en
Feedback
ፈለገ ጥበባት +++

ፈለገ ጥበባት +++

Open in Telegram

+++የቀደምት ኢትዮጵያውያን ስልጣኔን ማሳየት እንዲሁም ገዳማት እና አድባራትን ማሳወቅ፡፡+++ የተረሱ አድባራትና ገዳማትን ማስታወስ ፤የ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያንን ጥበብ እውቀትን በምንችለው ሁሉ መመርመር የአባቶቻችን ልጆች በመሆን ትላንት በዛሬ እና በነገ ውስጥ ማስቀጠል ማስቻል ነው።

Show more
7 163
Subscribers
-524 hours
-267 days
-7330 days
Posts Archive
  '' እየኖሩ መሞት ወይስ እየሞቱ መኖር''!   አባ ሆይ ሰው ኖረ የሚባለው ምን ሲያደረግ ነው ? አልኳቸው ። ልቦናየን በእየለቱ ሰቅዞ ከሚይዘኝ መልስ ፍልጎ ካጣሁለት የህይወት ፍልስፍና አንዱን..መልስ ይሰጡኝ ዘንድ እየተማጸንኩ። በእርግና ምክኒያት ከተዳከሙ እና ከፈዘዙ አይኖቻቸው ባሻገር አስተወለው እየተመለከቱኝ ። በእውቀትና በጥበብ የታጨቀውን የአእምሮአቸውን በር ሊከፍቱ ሲዳዱ በሽበት የመላ  ጽሕማቸውን እና  የራሰቸውን ጠጉር ይዳስሳሉ። ሊቁ ሲኖዳ ከወረቅ የነጠረ ከልማዝ የከበረ ሃሳባቸውን ለማግኘት ደጂ ፀናት ያስፈልጋል ። አባ ሲኖዳ የራስ ጠጉራቸውና ጽሕማቸውን መነካካት ከጀመሩ እንደ ልብ ከማይገኘው ወቅያኖስ ከሆነው ከተቀበረው የእወቀት ማዕድናቸው እየዘገኑ በአንደበታቸው በኩል ገጸ በረከታቸውን ሊሰጡ እንደሆን አውቃለሁ።  የ አእምሮ ማህደራቸውን የእወቀት ከረጢቱን  የሚከፍተቱ ቁልፉ ከራስ ጠጉራቸውን  እና ከ ጢማቸው ጠጉር ያለ ይመስል.....። ለበርካታ ጊዜያት ከመናገር አንደበታቸው የተቆጠበ ታላቁ ሊቅ ሲኖዳን የአንደበታቸው በር ከከፈቱ የጥበብ ማር ከሚያዘንበው ከንፈራቸው እጂግ በሚያስደንቅ የእወቀት ሰረገላ ከ ጸርአርያም  እስከ በርባኖስ ያሉትን የአለም እንቆቅልሾች ይፈቱ ዘንዱ ይነቃሉ። አባት ሆይ ሰው መሆን ምንድን ነው ? ሰውስ ኖር የሚባለው ምን ሲያደርግ ነው?  ጎተራው በእልህ ስለሞላ? አቁማዳው ስላልጎደለ? ነግዶ ስላተረፈ? ሩጦ ስለቀደመ? ማዕዱ ሙሉ ስለሆነ? ገነዘብ በከረጢቱ ስለሞላ? ለአካሉ መልካም ጨረቅን ለኑሮው የተዋቡ ቤቶች ስላሉት?  ሰው ኖረ የሚባለው መቸ ነው?... እሱ ባልሰራው ደምግባት መመካቱ? ለዘላለም በማይጸና መነበር መሾሙ? በሰወች መከበቡ ?  ስለ እውነት ደስታ ምንድን ነው? ሰውስ ኖረ የሚባለው እንዴት ነው? ...አልኳቸው አረጋዊውን ሊቅ። እንደወትሮው የአንደበታቸውን በር እንዳይዘጉበኝ እየተማጸንኩ ..... ጽሕማቸውን እና የራስ ጠጉራቸውን መደባበስ ጀመሩ.....አይኖቸ ጠበቡ ጀሮወቸ ተከፈቱ ...ካቀረቀሩበት እየተቃኑ ...''ተመልከተው ዙሪያህን  እይ አለሙን'' !  አሉኝ ''እየበሉ የማይጠግቡ ጠጥተው የማይረኩ ለብሰው የተራቆቱ በተዋበ ህንጻ እየኖሩ በብረድና ቁር የሚሰቃዩ ፤ እያላቸው ያጡ፤ እየኖሩ የሞቱ፤  ቤታቸው ሙሉ ሁኖ  በጎደለ ድንኮን ውስጥ ከሚኖሩ ሰወች  ያነሰ ደስታ ያላቸው  ለምን ይመስልሃል? የሚያስፈልጋቸው ነገር ሁሉ ከበቂ በላይ ሳለ ጎደሎወቻቸው የበዙበት ምክኒያት  ስለምን ነው? ሳይደሰቱ የሚስቁ፤ ሳያጡ የሚቸገሩ ሰወች አለማችን ላይ  የበዙበት ምክኒያት ምንድን ነው? መኖራቸው ትርጉሜ ያጠባቸው ሞታቸውን የሚመኙ..   ያላቸውን ትተው የሌላቸውን ሲፈልጉ፤ የሚፈቀረውን  ጠልተው የሚጠላውን የሚያፈቅሩ፤ ያላቸወን ጥለው የሌላቸውን የሚያሳድዱ፤ ያሳደዱት ሲያገኙ፣ የነበራቸውን ያልነበራቸውን ያሳደዱትን ሁሉ ዋጋ የሚያጣባቸው፤ ስለምን ይመስልሃል...?  ልጀ ! እንደ ሰው ክቡር ሁኖ ተፈጥሮ እንደ እርያ መኖሩ ስለ ምን ይመስልሃል?  ስቀው የማይደሰቱ ፣አይተው የማያስተውሉ ፣ሰምተው የማያዳምጡት  አግኝተው በቃኝ የማይሉት ስለ ምን ይሆን? ፈልጎ ያገኘውን ስለምን ያጣዋል?  ወዶ ያፈቀረውን ስለምንስ ይጠላዋል? አንተ ከንቱ ሰው ዙሪህን ተመልከት ...የጎደላቸውን ሲያሳደዱ የሞላላቸውን የሚያጡ ሰወች ምን ባይገባቸው ነው? ህይወትን በጎደላቸው ልክ የሚመዝኑ ብኩኖች እንዴት ደስታን ያግኙ? ባላቸው ፣በሚያወቁት፣ በያዙት፣ ባገኙት፣ በሚኖሩበት ዛሬ ፣ ያልተደሰቱ በሌላቸው ፣በማያውቁት፣ ባልያዙት፣ ምኞት በሆነች ነገ  እንዴትስ ደስታ ይገኛል ?    ከስጋዊና ደማዊ ሃሳብ ውጭ  ረቂቅ እወቀትና ህይወት ጠቢባን የሚያጣጥሙት አለም እንዳለ ለማይረዳ ሆዱ አምላኩ ለሆነ ፍጡር  ደስታና እርካታ ከቁሳዊ ሃብት ማግኘትና ማጣት በዘለለ መለኪያ አይኖረውም... እንግዲያውስ ደስታ የሚገኘው..ሌሎች ሰዎች ያጡትን  የሚፈልጉትን ያለስስት መስጠች እጂን መዘርጋት የጠየቁህ እንዲያገኙ  ከረዳህ የምትፈልገውን ነገር ሁሉ ማግኘት ትችላለህ። ልጀ ሆይ አኔን ተመልከት እንደምታየኝ በደሳሳ ጎጆ ነው የምኖረው  የነተበ ጨረቅ ለብሸ ለእግሮቸ ጫማ ሳልሻ ደስት ሆነ መሶብ አንድም ቀን  ሳይኖረኝ  አለሁ   ግን ደስተኛ ነኝ አይኖቸ ብርሃንን ያያሉ.. ጀሮወቸ  ያደምጣሉ..እጆቸ ይዳስሳሉ...ልብና ኩላሊቶቸ በአግባብ ይሰራሉ መሽቶ ያነጋልኛል ...አውሎ ያስመሸኛል....ራሳችን እግዚአብሔር የሰጠኝ እልፍ ነው ስለምን እልፍ እያለኝ በጥቂቱ ደስታየን አጣለሁ?  ደስታ ራስህ ላይ  የተመሰረተ ነው ፤ አረቀህ አትቅበረው ሲሳካልህ ከጉድጓድ የምታወጣው ያለተሳካልህ ሲመስል አረቀህ የምትቀብረው አይደለም...   ደስታ ማለት የምታስበው፣ የምትናገረው እና የምትሰራው ነገር ሲስማማ ነው ...አእምሮህን መልካም ሃሳብ እንዲያፈልቅ ግራው ፤ አንደበትህ የተመጠነ በጥበብ የተዋጀ ይሁን፤ ስራህ በአእምሮ ያሰብከዎ በአንደበትህ የተናገርከው ይሁን ....እውነተኛ ደስታ ያኔ ታገኘዋለህ! ልብ በል ..ሰው ኖረ የሚባለው ለልቦናው ጥበብን ለአእምሮው እውቀትን ሲያገኝ ነው።'' አሉ ሊቁ ሲኖዳ ልጀ ሆይ  ብለው  አረጋዊው ሊቁ  ከተቀመጡበት  ከበርጩሜ ወንበራቸው ግራ ቀኝ አቀርቅረው እየተመለከቱ  በቀይ አፈር ከተለቀለቀችው አንስተኛ ጎጆ አንዳች ነገርን ይፈልጉ ይመስል። ''ልጀ ሆይ በእውነት ጥበብ አትጮህምን?. ማስተዋልስ ድምጽ አትሰጥምን? ከአዳም ልጆች አንድ ሚስጥር ተሰውሯል እሱም ጥበብ ናት ....ገንዘብ ላደረገው ሰው እውቀት የሕይወት ምንጭ ናት ። ሰው ኖረ የሚባለው ሕይወቱን በእውቀትና በጥበብ ሲያጸናት ነው። ያኔ የሰው ሕይወት ጎዳናው ያማረ የተዋበ ይሆናል ..ሰው ኖረ የሚባለው በእውቀትና በጥበብ መንገድ ሲጓዝ ነው።  ያኔ ሕይወትን ከስጋዊና ደማዊ ከቁሳካላዊ ሃሳብ ባሻገር በደስታ ትኖራታለህ..ያኔ ሰው ቢበላ ይጠግባል ቢጠጣ ይረካል ቢስቅ ይደሰታል....ቢሞት እንኳ ይኖራል!  ጥበብን ስትለብሳት ያኔ እየኖርክ መሞት እንጂ እየሞትክ አትኖርም!....አሉ ሊቁ ሲኖዳ  አናብርትና አናብስት ከሚርመሰመስበት ታላቁ ገዳም ከብዙሃኑ ተሰውረው... ካልታተመው መጽሐፍ የተቀነጨበ ! ሃሳብ አስተያየት @Nabuti21 ላይ አድርሱኝ።

ኢትዮጵያ መቸ ነጻ ትወጣለች? እንዴት ? በማን ?....... የሁላችንም ጥያቄ ነው? ሁላችንም መስማት የምንፈልገውን መልስ ነው...አባቶቻችን ሁላችንም ልናውቀው የሚገባ የመውጫ መንገድ ተናግረዋል..... በፈለገ ጥበባት ይዠላችሁ እመጣለሁ ! ጠብቁኝ!

ዶክተር አባ ፍቅር ... በተለያዩ  የአለም ክፍሎች  ትላላቅ ዮኒቨርትቲወች የተማሩ አለማቀፍ ከሆኑ  8 ቋንቋ በላይ የሚናገሩ አለምን ትተው ገዳም የገቡ በምናኔ የሚኖሩ መነኩሴው  ዶርክተሩ አባ ፍቅር ...የህይወት ውጣ ውረዳቸው ሊያካፍሉን ፤ ከ ቅንጡ ና  ከተዋቡ ከተሞች የኢትዮጵያ ዱር እና ገደልን ገዳማትን መረጠው እንዴት በምናኔ እንደኖሩ.. እጂግ ውብና ውድ ልብሶችን ትተው የወየበ አስኬማን አጥልቀው የተቆራፈደ የምንኩስና ልብስን የለበሱ .....ከህይወት ልምዳቸው ሊያካፍሉን ፤ በእወቀት ከካበተው ባህር ከሆነ ጥበባቸው ሊያጠጡን.......ፈቃዳቸው ሁኖ ቃለ መጠየቅ አድርገናል.....ለ እለተ ሰንበት ስጦታ አድርጌ አቀርብላችሁ አለሁ...... በፈለገ ጥበባት የዮቲብ ቻናል ይጠብቁን ..ላይክና ሳብስክራይብ በማድረግ ይከታተሉን!

በመላው አለም የምትኖሩ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን በሙሉ ሁላችንም ልናውቀው የሚገባ መልዕክት ነው። ምድር በቀራት ቀጣይ እድሜ በዘመናችን ምን ሊከሰት ይችላል?  ከምስራቅ የሚመጡ ነገስታት ...የኤፍራጥስ ወንዝ መድረቅ....የሃሳዊ መሲህ መምጣት..የአርማጌዶን ጦርነት ...ዘንዶው... እንሆ እንደ ሌባ ሆኘ እመጣለሁ ራቁቱን እንዳሄድ ርፍቱንም እንዳያዮ    ነቅቶ  ልብሱን የሚጠብቅ ብጽእ ነው ......ሙሉውን በዮቲብ ቻናላችን ገብታችሁ ተመልከቱ! 

ህይወት ጅረት ናት አንዳንዴ ጀርት በሆነች ህይወት መስመር ውሰጥ አባጣና ጎርባጣ ማግኘት ና ማጣት ፤ ከፍ ብሎ ኖሮ ዝቅ ማለት ፤ደስታና ሃዘን ...ሳቅና መራር ለቅሶ ..በሆነ ጊዜ ነጉስ ሁነን የኖረበት ምድር ፤  በሌላ ጊዜ ባርያ አድርጋ ቀንበሯን የጫነችብን  ሰወች አለን አይደል? ትላንት ሙሉ ተስፋ፣ ብርሃናዊ ኑሩ፣ ዛሬ ደግሞ በደቅድቅ ጨለማ ውስጥ የመኖር ያክል አለም ፊቷን ያዞረችብን አለን አይደል? በአደባባይ እየሳቅን በድንኳናችን ውስጥ ተወሽቀን የምናለቅስ፤ መኖር ከመሞታችን ጋር እኩል የሆነብን በተሰመረልን የምንጓዝ ፤ህይወት በመራችን ብኩን በሆነ ርምጃ  ፤ መዳረሻ በሌለው መነሻ የምንጓዝ ፤አለማው ላልታወቀ ሩጫ የምንሽቀዳደም ብዙወቹ አለን አይደል? በየ ጓዳችን ይህንን በመሰል የዢዋዢዌ ጨዋታ የምንናጥ ? በአመናቸው የተካድን፤ በወደድናቸው የተጠላን፤ ባከበርናቸው የተናቅን....ትዳር የእግር እሳት የሆነብን ፤ ልጆች ወልዶ ማሳዳግ የተሳነን፤ ኑሮአችን አልሞላልን ብሎ ቁርስን በልቶ ምሳ መድገም ቅንጦት የሆነብን ፤ እንደ አሽዋ ተበትነን የቤተሰብ ናፍቆት የሚያላውሰን ፤ ብዙ ሁነን አደገን  ብቻችን ቤት ታቀፍን በናፍቆት የምናለቅስ አለን አይደል?  የኢትዮጵያ ነገር አሳስቦን የምንቆዝም ...... በአንሶላና በትራሳችን እንባችን እየጠረግን   የማያጓጓውን ዛሬን፤  ሸከም የሆነብን  ነገን፤ እየፈራን የምንኖር አለን አይደል? ለጭንቀቶቻችን መፍትሔ፣ ለመከራችን መውጫ መንገድ፣  ጠፍቶን በሰው ተከበን ሰው ያጣን ከ አውላላ ሜዳ ላይ እንደ እንቦሳ ላም የምንቃትት አለን አይደል በየ መንደሩ?   አይዞህ ብሎ የሚበረታን ፤ ችግራችንን የሚጋራን ፤ሸክማችንን የሚሸከምልን፤ በእርምጃችን ልክ የሚጓዝ ፤ ህመማችን የሚያመው፤ ሳንነገርው የሚረ'ዳን ፤ሳንጠይቀው የሚሰጠን ሳንለምነው የሚመጸወተን .....ይህ ሁሉ ቀርቱ እህህህ በሎ የሚሰማን ጀሮ በማጣት ከ እበደት በረ ላይ የቆምን እንደ ሚያላዝን የለሊት ውሻ ፤እንደ ሚጮህ የቀትር ቁራ...የውስጥ ጩኸታችን የሚያደነቁርን የማንሸሸው ርግማን የሆነብን  .....አለን አይደል ከየጣሪያ ስር ከመጋረጃችን ጀርባ ተጠልለን ...... ከ አምላካችን ጋር የተኳርፍን፤ ለጸሎት ጥያቄወቻችን መልስ የላቸውም ብለን የደመደምን...ከኪዳኑ የራቅን፣ ከቅደሴው የሸሸን፣ የእጣኑ ሽታ ማዕዛው የጠፋብን ፣ ከሩቅ ቁመን የዕለት ጉርሱን እንደ አጣ ነዳይ ያቀረቀርን፣ አለን አይደል ብዙ ሁነን ጩኸታችንን ሊያሳብደን ዝምታችን ሊያፍነን የደረሰ..... አው ብዙ ነን .......የተጨነቀችን ነብስ፤ አድማጭ ያጣችን  አንደበት .....ጅሮ ሰጥቸ  ልሰማ...የምችለውን መፍትሔም ካለም ልሞክር  እኔ አለሁ ለወገኔ ብያለሁ.... @Nabuti21  ላይ ታገኙኛላችሁ!