Prosperity Party - ብልፅግና
Open in Telegram
This is an official telegram channel of prosperity party.
Show moreEthiopia4 794The category is not specified
5 357
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 16ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ
=====
ጥር 6 ቀን 2015 ዓ.ም
አዲስ አበባ
16ኛ መደበኛ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ ውሳኔዎች
የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 16ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ።
1. ምክር ቤቱ በቅድሚያ የተወያየው ለሁለተኛው ምዕራፍ የዘላቂ መሬት አያያዝ ፕሮጀክት ማስፈጸሚያ የሚውል ከዓለም ዐቀፍ የልማት ማህበር ጋር የተደረገ 107,174,255.00 (መቶ ሰባት ሚሊዮን አንድ መቶ ሰባ አራት ሺ ሁለት መቶ አምሳ አምስት) የአሜሪካ ዶላር የብድር ስምምነት ላይ ነው፡፡ ብድሩም የአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ ለመገንባት እና የመሬት ምርታማነትን በማሳደግ የአርሶ አደሩን ገቢና አኗኗር ለማሻሻል መንግስት የሚያደርገውን ጥረት የሚደግፍ፤ ወለድ የማይታሰብበት እና በ40 ዓመታት ተከፍሎ የሚያልቅ መሆኑ ከአገሪቱ የብድር ፖሊሲ ጋር የሚጣጣም መሆኑን በማረጋገጥ ምክር ቤቱ ስምምነቱን በሙሉ ድምጽ በማጽደቅ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ ወስኗል፡፡
2. በመቀጠል ምክር ቤቱ የተወያየው የኤክሳይዝ ታክስ አዋጅን ለማሻሻል በቀረበ ረቂቅ አዋጅ ላይ ነው፡፡ ከየካቲት 2012 ጀምሮ ስራ ላይ በዋለው የኤክሳስ ታክስ አዋጅ ያስገኘውን ጠቀሜታ እንዲሁም የታዩትን ክፍተቶች በመገምገም በአንዳንድ ምርቶች ላይ የተጣለውን የማስከፈያ ምጣኔ ማስተካከል ተገቢ ሆኖ በመገኘቱ የአዋጁ ማሻሻያ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በቀረበው ረቂቅ የማሻሻያ አዋጅ ላይ ከተወያየ በኋላ ግብዓቶችን በማከል ወደ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡
3. በመቀጠል ምክር ቤቱ የተወያየው የአርማወር ሐንሰን የምርምር ኢንስቲትዩትን ለማቋቋም በቀረበው ረቂቅ ደንብ ላይ ነው፡፡ የኢንስቲትዩቱን ተግባርና ኃላፊነት ግልጽ ማድረግ፣ እያከናወነ ያለውን የምርምር ምህዳር በሌሎች የጤና ምርምር ስራዎች አስፍቶ እንዲሰራ ለማስቻል፣ ቅንጅትን የሚያጎለብት፣ ብክነትን የሚቀንስና ውጤታማነትን የሚያበረታታ አደረጃጀት እንዲኖረው የሚያስችል ረቂቅ ደንብ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ ደንቡ ላይ በስፋት ተወያይቶ ግብአቶችን በማከል በሙሉ ድምጽ ያጸደቀ ሲሆን ደንቡ በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ስራ ላይ እንዲውል ወስኗል፡፡
4. ምክር ቤቱ በመቀጠል የተወያየው የኢትዮጵያ የደም እና ቲሹ ባንክ አገልግሎትን ለማቋቋም በቀረበው ረቂቅ ደንብ ላይ ነው፡፡ ቀደም ሲል ብሄራዊ የደም ባንክ ይሰጥ የነበረውን አገልግሎት በማስፋት የደም ተዋፅኦዎችን፣ ሪኤጀንቶችን እና የደም ውሃ በአገር ውስጥ ማምረት እንዲሁም የቲሹ (ህብረ-ህዋስ) ንቅለ ተከላ ህክምና አገልግሎትን የመደገፍ፣ የህብረ-ህዋስ ለጋሾችን የማስተባበር እና ተያያዥ ተግባራትን እንዲያከናውን የሚያስችል ስልጣን ያለው ተቋም በማስፈለጉ ረቂቅ ደንብ ተዘጋጅቶ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ ደንቡ ላይ በስፋት ተወያይቶ ግብአቶችን በማከል በሙሉ ድምጽ ያጸደቀ ሲሆን ደንቡ በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ስራ ላይ እንዲውል ወስኗል፡፡
5. ሌላው ምክር ቤቱ የተወያየበት አጀንዳ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩትን ለማቋቋም የቀረበው ረቂቅ ደንብ ነው፡፡ የህብረተሰብ ጤና አደጋዎችን አስቀድሞ የመተንበይ፣ የመከላከል እና ምላሽ የመስጠት ውጤታማ ስርዓት መዘርጋት በማስፈለጉ፤ የሀገሪቱ የጤና ላቦራቶሪ ዘርፍ ለህብረተሰብ ጤና ክብካቤ፣ ህክምና እንዲሁም ለስርዓተ ምግብ ምርምሮች ጥራቱን የጠበቀ አገልግሎት እንዲሰጥ ማስቻል የሚገባ በመሆኑ፤ የማህበረሰብ ጤና ፖሊሲና ስትራቴጂዎችን አፈፃፀም በጥልቀት የሚከታተልና የሚገመግም ተቋም በማስፈለጉ ረቂቅ ደንብ ተዘጋጅቶ ለምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ ደንቡ ላይ በስፋት ተወያይቶ ግብአቶችን በማከል በሙሉ ድምጽ ያጸደቀ ሲሆን ደንቡ በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ስራ ላይ እንዲውል ወስኗል፡፡
6. በመቀጠል ምክር ቤቱ የተወያየው የኢትዮጵያ የምግብ እና የመድኃኒት ባለስልጣንን አደረጃጀት፣ ሥልጣንና ተግባር ለመወሰን በቀረበው ረቂቅ ደንብ ላይ ነው፡፡ የምግብ፣ የመድኃኒት፣ የህክምና መሣሪያ፣ የባህላዊ መድኃኒት፣ የትምባሆ እና ተያያዥ ምርቶችን አመራረት፣ ዝውውር፣ አቅርቦት እና አጠቃቀምን በሚመለከት የቁጥጥር እና ክትትል ስርዓት መዘርጋት፣ የቁጥጥር ተግባሩን ለማከናወን አስፈላጊ የሆኑ ላቦራቶሪዎችን የማደራጀት፣ ህገ ወጥ ተግባራት ሲፈጸሙም ተገቢውን እርምጃ የሚወስድ እንደሁም ቁጥጥር የሚደረግባቸው ምርቶች አመራረትና አጠቃቀም በአለም አቀፍ ስታንዳርዶች መሰረት መከናወናቸውን የሚያረጋግጥና የሚያስፈጽም ስልጣን እና አደረጃጀት ባለስልጣኑ እንዲኖረው የሚያስችል ረቂቅ ደንብ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ ደንቡ ላይ በስፋት ተወያይቶ ግብአቶችን በማከል በሙሉ ድምጽ ያጸደቀ ሲሆን ደንቡ በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ስራ ላይ እንዲውል ወስኗል፡፡
7. በመጨረሻም ምክር ቤቱ የተወያየው ከቱርክ ሪፐብሊክ እና ከተባበሩት አረብ ኤምሬቶች መንግስታት ጋር በወንጀል የሚፈለጉ ግለሰቦችን አሳልፎ የመስጠት እና በወንጀል ጉዳዮች የጋራ የህግ ትብብር ለማድረግ በተፈረሙ የሁለትዮሽ ስምምነቶች ላይ ነው፡፡ በወንጀል የሚፈለጉ ሰዎችን አሳልፎ የመስጠት የሁለትዮሽ ስምምነቶቹ በወንጀል ጉዳይ የሚፈለጉ ግለሰቦችን አሳልፎ በመስጠት ረገድ ለሚደረገው የሁለትዮሽ ትብብር የሕግ ማዕቀፍን የሚፈጥሩ ከመሆኑም በላይ በተዋዋይ ሃገራት የህግ የበላይነት መረጋገጥ ፋይዳቸው የጎላ ነው፡፡ በወንጀል ጉዳዮች የጋራ የፍትህ ትብብር ስምምነቶቹም በተደራጁ፣ ድንበር ዘለል በሆኑ እንዲሁም በሁለቱ ሀገራት ግዛቶች ውስጥ የሚፈጸሙ ወንጀሎችን አስመልክቶ በሚከናወኑ የምርመራ፣ የክስና የፍርድ ሂደቶች መረጃዎችንና ማስረጃዎችን ለመለዋወጥ እንዲሁም የወንጀል ፍሬዎችን ዝውውር በመግታት ረገድ ፋይዳቸው የላቀ የትብብር የሕግ ማዕቀፎች በመሆናቸው የሁለትዮሽ ስምምነቶቹ ለምክር ቤቱ ቀርበዋል፡፡ ምክር ቤቱም በቀረቡት የሁለትዮሽ ስምምነቶች ላይ በጥልቀት ከተወያየ በኋላ ይጸድቁ ዘንድ ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፉ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡
//
#PMOEthiopia
"ኃላፊነት የጎደላቸው አካላት ለአደገኛ የፖለቲካ አጀንዳ ሲባል
እየፈጠሯቸው የሚገኙ መሠረተ ቢስ ውንጀላዎችን ኢትዮጵያ ታወግዛለች!!" - የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
በምዕራባውያን የተለያዩ አካላት አማካኝነት በኢትዮጵያ ላይ የሚነዙ የሐሰት ስም ማጥፋቶችን የኢትዮጵያ መንግሥት ፈጽሞ አይታገሥም።
እነዚህ አካላት ኢትዮጵያ ውስጥ የከፉ ወንጀሎች ሊፈጸሙ ይችላሉ በሚል የሕወሐትን ጊዜ ያለፈበት ፕሮፓጋንዳ እንደ በቀቀንመድገማቸው አሳፋሪ ነው።
እነዚህ አካላት የሚከሱት ፍንጮችን ወይም ተጨባጭ ክስተቶችን መሠረት አድርገውአይደለም፤ የመፈጸም ዕድል አለ በሚል ያልተጨበጠ ግምት እንጂ።
እጅግ የሚያሳዝነው ደግሞ የተሻለ ስም ያላቸው ተቋማት ሳይቀሩ ይሄንን በኢትዮጵያ ላይ ተቀነባብሮ የሚለቀቅ ፕሮፓጋንዳ ለመቃወም አለመቻላቸው ነው።
ጥቂቶቹም ስለ ኢትዮጵያ የተነገረውን ስምማጥፋት በማመን ሳይሞኙ እንዳልቀሩ ይገመታል። አንዳንዶችም እነዚህን የሐሰት ክሶች ኢትዮጽያን ለማንበርከክ ሊጠቀሙባቸው ይፈልጋሉ።
ይሄን መሰል አስደንጋጭ ክሶችን አቅርቦ የኢትዮጵያ መንግሥትን በማስጨነቅ በሕወሐት ላይ እየወሰደ ያለውን የመከላከል ርምጃ ለማስቀየስ የሚችሉ መስሏቸው ከሆነ ተሳስተዋል።
አንዳንዶችም የሚችሉትን ሁሉ በማድረግ ይህንን ቡድን ለማዳን እየተረባረቡ ነው። አንዳንድ ምዕራባውያን ባለ ሥልጣናት ጭምር ይሄንን የሐሰት ክስ የሚነዙት ኢትዮጵያ ትእዛዛቸውን አልቀበል ስላለቻቸው መሆኑን በይፋ መናገር ጀምረዋል። ይህ ጊዜ አመጣሽ የሐሰት ክስ መሬት ላይ ያለውን እውነታ ጨርሶ አይቀይረውም።
እነዚህ ጉምቱ ተቋማትና ወሳኝ ተዋንያን፣ በቂ ግንዛቤ ሳይኖራቸው በዚህ የሃሰት ዘመቻ እየተሳተፉ ይገኛሉ። ይሄን የመሰሉ የከፉና ሊወገዙ የሚገባቸው ውንጀላዎች ለፖለቲካ ዓላማ መዋላቸው ኃላፊነት የጎደለውና አሳፋሪ ነው።
ይህን ለመሰለው አደገኛ ስም ማጥፋት ምላሽ ሳይሰጡ ታግሦ ማለፍ የሚቻል ባለመሆኑ በከፋ መልኩ በኢትዮጵያ ላይ ያልተረጋገጡና ፖለቲካዊ ዓላማ ያላቸውን ውንጀላዎች ከሚያቀርቡ ከአንዳንድሀገራትናተቋማት ጋር ያለውን ግንኙነት የኢትዮጵያ መንግሥት መልሶ እንዲያጤን ተገድዷል።
የኢትዮጵያ መንግሥት ከመነሻውም በግልፅ እንዳስታወቀው በአፍሪካ ኅብረት በኩል እየተደረገ ላለው የሰላም ንግግር ቁርጠኛ ነው።
ምክንያቱም ግጭቱን በሰላማዊና ቋሚ በሆነ መንገድ ለመፍታት የጸና አቋም አለውና። በሌላም በኩል በግጭቱ ምክንያት የተከሠቱ የሰብአዊ መብትና የሰብአዊነት ጥሰቶችን ተጠያቂ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኑን ለመግለፅ ይወዳል፡፡
ጥቅምት 18 ቀን 2015 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
የብልጽግና ፓርቲ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ መደበኛ ስብሰባውን በጅግጅጋ ማካሄድ ጀመረ።
ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴው በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ እየመከረ ይገኛል። ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴው ተወያይቶ የተለያዩ አቅጣጫዎችን ያስቀምጣል ተብሎ ነው የሚጠበቀው።
#prosperity
የመኖርያ ቤት ኪራይ መጨመርም ይሁን ተከራይን ማስወጣት የሚከለክለው ደንብ ለቀጣይ ስድስት ወራት ተራዘመ
*******************
የመኖርያ ቤት ኪራይ መጨመርም ይሁን ተከራይን ማስወጣት የሚከለክለው ደንብ ለሚቀጥሉት ስድስት ወራት መራዘሙን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዜጎች ላይ የሚደርሰውን የኑሮ ጫናን ለመቀነስ በመኖርያ ቤት ተከራዮች ላይ የኪራይ ዋጋ ጭማሪ እና ተከራይን ማስለቀቅን የሚከለክል ደንብ አውጥቶ ተግባራዊ ማድረጉ ይታወቃል፡፡
ይህም ደንብ በተለያየ ጊዜ እየተራዘመ ላለፈው አንድ አመት ተግባራዊ ተደርጎ ቆይቷል፡፡
ስለሆነም የከተማ አስተዳደሩ አሁን ያለውን አጠቃላይ ነባራዊ ሁኔታ እና የህብረተሰቡን የኑሮ ጫና ከግምት ባስገባ ወቅቱን በአብሮነትና በመተሳሰብ ለማለፍ ይረዳ ዘንድ ይህ ደንብ ለሚቀጥሉት ስድስት ወራት እንዲራዘም ወስኗል፡፡
በመሆኑም ይህንን ክልከላ በመተላለፍ ተከራዮችን የሚያስወጡ እና የኪራይ ዋጋን የሚጨምሩ አካላት ላይ ማህበረሰቡ በሚከተሉት የስልክ ቁጥሮች ጥቆማውን ለከተማ አስተዳደሩ ማድረስ እንደሚችል ያስታውቃል፡፡
አጭር ቁጥር ፡- 9977
የሞባይል ስልኮች
09-00640830
09-00640789
በፓርቲያችን 1ኛ ጉባኤ ላይ ከዚህ በታች በዝርዝር የተጠቀሱ ነጥቦች ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎቻችን ሆነው በከፍተኛ ትኩረት እንድንፈፅማቸው የተቀመጡ አቅጣጫዎች ናቸው፡፡
#prosperity
ወጣቶች በሥራ ላይ የሚያተኩሩ፤ ሀገራቸውን ለማወቅ የሚተጉ፣ የሀገራቸውን ጸጋ የሚያለሙ፣ ፈጣሪያቸውን አመስጋኝ መሆን አለባቸው። ሀገራቸው ኢትዮጵያ ትልቅ እንደ ነበረች አስታውሰው ወደ ቀደሞ ከፍታዋ እንድትመለስ በኅብረ ብሔራዊ አንድነት ማጽናት የዚህች ድንቅ ሀገር ልጆች ግዴታ ነው። ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ
የኢፊዴሪ ጠቅላይ ሚኒስቴር
የታላቁ ኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ 2ኛው ተርባይን የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት ጀመረ
******** በአፍሪካ ግዙፉ የኃይል ማመንጫ የሆነው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በሁለተኛ ተርባይኑ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት ጀምሯል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን ጨምሮ የተለያዩ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች በቤንሻንጉል ጉሙዝ ጉባ ወረዳ በታደሙበት ዝግጅት ነው በዛሬው ዕለት ሁለተኛው ተርባይን ኃይል ማመንጨት የጀመረው።
የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ካሉት 13 ተርባይኖች መካከል ዩኒት 9 የሚባለው ሁለተኛው ተርባይን የተሳካ ተከላ እና ሙከራ ከተደረገ በኋላ ኃይል የማመንጨት ስራው እውን ሆኗል።
ዛሬ በይፋ ሥራ የጀመረው ሁለተኛው ዩኒት 375 ሜጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም እንዳለው ተገልጿል።
ቃላችንን አላጓደልንም!!
በማራኪ አያሌው
ከአራት ዓመታት በፊት ሀገራዊ ለውጡ ሲበሰር የህዝባችን የለውጡን ፍሬዎች የማጣጣም ተስፋ ላቅ ያለ ነበር፡፡ የለውጥ አመራሩም ይህን የሕዝቡን ፍላጎት ለማርካት ሲረባረብ ቆይቷል፡፡ ህዝባችን በለውጡ ዘመን የእንጦጦ ከፍታ ከጫካነት ወደ ውብ ተፈጥሯዊ መዝናኛነት ሲቀየር ተመልክቷል፡፡ የቤተ መንግስት ቅጥር ጊቢ ለምቶና ተውቦ ሲበረከትለት፤ ጎርጎራና ወንጪ የልማቱ ተቋዳሽ ሰሆኑ አይቷል፡፡
የተቋማትና የምጣኔ ሃብት ሪፎርምን፣ የዜጎችና የሀገር ክብርና ፍቅር ከፍ ማለትን፣ ሳይፈልግ የተጫነበት የልዩነት ትርክት በአዲስ የአብሮነትና የወንድማማችነት ትርክት መቀየርን ሲመለከት ለሀገር አንድነት መሰረት እየተጣለ በመሆኑ ተስፋው ያልለመለመ ኢትዮጵያዊና የኢትዮጵያ ወዳጅ የለም፡፡ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብም በለውጡ ላደረጉት አበርክቶ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ የሰላም ኖቤል ሽልማትን በማበርከት አድናቆቱን ቸሯል፡፡
ከለውጡ በተቃራኒ የነበሩት አካላት ግን እጃቸውን አጣጥፈው አልተቀመጡም፡፡ የሕዝቡን ፍላጎትና ውሳኔ አሜን ብለው መቀበል አልፈለጉም፡፡ አንድም በፍርሃት፤ ሁለትም እኔ ከሞትኩ … እንደሚሉት ሆኖባቸው ከውጪ ሃይሎች ጋር ጭምር ተቀናጅተው በሚለኩሱት እሳት ብዙ መከራ አስተናግደናል፡፡ የዜጎች ሞት፤ መፈናቀል፤ ግጭት፤ የመሰረተ ልማት ውድመት፣ ወዘተ ... ጉዟችንን አድካሚ፤ ድላችንንም በፈተና የታጀበ እንዲሆን አድርገውታል፡፡
አንዳንድ የውጪ ሃይሎች እነሱ በቀየሱልን መንገድ ብቻ እንድንራመድ በየምዕራፉ የነበረው ጉተታ አይዘነጋም፡፡ በታላቁ የሕዳሴ ግድብ፤ በምርጫና በተለያዩ ጉዳዮች "እኛ ካልወሰንላችሁ" የሚለው መረን የለቀቀ ጣልቃ ገብነታቸው ከምኞት ባያልፍም ዋጋ አስፍሎናል፡፡ እኛ ግን በየግንባሩ የተከፈተብንን ዘመቻ በጋራ በመመከት እጣ ፈንታችን እንደ ሀገር በአንድ ላይ የተሰናሰለ በቀላሉ የማንሰበርና የማንበታተን ጠንካራ ሕዝብ መሆናችንን በዓለም አደባባይ አስመስክረናል፡፡
በነዚህ ዓመታት በአንድ በኩል ችግሮችን በመቀልበስና የሀገር አንድነትን በማስጠበቅ በሌላ በኩል ልማትን በማፋጠን የለውጥ አመራሩ ቃሉን ሳያጓድል ቀጥሏል፡፡ እንደ ሀገር ያነገብነው ራዕይ እና ሕዝቡ የሰጠን አደራ ከሚፈታተኑን ችግሮች በላይ ናቸውና የብልፅግና ጉዟችን ከስኬት ማማ ሳይደርስ አይቆምም፡፡ የሰፊውን ሕዝብና የሀገርን ተስፋ ያለመለሙትን የለውጡን መልካም ወረቶች እያካበትን የፍርሃት ቆፈን ለብሶ ከፊታችን የቆመውን ፀረ ለውጥ ሃይል አልፈንው እንሄዳለን፡፡
#Prosperityparty #prosperity
የተጠና እርምጃ በመውሰድ በአሸባሪው ሸኔ ላይ ኪሳራ ማድረስ ተችሏል - የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 30፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የተጠና እርምጃ በመውሰድ በአሸባሪው ሸኔ ላይ ኪሳራ ማድረስ መቻሉን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ፡፡
የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰላማዊት ካሳ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡
በመግለጫቸውም፥ የአሸባሪው ሸኔን ጥቃትን የመከላከልና ቡድኑን የማስወገድ ዘመቻዎች ሲካሄዱ መቆየታቸውን አንስተዋል፡፡
በተለይ በኦሮሚያ ክልልና አዋሳኝ አካባቢዎች የሽብር ቡድኑ እየረበሸ እንደሚገኝ አንስተው፥ በፌዴራልና ኦሮሚያ ክልል የጸጥታ ሃይሉ ጥምረት ባለፉት ጥቂት ሳምንታት ዘመቻው ሲካሄድ መቆየቱን ገልጸዋል፡፡
በዘመቻውም ትልልቅ ስኬቶች ተመዝግበዋልም ነው ያሉት፡፡
ሲወሰዱ የነበሩ ዘመቻዎች በተጠኑ ቦታዎች ላይና የተወሰኑ ቦታዎች ዒላማ በማድረግ የሽብር ቡድኑን እንቅስቃሴ ከግምት ውስጥ በማስገባት ሲካሄድ መቆየታቸውን አመልክተዋል፡፡
እንደአብነት ከጥቂት ቀናት በፊት የተወሰደውን እርምጃ አስመልክቶ እንዳሉት ፥ በሆሮጉድሩ ወለጋ ዞን የሱሉላ ፊንጫ ወረዳ ላይ በተፈጸመው እርምጃ በርካታ የሸኔ ታጣቂዎች ላይ እርምጃ ተወስዷል ነው ያሉት፡፡
በአካባቢው የፊንጫ ስኳር ፋብሪካ ይዞታ የሸንኮራ አገዳ ማሳ ውስጥ በመሸሸግ የተከፈተባቸውን እርምጃ ለመሸሽ ሲሞክሩ እንደነበር አንስተዋል፡፡
በዚህም የተጠና እርምጃ በመውሰድ በአሸባሪው ሸኔ ላይ ኪሳራ ማድረስ ተችሏል ነው ያሉት ሚኒስትር ዴኤታዋ፡፡
አገራችን ኢትዮጵያ በታሪክ መዝገብ ውስጥ በደማቅ ቀለም ተጽፋ የምትገኝ፤ ከአለም ስልጣኔ በፊት የስልጣኔ ባለቤት የነበረች የመቻቻል እና የብዝሃነት አገር ናት፡፡ ኢትዮጵያ ታላቅ አገር ናት ሲባልም እንደው በቃል ብቻ ለማለት ሳይሆን በተጨባጭ ታላቅነቷን የሚመሰክሩ በርካታ መገለጫዎች ስላሏት ጭምር ነው።
ኢትዮጵያን በማንም ሃይል ፍላጎትም ሆነ ንግግር ዝቅ ማድረግ እንዳይቻል አድርገው ከፍ ያደረጓት አባቶቻችንን ስብዕና ተላብሰን እና አገር ከፍ ስትል ከፍ የሚለው የዜጎቿ ክብር መሆኑን በመገንዘብ ሁሌም ቢሆን እንደታሪካችን ንግግራችንም ተግባራችንም ኢትዮጵያን የሚመጥን ሊሆን ይገባል፡፡
ኢትዮጵያን ለማሻገር በሚደረገው የትግል ምዕራፍ የሚገጥሙ ችግሮች ሁሉ በጽናታችን ልክ የምንሻገራቸው እንጂ ወደፊት ከመገስገስ የሚያቆሙን ሊሆኑ አይገባም፡፡ የትናንት ታሪካችን የሚያስተምረን ይሄንኑ ነውና፡፡ በመሆኑም ዛሬም፣ ነገም፣ ወደፊትም በጽናት በመቆም ትኩረታችን ችግሮቻችንን ከስር ከስር እየነቀሉ ኢትዮጵያን ማጽናት ላይ ሊሆን ይገባል፡፡
የኢትዮጵያን ብልጽግና ማረጋገጥ የሚቻለውም ችግር የማይበግረውና በአገራዊ ጥቅሙ የማይደራደር ጽኑ ትውልድ በመገንባት ብቻ ነው፡፡
የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አደም ፋራህ በብልፅግና ፓርቲ ዋና ፅ/ቤት ቅጥር ጊቢ ውስጥ እየተሰሩ ያሉ የአረንጓዴ አሻራ እንቅስቃሴዎችን ጎብኝተዋል፡፡
አቶ አደም በጉብኝቱ ወቅት የተተከሉ ችግኞች ለምግብነት የሚውሉ እና በአጭር ጊዜ ውስጥ የሚደርሱ መሆናቸው በበጎ የሚታይ እንደሆነ ገልፀው የተጀመሩ እንቅስቃሴዎች አበረታች እንደሆኑ እና ይበልጥ ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡
ፅ/ቤቱም ለጉዳዩ ልዩ ትኩረት በመስጠት ተጨማሪ ባለሙያዎችን ጭምር በመመደብ የተጀመሩ እንቅስቃሴዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ አቅጣጫ አስቀምጠዋል፡፡
በጅምር ላይ ያሉ ተግባራትም በሳይንሳዊ መንገድ እየዳበሩ መቀጠል እንደሚገባቸውና የዋና ፅ/ቤቱ ተሞክሮዎች በሁሉም ቅርንጫፍ ፅ/ቤቶች ውስጥ መስፋፋት እንዳለባቸው ገልፀዋል፡፡
የማክሮ ኢኮኖሚ ኮሚቴ ስብሰባችንን አካሂደናል። ባለፈው ዓመት የሚያበረታታ የወጪ ንግድ አፈጻጸም፣ ቀጥተኛ የውጭ ሙዓለ ነዋይ ፍሰት መጨመር ታይቷል። ባለፉት ሁለት ወራት የዋጋ ግሽበት መቀነስ፣ ከፍተኛ የአረንጓዴ ዐሻራ ክንውን፣ የበጎ ፈቃደኝነት ተግባራት፣ የሬሚታንስ ጭማሪ እና በቴክኖሎጂ የታገዘ የሥራ ክንውን የተመዘገቡበት እንደ ሆነ አረጋግጠናል። በዚህ ዓመት የተገኙ ስኬቶችን አጠናክሮ መቀጠል በእጅጉ አስፈላጊ ነው።
Our macroeconomic committee meeting today confirmed remarkable export performance this past year; better FDI flows; decreased inflation past two month;
optimal green legacy, volunteer activities, remittance and automation performance. It is key we build and expand on this year’s achievements.
ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር
አባይ…ዋናችን
(በማራኪ አያሌው)
በሀገራችን ስነ-ቃል ውስጥ እንደ አባይ ገዝፎ የሚጠቀስ የለም፡፡ ፍቅር፣ ናፍቆት፣ ቁጭትና ብሶትን ለመግለጽ በምንጠቀማቸው ተረትና ምሳሌዎች እንዲሁም ዘፈንና እንጉርጉሮ ውስጥ አባይ የላቀ ስፍራ አለው፡፡ በተረትና ምሳሌዎቻችን ወንዝ ወይም ግዑዝ ፍጡር እስከማይመስል ድረስ አባይ ውሃነቱን ትቶ ሰብዓዊ ማንነት ተላብሶ ሲወደስና ሲወቀስ ይታያል፡፡ ከአይበገሬነቱ፣ አባካኝነቱና አስቸጋሪነቱ በተጨማሪ ለጋስነቱና ውብ ተፈጥሮው በስነ-ቃሎቻችን ውስጥ ይንጸባረቃል፡፡
ከሀገራችን አልፎ በሌሎች ወግና ልማድ እንዲሁም ስርዓተ አምልኮ ውስጥም ይህ ወንዝ የገነነ ቦታ አለው፡፡ የጥንቶቹ ግብጾች ለም አፈር እየተፋ በምርት የሚያንበሻብሻቸውን የወንዝ አምላክ ሃፒ ብለው ሲሰይሙት፤ ለቸርነቱ መስዋዕት ሲሰውለት እንደነበር በወንዙ ዙሪያ የተጻፉ ጽሁፎች ያትታሉ፡፡ እነዚህ ህዝቦች ወንዙ ከሁለት ተራሮች ግርጌ ወደ ምድር ወጥቶ በግብጽ ምድር ላይ እንደሚፈስ እንጂ ትክክለኛ የወንዙ ምንጭ የት እንደሆነ እንኳን አያውቁም ነበር፡፡
የወንዙ ምንጭና ለግርጌዎቹ ህዝቦች ፍሰሃ የሆነው የወንዙ ውሃ 86 በመቶው ከእኛው የኢትዮጵያ ምድር ሲሄድ ለታላቅነቱ የንግስና አክሊል ደፍተንለት በእንጉርጉሮ ለዘመናት ለትውልዶች ያለ ልዩነት ስንሸኝ ለእኛ ብቻ የተሰጠን ሳይሆን፤ አባይ ከተፋሰሱ ህዝቦች አልፎ ለሌሎች የሚበቃ የልማት ዋርካ እንደሚሆን ሳንጠራጠር ነበር፡፡ የወንዞች ሁሉ አውራ ዋናችን የሆነው አባይ የእኛን አፈር ጠራርጎ ለሌላው ሲሳይ ሲሆን ልጓም ለማበጀት እጅ አጥሮን በነበረ ጊዜ እንኳ አባይ ከማንም በላይ ለእኛ ቅርብ ነበር፡፡
በሺህ ኪሎ ሜትሮች ርቀት ከወንዙ ሸለቆ በማለዳ እሸት ከሚቋደሱ፤ መረብ ዘርገተው የአሳ ምርት ከሚያፍሱት የበለጠ ተስፋው ፊታችንን ሲያወዛ፤ ወዲያ ማዶ በወንዙ ብርሃን ጨለማ ሲረታ፤ እኛ ጨረቃ እየሞቀን ስለ ታላቅነቱ አንጎራጉረናል፡፡ ለሙን አፈር ለማስረከብ ሲጣደፍ፤ ድፍርስ መልኩን እያየን ‹‹ዛሬስ አባይን ከፋው›› ብለን፤ በወንዙ ዳር በሚገላበጠው አዞ ውስጥ የነገዎቹን ጀልባዎች አሻግረን እያማተርን በሌላው ተጠቃሚነት ቅንጣት ታክል ሳንቀና ከአባይ ጋር ኖረናል፡፡ እንደ ወንዙ የውሃ መጠን የሚቀያየር ሳይሆን በትውልድ ዑደት የማይናወጥ ፍቅርን ለግሰን በጣና ካህናት ህብረ ዜማ፤ በሼኮቹ አዛን፤ በወፎቹ ዝማሬ አጅበን አባይን በእንግዳነት ለሚጠብቁት ስንሸኝ ቆይተናል፡፡
ሲያሰኘው በዝምታ፣ ሲሻውም እየተነፋረቀ የኛ ጉዳይ ግድ ሳይሰጠው ክረምት ከበጋ የሚገማሸረውን አባይ በአመጸኛ ልጅ መስለን በአዋሽ ስንጽናና ትውልድ በትውልድ ሲተካ የህዳሴው ትውልድ ፍትህን ሳያጓድል፤ መርህን ሳይሸረሽር እንቆቅልሹን እንዲፈታ በታሪክ ሲመረጥ ኢትዮጵያዊ ሁሉ በአንድነት ተሰልፎ አለኝታነቱን አስመስክሯል፡፡ ርብርቡም ፍሬ አፍርቶ አመጸኛውንና ዋናችንን አባይን ከቤቱ አሳድሯል፡፡ ከትውልድ ትውልድ እየተሸጋገረ በስነ-ቃል በልባችን ውስጥ የታተመውን፤ ከእኛ ጋር የተቆራኘውን ማንነት በተግባር ልናኖረው በጉባ ላይ ቃልኪዳን አስረን ከአባይ ጋር የልማትና የእድገት ጉዞ ጀምረናል ማለት ይቻላል፡፡
"የኢትዮጵያ መንግስት ከምንም በላይ ቅድሚያ የሚሰጠው ለሰላም ነው። በማንኛውም ጊዜ ድርድር ይደረጋል። ምክንያቱም ጥላቶቻችን እነዚህ በውስጥ ያሉ ሀይሎችን በመጠቀም ሀገራችንን እየጎዱ ነው። ስለዚህ ይህንን ከምንጩ ለማድረቅ የንግግር እድል ካለ እርሱን እንጠቀም ነው ዋናው ምክንያቱ። ድርድሩ ይሳካል አይሳካም ሂደቱ ይወስነዋል። ለንግግር ክፍት መሆን ግን ችግሩ አይታይኝም።"
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ
"የኢትዮጵያን የዳገት ጉዞ ከቻላችሁ ወደላይ ግፏት ደግፏት፤ ካልቻላችሁ ስሜት ካሸነፋችሁ ቢያንስ እንዳትንሸራተት ታኮ አስቀምጡላት፤ ጠላቶቻችን የሚፈልጉት ወደ ኋላ እንድትንሸራተት ነውና ያንን አታድርጉ"
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ
አብዝቶ ስለድህነት መናገር ብልጽግናን አያመጣም፡፡ አብዝቶ ስለጠላት መናገር ድልን አያጎናጽፍም፡፡ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ
ኢትዮጵያ ወደ ዳገት ጉዞ ላይ ነች ያለችው፡፡ ወደፊት በጣም ቅርብ ነው፤ የሚታይ ቢሆንም ግን ከባድ ነው፡፡ ወደኋላ መመለስ በጣም ሩቅ ነው ግን ቁልቁለት ስለሆነ ቀላል ነው፡፡ ከፍተኛ ጉልበት፣ አንድነት እና ትብብር ይጠይቃል፡፡ ከአቅም በላይ ተባብረን መግፋት ይፈልጋል፡፡ ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር)
#Prosperityparty
