en
Feedback
የEiABC ግቢ ጉባኤ

የEiABC ግቢ ጉባኤ

Open in Telegram

ይህ የEiABC ግቢ ጉባኤ ኦፊሻል የቴሌግራም ቻነል ነው። በዚህ ቻነል የግቢ ጉባኤ መልክዕክቶች ሌሎችም ክርስትናችንን ሊያጠነክሩ የሚችሉ ትምህርቶች በቀጥታ ይተላለፋሉ። ቻነሉን ይቀላቀሉ። 👇👇👇👇👇👇👇 👉 @eggmk1984 👈 👉 @eggmk1984 👈 👆👆👆👆👆👆👆 ሀሳብ አስታያየት ካላችሁ @Eiabcgbigubae_bot @eiabcgebigubae

Show more
855
Subscribers
-324 hours
No data7 days
+1130 days
Posts Archive
❗️#ጾመ_ፍልሰታን_ለምን_እንፆማለን?❗️ ,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,, 👉ፆመ ፍልሰታ እንደ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ መሠረት ከሰባቱ የአዋጅ አፅዋማት መካከል አንዱ ሲሆን ጾመ ፍልሰታ ለማርያም ተብሎ ተወስኖ ይጾማል። #ፍልሰታ :- ፈለገ፣ ተሰደደ (ተገለጠ) ፣ መከፈት፣ መገለጥ፣ ከሚለው የግእዝ ስውር ቃል የተገኘ ሲሆን የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን ትንሳኤ ያመለክታል። 🌕የጾሙ ዋና ምክንያት ሐዋሪያት የእመቤታችንን የእረፍቷን ነገር አስመልክተው የጾሙት ፆም ነው። *ታሪኩን በአጭሩ እንዲህ እንመለከታለን :- 🌕እመቤታችን በጥር እሁድ በ21 ቀን አረፋለች ። ሐዋሪያት በአጎበር አድረገው ወደ ጌቴሴማኔ ይዘው ሲሄዱ አይሁድ ቀድሞ ልጇን ተነሳ አረገ እያሉ ሲያውኩን ኖረዋል። ዛሬ ደግሞ እሷን ተነሳች አረገች እያሉ ሊያውኩን አይደለምን ስለዚህ አስክሬኗን በእሳት እናቃጥላለን ብለው ተነሱ። 🌕ታውፋንያ የሚባል አይሁዳዊ ተራምዶ አጎበሯን ጨበጠው መልአኩ ሁለት እጁን ቆረጠው፣ እጁ ከአጎበሩ ተንጠጥሎ ቀረ ከዚህ በኃላ መላዕክት የእመቤታችንን አስክሬን ወስደው በገነት አኑረዋታል። 🌕በ8 ወሩ በነሐሴ ሐዋርያት አስከሬኗን እንደገና ከጌታ ተቀብለው በፀሎት እና በምህላ እሑድ ሥጋዋን ቀብረዋታል። ማስከኞ ተነስታለች። ከመትንሳኤ ወልድ/ እንደ ልጇ ትንሳኤ ያሰኘው ይህ ነው፡፡ በዚህ የቀብር ስነ ስርዓት ላይም ከ12 ቱ ሐዋርያት አንዱ ቅዱስ ቶማስ አልነበረም። 🌕ቅዱስ ቶማስም ደመና ጠቅሶ ከሀገረ ስብከቱ ሲመጣ ስታርግ አገኛት፣ ወፈቀደ ይደቅ እምደመናሁ/ ከሚጓዝበት የደመና ጉዞ ላይም ለመውደቅ ወደደ ተበጠበጠ፣ ቀድሞ የልጇን ትንሳኤ ሳላይ ቀረሁ ዛሬ ደግሞ ያንቺን ትንሳኤ ሳላይ ቀረሁ ብሎ፣ አይዞህ አትዘን ወንድሞችህ ሐዋርያት ትንሳኤዬን ዕረገቴን አላዩም አንተ አይተሀል ፣ ተነሳች አረገች ብለህ ንገራቸው ብላ ምልክት ይሆነው ዘንድ የያዘችውን ሰበን ሰጥታ ሰደደችው። 🌕 ከዚህ በኃላ ቶማስ የእመቤታችን ነገር እንደምን ሆነ ብሎ ሐዋርያትን ጠየቃቸው አግኝተን ቀበርናት አሉት፣ ሞት በጥር በነሐሴ መቃበር ተው ይሄ ነገር አይመስለኝም አላቸው። 🔷 ቅዱስ ጴጥሮስም አንተማ ልማድህ ነው ፣ አንተ ብቻ ተጠራጥር አትቀርም አንተ እየተጠረጠርክ ሰውን ሁሉ ስታጠራጥር ትኖራለህ አለው። 🌕እርሱም የያዘውን ያውቃልና ፀጥ ብሎ ይሰማቸዋል። ከዚህ በኃላ ጴጥሮስ ተቆጥቶ ሂዶ መቃብሩን ቢከፈተው አጣት፣ ደንግጦ ቆመ፤  አታምኑኝም ብዬ ነው እንጂ እመቤታችን ተነሰታለች፣ አረጋለች አላቸው  የያዘውን ሰበን ሰጥቶአቸው ለበረከት ተከፋፍለው ወደ ሀገረ ስብከታቸው ተበታትነዋል። 🌕 በዚህ ምክንያት በአመቱ ቶማስ ትንሳኤሽን፣ ዕረገትሽን አይቶ እኛ ሳናይ ብለው ቅዱሳን ሐዋሪያት ነሐሴ 1 ሱባኤ ጀመሩ  ሱባኤ በጀመሩ በ14 ተኛው ቀን  ትኩስ በድን አድርጎ ሰጣቸው ከቀበሯትም በኃላ በነሐሴ 16 ቀን በክብር ተነስታለች። 🔵 በዚህ ቀን ጌታችን መድሐኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቀድሶ እመቤታችንም ከልጇ እጅ ቆርባለች። ከዚህ ጊዜ ጀምሮ የሐዋርያት ቤተ ክርስቲያን የእመቤታችንን በረከት ለማግኘት ይህቺ ጊዜ ትፆማለች።   ✨✨ እኛም ከእናታችን ከቅድስት ኪዳነ ምህረት በሱባኤውና በፆሙ ስንጠነክር የእሷ አማላጀነት የልጇ የመድሐኔዓለም ቸረነት ከመከራ ስጋና ከመከራ ነፍስ አድኖ ለንሰሀ ጥሪ እንደሚያበቃንና ቅዱስ ስጋውን እና ደሙን ለመቀበል እንደሚፈቅድልን አምነን ልንጾምና ልንጸልይ ይገባናል ።✨✨ ፨፨፨ ወስብሐት_ለእግዚአብሔር ፨፨

በንስሓ እና በቅዱስ ቁርባን ዙሪያ  ያልተመለሱላችሁ ጥያቄዎች ካሉ ከታች ያለውን የGoogle Form ሊንክ በመጫን መጠየቅ ትችላላችሁ። በሚቀጥሉት ክፍሎች ምላሽ የምንሰጥባቸው ይሆናል፦ https://forms.gle/NwDShgbgz77xjbMb8

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ። አሜን!❖ ኃጢአትን ለንስሓ አባት መናዘዝ ለምን አስፈለገ? ☞ ስልጣነ ክህነት የማሰር የመፍታት ስልጣን ከእግዚአብሔር ስለተሰጣቸው፡፡
"እውነት እላችኋለው በምድር የምታስሩት ሁሉ በሰማይ የታሰረ ይሆናል፡በምድርም የምትፈቱት ሁሉ በሰማይ የተፈታ ይሆናል" ማቴ.፲፰፥፲፰
☞ ራሱ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያዘዘው ትዕዛዝ ስለሆነ፡፡
"ሄደህ ራስህን ለካህን አሳይ፡ ለእነርሱም ምስክር እንዲሆን ስለመንጻትህ ሙሴ እንዳዘዘ መሥዋዕት አቅርብ አለው"ሉቃ.፭፥፲፬
☞ ኑዛዜ ማድረግ በመጽሐፍ ስለታዘዘ
"ከእነዚህ ነገሮች በአንዲቱ በደለኛ ቢሆን የሠራው ኃጢአት ይናዘዛል፡ስለሠራው ኃጢአት ለእግዚአብሔር የበደልን መስዋዕት ያመጣል.....ካህኑ ስለኃጢአቱ ያስተሰርይለታል....እርሱም ይቅር ይባላል"፡፡ዘሌ.፭፥፭-፮፣፲
☞ ከእኛ ይልቅ ለእግዚአብሔር ቅርብ ስለሆኑ ዕለት ዕለት እግዚአብሔርን በቅዳሴው ስለሚያመሰግኑ ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን በየቀኑ እየፈተቱ ስለ እኛ ኃጢአት ይቅር እንዲለን ስለሚለምኑ፡፡ ከኃጢአት እና ከበደል ያነጻን ዘንድ ንስሐን የሠራልን አምላካችን እግዚአብሔር ይመስገን ። እንደሚታወቀው ከሐምሌ ፳፩ አንስቶ የግቢ ጉባኤያችን የንስሐ ወር በይፋ ተጀምሯል። "እስካሁን የንስሐ አባት የሌለን አባት በመያዝ፣ ያለን ደግሞ ወደ አባቶቻችን በመቅረብና በመናዘዝ ሕይወታችንን እናድስ።" ማንኛውንም ጥያቄ ካላችሁ እኛን ማግኘት ትችላላችሁ፦ 👉 ሙሉነህ አበበ 0915852875  | @mule_yemariam_lij 👉 አቤል ይልማ 0910212621 | @Bell_1221 ❖ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር። አሜን!-ይቆየን❖ ንስሐ ንዑስ ክፍል EIABC ግቢ ጉባኤ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን !!! ሐምሌ ፴ (30) ቀን ስንክሳር 👉እዚህ ይጫኑ👈 የEiABC ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል

📢 ልትቀላቀሏቸው የሚገቡ የግቢ ጉባኤያችን ቻናሎች እና ግሩፖች 1️⃣ 📡 የግቢ ጉባኤያችን Official Channel 🔗 https://t.me/eggmk1984 2️⃣ 📚 የግቢ ጉባኤያችን ላይብረሪ 🔗 https://t.me/+VY4V0eZS1bnkggrC 3️⃣ 🎓 ናታኒም 🔗 https://t.me/gibigubae712 4️⃣ 👨‍🎓 የአብነት ተማሪዎች ግሩፕ 🔗 https://t.me/+M3aOnphiNCwzMDQ0 5️⃣ 🎵 የመዝሙር ጥናት ግሩፕ 🔗 https://t.me/+eKW2dF9KR-R-ctKC 6️⃣ 🌧 ክረምትን በአብነት 🔗 https://t.me/+Lt5Ryl0T0R0xMDhk

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን !!! ሐምሌ ፳፱ (29) ቀን ስንክሳር 👉እዚህ ይጫኑ👈 የEiABC ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል

🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔 አለሁ በወሬ ተመልሷል!!! በህብረት ሆነን አዋጥተን የግቢ ጉባኤያችንን አገልግሎት ተደራሽነት እናሳደግ የክፍያ ጥቅሎች - ካህናተ ሰማይ: 24 ብር - ናታን:
🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔           አለሁ በወሬ ተመልሷል!!! በህብረት ሆነን አዋጥተን የግቢ ጉባኤያችንን አገልግሎት ተደራሽነት እናሳደግ የክፍያ ጥቅሎች - ካህናተ ሰማይ: 24 ብር - ናታን: 50 ብር - ሰአሊ ለነ ቅድስት: 64 ብር - አዳም: 100 - ዳዊት: 150 ብር -ኤፌሶን:200 ብር - ነፃ ፈቃድ: የፈለጉትን ያህል ▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰ 1000691195458  Aschale and Hasset and Ergete ላይ መላክ ይችላሉ ። ከፍለው ከጨረሱ በኋላ screenshot በሚከተሉት ግሩፖች በመላክ ተባበሩን -ካህናተ ሰማይ: @kahinatesemayEiABC - ናታን: @natanEIABC - ሰአሊ ለነ ቅድስት: @sealilenekidistEiABC - አዳም: @adamEiABC - ዳዊት: @mezmuredawitEiABC -ኤፌሶን:@ephesonEiABc - ነፃ ፈቃድ: @netsafikadEiABC 📩 ሐሳብ ፣ መልእክት ፣ ጥያቄ እንዲሁም አዲስ መመዝገብ ከፈለጋቹ ከፈለጋቹ  @ @Yilililili1@suz26@Emoojji  ላይ ብትልኩልን ይርሰናል፡፡               ሠናይ ቀን !!!

🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔           አለሁ በወሬ ተመልሷል!!! በህብረት ሆነን አዋጥተን የግቢ ጉባኤያችንን አገልግሎት ተደራሽነት እናሳደግ የክፍያ ጥቅሎች - ካህናተ ሰማይ: 24 ብር - ናታን: 50 ብር - ሰአሊ ለነ ቅድስት: 64 ብር - አዳም: 100 - ዳዊት: 150 ብር -ኤፌሶን:200 ብር - ነፃ ፈቃድ: የፈለጉትን ያህል ▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰ 1000691195458  Aschale and Hasset and Ergete ላይ መላክ ይችላሉ ። ከፍለው ከጨረሱ በኋላ screenshot በሚከተሉት ግሩፖች በመላክ ተባበሩን -ካህናተ ሰማይ: @kahinatesemayEiABC - ናታን: @natanEIABC - ሰአሊ ለነ ቅድስት: @sealilenekidistEiABC - አዳም: @adamEiABC - ዳዊት: @mezmuredawitEiABC -ኤፌሶን:@ephesonEiABc - ነፃ ፈቃድ: @netsafikadEiABC 📩 ሐሳብ ፣ መልእክት ፣ ጥያቄ እንዲሁም አዲስ መመዝገብ ከፈለጋቹ ከፈለጋቹ  @ @Yilililili1@suz26@Emoojji  ላይ ብትልኩልን ይርሰናል፡፡               ሠናይ ቀን !!!

በሕይወትህ ስኬትን ለማግኘት ፈጣን አቋራጭ መንገድ ለመፈለግ አትጣድፍ። እውነተኛ ስኬት የሚገኘው በዕለት ተዕለት ትጋት: በትዕግስትና በንጹሕ ላብ ነው።                         ሊቁ አውግስጢኖስ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ። አሜን !! "ስለ ኃጢአትህ ንሰሓ መግባትን አትፍራ" ፨ንስሓ ማለት አንድ ሰው በሠራው ጥፋት፣ባደረገው ስህተት፣በፈጸመው ኃጢአት ማዘኑና መቆርቆሩን፣መፀፀቱን ዳግመኛም ያንን የመሰለ ኃጢአት ላለማድረግ የሚወሰነው ውሣኔ ነው፡፡
የንስሓ ቅድመ ዝግጅቶች ምንላቸው ምን ምን ናቸው?
💠በአጥቢያችን ከሚገኝ ቤተ ክርስቲያን አበ ነፍስ (የንስሓ አባት) መያዝ 💠የሠራነውን ኃጢአት ማመን 💠በሠራነው ኃጢአት ከልብ አብዝተን መቆርቆር መፀፀት ማዘንና ማልቀስ ይቅር እንዲለን በትህትና ራስን በማዋረድ መጠየቅ 💠በንስሓ ውስጥ መኖር የሚያሰጣቸውን የህሊና እረፍትና በረከት መገንዘብ 💠ከእኛ ኃጢአት ይልቅ የእግዚአብሔር ቸርነትና ይቅር ባይነት እንደሚበልጥ እና ይቅር እንደሚለን ያለጥርጥር ፍጹም ማመን 💠ወደ አበ ነፍሳችን ሄደን ንስሐ ለመግባት እና ቀኖናችንን ለመቀበል ማሰብ እና መወሰን 💠ከልጅነት እስከ ዕውቀት የሠራናቸውን ኃጢአቶች ማስታወስ ከተቻለም ለማስታወስ ይረዳን ዘንድ በጽሑፍ መያዝ 💠ዳግም ወደ ሠራነው ኃጢአት እንደማንመለስ ለራሳችን ቃል መግባትና መወሰን፣ኃጢአትን መጸየፍ 💠ወደ አበ ነፍሳችን ሄደን የሰራነውን ኃጢአት በሙሉ አንድም ሳያስቀሩ በዝርዝር መናዘዝ 💠የሚሰጠንን ቀኖና በትክክል መተግበር (መፈጸም) 💠ዳግም ወደ ኃጢአት እንዳንመለስ ራሳችንን በቃለ እግዚአብሔር ማነጽ ከኃጢአት እና ከበደል ያነጻን ዘንድ ንስሐን የሠራልን አምላካችን እግዚአብሔር ይመስገን ። እንደሚታወቀው ከሐምሌ ፳፩ አንስቶ የግቢ ጉባኤያችን የንስሓ ወር በይፋ ተጀምሯል። "እስካሁን የንስሓ አባት የሌለን አባት በመያዝ፣ ያለን ደግሞ ወደ አባቶቻችን በመቅረብና በመናዘዝ ሕይወታችንን እናድስ።" ማንኛውንም ጥያቄ ካላችሁ እኛን ማግኘት ትችላላችሁ፦ 👉 ሙሉነህ አበበ 0915852875  | @mule_yemariam_lij 👉 አቤል ይልማ 0910212621 | @Bell_1221 ❖ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር። አሜን!-ይቆየን❖ ንስሓ ንዑስ ክፍል EIABC ግቢ ጉባኤ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን !!! ሐምሌ ፳፰ (28) ቀን ስንክሳር 👉እዚህ ይጫኑ👈 የEiABC ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን !!! ሐምሌ ፳፯ (27) ቀን ስንክሳር 👉እዚህ ይጫኑ👈 የEiABC ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል

እውነተኛው ክርስትና "እኔ" ሳይሆን "እኛ" እያሉ የሚኖሩት ሕይወት ነው። ክርስትናም ፍቅር ነው። እንደ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ እንደነ ቅዱስ ባስልዮስ የድሆች ቁስል ከተሰማህ ረሃባቸው ከራበህ አንተ ክርስትያን ነህ። እስከ መስዋዕትነት ለመድረስ ከችግረኞች ጎን ከቆምክ የሚያስፈልግህ ሁሉ የሚያስፈልጋቸው መሆኑን ካመንክ እውነተኛ የክርስቶስ ተከታይ ነህ፡፡ #አቡነ_ሺኖዳ_lll

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን !!! ሐምሌ ፳፮ (26) ቀን ስንክሳር 👉እዚህ ይጫኑ👈 የEiABC ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል

"የእግዚአብሔር ቃል ሕያውና የሚሠራ ነው፤ ከሁለት አፍ ካለው ሰይፍ ሁሉ ይልቅ የተሳለ ነው።" ዕብራውያን 4፥12 ሰላም የእግዚአብሔር ቤተሰቦች! ✨ በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የአብነት ትምህርት ሊጀም
"የእግዚአብሔር ቃል ሕያውና የሚሠራ ነው፤ ከሁለት አፍ ካለው ሰይፍ ሁሉ ይልቅ የተሳለ ነው።" ዕብራውያን 4፥12 ሰላም የእግዚአብሔር ቤተሰቦች! ✨ በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የአብነት ትምህርት ሊጀምር ቀናቶች ብቻ ቀርተውታል። እናንተም ይህንን የቃለ እግዚአብሔር ማዕድ ትሳተፉ ዘንድ ተጋብዛችኋል። 🙏📚 የሚጀምርበት ቀን: ረቡዕ ሐምሌ 29 🗓️ ሰዓት: ማታ ከ2:00 ጀምሮ ⏰ ለመመዝገብ +251951052882  @kiremtnbeabnet +251900048575 @mia0925 የመማሪያ ግሩፕ ይቀላቀሉ https://t.me/+s6vpk4Q7NOs4NDNk

"የእግዚአብሔር ቃል ሕያውና የሚሠራ ነው፤ ከሁለት አፍ ካለው ሰይፍ ሁሉ ይልቅ የተሳለ ነው።" ዕብራውያን 4፥12 ሰላም የእግዚአብሔር ቤተሰቦች! ✨ በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የአብነት ትምህርት ሊጀምር ቀናቶች ብቻ ቀርተውታል። እናንተም ይህንን የቃለ እግዚአብሔር ማዕድ ትሳተፉ ዘንድ ተጋብዛችኋል። 🙏📚 የሚጀምርበት ቀን: ረቡዕ ሐምሌ 29 🗓️ ሰዓት: ማታ ከ2:00 ጀምሮ ⏰ ለመመዝገብ +251951052882  @kiremtnbeabnet +251900048575 @mia0925 የመማሪያ ግሩፕ ይቀላቀሉ https://t.me/+s6vpk4Q7NOs4NDNk

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን !!! ሐምሌ ፳፭ (25) ቀን ስንክሳር 👉እዚህ ይጫኑ👈 የEiABC ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ። አሜን !! 1. ንስሓ ማለት ምን ማለት ነው? ☞ ንስሓ ማለት፦ "ነስሐ" ከሚል የግዕዝ ግስ የወጣ ቃል ነው፡፡ የቃሉ ፍች ሐዘን፣ ፀፀት፣ ቁጭት፣ ምላሽ፣ መቀጮ፣ ቅጣት፣ ቀኖና፣ የኃጢአት ካሣ ማለት ነው፡፡ ንስሓ ማለት ደግሞ አንድ ሰው በሠራው ጥፋት፣ባደረገው ስህተት፣በፈጸመው ኃጢአት ማዘኑና መቆርቆሩን፣መፀፀቱን ዳግመኛም ያንን የመሰለ ኃጢአት ላለማድረግ የሚወሰነው ውሣኔ ነው፡፡ • በሰዎች ሕይወት ውስጥ ደግሞ ንስሓ የሚከተሉትን ፍቺዎችን ይዞ እናገኘዋለን፡፡ ❖ ንስሓ ወደ እግዚአብሔር መመለስ ነው፡፡ ❖ ንስሓ ከእግዚአብሔር ጋር መታረቅ ነው፡፡ ❖ ንስሓ ከኃጢአት እንቅልፍ መንቃት ነው፡፡ ❖ ንሰሓ ወደ መንፈሳዊ ሕይወት መመለስ ነው፡፡ ❖ ንስሓ ከእግዚአብሔር የሚሰጥ እግዚአብሔርን የሚያስወድድ ከንጹሕ ልብ የሚመነጭ ጸጋ ነው፡፡ ❖ ንስሓ ከኃጢአትና ከዲያብሎስ ባርነት ነፃ መውጣት ነው፡፡ ❖  ንስሓ ስለእግዚአብሔር ፍቅርና ስለ ቅድስና ብሎ ኃጢአትን መተው ነው፡፡ ❖ ንስሓ  ወደ መንግሥተ እግዚአብሔር የሚያስገባ ቁልፍ ነው፡፡ ❖ ንስሓ የመንግሥተ ሰማያት መግቢያ በር ነው፡፡ ከኃጢአት እና ከበደል ያነጻን ዘንድ ንስሐን የሠራልን አምላካችን እግዚአብሔር ይመስገን ። እንደሚታወቀው ከሐምሌ ፳፩ አንስቶ የግቢ ጉባኤያችን የንስሓ ወር በይፋ ተጀምሯል። "እስካሁን የንስሓ አባት የሌለን አባት በመያዝ፣ ያለን ደግሞ ወደ አባቶቻችን በመቅረብና በመናዘዝ ሕይወታችንን እናድስ።" ማንኛውንም ጥያቄ ካላችሁ እኛን ማግኘት ትችላላችሁ፦ 👉 ሙሉነህ አበበ 0915852875  | @mule_yemariam_lij 👉 አቤል ይልማ 0910212621 | @Bell_1221 ❖ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር። አሜን!-ይቆየን❖ ንስሓ ንዑስ ክፍል EIABC ግቢ ጉባኤ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን !!! ሐምሌ ፳፬ (24) ቀን ስንክሳር 👉እዚህ ይጫኑ👈 የEiABC ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል