የአ/አ/ሳ/ቴ/ዩ ግቢ ጉባኤ
Open in Telegram
Contact= +251901629875 ✍️የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተከርስቲያን ያከበረቻቸው ቅዱሳን ታሪክ ✍️ የቤተክርስትያኗን ትክክለኛ አስተምህሮዋን የያዙ መጽሐፍት ✍️ አጭርና ተከታታይ ትምህርቶች ✍️ ለመናፍቃን ጥያቄዎች መልስ ✍️ ወቅታዊ መረጃዎች ✍️ ስብከቶችን የሚያቀርብበት ገፅ ነው፡፡ በመርሐግብሩ ላይ አስተያየት ፥ ሐሳብ ፥ ጥያቄ ካለዎት ይጻፉልን @gibigubae_hasab_bot
Show more7 075
Subscribers
+224 hours
+67 days
-330 days
Posts Archive
7 075
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
🙏 እስከ መጨረሻው በማንበብ ይተባበሩን፤ ለሌሎችም ያጋሩት! 🙏
የሚዲያ ክፍላችን ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ እግዚአብሔር በሰጠን አቅም ሁሉ ታላላቅ ሥራዎችን ሲሠራ ቆይቷል። በተለይም በዚህ በዲጂታል ዘመን የቤተክርስቲያንን አስተምህሮ ማዳረስ፣ የእግዚአብሔርን ቃል በጽሑፍም ሆነ በቪዲዮ ተደራሽ ማድረግ ዋነኛውና ውዱ አደራችን ነው።
ባለፉት ዓመታት ከቅን ወንድምና እህቶቻችን ስልክ እየተዋስን የተለያዩ ትምህርቶችንና መርሃ ግብሮችን ስናቀርብላችሁ ቆይተናል። ነገር ግን ካቀድነው ትልቅ ራእይ አንጻር ሲታይ እስከ አሁን የሠራነው በጣም ጥቂቱን ብቻ ነው።
የእቅዳችን ዋና ዋና ግቦች፦
በዲጂታል ዘመን ቃለ እግዚአብሔርን ማዳረስ፤ በግቢ ውስጥ ያሉትንና ተመርቀው የወጡትን የግቢ ጉባኤያችንን ፍሬዎች የሚያገናኝና ካሉበት ቦታ ሆነው የሚያገለግሉበትን መንገድ በማመቻቸት ቤተሰባዊነታችንን ማጠናከር፤ ከመደበኛ መርሐ ግብራችን በተጨማሪ የጉዞ፣ የምሩቃን ሕብረት፣ የምረቃ መርሃ ግብር (Graduation ceremony)፣ የሃፍ ላይፍ (Half-Life) እና የአዲስ ተማሪዎች መቀበያ (Freshman welcoming event) ፕሮግራሞችን በቪዲዮ መዝግቦ ማሰናዳት እና በዶክመንተሪ መልክ ለእይታ ማብቃት፤እነዚህን ትላልቅ ሥራዎች አቅደን የተነሳን ቢሆንም የራሳችን የቀረጻ ማቴሪያል አለመኖሩ ዋና ማነቆ ሆኖብናል። እንደሚታወቀው የተውሶ ስልክ በፈለግነው ሰዓት ለማግኘት አዳጋች ከመሆኑም በላይ ለአገልግሎቱ ስፋት በቂ አይደለም። የሚዲያ ቡድናችን ይህንን ችግር ለመቅረፍ በግቢያችን ውስጥ የግራፊክስ ዲዛይን እና ቪዲዮ ኤዲቲንግ ሥልጠና በመስጠት እስከ 40,000 ብር ለመሰብሰብ ጥረት ያደረገ ቢሆንም፣ ለዕቃዎቹ ግዢ አሁንም ገና ብዙ ይቀረናል።
"ሀምሳ ሎሚ ለአንድ ሰው ሸክሙ፣ ለሀምሳ ሰው ጌጡ ነው"እንደሚባለው እኛም ኦርቶዶክሳውያን ከተባበርን ማንኛውንም ነገር ማሳካት እንችላለን። ይህ ቅዱስ አገልግሎት ሳይቋረጥ እንዲቀጥልና ይበልጥ እንዲስፋፋ ሁላችሁም የበኩላችሁን አሻራ እንድታስቀምጡ በአክብሮት እንጠይቃለን። 📌 በምን በምን መረዳት ይችላሉ? 1️⃣ መረጃ በማጋራት (Share)፦ ለዚህ መርሃ ግብር የተዘጋጀውን ፖስተር በቴሌግራም፣ በኢንስታግራም Story፤ እንዲሁም በቲክቶክ እና በዩቲዩብ የተለቀቁትን ቪዲዮዎች Share በማድረግ ተደራሽነቱን ማፋጠን። 2️⃣ ሰዎችን በመጠቆም፦ ድጋፍ ሊያደርጉልን የሚችሉ ሰዎችን (ለምሳሌ ቲክቶከሮችን) Mention ማድረግ፤ ወይም በገንዘብና በዓይነት ሊረዱን የሚችሉ ኦርቶዶክሳውያንን ካወቃችሁ ስምና ስልክ ቁጥራቸውን ከዚህ በታች በተቀመጠው የጉግል ፎርም ሊንክ ያስቀምጡ፦ https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSc4PIhwq7W2ysKVATYxxuDx3gOxhb4-LdsqyG4d807sPXPPPg/viewform?usp=header 3️⃣ በዓይነት ድጋፍ በማድረግ፦ ለሥራችን አስፈላጊ የሆኑ የቴክኖሎጂ ዕቃዎችን በመስጠት፦ 📷 ካሜራ (Camera) 📐 የካሜራ ስታንድ (Tripod) 🎙 ማይክሮፎን (Microphone) 💾 ኤክስተርናል ሃርድዲስክ (External Hard Drive) 🎥 ጊምባል (Gimbal / Stabilizer) 4️⃣ በገንዘብ ድጋፍ በማድረግ፦ «አነሰ፣ በዛ» ሳያሉ አቅማችሁ የፈቀደውን ያህል በመለገስ የዚህ በረከት ተካፋይ ይሁኑ! 💳 የባንክ እና የስልክ አድራሻዎች፦ CBE (ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ):
1000792257686
(Egzihareya Solomon And/or Arsema)
Telebirr (ቴሌብር): 0958313628 (Arsema)
📞 ለበለጠ መረጃ (በስልክ ለመደወል ቁጥሮቹን ይነኩ)፦
📱 +251 98 332 9770
📱 +251 90 549 6768
ለምታደርጉት ትብብር ሁሉ እግዚአብሔር አምላክ በረከቱን ያድላችሁ!🙏
▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰
የአ/አ/ሳ/ቴ/ዩ ግቢ ጉባኤ
📥 @gibigubaeHasabon_bot ጻፉልን
🏷 @aastugibigubae ተከታተሉን
📷 @GGgallery1 የፎቶ ማኅደራችን
▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰
TikTok | Instagram | YouTube7 075
🌼 "አንዷን ጳጉሜ ለግቢ ጉባኤያችን!" 🌼
“ዓመታትን በቸርነትህ ታቀዳጃለህ።” (መዝሙረ ዳዊት 65:11)
የሚዲያ ክፍላችን ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ እግዚአብሔር በሰጠን አቅም ሁሉ ታላላቅ ሥራዎችን ሲሠራ ቆይቷል። በተለይም በዲጂታል መንገድ የቤተክርስቲያንን አስተምህሮ ማዳረስ፣ የእግዚአብሔርን ቃል በጽሑፍም ሆነ በቪዲዮ ተደራሽ ማድረግ ዋነኛውና ውዱ አደራችን ነው።
ባለፉት ዓመታት ከቅን ወንድምና እህቶቻችን ስልክ እየተዋስን የቻልነውን ያህል የተለያዩ ትምህርቶችንና መርሃ ግብሮችን ስናቀርብላችሁ ቆይተናል። ይህንን የቀረጻ ዕቃ ችግር ለመቅረፍና አቅማችንን ለማሳደግ ሚዲያ ቲማችን በግቢያችን ውስጥ የግራፊክስ ዲዛይን እና ቪዲዮ ኤዲቲንግ ሥልጠና በመስጠት እስከ 40,000 ብር ገቢ መሰብሰብ ችሏል።
ሆኖም ካቀድነው ትልቅ ራእይ አንጻር እንዲሁም ሙሉ የቀረጻ ዕቃዎችን (ካሜራ፣ ማይክ እና ስታንድ) ለመግዛት አሁንም ገና ብዙ ይቀረናል። ሁልጊዜ ስልክ እየተለመነ የታቀደውን ትልቅ አገልግሎት ከግብ ለማድረስ የማይታሰብ በመሆኑ ይህንን ቀሪ ክፍተት አብረን የምንሞላበት ልዩ መንገድ አዘጋጅተናል።
ካቀድናቸው የገቢ ማሰባሰቢያ መንገዶች ውስጥ አንዱ "አበባ አየሁሽ" ነው።
"ሀምሳ ሎሚ ለአንድ ሰው ሸክሙ፣ ለሀምሳ ሰው ጌጡ ነው" እንደሚባለው፤ በአዲስ አበባ እና በዙሪያዋ ያላችሁ እህቶቻችን በአንድነት በመሆን "አበባ አየሁሽ" እየዞርንና ወደተለያዩ ድርጅቶች በመሄድ ለሚዲያ ክፍላችን ዕቃዎች መግዣ የሚሆን ገቢ እናሰባስባለን!
📌 በዚሁ መርሃ ግብር፦
የበረከት ተካፋይ ይሆናሉ፦የሚዲያ ክፍላችን በቋሚነት የራሱ ዕቃ ኖሮት አገልግሎቱን ዳር እንዲያደርስ ትልቅ አሻራ
ጥሪው ለማን ነው? በግቢ ውስጥ ያላችሁ እህት እና ወንድሞቻችን ፣ ተመርቃችሁ የወጣችሁ የቀድሞ አባላት እንዲሁም በአዲስ አበባና በዙሪያዋ የምትገኙ እህቶቻችን በሙሉ!
ዕድሜን በዓመታት እየሰጠ ለሚያኖረን አምላክ እኛም እግዚአብሔር ከሰጠን ዕድሜ አንዷን ቀን ለግቢ ጉባኤያችን እንስጥ፤ ኑ፣ አብረን የበረከት ሥራ እንሥራ!
📞 ለበለጠ መረጃ፦
ስልክ፦ +251983329770
ቴሌግራም፦ @Zarsuu
ለመመዝገብ፦ ከታች ያለውን የ Google Form ሊንክ ይጠቀሙ!👇👇👇
ለተሳትፎዎና ለትብብርዎ ሁሉ እግዚአብሔር አምላክ በረከቱን ያድላችሁ!
https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSdoJnuvcFVc32RxZU6c-dtLK-dU_tv5rqyI0olH2zy9JT5YDw/viewform?usp=publish-editor
▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰
የአ/አ/ሳ/ቴ/ዩ ግቢ ጉባኤ
📥 @gibigubaeHasabon_bot ጻፉልን
🏷 @aastugibigubae ተከታተሉን
📷 @GGgallery1 የፎቶ ማኅደራችን
▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰
TikTok | Instagram | YouTube
7 075
እንኳን የኢትዮጵያ ብርሃን፣ ሐዲስ ሐዋርያ ለሆኑት ለታላቁ አባታችን ለአቡነ ተክለ ሃይማኖት ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላምና በጤና አደረሳችሁ! 🕊✨
“ጻድቅሰ ከመ በቀልት ይፈሪ ወይበዝኅ ከመ ዝግባ ዘሊባኖስ፤ ጻድቅ እንደ ዘንባባ ያፈራል እንደ ሊባኖስ ዝግባም ያድጋል።” (መዝ. 91፥12)
«ተክል» ማለት ፍሬያማ ዕንጨት፣ ዛፍ፣ ገነታዊ ዕፅ፣ ሕግና ሥርዓት ማለት ሲሆን «ሃይማኖት» ማለት ደግሞ አምኖ መመስከር ነው። «ተክለ ሃይማኖት» የሚለው ሐረግ የሃይማኖት ተክል፣ የጽድቅ ፍሬን ያፈራ፣ የጻድቃን መጠለያ ዕፅ ማለት ሲሆን «የአብ፣ የወልድ፣ የመንፈስ ቅዱስ ተክል» የሚልም ምሥጢራዊ ትርጓሜ አለው።
ጻድቁ አባታችን በእግዚአብሔር ድንቅ ጥበብና በሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ብሥራት በሸዋ ሀገረ ስብከት ኢቲሳ በሚባል ቦታ ከአባታቸው ከካህኑ ጸጋ ዘአብና ከእናታቸው ከቅድስት እግዚእ ኀረያ መጋቢት 24 ቀን ተፀንሰው ታኅሣሥ 24 ቀን 1212 ዓ.ም ተወለዱ። በተወለዱ በሦስተኛው ቀን ከእናታቸው ዕቅፍ ወርደው «አሐዱ አብ ቅዱስ፤ አሐዱ ወልድ ቅዱስ፤ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ» በማለት ቅድስት ሥላሴን አመስግነዋል። ወላጆቻቸው «ፍሥሐ ጽዮን» ብለው ሲሰይሟቸው «ተክለ ሃይማኖት» የሚለውን ስም ግን የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ሚካኤል አውጥቶላቸዋል።
በ15 ዓመታቸው ዲቁናን፣ በ22 ዓመታቸው ቅስናን ከግብፃዊው ጳጳስ ከአባ ቄርሎስ ተቀበሉ። ጐልማሳ በሆኑ ጊዜ አራዊትን ሊያድኑ ወደ ዱር በሄዱበት ሰዓት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቅዱስ ሚካኤል ክንፍ ላይ ተገልጦ፦
“ወዳጄ ሆይ አትፍራ፤ እንግዲህ የኃጢአተኞችን ነፍስ ወደ ሕይወት የምታጠምድ ትሆናለህ እንጂ አራዊትን የምታድን አትሆንም፤ ስምህም ተክለ ሃይማኖት ይሁን”
ብሎ ሾማቸው። አባታችንም ይህን ጥሪ ሲሰሙ ቤታቸውን እንደተከፈተ ትተው፣ ሀብታቸውን ለድሆች አፎተው፣ ምርኩዛቸውን ይዘው ወንጌልን ለማስተማር ወጡ። በመላው ኢትዮጵያ እየተዘዋወሩ ወንጌልን በመስበክ፣ ጣዖታትን በማፍረስና ድውያንን በመፈወስ 12,300 ነፍሳትን አጠመቁ፤ ከሀዲውን ንጉሥ ሞተለሚንም አሳምነው በክርስትና ሃይማኖት አጸኑት።
ከዚህ በኋላ በሐይቅ እስጢፋኖስ ከአባ ኢየሱስ ሞዓ የምንኩስና ልብስ፣ ከደብረ ዳሞ ከአባ ዮሐኒ ቆብና አስኬማ ተቀበሉ፤ ወደ ኢየሩሳሌምም ተጉዘው ቅዱሳት መካናትን ጎበኙ። ከዚያም ተመልሰው በደብረ ሊባኖስ (ግራርያ) ዋሻ ውስጥ ገብተው በቀኝ፣ በግራ፣ በፊታቸውና በስተኋላቸው የተሳሉ ፍላጻዎችን ተክለው፣ አጽመ ሥጋቸው እስኪበተንና እግራቸው እስኪሰበር ድረስ 7 ዓመት ሙሉ በጾምና በጸሎት ያለ እረፍት ቆመው ተጋደሉ።
የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ከእመቤታችን፣ ከቅዱሳን መላእክትና ከጻድቃን ጋር ተገልጦላቸዋል፤ መድኃኒታችንም፦
“ወዳጄ ሆይ በመከራዬ መሰልከኝ፤ እነሆ ስምህን ለሚጠራ፣ መታሰቢያህን ለሚያደርግ፣ ገድልህን ለሚጽፍና ለሚያነበው፣ በስምህ ለሚያስቁርብና ለሚመጸውት ሁሉ እስከ ዐሥር ትውልድ እምርልሃለሁ”
ብሎ ታላቅ የቃል ኪዳን አክሊል አጎናፀፋቸው። ጻድቁ አባታችን በ99 ዓመታቸው ከ8 ወር ከ1 ቀን በለመለመ ዕርጅና ነሐሴ 24 ቀን አርፈዋል።
የእግዚአብሔር ቸርነት፣ የጻድቁ አባታችን የአቡነ ተክለ ሃይማኖት ጸሎትና በረከት አይለየን፡፡🙏
▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰
የአ/አ/ሳ/ቴ/ዩ ግቢ ጉባኤ
📥 @gibigubaeHasabon_bot ጻፉልን
🏷 @aastugibigubae ተከታተሉን
📷 @GGgallery1 የፎቶ ማኅደራችን
▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰
TikTok | Instagram | YouTube
7 075
እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የትንሣኤና ዕርገት በዓል አደረሳችሁ፡፡! 🕊✨
“ተንስእ እግዚኦ ውስተ ዕረፍትከ አንተ ወታቦተ መቅደስከ፤ ” (መዝ. 131፥8)እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በዚህ ምድር የኖረችው ስልሣ አራት ዓመት ነው፡፡ ያረፈችው ጥር 21 ቀን ነው፤ ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በመደነቅ፦
“ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ፣ ሞታ ለማርያም የዐጽብ ለኵሉ፤ ሞትስ ለሚሞቱ ይገባል የማርያም ሞት ግን ድንቅ ነው” (ድጓ ዘአስተርእዮ ማርያም)በማለት ስለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዕረፍት ገልጿል። ጥር 21 ቀን ጌታችን እልፍ አዕላፋት መላእክትን አስከትሎ መጥቶ በቃለ አቅርንት በዝማሬ መላእክት የእመቤታችንን ነፍስ ከሥጋዋ ለይቶ አሳርፏታል፡፡ በዚህም ዕለት ቅዱሳን ሐዋርያትን በደመና ጠቅሶ ሥጋዋን እንዲቀብሩ አዘዛቸው፤ እነሱም ሊቀብሯት ወደ ጌቴሴማኒ ይዘዋት በሄዱ ጊዜ አይሁድ «እንደ ልጇ ‘ተነሣች፤ ዐረገች’ እያሉ እንዳያውኩን ኑ ሥጋዋን በእሳት እናቃጥላት» ብለው ተነሡ፡፡ ታውፋንያ የሚባል አይሁዳዊ ተራምዶ አጎበሩን ቢጨብጠው የእግዚአብሔር መልአክ ሁለት እጆቹን ቀጣው፤ ከአጎበሩ ላይ ተንጠልጥለው ቀሩ፤ “በድያለሁ” ብሎ በመለመኑ በእመቤታችን ምልጃ እጆቹ ተመልሰውለት እንደነበሩ ሆኑ፤ ከዚህ በኋላ ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስንና እመቤታችንን በደመና ነጥቆ ወደ ገነት ወስዶ ከዕፀ ሕይወት ሥር አስቀመጣት፡፡ ቅዱስ ዮሐንስም ከጥቂት ቀናት በኋላ ወደ ሐዋርያት ተመልሶ ሲመጣ ሐዋርያት “የእመቤታችን የከበረ ሥጋ እንደምን ሆነ?” አሉት፤ ከገነት ዕፀ ሕይወት ሥር መኖሩን ነገራቸው፡፡ ቅዱሳን ሐዋርያትም ቅዱስ ዮሐንስ ያየውን ያዩ ዘንድ ከነሐሴ አንድ ቀን ጀምረው ሱባኤ ገብተው እግዚአብሔርን በጸሎት መጠየቅ ጀመሩ፡፡ ሁለት ሱባኤ ሲፈጸም ማለትም ነሐሴ 14 ቀን ጌታችን የእመቤታችንን ትኩስ ሥጋ ለሐዋርያት ሰጣቸው፤ እነሱም በታላቅ ዝማሬ ወስደው በጌቴሴማኒ ቀብረዋታል። ነገር ግን እመቤታችንን ሲቀብሯት ቅዱስ ቶማስ አልነበረምና በደመና ተጭኖ ወደ ኢየሩሳሌም ሲመጣ ቅዱስ ዳዊት «ተንስእ እግዚኦ ውስተ ዕረፍትከ አንተ ወታቦተ መቅደስከ፤ አቤቱ ወደ ዕረፍትህ ተነሥ አንተና የመቅደስህ ታቦት» (መዝ. 131፥8) ብሎ ትንቢት የተናገረው ተፈጽሞ፣ በሦስተኛውም ቀን ክርስቶስ በራሱ ሥልጣን ሞትን አሸንፎ እንደተነሣ የቃል ማደሪያ የሆነችው እመቤታችንም በልጇ በክርስቶስ ኃይልና ሥልጣን ተነሥታ ዐረገችና “ከመ ትንሣኤ ወልዳ” እንደ ልጇ ትንሣኤ ተነሥታ ስታርግ ያገኛታል፡፡ ቅዱስ ቶማስም “ቀድሞ የልጅሽን ትንሣኤ ሳላይ አሁንም የአንቺን ትንሣኤ ሳላይ” ብሎ “ወፈቀደ ይደቅ እምደመናሁ” (ከደመናው ሊወድቅ ወደደ)፤ እመቤታችን “አትዘን” ብላው ሌሎች ሐዋርያት ትንሣኤዋንና ዕርገቷን እንዳላዩ ነግራው “አንተ አይተሃል፤ ሄደህ ተነሣች፣ ዐረገች ብለህ ንገራቸው” ብላ የያዘችውን ሰበን ሰጥታ ልካዋለች፡፡ ከዚያም “የእመቤታችን ነገር እንደምን ሆነ?” ቢላቸው “ቀበርናት” አሉት፡፡ እሱም “ሞት በጥር ነሐሴ መቃብር አይደረግም” አላቸው፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ “አንተ መጠራጠር ልማድህ ነው፤ ቀድሞ የጌታን ትንሣኤ ተጠራጠርክ አሁንም አታምንም” ብሎ ወደ መካነ መቃብሩ ሄደው መቃብሩን ቢከፍቱት አጧት፤ ደነገጡ፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ቶማስም “አታምኑኝም ብዬ እንጂ እመቤታችን ተነሥታ ዐርጋለች” ብሎ የሆነውን ሁሉ ነገራቸው፤ ሰበኑንም ሰጣቸው፤ ለበረከትም ተካፈሉት፤ በሰበኑም ሕሙማንን ሲፈውሱበት፣ ገቢረ ተአምራት ሲያደርጉበት ኖረዋል፡፡ በቅዳሴ ጊዜ ሠራዒ ዲያቆን በሚይዘው መስቀል ላይ የሚታሠረው ልብስ፣ አባቶች ካህናት የሚጠመጥሙት ሻሽና በመስቀላቸው ላይ የሚያደርጉት ልብስ የእመቤታችን ሰበን ምሳሌ እንደሆነ የቤተ ክርስቲያን መምህራን ያስተምራሉ፡፡ ቅዱሳን ሐዋርያትም በዓመቱ “ቅዱስ ቶማስ ትንሣኤሽንና ዕርገትሽን አይቶ እኛ ሳናይ” ብለው ከነሐሴ አንድ ቀን ጀምረው ሱባኤ ገቡ፡፡ በነሐሴ 16 ቀን ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የለመኑትን የማይነሣ ነውና እመቤታችንን መንበር፣ ቅዱስ ጴጥሮስን ንፍቅ (ረዳት) ቄስ፣ ቅዱስ እስጢፋኖስን ገባሬ ሠናይ ዲያቆን አድርጎ ቀድሶ አቁርቧቸዋል፡፡ እመቤታችንን ሐዋርያት በግልጽ እያዩዋት ከጌታችን ጋር በክብር፣ በይባቤና በዝማሬ ወደ ሰማይ ዐርጋለች፡፡ ቤተ ክርስቲያን ይህንን መታሰቢያ በየዓመቱ በታላቅ ድምቀት ታከብረዋለች፡፡ የእግዚአብሔር ቸርነት፣ የእመቤታችን ምልጃ፣ የሐዋርያት በረከት አይለየን፡፡🙏 ▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰ የአ/አ/ሳ/ቴ/ዩ ግቢ ጉባኤ 📥 @gibigubaeHasabon_bot ጻፉልን 🏷 @aastugibigubae ተከታተሉን 📷 @GGgallery1 የፎቶ ማኅደራችን ▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰ TikTok | Instagram | YouTube
7 075
እንኳን ለደብረ ታቦር በዓል በሰላም አደረሳችሁ!!!
ታቦርና አርሞንኤም በስምህ ደስ ይላቸዋል (መዝ. 88፥12)
‹‹ደብረ ታቦር›› የሁለት ቃላት ጥምር ሲሆን ‹‹ደብር›› ማለት ተራራ፣ ‹‹ታቦር›› ደግሞ በናዝሬት አካባቢ በሰማርያ አውራጃ በገሊላ ወረዳ የሚገኝ የረጅም ተራራ ስም ነው፡፡ የደብረ ታቦር ተራራ ከገሊላ ባሕር በምዕራባዊ በኩል 10 ኪሎ ሜትር ርቀት የሚገኝ ሲሆን፤ ከፍታው ከባሕር ጠለል በላይ 572 ሜትር ያህል ነው፡፡ በዚህ ተራራ ላይ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ብርሃነ መለኮቱን እንደሚገልጽ አስቀድሞ ልበ አምላክ ክቡር ዳዊት በመዝሙሩ “ታቦርና አርሞንኤም በስምህ ደስ ይላቸዋል” ብሎ ተናግሮ ነበር (መዝ. 88፥12)፡፡ታሪካዊና ምሳሌያዊ ምስጢሩ፦ በዘመነ መሳፍንት፦ ባርቅ ሲሳራን ከነሠራዊቱ ድል ያደረገው በደብረ ታቦር ተራራ ላይ ነበር (መሳ. 4፥6)፡፡ ባርቅ የጌታችን፣ ሲሳራ ደግሞ የአጋንንት ምሳሌ ነው። ጌታችን በደብረ ታቦር ክብሩን በመግለጥ በአይሁድ እያደረ አምላክነቱን እንዲጠራጠሩ ያደረጋቸውን አጋንንት ድል የማድረጉ ምሳሌ ነው፡፡ የነቢያትና የአበው ታሪክ፦ በዚህ ተራራ ነቢዩ ሳሙኤል ትንቢት ተናግሮበታል፤ ንጉሥ ሳኦልም ከሦስት ሰዎች ጋር ተገኝቶበታል (1ኛ ሳሙ. 10፥3)፡፡ አብርሃምና ኖኅ በዚህ ተራራ ላይ ቀስተ ደመና ተተክሎ አይተዋል፤ አባታችን ኖኅም ይህንን ተራራ ‹‹መካነ ብርሃን፤ የብርሃን ቦታ›› ብሎ ጠርቶታል፡፡ በወንጌልና በቅዱስ ያሬድ፦ የወንጌል ጸሐፊያን ‹‹ረጅም ተራራ፣ ቅዱስ ተራራ›› ብለውታል፤ በትውፊትና በሲኖዶስ ግን ስሙ ታቦር መሆኑ ይታወቃል፡፡ ኢትዮጵያዊው ሊቅ ቅዱስ ያሬድም በድጓው ደብረ ታቦር እያለ አስፋፍቶ ጽፎታል፡፡ ነገረ ተዋሕዶና ተስእሎተ ቂሣርያ፦ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሰው የሆነ አምላክ ነው፤ አምላክነቱ የባሕርይ ገንዘቡ ነው፡፡ ክቡር ዳዊት “እግዚአብሔር ግን ከዓለም አስቀድሞ ንጉሥ ነው፣ በምድርም መካከል መድኀኒትን አደረገ” (መዝ. 72፥12) እንዳለ በቀራንዮ ዓለሙን አድኗል፡፡ ጌታችን በፊሊጶስ ቂሳርያ ደቀመዛሙርቱን ‹‹ሰዎች የሰውን ልጅ ማን ይሉታል?›› ብሎ በጥያቄ ባስተማረበት (ተስእሎተ ቂሣርያ) ቅዱስ ጴጥሮስ ‹‹አንተ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ነህ!›› ብሎ መሰከረ (ማቴ. 16፥16)፡፡ ከዚህ ምስክርነት ከስድስት ቀን በኋላ (ነሐሴ 13 ቀን) አዕማድ ሐዋርያት የተባሉትን ጴጥሮስን፣ ያዕቆብንና ዮሐንስን ይዞ ወደ ተራራው ወጣ፡፡ የደብረ ታቦር ተራራ ምሳሌነት፦ የወንጌል ምሳሌ፦ ተራራ ሲወጡት ያስቸግራል፤ ከወጡት በኋላ ግን ደስ ይላል፡፡ ወንጌልም ሲማሯት ታስቸግራለች፤ ከተማሯት በኋላ ግን ጽድቅንና ኃጢአትን ለይታ ስታሳውቅ ደስ ታሰኛለች፡፡ የመንግስተ ሰማያት ምሳሌ፦ ተራራን በብዙ ጻዕር እንዲወጡት መንግስተ ሰማያትንም በብዙ መከራ ያገኟታልና (ሐዋ. 14፥22)፡፡ የቤተክርስቲያን ምሳሌ፦ በደብረ ታቦር ምስጢረ ሥላሴ እንደተገለጠ በቤተ ክርስቲያንም ቅድስት ሥላሴ ይነገሩባታል፡፡ ተራራ መሠረቱ ከመሬት አናቱ ከሰማይ እንደሆነ ሁሉ፤ የቤተ ክርስቲያንም መሠረቷ በምድር ሲሆን ራሷ (ክርስቶስ) በሰማይ ነውና፡፡ በፊታቸው ተለወጠ፤ ፊቱም እንደ ፀሐይ በራ ሦስቱ ሐዋርያት በተራራው ሳሉ ጌታችን ሲጸልይ መልኩ በፊታቸው ተለወጠ፡፡ ይህም የመለኮቱን ብርሃን ሲገልጥ ነው እንጂ ውላጤ/መለወጥ አይደለም፡፡ “እኔ እግዚአብሔር አልለወጥም” እንዳለ (ሚል. 3፥6) በእርሱ ዘንድ መገለጥ እንጂ መለወጥ የለም፡፡ ፊቱ እንደ ፀሐይ ብሩህ ሆነ፤ ልብሱም እንደ በረድ ጸዓዳ ሆነ፡፡ ጌታችን በተወለደ በ32 ዓመት ከ6 ወር ከ13 ቀን፣ በዘመነ ማቴዎስ፣ በወርኃ ነሐሴ በዕለተ እሑድ በደብረ ታቦር ብርሃነ መለኮቱን ገልጧል፡፡ የሙሴ የፊቱ ብርሃን የጸጋ ሲሆን (ዘፀ. 34፥29)፣ የክርስቶስ ግን የባሕርይ ብርሃን ነው፡፡ ሙሴና ኤልያስ ከእርሱ ጋር ሲነጋገሩ ታዩአቸው፦ ከሞተ ብዙ ዘመን የሆነውን ሙሴን ከመቃብር አስነስቶ፣ በእሳት ሠረገላ ያረገውን ኤልያስን ደግሞ ከብሔረ ሕያዋን አምጥቶ በደብረ ታቦር እንዲገኙ ያደረገበት ምክንያቶች፦ ሙሴ "እኔ ባህር ብከፍልም እስራኤልን ማዳን ያልተቻለኝ ደካማ ነኝ፤ የእኔን ፈጣሪ እንዴት ሙሴ ይሉሃል?" ሲል፤ ኤልያስም "እኔ ሰማይ ብለጉም እስራኤልን ማዳን የማይቻለኝ ነኝ፤ !" በማለት የክርስቶስን የባሕርይ አምላክነቱን መስክረዋል፡፡ የትንቢት መፈጸም፦ ለሙሴ "ጀርባዬንም ታያለህ፤ ፊቴ ግን አይታይም" (ዘፀ. 33፥13-23) ተብሎ የተነገረው ትንቢት ተፈጽሞ፣ ዘመኑ ሲፈጸም የአምላኩን ፊት በደብረ ታቦር ለማየት ታድሏል፡፡ የሕግና የነቢያት፣ የደናግልና የሕጋውያን ምሳሌ፦ ደብረ ታቦር የቤተክርስቲያንና የመንግስተ ሰማያት ምሳሌ በመሆኗ፤ ከሕግ/ኦሪት ሙሴን፣ ከነቢያት ኤልያስን፤ እንዲሁም ከሕጋውያን ሙሴን፣ ከደናግል/መናንያን ኤልያስን አምጥቶ አሳይቷቸዋል፡፡ በቅዳሴ ጊዜ የሚቆሙት (5 ቀዳሾች) ልዑካንም የነዚህ የአምስቱ (ሙሴ፣ ኤልያስ፣ ጴጥሮስ፣ ያዕቆብ፣ ዮሐንስ) ምሳሌዎች ናቸው፡፡ ጴጥሮስም ‘በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው’ አለው ቅዱስ ጴጥሮስ ይህንን ምስጢረ መለኮት ካየ በኋላ፦ “ሆይ በዚህ መኖር ለእኛ መልካም ነው” አለ፡፡ አምላካዊ ፈቃድህስ ከሆነ በዚህ ተራራ ላይ "አንድ ለአንተ፤ አንድ ለሙሴ፤ አንድ ለኤልያስ ሦስት ዳስ እንሥራ" ብሎ ጠየቀ፡፡ ጴጥሮስ አርቆ መናገሩ ትሕትናውን የሚያሳይ ቢሆንም፣ ጌታችንን በተራራ ላይ በሰው ሠራሽ ቤት ይኖር ዘንድ በመጠየቁ ድክመቱን ያሳያል፤ ጌታችን የሄደው ብርሃኑን ሊገልጥ እንጂ እዚያ ለመኖር አልነበረምና ቅዱስ ሉቃስ "የሚለውን አያውቅም ነበር" ብሎታል፡፡ ከደደመናው የመጣው ቃል፦ ቅዱስ ጴጥሮስ ይህንን ሲናገር ብሩህ ደመና መጥቶ ጋረዳቸው፡፡ ከደመናውም፦ “የምወደው የምወልደው ልጄ ይህ ነው እርሱንም ስሙት” የሚል ቃል መጣ፡፡ በዚህም የሥላሴ ምስጢር ለዓለም ለሦስተኛ ጊዜ ተገለጠ (አብ በደመና ተመስሎ ሲናገር፣ ወልድ በተዋሕዶ ሥጋ፣ መንፈስ ቅዱስ በነጭ ደመና)፡፡ የሀገራችን ሃይማኖታዊ ባህልና ማጠቃለያ፦ በሀገራችን ኢትዮጵያ ወጣቶች የነጎድጓዱ ምሳሌ አድርገው ጅራፍ በማጮኽ፣ የብርሃን ጎርፍ ምሳሌ አድርገው ችቦ በማብራት በዓሉን ያከብሩታል፡፡ የቀደሙ አባቶቻችን ሃይማኖታዊ አስተምህሮውን በባህላችን ውስጥ እንድንይዘው አድርገዋል፡፡
ሆኖም በዓለ ደብረ ታቦር በዋናነት የነገረ ተዋሕዶ ማሳያ እንጂ የባሕል ትርኢት ብቻ አለመሆኑን ተረድተን፣ መሠረተ እምነታችንን ጠንቅቀን ልናውቅ ይገባል፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ “ለእኛ በዚህ መኖር መልካም ነው” እንዳለው፣ እኛም በደብረ ታቦር በተመሰለች በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ጸንተን እስከ ሕይወታችን ፍጻሜ እንድንኖር አምላካችን ይርዳን፡፡▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰ የአ/አ/ሳ/ቴ/ዩ ግቢ ጉባኤ 📥 @gibigubaeHasabon_bot ጻፉልን 🏷 @aastugibigubae ተከታተሉን 📷 @GGgallery1 የፎቶ ማኅደራችን ▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰ TikTok | Instagram | YouTube
7 075
✨እነሆ ገጸ በረከት ✨
መዓዛ ቅዱሳን ዲጂታል መጽሔት 6ተኛ ዕትም ተለቀቀ !!
መልካሙን የእግዚአብሔርን ቃል ሕማሙን እያሰብን እናነብ ዘንድ ተጋብዘናል ።https://online.fliphtml5.com/xuhyi/vaxd/ ነሐሴ 8/2018 ዓ.ም በመጽሔቱ ላይ ማንኛውም ዓይነት ሐሳብ አስተያየት ወይም ጥያቄ ካላችኹ @meaza_kidusan_metshet_bot ላይ ያገኙናል። ▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰ የአ/አ/ሳ/ቴ/ዩ ግቢ ጉባኤ 📥 @gibigubaeHasabon_bot ጻፉልን 🏷 @aastugibigubae ተከታተሉን 📷 @GGgallery1 የፎቶ ማኅደራችን ▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰ TikTok | Instagram | YouTube
7 075
ተወዳጁ መዓዛ ቅዱሳን ዲጂታል መጽሔት6ተኛ እትሙን እነሆ ለፍልሰታ በረከት ሊለን ጥቂት ሰዓታት ብቻ ቀሩት! 🌟 በ6ኛው እትም የሚያገኙዋቸው ይዘቶች፡
🌧️ ዘመነ ክረምትና የቤተክርስቲያን አስተምህሮ 📜 ዜና ሐዋርያት (ክብራቸው፣ ቅድስናቸውና ተጋድሏቸው) 🎨 ኪነ-ጥበብ (ፍልሰታና ክረምት ከመንፈሳዊ ሕይወት ጋር) 🕊️ መዓዛ ቅዱሳን (የፍልሰታ ጾም የልጅነት ትዝታዎች) 🔬 ነገረ-ሰብእ (ስለ ሰው ልጅ ተፈጥሮ በሳይንስ እይታ) 🕯️ ሱባዔ (ሱባዔ ለምንና እንዴት ) ☦️ ፍልሰታ ለማርያም (የእመቤታችን ዕረፍትና መፍለስ)መዓዛ ቅዱሳን ፮ኛ እትም ነገ ይጠብቁን!
7 075
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
❤️ ነሐሴ (7) ቀን ❤️
እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የፅንሰት በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላም አደረሰን!
✝️ ✝️ ✝️
📖 የእመቤታችን የፅንሰት አጭር ታሪክ
ጻድቁ ኢያቄም እና ቅድስት ሐና በ እግዚአብሔር ፊት በቅንነትና በደግነት የሚኖሩ እውነተኛ አማኞች ነበሩ። ነገር ግን በጋብቻ ዘመናቸው ልጅ ባለመውለዳቸው ምክንያት እጅግ ያዝኑ ነበር። በወቅቱ የነበሩ የእስራኤል ልጆችም “ልጅ ያልወለደ ከእግዚአብሔር በረከትን ያጣ ነው” እያሉ ያቃልሏቸውና ይነቅፏቸው ነበር። ቅዱሳኑ ግን በሰው ነቀፌታ ተስፋ ሳይቆርጡ፣ “የአባቶቻችን የእስራኤል አምላክ ሆይ! ለአይናችን ማረፊያ፣ ለልባችን ተስፋ የሚሆን ፍሬ ስጠን” እያሉ ዘወትር በጾምና በጸሎት ወደ አምላክ ይለምኑ ነበር።
ከዕለታት አንድ ቀን ቅድስት ሐና በቤቷ አትክልት ስፍራ ሳለች፣ አንዲት ርግብ ከልጆቿ ጋር ስትጫወት ተመለከተች። በዚያን ጊዜ ልቧ ተነክቶ፦ “አቤቱ ጌታዬ! ለዚች ግእዛን ለሌላት እንስሳ ልጅ የሰጠህ አምላክ፣ ምነው ለኔ ልጅ ነሳኸኝ?” ብላ ምርር ብላ አለቀሰች።
ከዚህ በኋላ ቅዱስ ኢያቄምና ቅድስት ሐና ወደ ሊቀ ካህናቱ ዘካርያስ ዘንድ በመሄድ ታላቅ ስዕለት ተሳሉ፦
“ወንድ ልጅ ብንወልድ ተምሮ ቤተ እግዚአብሔርን እንዲያገለግል፤ ሴት ልጅም ብንወልድ ውኃ ቀድታ፣ መሶበ ወርቅ ሰፍታ፣ መጋረጃ ፈትላ ካህናትን አገልግላ እንድትኖር ለእግዚአብሔር ቤት አገልጋይ እናደርጋለን” አሉ፤ ሊቀ ካህናቱ ዘካርያስም ጸሎታቸውን አሳርጎ ባረካቸው።
ሐምሌ 30 ቀን ቅዱሳኑ አስደናቂ ራእይ አዩ፦ ጻድቁ ኢያቄም፦ “ሰባት ሰማያት እንደ መጋረጃ ተገልጠው፣ ከላይኛው ሰማይ ነጭ ወፍ ወርዶ በራሴ ላይ ሲቀመጥ አየሁ” አለ። ቅድስት ሐና፦ “እኔም ነጭ ርግብ መጥታ በራሴ ላይ ወርዳ፣ በጆሮዬ ገብታ በማኅፀኔ ስትተኛ አየሁ” አለችው። ይህንን ራእይ ካዩ በኋላ “ፈቃደ እግዚአብሔር ይሁን” ብለው ዕለቱን አልጋና ምንጣፍ ለይተው ለሰባት ቀን ያህል በጸሎት ተለይተው ሰነበቱ።በሰባተኛው ቀን የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ለጻድቁ ኢያቄም በተራራ ላይ ሲጸልይ በተገለጸለት ጊዜ፦ “ሚስትህ ሐና ትፀንሳለች፤ ዓለሙ ሁሉ ደስ የሚሰኝባትን፣ ለብዙዎች የሕይወት ብርሃንና ድኅነት የምትሆን ሴት ልጅ ትወልድልሃለች” ሲል አበሰረው። መልአኩ ለቅድስት ሐናም ተገልጦ የጌታን ፈቃድ ነገራት። በብስራተ መልአክና በፈቃደ እግዚአብሔር፣ እሁድ ዕለት በነሐሴ 7 ቀን ከሰው ሁሉ የበለጠች፣ ከመላእክትም የከበረች፣ የዓለም ሁሉ መመኪያ የሆነችው አምላክን የምትወልደው እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በማኅፀነ ሐና ተፀነሰች። ✝️ ✝️ ✝️ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነትና በረከት፣ የቅዱስ ኢያቄምና የቅድስት ሐና ጸሎት አይለየን።🙏 ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ ▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰ የአ/አ/ሳ/ቴ/ዩ ግቢ ጉባኤ 📥 @gibigubaeHasabon_bot ጻፉልን 🏷 @aastugibigubae ተከታተሉን 📷 @GGgallery1 የፎቶ ማኅደራችን ▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰ TikTok | Instagram | YouTube
7 075
እንኳን ለጾመ ፍልሰታ አደረሳችሁ! 🕊✨
📌 ጾመ ፍልሰታ ምንድን ናት? ከነሐሴ 1 እስከ ነሐሴ 16 ቀን የሚጾመው ይህ ጾም፣ በቅዱሳን ሐዋርያት ሥርዓት የተሠራ፣ ሁላችንም በኅብረት ወደ እግዚአብሔር አምላካችንና ወደ እመቤታችን በጸሎትና በሱባኤ የምንቀርብበት መንፈሳዊ ወቅት ነው፡፡
📖 የጾሙ ታሪክና አመጣጥ · እመቤታችን በ64 ዓመቷ ካረፈች በኋላ ሐዋርያት ሥጋዋን ሊያሳርፉ ሲሄዱ አይሁድ በተንኮል ሥጋዋን ሊቀሙ በመሞከራቸው፣ መላእክት ክቡር ሥጋዋን ወደ ኤደን ገነት ወሰዱት፡፡ · ሐዋርያት በጾምና በጸሎት ሱባኤ ሲይዙ፣ በ14ኛው ቀን ጌታችን ሥጋዋን ሰጥቷቸው በጌቴሴማኒ ሥጋዋን አሳረፉ፤ በ3ኛው ቀንም እንደ ልጇ ሞትን ድል አድርጋ ተነሣች፡፡ · ሐዋርያው ቅዱስ ቶማስ ከሀገረ ስብከቱ ሲመለስ እመቤታችን በደመና ስታርግ ተመልክቶ ሰበኗን (መቀነቷን) ተቀበለ፡፡ · ሐዋርያትም ቅዱስ ቶማስ ያየውን ዕርገቷን ለማየት በዓመቱ ነሐሴ 1 ቀን እንደገና ሱባኤ ገብተው በ16ኛው ቀን ትንሣኤዋንና ዕርገቷን ለማየት በቅተዋል፡፡💡 ኦርቶዶክሳውያን የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ዕረፍትና ትንሣኤ በማሰብ፣ ከልጇ ከወዳጇ የሚገኘውን ጸጋና በረከት ተስፋ በማድረግ የአባቶቻችንንና የእናቶቻችንን ፈለግ ተከትለን በየዓመቱ ጾመ ፍልሰታን እንጾማለን፤ የምንችል ደግሞ ንስሐ ገብተን አስቀድሰን ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን እንቀበላለን፡፡ በዚህ ጾም በተለይ አረጋውያንና ሕፃናት ብቻ ሳይሆኑ፣ መላው ኦርቶዶክሳውያን ንስሐ ገብተን፣ ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን በመቀበል መንግሥቱን ለመውረስ መዘጋጀት ይኖርብናል፡፡ 🔔 በጾሙ ወቅት የሚደረጉ መንፈሳዊ አገልግሎቶች
🌌 ሌሊት፦ የአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ የሰዓታት ጸሎት ይደረጋል፡፡ ☀️ ቀን፦ የቅዱስ ኤፍሬም ውዳሴ ማርያም ትርጓሜ ይነበባል፡፡ ⛪️ ቅዳሴ፦ የአባ ሕርያቆስ ቅዳሴ ማርያም ይቀደሳል፡፡የእግዚአብሔር ቸርነት፣ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት፣ የቅዱሳን ሐዋርያት ጸጋና በረከት አይለየን፡፡" 🙏 መልካም የሱባኤ ጊዜ ይሁንልን!
7 075
ሰላም የእግዚአብሔር ቤተሰቦች፤ እንዴት ናችሁ!
በመጀመሪያ መልእክቱን ለማድረስ በመዘገየታችን ይቅርታ እንጠይቃለን🙏
ውድ የ2018 ዓ.ም የግቢ ጉባኤያችን ተመራቂ አባላት፤ እንዲሁም ከዚህ በፊት ተመርቃችሁ እስካሁን ወደ ምሩቃን ኅብረት የቴሌግራም ግሩፕ ያልተቀላቀላችሁ፣ ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን የተለያዩ የሥራ ዕድሎችን እና አስፈላጊ መረጃዎችን መከታተል ትችላላችሁ።የግሩፑ ሊንክ፦ https://t.me/+UWw7z5kW0cI1OTU0 ▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰ የአ/አ/ሳ/ቴ/ዩ ግቢ ጉባኤ 📥 @gibigubaeHasabon_bot ጻፉልን 🏷 @aastugibigubae ተከታተሉን 📷 @GGgallery1 የፎቶ ማኅደራችን ▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰ TikTok | Instagram | YouTube
7 075
የ Freelance አገልጋይነት በይፋ ተጀምሯል!💡 ለመሆኑ ‘ችሎታ የለኝም’ በሚል ሰበብ ከበረከት እየሸሻችሁ ነው🤔? . . .ነቢዩ ዮናስም እኮ ባህር ውስጥ እስኪገባ ድረስ ሰበብ ይደረድር ነበር! 😊
እኛ ጋር ግን ‘የምችለው ነገር የለም’ ብሎ መጨነቅ አይሰራም፤ ዋናው ፍላጎቱ ይኑር እንጂ እዚያው እያገለገላችሁ ፣ እየተማራችሁ ልምድ እያካበታችሁ ምርጥ ባለሙያ ትሆናላችሁ ።እንዲያውም የትም ቦታ ሆናችሁ፣ ባመቻችሁ ሰዓት በዲጂታል ዓለም ተጠቅማችሁ የምታገለግሉበት ልዩ የፍሪላንስ ዕድል ነው። አሁን ከምታውቁት የሶሻል ሚዲያ አጠቃቀም በላይ በተግባር የምታዩበትና ጥበብን ለክርስቶስ የምትሰጡበት ጊዜው አሁን ነው!" 🤔 እስኪ አስቡት! አናንተ በምታዘጋጁት ድንቅ የግራፊክስ ዲዛይን፣ በምትቀርጹት ቪዲዮ፣ በምታቀናብሩት ድምፅ ወይም በምትጽፉት ልብ የሚነካ ጽሑፍ ምክንያት አንድ ሰው በመርሐግብሩ ተማርኮ ወደ ቤተክርስቲያን ቢመጣና ቢቀደስ... ከዚህ በላይ ምን ትልቅ ጸጋ አለ? ሰዎችን ወደ እግዚአብሔር ቤት ማቅረብ ማለት እኮ ትውልድን ማዳን ነው! ቴክኖሎጂንና ሰማያዊ በረከትን በአንድ ላይ አጣምሮ ፍቅርና አንድነት ባለው የወንድማማችነት ኅብረታችን ውስጥ ለማገልገል አሁኑኑ ይከላከሉን።
ፍላጎት ብቻ ይበቃናል፤ የቀረውን እኛ ጋር ታገኛላችሁ። ‘እኔን!’ ብላችሁ ዛሬውኑ በሚዲያ ክፍላችን ተመዝገቡና የጥበብ ባለቤት ለሆነው አምላክ እናገልግል!😊🎯 በሚዲያ ቲማችን ውስጥ ከዚህ በታች በተዘረዘሩት ዘርፎች ለማገልገል ፦
📝 Content Creator 🎥 Cameraman 🎬 Video Editor 🎨 Graphics Designer 🎙️ Social Media Host & Scriptwriter📌 ለመመዝገብ ከታች ያለውን ሊንክ ይጫኑ፦ https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSf6ix5ckLZRxDvE8xiPvWYxvtoXP61o9gi4KyOm5_NbivLD2w/viewform?uspsharinouid= ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ ▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰ የአ/አ/ሳ/ቴ/ዩ ግቢ ጉባኤ 📥 @gibigubaeHasabon_bot ጻፉልን 🏷 @aastugibigubae ተከታተሉን 📷 @GGgallery1 የፎቶ ማኅደራችን ▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰ TikTok | Instagram | YouTube
