Jinka Polytechnic College
Open in Telegram
468
Subscribers
No data24 hours
+27 days
+2330 days
Posts Archive
ጂንካ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለቤት ዉስጥ ሥራ ሥምሪት ወደ ዉጪ ሃገር ለሚሄዱ የቅድመ-ስምሪትና የቅድመ-ጉዞ ግንዛቤ ማሳደጊያ ሥልጠና ለመስጠት እና ለማስመዘን ዝግጅቱን አጠናቆ ምዝገባ ጀምሯል፡፡
የምዝገባ ጊዜ ከሚያዚያ 9-19/2016 ዓ.ም
#ጂንካ_ፖሊ_ቴክኒክ_ኮሌጅ_የተቋም_ዉስጥ_ምዘናን_ለማዘመን_Digital_Examination_System_አበልጽጎ_ሥራ_አስጀመሯል
ምዘና የሥልጠና ጥራትን ለማረጋገጥ ወሳኙ ቁልፍ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ሆኖም በአግባቡ ካልተመራ በሚጠበቀዉ መጠን የሠልጣኞችን ብቃት ማረጋገጥ አይቻልም፡፡ ስለሆነም ቀደም ሲል የነበረዉን የተቋም ዉስጥ ምዘና ቱል ጥራት ችግር፣ ተቋሙ ለህትመት የሚያወጣዉ ወጪ ፣ ምዘና ለመስጠትና ለማረም የሚፈጀዉ ሰፋ ያለ ጊዜ እና ቀልጣፋ ያለሆነ የምዘና ሥርዓት የመሳሰሉት የምዘና ሥርዓቱን ዲጂታል ለመድረግ አስገድዷል፡፡ የዲጂታል ምዘና ሥርዓቱ በኮሌጁ የ ICT አሠልጣኞች የበለጸገ እና ቀደም ሲል ለአሠልጣኞችና ለሠልጣኞች በምዘና ሥርዓቱ ዙሪያ ሥልጠና እየተሰጠ ዝግጅት እየተደረገ የቆዬ ሲሆን ዛሬዉ ዕለት በቀን 13/07/2016 ዓ.ም በICT ዘርፍ ለ HNS level III ሰልጣኞች የማጠቃለያ የንድፈሃሳብ ምዘና በመሠጠት ሥራ ጀምሯል፡፡ ዛሬ በኮሌጃችን Digital Examination System ሲፈተኑ የቆዩ ሠልጣኞች ሲሲተሙ ለመጠቀም ቀላል እና ምቹ ዉጤታቸዉንም እንዳዩ እንደሆነ ገልጸዉ የምዘና ስርዓቱ በዚህ መልኩ እንዲቀጥል አመላክተዋል፡፡:
እንኳን ለአሪ ብሔረሰብ አዲስ ዘመን መለወጫ "ለድሽታ ግና" አደረሳችሁ እያልን እነሆ በተላለፈልን ጥሪ መሠረት ሁሉም የተቋሙ ማህበረሰብ በሰርቭስ ኮሌጅ ድረስ ከመጣ በኃላ በመሠባሰብ በጋራ ሆነን ወደ ጂንካ ሁለ ገብ ስቴድዬም ስለምንሄድ ከጠዋቱ 2:00 ኮሌጅ እንድንገኝ ጥሪ እናስተላልፋለን።
ካሣሁነን ጌታቸው የኮሌጁ ዲን።
የኮሌጃችን ማህበረሰብ እንኳን ደስ አላችሁ !! ጂንካ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በ2016 ዓ.ም በደቡብ ኢትዮጲያ ክልል ከሚገኙ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጆች በስራ አፈፃፀም አንደኛ በመውጣት የሰርተፊኬት ሽልማት ከእለቱ የክብር እንግዳና የክልሉ ቴ/ሙ/ት/ስ ቢሮ ኃላፊ አቶ አብዮት ደምሴ እጅ ተቀብለናል።
ይህ ውጤት በጋራ የመተባበር ስራ የተገኘ ስለሆነ በድጋሚ ኩራት ይሰማችሁ። በሚቀጥለው ዓመት ውጤታማነታችንን አስቀጥለን መስራት አለብን!!
