en
Feedback
Apostolic church of Ethiopia, Bole Hermon Branch

Apostolic church of Ethiopia, Bole Hermon Branch

Open in Telegram

"፤ እስራኤል ሆይ፥ ስማ፤ አምላካችን እግዚአብሔር አንድ እግዚአብሔር ነው፤" (ኦሪት ዘዳግም 6: 4)

Show more
3 851
Subscribers
+724 hours
+577 days
+17630 days
Posts Archive
የተወደዳችሁ ቅዱሳን ሰላም ይብዛላችሁ። " ነገር ግን መንፈስ ቅዱስ በእናንተ ላይ በወረደ ጊዜ ኃይልን ትቀበላላችሁ፥ በኢየሩሳሌምም በይሁዳም ሁሉ በሰማርያም እስከ ምድር ዳርም ድረስ ምስክሮቼ ትሆናላችሁ ....." ሐዋ 1:8 የተቀበልነው መንፈስ ለተጠራንበት ሥራ ለወንጌል የሚለይ ነውና በዚህ መንፈስ ኃይል ወንጌልን ከኢየሩሳሌማችን ( ከአጥቢያችን ) ከቤተሰዎቻችን ጀምረን የክብሩን ወንጌል ብርሃን ለመመስከርና ለማወጅ :- ፊታችን እሁድ የወንጌል ቀን ስለሆነ፤ እንደተመካከርነው (ለወጣቶች ይድረሳችሁ) በኮንፈረንሱ ምክንያት ጎፋ ስለነበራችሁ እያንዳንዱ ሰው አንድ ነፍስ ይዞ እንዲመጣ ከጸሎት ጋር የመከሩን ጌታ ለምነናል! እኛም አምነናል። " ለምነኝ፥ አሕዛብን ለርስትህ የምድርንም ዳርቻ ለግዛትህ እሰጥሃለሁ። " መዝ 2:8 ጌታ ኢየሱስ ለብዙ ህዝብ ጉባኤ ያድርጋችሁ! ያፍራችሁ!! ተባረኩ!!! @ACEBoleHermon

የተወደዳችሁ ቅዱሳን ሰላም ይብዛላችሁ ። የእህት ሀና እሸቱ (የወ/ም አዲሱ ባለቤት) እናቷ ስላረፉ ቀብር ዛሬ (ቅዳሜ) ሲሆን ቦታዉ አዳማ ስለሆነ መድረስ የማትችሉ እየደወላችሁ እንድታፅናኗት በክርስቶስ ፍቅር እንጠይቃለን ። የእህት ሀና ስልክ ቁጥር  0912221233 የፍቅር ህብረት አስተባባሪዎች

የተወደዳችሁ ቅዱሳን በወጣቶች ኮንፈረንስ ምክንያት አዳር ጸሎት አይኖረንም። @ACEBoleHermon

📌 የተራራው ስብከት ክፍል 7 " ልበ ንጹሖች ብፁዓን ናቸው፥ እግዚአብሔርን ያዩታልና።" ማቴ 5:8 @ACEBoleHermon

ዛሬ ከጾም ጸሎቱም በኋላ ማታ የአዳር ጸሎቱም ይኖራል። @ACEBoleHermon

የተወደዳችሁ ቅዱሳን ሰላም ይብዛላችሁ ። " አደርግላቸው ዘንድ የእስራል ቤት ይሹኛል.." ህዝ36፥37 እንደሚል ይደረግን ዘንድ ፊቱን እንሻለን!! ከዛሬ ሰኞ ሐምሌ 20 ቀን ጀምሮ እስከ እሁድ ሐምሌ 26 ቀን የያዝነው ጾም ጸሎት ርዕስ እነሆ:- ➣ " ለሰልፍም ኃይልን ታስታጥቀኛለህ፤ በላዬ የቆሙትን በበታቼ ታስገዛቸዋለህ። " 2 ሳሙኤል 22:40 ከኃይል በታች በመሆናችን የሃይል መታጠቂያችን ስለተፈታ በጠላት ላይ የበላይ ልንሆን ሲገባን ገዢነት የእኛ ሊሆን ሲገባ ጠላት በላያችን እንዴት ይቆማል!ይሰለጥናል ! ብዙ ነገሮች በላያችን በረቱ! በቃ! እንበል!! ወደ ሃይላችን እንመለስ! የሃይል መታጠቂያችንን የምንታጠቅበት ሳምንት......... ነገር ግን መንፈስ ቅዱስ በእናንተ ላይ በወረደ ጊዜ ኃይልን ትቀበላላችሁ፥ ..." ሐዋ1፥8 መንፈስ ቅዱስ በሃይል ይውረድ!! በላያችን የቆመው ከእግራችን በታች ይረገጥ!! የጠላታችንን ከፍታ ያስረግጠን!!! " ሕዝቡንም እጅግ አበዛ፥ ከጠላቶቻቸውም ይልቅ አበረታቸው። " መዝ105:24 " በመንፈሴ እንጂ በኃይልና በብርታት አይደለም፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር። ዘካ4፥6 በመንፈስ ቅዱስ ኃይል እኛም ልጆቻችንም ከጠላቶቻችን ይልቅ የምንበረታበት ሳምንት!! " ደግሞ አንድ ሺህ ለካ ልሻገረውም የማልችለው ወንዝ ሆነ፤ ውኃውም ጥልቅ ነበረ፥ የሚዋኝበትም ውኃ ነበረ፤ ሰው ሊሻገረው የማይችለው ወንዝ ነበረ።" ህዝ47 ፥5 የመንፈሳዊ ህይወት ልካችንን.. በእኛ ሳይሆን በእርሱ ልክ እየለካ ወደ አየልን ልክ ያደርሰን ዘንድ ወደወንዙ ለመግባት እንደ ህዝቅኤል ፈቃደኛ እንሁን። ሰው ሊሻገረው (ስጋና ደም)ሊያልፈው ወደማይችለው ወንዝ ውስጥ ያጥልቀን!!! " በኋለኛው ዝናብ ጊዜ ከእግዚአብሔር ዘንድ ዝናቡን ለምኑ፤ እግዚአብሔር መብረቅ ያደርጋል.." ዘካ10፥1 " ስለዚህም ነገር ጾምን፥ ወደ እግዚአብሔርም ለመንን፤ እርሱም ተለመነን።" ዕዝ8፥23 @ACEBoleHermon

የተወደዳችሁ ወጣቶች ጸጋ ይብዛላችሁ ። ዛሬ የአርብ አዳር ጸሎት ስንመጡ ከተለመደው ሰአት ትንሽ ቀደም ብላችሁ ብትመጡልን ትንሽ የጽድቅ ስራ ስላለች ተባብረን እንሰራታለን ። ጌታ ኢየሱስ ይባርካችሁ ። @ACEBoleHermon

📌 የተራራው ስብከት ክፍል 6 " የሚምሩ ብፁዓን ናቸው፥ ይማራሉና።" ማቴ5፥7 @ACEBoleHermon