ፈለገ ጥበባት +++
Open in Telegram
+++የቀደምት ኢትዮጵያውያን ስልጣኔን ማሳየት እንዲሁም ገዳማት እና አድባራትን ማሳወቅ፡፡+++ የተረሱ አድባራትና ገዳማትን ማስታወስ ፤የ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያንን ጥበብ እውቀትን በምንችለው ሁሉ መመርመር የአባቶቻችን ልጆች በመሆን ትላንት በዛሬ እና በነገ ውስጥ ማስቀጠል ማስቻል ነው።
Show more7 163
Subscribers
-524 hours
-267 days
-7330 days
Posts Archive
7 163
ለሰማይ ለምድር ወደ ከበደ እጂግ አስደናቂ የቅዱሳን የመናንያን ቦታ ሰሞኑን አቅንቸ ነበር።
ሱዳን ጠርፍ ከነጋዴ ባህር በእግር ለሚጓዝ 8 ስዓት፤ ከ 40 ዲግር ሲሊሸስ የሚልቅ ሃሩር ቃጠሎ፤ ከሙቀቱ የተነሳ ድንጋዩ ተልባ የሚያስቆላ፤ የስውራኑን በረከት ልካፍል በርሃ ወርጃለሁ....
ለአይንም ለልብም እንግዳ የስውራኑ መኖርያ ድንገት ታይተው የሚሰወሩ፤ እንደ መልካም ፅጌረዳ ማዕዛው የሚያውድ፤ እንኳን መነኮሳቱ የገዳሙ ከብቶች በቃላት ትዕዛዝ ን የሚፈጽሙበት ...እንደ ነፋስ የሚከንፉ ፤እንደ ፀሐይ የሚያበሩ ፤እንደ መላዕክት የሚኖሩ ....ታምራት የመላበት ፤ወንጌል የሚኖርበት ፤ኢትዮጵያን ከሚወረወርባት ጦር ፍላጻ ሁነው የሚጠብቁ፤ ከታሰበባት ደባ በጸሎታቸው የሚያፈራረሱ፤ ሃያላኑን የሚያዋርዱ፤ ብርቱወችን የሚያልፈሰፈሱ ፤ ሴረኖችን የሚበትኑ ........በአለም የተማሩ አብዝተው የተመራመሩ አንቱ የተባሉ ከመላው አለም የተሰባሰቡ አለምን የተው፤ ቅዱሳን ስውራን መናንያን ከ አለም ጫጫታ ረቀው፤ ሰው ወደ ማይቀርበበት በርሃ ተሰደው ወደ ሚገኙበት .... እጂግ ድንቁ የኢትዮጵያን ከሚጠበቁ ገዳማት ዋናው ፤ ጥንታዊው ማህበረ ሥላሴ ገዳም ተጉዠ ለአይንም ለልብም እንግዳ ነገሮችን ከመነኮሳቱ ጋር በመዋል በማደር ተመልከቻለሁ.....የተመለከትኩትን ያጋጠሙኝን አስደናቂ ሁነቶች በዝርዝር እግልጽላችሁ አለሁ!
ያላችሁን ሃሳብ አስተያየት @Nabuti21 ላይ አድርሱኝ !
7 163
የሊቃውንቱ ስውር ጥበብ ለበርካታ በሽታወች ፈወስ የምትሆን አስደናቂዋን እጽዋት በጣና ገዳማት አገኘኋት። ለበርካታ በሽታወች ፈወስ የምትሆን ራሷን ደብቃ የምትኖር ተፈላጊዋ ታምረኛዋ እጽዋት ከብዙ ድካም በኋላ ተገኝታለች.....በፈለገ ጥበባት የዮቲበ ቻናል ከደቃቃወች በኋላ ሙሉ መረጃውን ይዠላችሁ እመጣለሁ!....
7 163
ከደቂቃወች በኋላ
ከዋልድባ መነኮሳት ከሆኑት አባት ጋር ቆይታ አድርገናል ስለ መጭው ጊዜ ስለ ቤተክርስቲያናችን ፈተና መቋጫ፤ መናንያንን ስለ ኢትዮጵያ መን ይላሉ ምንሰሰ መልዕክት አላቸው ? የዚህ ሁሉ መከራ ማብቂያ መቸ ነው.....
በተለያዩ የአለም ክፍል የተበተኑ ኢትዮጵያውያን ወደ አገራተው የሚገቡበት ጊዜ......
ይህንን ፕሮግራም ከ አበው አንደበት የምታደምጡት ይሆናል .....ፈለገ ጥበባት የዩታብ ቻናልን ሳብስክራይብ አድርጉ ና ጠብቁኝ!
7 163
ጊዜ በግንባራቸው ፍግም እያሉ ወደቁ፡፡ ‹የኢትዮጵያ ሕዝብ አምላካቸው ሊረዳቸው መጣ፡፡ እንግዲህ ማን ያድነናል› አሉ፡፡ ምድር ጠበበቻቸው፡፡ በዚህም
ጊዜ የአትዮጵያ ሠራዊት የሮምን የጦር ሠራዊት ፈጁዋቸው፡፡ የተረፉትንም ማረኳቸው፡፡ ፈጽመውም እስኪያጠፏቸው ድረስ በሮማውያን ላይ በእግዚአብሔር
ሥልጣን የኢትዮጵያውያን እጅ እየበረታች ሄደች፡፡ ከዚህም በኋላ ንጉሡ ሣህለ
ማርያም በእግዚአብሔር ኃይልና በተአምራት አድራጊው በቅዱስ ጊዮርጊስ ተራዳኢነት የሮማውያንን የጦር ሠራዊት በጦርነት ድል አድርጎ የድል አክሊል
ተቀዳጀ፡፡
ስለዚህም ‹በዳዊት የምስጋና ቃል የድል ዘውድ ያቀዳጀኝን እግዚአብሔርን ባለ ዘመኔ ሁሉ አመሰግነዋለሁ፡፡ ለፈጣሪዬም እዘምራለሁ› አለ፡፡ ሕዝቡም ሁሉ ‹በክብር ከፍ ከፍ ያለ እግዚአብሔርን በፍጹም ምስጋና እናመሰግነዋለን የሮማውያንን ኃይል ቀጥቅጦ አጥፍቷልና፣ ሠረገሎቻቸውንም ሰባብሯልና፣
ሠራዊቱንም ሁሉ በምድር ላይበትኗቸዋልና…› እያሉ አመሰገኑ፡፡ በፈጣሪው በኢየሱስ ክርስቶስ ኃይል በጦርነቱ መካከል የረዳቸውን ቅዱስ ጊዮርጊስንም
በፍጹም ማድነቅ እያደነቁ አመሰገኑት፡፡ ሮማም የጦር ሠራዊት በኢትዮጵያውያን ፊት ተዋረዱ፡፡ ዳግመኛም በኢትዮጵያ ላይ እጃቸውን ከፍ ከፍ አላደረጉም፡፡
በምኒልክም ዘመነ መንግሥት ኢትዮጵያ ከጦርነት ለ40 ዓመት ያህል አረፈች፡፡
የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ምኒልክም ከአድዋ ጦርነት ከተመለሰ በኋላ አዲስ አበባ በምትባለው ከተማው መካከል በቅዱስ ጊዮርጊስ ስም የተዋበች ቤተ
ክርስቲያን አሠራ፡፡ ስሟንም ‹ገነተ ጽጌ›› ብሎ ሰየማት፡፡
ታድያ ይህ ከሺ አመታት በፊት ከታቦተ ጽዮን ጋር በሚስጥር ወደ ኢትዮጵያ የመጣው ሞዓ መንግስት የተባለ መግነጢሳዊ ሀይል የተላበሰ ቅዱስ እቃ እንደ ታቦት በመነበር በክብር ይቀመጣል።
ከ አድዋ ጦርነት ወዲህ በጥቂት ሰወች ብቻ ወደ ሚታወቅ ሚስጥራዊ ቦታ ተመለሶ ሃይል ባለው ቦታ በሚስጥር ተቀምጧል።
ሞኣ መንግሰት ፦ይህ ረቂቅ ታላቅ ሃያል ሲሆን በሀገሪቱ መከራ ፣ቸነፈር ፣ረሀብ ፣ ሰውን የሚገል የሚያሰቃይ አንባገንን መንግስት ሲነሳ ከመንበሩ በክብር ይወጣል ፤ በካህናት ምህላ ተይዞ ይጸለይበታል፤ ይህ ጠላትንም አሳፍሮ አዋርዶ ይልካል። ሀገርን ሰላም ያረጋል ምህረትንም ያወርዳል።
ታዲያ ጣሊያንን የመሰለ ሀያል ብረቱ ጠንካራ በጊዜው እንኳን በአፍሪካ በአውሮፖ የሚወዳደራት የሌላ ሃያል ሀገርን አንዲት የተንኮታኮተች የምትመስል ሀገር በስአታት አሳፍራ የላከቻት ዋናው ሚስጥር በዚህ ሞኣ መንግስት በተባለው ሀይል ባለው ሱባኤ ተይዞ ተጸልዮ ድልን ስለሚያሰጥ ነው። በአጭሩ ይህ ሞኣ መንግስት ማለት ለመፈንቅለ መንግስት የሚውል ነው..
ታዲያ ከእግዚአብሔር ለሙሴ የተሰጠው ከ3 ሺ አመት ቀፊት በቀዳማዊ ሚኒሊክ ወደ ኢትዮጵያ የመጡት አምስቱ ታላቅ ሃይል ያላቸው ዕቃወች በፍጹም በፍጹም ተለያይተው ሊኖሩ አይችሉም።
እኒህም ወደ እኛቱ ምድር የመጡበት ዋና ምክኒያት እስከ ቅርብ ጊዜ ሞኣ አንበሳ ዘእምነገድ ይሁዳ ስዮመ እግዚአብሔር የሚለው ስረወ መንግስት ከአለም ሲጠፋ ከሰሎሞን ሚኒሊክ እስከ ሃይለ ሥላሴ ንጉስ ጸንቶ የኖረባት ሀገር ስለሆነች ነው። በእርግጥ ይህ የዘር ሐረግ ስረው መንግስት ተቋረጧል ቢባልም ዳግም እንደሚመጣ ይታመናል።
ታድያ ይህ ቅዱስ እቃ የት ይገኛል በምን ሁኔታ የሚለው እግዘብሔርን የእሱን ሰወች ሲያስነሳ ወደ ፊት ይገለጣል።
አበው ለጠቢብ ትበቁ አሃቲ ቃል ይላሉ
ለጠቢብ ሰው አንድ ቃል ትበቃለች እሷን አምለቶና አስፍቶ አራቆ ና ተመራምሮ ትንሿን እውነት ሊያገዝፍ ጥቂቷን ሊያበዛ ጠባቧን ሊያሰፋ በጥብና በማስተዋል ከተጓዘ ከታሪክ ሊቋደስ ካለማወቅ ሊላቀቅ እና በእውቀት ህያው ሊሆን ይችላል።
የጥበብ ጫፋ እንጂ መዳረሻው አይነገርም
ጠቢብ ሰው ታላቅ ሃይል አለው እውቀት ያለው ሰው ብርታትን ይጨምራል እንዲል መጻህፍ በእውቀትና በጥበብ በማስተዋል እንኖር አሜላከ ጊዮርጊስ ይርዳን ።
ይህ ፈለገ ጥበባት ነው ዩቲዩብ መከታተል የምትችል ፈለገ ጥበባትን ላይክ ሳብስክ ሸር በማድረግጨተከታተሉን።
ሀሳብ አስተያየት በኮሜንት መስጫ ሳጥን አስቀምጡልኝ ።
በውስጥ መስመር ማግኘት የምትፈልጉ @Nabuti21 ላይ ታገኙኛላችሁ ።
7 163
የሚኒሊክ ጀብድ የአድዋው ድል የፈረሰኛው ጊዮርጊስ እርዳታ እና ያልተነገረለት ታላቅ ሀያል ያለው ሞኦ መንግስት የተሰኘው ሀያል ቅዱስ ንዋይ ...
ለበርካታ ሽ አመታት ተጠብቆ ይኖር የነበረ መግነጢሳዊው ቅዱስ ዕቃ ከገዳማቱ ወጣ።
የዛሬ 127 አመት እለተ ቅዳሜ ማታ በአድዋ አቅራቢያ በሚገኘው እምየ ምኒሊክ ባከበሩት የቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ታላቅ ሱባኤ ተይዟል ::
ካህናት በግራና በቀኝ
"ነዓ ነዓ ነዓ ጊዮርጊስ እንዘ ትፄአን በፈርስ እያሉ ይለምናሉ።
ሊቃውንቱ በማህሌት ቀሳውስቱ በማይጠንቱ እግዚአብሔርን ይለምናሉ።
እምየ ሚኒሊክ የንግስና ልብሳቸውን አውልቀዉ ቃልኪዳናቸውን ከጊዮርጊስ ጋር ሊያደርጉ '' ጊዮርጊስ ሆይ ተራዳን'' እያሉ ከቤተመቅደሱ ፊት ለፊት ታጥቀው ይማፀናሉ::
ጀግኒት ጣሂቱ
አቤቱ ከጠላቶቻችን አድነን
በላያችንም ከቆሙት አስጥለን "
እያለች ፈጣሪን ትማፀናለች
፡
በዚያም ጊዜ የአክሱም ጽዮን መነኮሳትና ካህናት የእመቤታችንን ሥዕል ይዘው ወደ ንጉሡ ወደ ምኒልክ መጥተው ከሊቀ ጳጳሱ ከእነ አቡነ ማቴዎስ ጋር
ተቀላቀሉ፡፡ ከዚያም ሌሊቱን ሙሉ ጸሎተ ምሕላ ሲያደርሱ አደሩ፡
የንጉሥ ሣህለ ማርያምን ሚስት ወለተ ሚካኤል (እቴጌ ጣይቱም) ሌሊት በታቦተ ቅዱስ ጊዮርጊስና በእመቤታችን ሥዕል ፊት በጸሎትና በስግደት እያደረች ሲነጋ ወደ ጦርነቱ ቦታ በመሄድ እጅግ በሚያስደንቅ የአነጋገሯ ኃይለ ቃል በጦርነቱ መካከል እየተገኘች ለንጉሡ ወታደሮች የሞራልና የብርታት ድጋፍ ትሰጣቸው
ነበር፡፡ በዕውነትም ለተመለከታት ሁሉ እንደኃይለኛ ተጋዳይ አርበኛ ትመስል ነበረ እንጂ የሴቶች የተፈጥሮ ባሕርይ በእርሷ ላይ አይታይባትም ነበር፡፡ የንጉሡም
ወታደሮች የንግሥቲቱን የጀግንነት አነጋገር በሰሙ ጊዜ በእሳት ላይ እንደተጣደ የብረት ምጣድ ልባቸው ጋለ፡፡ ይልቁንም ላም እንዳየ አንበሳና ፍየል እንዳየ ነብር
እየተወረወሩ በጦርነቱ መካከል በመግባት የጠላትን ጦር በሰይፍ ይጨፈጭፉት ነበር፡፡ መጽሐፍ ‹ሹመቱን ሽልማቱን ያየ አርበኛ ከጦርነት ከሰልፍ ወደኋላ
አያፈገፍግም› ብሎ ተናግሯልና፡፡ በዚያንም ጊዜ ንጉሡ ሣህለ ማርያም (ሚኒልክ) በጦርነቱ መካከል ሳለ ሊቀ
ጳጳሱ አቡነ ማቴዎስ እንዲሁም የአክሱም መነኮሳት ሌሎቹ ካህናት በሙሉ ታቦተ ቅዱስ ጊዮርጊስንና ሥዕለ ማርያምን ይዘው ከንጉሡ በስተኋላ በደጀንነት
ቆመው ጸሎተ ምሕላ ያደርሱ ነበር፡፡ ንግሥቲቱ ወለተ ሚካኤል በጸሎት ጊዜ በመዓልትም በሌሊትም ከእነርሱ አትለይም ነበር፡፡ የጽዮን አገልጋዮችም
በእግዚአብሔር በሕጉ ታቦት ፊት መለከት ይነፉ ነበር፡፡ በዚህም ዕለት ይኸውም የካቲት 23 ቀን በሮማውያንና በኢትዮጵያውያን መካከል ከፍተኛ ጦርነት ሆነ፡፡
ከጦርነቱ ቀደም በሎ አንድ ሚስጥራዊ ነገር ተፈጽሞ ነበር ይህ ሚስጥር ከጥቂት ሚስጥር አዋቂ ሰወች በስተቀር በህዝብ ዘንድ አይታወቅም ...ይህ ጦርነት ከመከወኑ በፊት አንቱ የተባሉ የአቡሻህር ሊቃውነት ተሰበሰቡ ።
ንጉሰ ነገስት ሚኒልክ ብልህ አርቆ አሳቢ አስተዋይ ነበሩና የሊቃውንቱን ጥበብ በሚገባ ሸምተዋል።
ንጉሱ በብላቴና ዘመናቸው በ አጼ ቴውድሮስ እስር ላይ ሳሉ ጎንደር አዘዞ ተክልሃይማኖት ከተባለ ጥንታዊ ቤተክርስቲያን ቀለብ ተሰፍሮላቸው ለሊቃውቱ በአደራ ተሰጠው ብዙ የቤተክርስቲኒቱን እውቀት እንዲሸመቱ ሁነዋል።
አጤ ሚኒሊክ ብልህ እና አስተዋይ ስለነበሩ የሊቃውንቱን ጥበብና እውቀት በሚገባ ሲሰሙ ነበር ያደጉ።
በንግስና ዘመናቸውም ካከበሯቸው እና ትኩረት ከሰጧቸው ሊቃውነቶች በዋናነት የአቡሻህር ሊቃውነትን ከመላ ኢትዮጵያ በማሰባሰብ ተገቢውን ክብር በመስጠት ብልሀት ያዧቸው።
ዛሬ ላይ 1 ወይ 2 ብለን በጣት የሚቆጠሩ የአቡሻህር ሊቆች እጂግ በጣም ምጡቆች ፣ሚስጥር ጠንቃቂ ነገር አዋቂ እጂግ መንፈሳዊ ጸጋ የተላበሱ ሰማያትን ተመልክተው ስለ መጭው የሚተነብዩ የቀናትን ሀያልነት የሽንፈትና የድል መገኛ ዕለቶችን ጭምር የሚያውቁ አዝማናትን የሚመረምሩ እጂግ ጠቡብና መንፈሳዊ ሰወች ናቸው።
ታዲያ እኒህ ንጉስ ይህንን እውነት በጉባኤ ቤት ሲሰሙ አደገዋልና የአቡሻህር ሊቃውንትን ሰብስበው መፍትሔ ጠየቁ .....ኢትዮጵያ ጣልያንን በስአታት የአሸነፈችበት ምክኒያት ሶስት ሚስጥሮች ናቸው።
ታድያ ዋናው ሚስጥር የተገለጠው በዚህ እለት ብዙ ሽ አመታትን በሚስጥር የተቀመጠ አንድ ድንቅ እቃ ካለበት በሚስጥር እንዲወጣ ታዘዘ ።
ኢትዮጵያ በቀዳማዊ ሚኒልክ ማለትም ከ 3ሺ አመት በፊት ከ እስራኤል ከሌላውያኑ ጋ በሚስጥር የገቡ ታቦተ ጽዮንን ጨምሮ አምስት ሚስጥራዊ መለኮታዊ ሀብታት አሏት።
ከታቦተ ጽዮን ጋር ከመጣው አንዱ እና ሃያሉ እቃ ሞዐ መንግስት ይባላል።
ሞዐ ማለት አሸናፊ ማለት ነው መንግስት ደግሞ ያው መንግስት ነው። አሸናፊ መንግስት የሚል ትርጉም ያለው ድንቅ ቅዱስ እቃ ነው።
ታዲያ ይህ ሚስጥራዊ እቃ በአገሪቱ መራር አገዛዝ ሲመጣ አስከፊ ንጉስ ሲነግስ አገር በ መከራ እና ችግር ውስጥ ስትሆን ካለበት በክብር ይወጣል ራሱን የቻል መለኮታዊ ሀይል ያለው ጸሎት ይጸለይበታል ነገስታቱን ከ መንበራቸው ሹማምኑትን ከስልጣናቸው ጦርኞችን ከጦራችው ይለያል መንግስት ይወድቃል የሀያላኑን ሀያላቸውን ይነሳል ።
ታዲያ ይህ ድንቅ ዕቃ ነበር በአቡሻህር ሊቃውነቶች እና በቅዱሳነ አባቶች ሃይል ካለበት በክብር ወጥቶ የኢትዮጵያን ህዝብ ሃይልን ያጎናጸፋቸው።
በዚህ ዕለት የታዩት በርካታ አስደናቂ ታምራት ከሰማይ ይወጡ ነበር አካባቢው በቀስተ ደመና ተከቦ የሚያስገመግም ድምጽ ይሰማ ነበር።
ይህ ሞዐ መንግስት የተባለ ቅዱስ እቃ ዛሬ ለይ ከአለም ተሰውሮ በታላቅ ክብር ከሌሎች መግነጢሳዊ ሀይል ካላቸው ቅዱስ እቃወች ጋር አንድ ታላቅ ገዳም በ አናብስትና በአናብርት እየተጠበቀ በሚስጥ ተሸሽጎ ይገኛል ።
ታድያ ሌላው ሚስጥር በዚህ ዕለት ሲጎሰም የነቀረው ከ ጉማሬ ቆዶ የተሰራው ዛሬ ላይ ጣና ቂርቆስ የሚገኘው ነጋሪትም በሚጎሰምበት ዕለት የሚያወጣው ድምጽ ታላቅ ሚስጥራዊ ነገር ይፈጸም ነበር ።
በአድዋ ላይ ድል ስላደረገው የጊዮርግስ መገለጥ ሃይሉ ምንጭ ምክኒያት ከዚህው ሞዓ መንግስት ጋር የሚቀዳ ታሪክ አለው።
ብዙ ጊዜ በአድዋ ታቦት አብሮ መዝመቱ ቅዱስ ጊዮርጊስም መዋጋቱ ይገለጣል ነገር ግን ዋናው ሚስጥር ሲነገር አይስተዋልም።
በዚህም ምክኒያት ነው አገር ስትታመም እና ልትዋረድ ስትል በእግዚአብሔር ፈቃድ በጠብብት ሊቃውንተ ጥበብ የተቀመረው ይህ ሚስጥር ሲገለጥ
ወዲያውም በሰማይ ታላቅ ተአምር ተደረገ፡፡
ይኸውም የቀስተ ደመና ምልክት ታየ፡፡ ከዚያም ቀስተ ደመና ውስጥ መልኩ አረንጓዴ የሚመስል ጢስ ይወጣ
ነበር፡፡ ከዚያም ጢስ ውስጥ እንደክረምት ነጎድጓድ ያለ ድምፅ ተሰማ፡፡ ከዚያም የነጎድጓድ ድምፅ የተነሣ በሮማውያን ወታደሮች ዘንድ ከፍተኛ ድንጋጤና ሽብር
ሆነ፡፡ ለመዋጋትም አልቻሉም፡፡ ይልቁንም ኃያሉ ገባሬ ተአምር ቅዱስ ጊዮርጊስ በአምባ ላይ ፈረስ ተቀምጦ ከነፋስ ሩጫ ይልቅ እየተፋጠነ በአየር ላይ በተገለጠ
7 163
ሰላም
አድዋ!
አለምን ያስደነቀው ፣አለም ካስተናገደችው ጥቂት አስደናቂ ነገሮች ፣ የአድዋ ጀብድ የኢትዮጵያ የአሸናፊነት ምስጢር እና አባቶቻችን የተጠቀሙት እጂግ አስደናቂ ምስጢር ምንድን ነው?
7 163
ሰላም
በአገር ውስጥ ሆነ በውጭ የምትኖሩ ወገኖቻችን ።
እንደሚታወቀው ፈለገ ጥበባት የተለያዩ ሃሳቦችን ለአንባቢ ለአመታት ሲያደርስ ቆይቷል ።
ዋና አላማችን በሃይማኖቱ የጠንከረ፤ ባህልና ትውፊታዊ ማንነቱ ን የጠበቀ፤ በእወቀትና በጥበብ ህይወቱን የሚመራ ፤ ምዕመንን እንደ አቅማችን ማብቃት ነው።
በተለያዩ በአለም ክፍል የምትኖሩ ኢትዮጵያውያን
በተለያዩ ምክንያቶች ተስፋ የቆረጣችሁ፤ በሃይማኖታዊ ጥያቄ የምትናጡ፤ የተለያዩ ቤተሰባዊ ሆነ ማህበረሰባዊ ቁርሾ ተጠቂ የሆናችሁ፤ በትዳራችሁ የምትፈተኑ፤ ክርስትናዊ ህይወትን ለመምራት መንገድ የጠፋባችሁ ...በተለያየ ችግር ያላችሁ ወገኖቻችን እግዘብሔር በፈቀደ ችግሮቻችሁን በማድመጥ አስፈላጊውን መፍትሄ በእኛም ሆነ እንዲሁም በተለያዩ አባቶቻችን አጋዢነት ችጎሮቻችሁን ለመስማት መፍትሄም ለመፈለግ ከጎናችሁ ነን።
ወገኖቻችን ኢትዮጵያውያን በውስጥ መስመር ባስቀመጥኩት ሊንክ ማግኘት ትችላላችሁ ።
👇👇
@Nabuti21 🤏 ላይ እንገኛለን
7 163
ሰላም
በአገር ውስጥ ሆነ በውጭ የምትኖሩ ወገኖቻችን ።
እንደሚታወቀው ፈለገ ጥበባት የተለያዩ ሃሳቦችን ለአንባቢ ለአመታት ሲያደርስ ቆይቷል ።
ዋና አላማችን በሃይማኖቱ የጠንከረ፤ ባህልና ትውፊታዊ ማንነቱ ን የጠበቀ፤ በእወቀትና በጥበብ ህይወቱን የሚመራ ፤ ምዕመንን እንደ አቅማችን ማብቃት ነው።
በተለያዩ በአለም ክፍል የምትኖሩ ኢትዮጵያውያን
በተለያዩ ምክንያቶች ተስፋ የቆረጣችሁ፤ በሃይማኖታዊ ጥያቄ የምትናጡ፤ የተለያዩ ቤተሰባዊ ሆነ ማህበረሰባዊ ቁርሾ ተጠቂ የሆናችሁ፤ በትዳራችሁ የምትፈተኑ፤ ክርስትናዊ ህይወትን ለመምራት መንገድ የጠፋባችሁ ...በተለያየ ችግር ያላችሁ ወገኖቻችን እግዘብሔር በፈቀደ ችግሮቻችሁን በማድመጥ አስፈላጊውን መፍትሄ በእኛም ሆነ እንዲሁም በተለያዩ አባቶቻችን አጋዢነት ችጎሮቻችሁን ለመስማት መፍትሄም ለመፈለግ ከጎናችሁ ነን።
ወገኖቻችን ኢትዮጵያውያን በውስጥ መስመር ባስቀመጥኩት ሊንክ ማግኘት ትችላላችሁ ።
@Nabuti21 ላይ እንገኛለን
