ጽንተህ ቁም ።
መከራ ከዕረፍት በኋላ እንደሚመጣ ኹሉ ከመከራ በኋላም ዕረፍት ጠብቅ፤
ሁልጊዜ ክረምት ፣ሁልጊዜም በጋ፤
ሁልጊዜ ማዕበል፣ ወይም ሁልጊዜ ጸጥታ ፤
ሁልጊዜ ለሊት ፣ሁልጊዜም መአልት የለምና ፤
መከራ ቋሚ አይደለምና ከፈርኦን እጂ ወጥተን ከንአን የመንገባበት ዘመን አለ.....
አንተ ግን ባለህበት ጸንተህ ኑር!
ይህ ፈለገ ጥበባት ነው.....
ሃሳብ አሴተያየት ጥያቄ ካለ @Nabuti21 ላይ አድርሱኝ።
7 163
''የኢትዮጵያ ድንኮኖች ሲጨነቁ አየሁ''
እንሆ እየሆነ ያለውን ያስተዋለ አለ?
እየሆነ ያለው ሊሆን ግድ ነው ፤ ቤተክርስቲያን በሃና ወ ቀያፋ ተከባ ምዕመኗ የፈረኦናውያን ቀንብር ወድቆባቸዋል።
አንባቢ ሆይ በእውነቱ በጽሞና እያስተዋላችሁ ነውን?
ይህ ከስጋዊና ደማዊ ሃይሎች ብቻ ጋር ቤተክርስቲያን የምታደርገው ትግል አይደለም ። ይልቁንስ የመንፈሳዊ ውጊያ እንጂ.....
ማዕበሉ ጽኑ ወጀቡ ከባድ ነው በቀጭኗ መንገድ የተጓዘ እሱ ሁሉን ያልፋል።
እንግዲያውስ በያላችሁበት ጸንታችሁ ቁሙ! ክፉ ዘመን ተጠናውቷት በ ፈርኦናውያን ባርነት ስር የወደቀችው ምስኪኗ አምሳለ ራሔል ሆይ ምን ላድርግለሽ እናቴ? እንባሽን የሚያብስ አልወለድ ያለው የተጸነሰውን ሽል እንዴት ባለ ጥበብ ትውልጂው? ነፍስ ጡሯ በማህጸንሽ ያሉ ልጆችሽ የሚንጡሽ ምስኪና አምሳለ ራሔል ኢትዮጵያ ሆይ ድንኮንሽ ሲጨነቁ ያየው ነብየ እግዚአብሔር ለምን ይሆን ድንኳኗ ከወጀብና ከ ማዕበል የሚረጋው ዘመንንስ ያልነገረን?
ለሆነው... እየሆነ ላለው... ለወደፊቱ ለሚሆነው መከራ .....ንቁም በበህላዌነ !
7 163
ሁላችንም አዝነናል!
ንቁም በበህላዌነ
ይህ ሁሉ ሊሆን ግድ ነው !
እየሆነ ያለውን ነገር በጥሞና አስተውሉ ፤ ዙርያ ገባውን በጥንቃቄ ተመልከቱ ፤ አለም ከየት ወዴት እየሄደች እንደሆነ መርምሩ፤ የተመረጡት እስኪስቱ ድረስ የተባለው ዘመን ላይ መሆኑን ማን አስተዋለ?
የዘመኑን መለወጥ ተረድታችሉ ስለ ራሳችሁ እዘኑ!
ይህ ጉዳይ መልካም አጋጣሚም ነው ፤ እግዘብሔርን ስራውን ሲሰራ ለተንኮለኛው በመሰጠትም በመንሳትም፤ ሃሳዊውን በመሾምም ወደ ውረደቱ ፣ በመሻርም ወደ ዝቀታው ይጥለዋል....
ተንኮለኛው ከቀናው ሊለይ
ሃሰተኛው ከ እውነተኛው ሊታወቅ
በስውር የተገነባ ማንነት በግልጽ ሊገለጥ
የገማው የቆሸሸው የተበላሸው ሊነጠል ....
አማን በአማን እግዚአብሔር ኢትዮጵያውያን የሚያነሳበት ቀን አለው!
ሚደፈራርስ ሊጠራ ይመስለኛል
ንቁም በበህላዌነ.......
7 163
ሔኖክ ስለ ገለጻቸው ኔፍሊሞች
በኢትዮጵያውያን መዛግብት ግዙፋን ስለሚባሉት
የሰውን ልጀ ዘረ መል ኦንዴት እንዳዛቡ
ስለ ኔፍሊሞች በኢትዮጵያ ጥንታዊ መዛግብት ላይ ባገኘሁት አስደናቂ መረጃን በ ጹሑፍ ይዠላችሁ እቀርባለሁ።
