en
Feedback
ጦቢያ የግጥም መድብል

ጦቢያ የግጥም መድብል

Open in Telegram

አማራ ነኝ ያውም ትግሬ እንደ ሮሃ ተፈልፍዬ፣ልክ እንደ አክሱም ተገትሬ ምጠብቅሽ እልፍ ዘመን፣በጣይ እና በጨረቃ ስቀልድ ነው ኦሮሞ ነኝ፣ከተናገርኩ በሀቂቃ እንደውም ሁሉን ብሔር ነኝ፣ዘረኝነትን የምደቃ ዘሬ ሰው ነው፣ብሔሬም ሰው፣ሰው ነኝ በቃ ።።።።።።።።።። @WAS143 ይጎብኙ @WAS143 @WAS143 በቀጥታ ለማግኘት @WASYA @WASYA ማንኛውንም መልዕክት ለመላክ @WASYA

Show more
Ethiopia4 792The category is not specified
4 501
Subscribers
+424 hours
+467 days
+11330 days
Posts Archive
በእሾህ መንገድ መሀል (በእውቀቱ ስዩም) ያገሩ አየር ጠባይ፥ ቆላ ወይን -አደጋ ከላይ የሚያስፈራ፥ ከታች የሚያሰጋ ፥ አጉል ነው መንገዱ ቅጽሩም ሲገዝፍ ያድራል፥ በቁመት በወርዱ፥ እና ምን ይጠበስ? የማይቆም ጅረት ነኝ፥ የማይቀለበስ :: ቢገፏት ቢያዳፏት ከቅርንጫፏ ጋር የማትነጣጠል በወጀብ መሀከል፥ የምትደንስ ቅጠል፤ እንደዚህ ነኝ እኔ ምቾትስ ለምኔ ቀይ ምንጣፍ አያምረኝ ይመስገን ዘመኔ በእሾህ መንገድ መሀል፥ መጓዝ ላስተማረኝ :: @WAS143 @WAS143

ስግደት ለራስ አርባ ጊዜ ባከነብኝ ስጋ ወዜ። ተሳለምኩት መልኬን ባዋጅ ከንፈር ደርቆ እስከሚጃጅ። አመለኩት ክብር ዕውቀቴን አነደድኩት ትንሽ ቤቴን አነደድኩት ልጅነቴን አመድ ላይሆን ፍም ታቀፍኩኝ መኖር ሲኦል ተቃጠልኩኝ። ከየት ይምጣ? አዳኝ አባት አንዱ ላንዱ ሰው ከለባት። ተናከሰ ሰውነቴ። አንዱ ጣለኝ ሲለኝ። አንዱ ሳለኝ ሲለኝ። ተናከሰ ሰውነቴ የቱን ጥዬ? የቱን ልሳል? መሐል መሆን ነፍስ ያሳሳል። ኤልያስ ሽታኹን @WAS143 @WAS143

🍀🍀🍀 መርጌታ አለሙ የባህል ህክምና 0928934812 ትክክለኛዉን እና የቀደምት ሊቃውንት የአባቶቻችንን ጥበብ ይሻሉ ወይም ይፈልጋሉ ??0928934812 0928934812 እንግዲያውስ ከምንሰጣቸው የጥበብ አገልግሎት በትንሹ ከታች ተዘርዝረዋል 1  🍀🍀ለሀበት 2  🍀🍀ለመፈትሄ ስራ 3  🍀ለመስተፋቅር 4  🍀🍀ለስንፈተ ወሲብ 5  🍀🍀ለበረከት 6  🍀🍀 ለገቢያ 7  🍀🍀 ለትዳር እንቢ ላላቹሁ 8  🍀🍀 ለአይነ ጥላ 9  🍀🍀ለስልጣን 10🍀🍀ገንዘብ አልበረክት ላላችሁ 11🍀🍀ለግርማ ሞገስ 12🍀🍀ገንዘባቹሁን የተወሰደባቹሁ እንዲመለስላቹሁ የሚያደርግ 13🍀🍀አፍዝ አደንግዝ 14🍀🍀ለትዳር የሚሆን ኮኮብ ቆጠራ 15🍀ለሁሉ መስተፍቅር 16🍀🍀ለድምፅ 17🍀🍀ለብልት 18🍀🍀ለውጭ እድል 19🍀🍀 ወንድ ልጅ ብቻ እየወለዱ ሴት ልጅ መዉለድ ለተሳናቸዉ 20🍀🍀ለደም ግፊት 21🍀🍀ለመካንነት 22🍀🍀 ለህመም 23🍀🍀ኢቃማ ሳይኖራቹሁ ለምትንቀሳቀሱ እንዳትያዙ የሚያደርግ 24🍀🍀ሴት ልጅ ብቻ እየወለዱ ወንድ ልጅ መዉለድ ለተሳናቸዉ 25🍀🍀ለጥይት መከላከያ ወይም ጥይት እዳይመታ የሚያደርግ 26🍀እፀ መሰዉር 27🍀🍀ኤች አቪ ኤዲስን የሚያስወግድ ለሁለት ወር የሚወሰድ መድሀኒት ከምንሰጣቸዉ በትንሹ  ይህን ይመስላል     🍀 🍀በአካል መምጣት ለማትችሉ ወይም መዳኒቱን ለምትፈልጉ ከአገር  ውጭም  ሆነ  ከአገር ውስጥ  መዳኒቱን ባሉበት ቦታ እናደርሳለን   🍀🍀ልብ ይበሉ አንዳንድ ግለሰቦች በሀሰተኛ ግለሰቦች እየተጭበረበሩ  እደሆነ ደዉለዉ አሳዉቀዉናል እናም  ትክክለኛዉን የባህል መዳህኒት ለማግኘት እኛጋ ይምጡ 🍀🍀ለጥያቄ ይደውሉልን 🇪🇹 0928934812 0928934812

ትዝታ በትዝታ (በእውቀቱ ስዩም) ልጅ እያለን ከምወዳቸው በአላት አንዱ መስቀል ነው ፤ አመቱን ሙሉ ሰፈርተኛው በየወሩ የተወሰነ ብር ያዋጣል፤ በመዋጮው ብር የመስቀል ዋዜማ ሁለመናው ፍርምባና ሻኛ የሆነ በሬ ይገዛል፤ የመስቀል አነጋግ ላይ፥ ከሰፈራችን ራስጌ ያለች ሜዳ ላይ ይታረዳል፤ ረፋድ ላይ፥ የአበባ ጉንጉን የመሳሰሉ የቅርጫ መደቦች ሜዳው ላይ ይደረደራሉ፤ ሚስቶች ከቅርጫው ያልገባውን እጅግ ምርጥ የስጋ ብልት ቀነጫጭበው ወስደው አሳምረው ይከትፉታል፤ ከዚያ፥ ሜዳው ላይ ጉርድ በርሜል እሚያካክል ድስት ጥደው በአይነት በአይነት ይወጠውጣሉ፤ በማጀት ተወስኖ የቆየውን ሙያቸውን በይፋ ለማሳየት ይሽቀዳደማሉ፤ ምሳ ሰአት ላይ ወጡ፥ ጥብሱ፥ ዱለቱ ባይነት ባይነት ሆኖ በአባቶቻችን ፊት ይደረደራል:: የሰፈሩ ጉብላሊት ሴቶች ቤት እንዲጠብቁ ተፈርዶባቸዋል፤ ወንድ ልጆች ከዋዜማው ጀምሮ ስራ ይበዛብናል፤ በሬው በሌባ እንዳይሰረቅ ወይም ጠኔ ይሉንታ ያሳጠው ጅብ ጎኑን እንዳይዘበትረው ሌቱን ሙሉ ስንጠብቀው አድረናል፤ አሁን በቅርጫው ዙርያ የሚያንዣብቡትን አሞራዎች ስናባርር እንቆያለን፤ ባጭሩ የሰፈሩ የምድር ጦር እና የአየር ሀይል በኛ ቁጥጥር ስር ነው ፤ ለዚህ ሁሉ ተግባራችን ደሞዛችን ምንድነበር? እናቶች ከምግብ ወለል በታች፥ የሆነ “ መነኡኡ “ የተባለ ከበሬው አንጀት እና ደንዳኔ የተውጣጣ ምግብ ይሰሩልናል፤ መጀመርያ ምግቡን በፍቅር በሽምያ ነበር እምንበላው ፤ እየቆየን እየጎረመስን ስንሄድ እየደበረን መጣ ፡ ፡ አባቶቻችን ማእድ ለመሳተፍ ከፍተኛ ምኞት ተቀሰቀሰብን፥ አንድ ቀን አብሮ አደጌ እንዲህ አለኝ:: “ትምርት ቤት እንደምናደርገው ፤ አጭር ድራማ አዘጋጅትን እናዝናናቸው ፤ እንደሚያስቡት ትንንሽ ልጆች አለመሆናችንን ካሳየናቸው፤ ከሚበሉት ያበሉናል” ተስማማሁ፤ አራት ልጆች መለመልሁ፤ የድራማው ዝግጅት ስድስት ወር ገደማ ፈጀብን:: በቀጣዩ መስቀል ፥ የጋራ ምሳው ማእድ ከፍ እንዳለ፥ ካደፈጥኩበት ወጣሁና ለአዋቂዎች ፊት ቆምኩ፤ የትሪው የቢላዋውና የብርጭቆው ንክኪ ከሚፈጥረው ድብልቅልቅ በላይ ድምጤን አጠብድየ፥ “ከፈረስ አፍንጫ አይገባም ትንኝ ተመልካቾቻችን ጤና ይስጥልኝ “፥ ብየ ልቀጥል ስል ፥ የእርሻ መምህሩ ጋሽ የኔነህ ጣቱ ላይ የቀረውን ድልህ በሳር ያበሰ፥ “ አንተ ስልባቦት! ምናለ ብትተወን ብንጫወትበት “ ሲል ሰማሁት፤ የተመኛችሁትን የምታገኙበት በአል ይሁንላችሁ ወገን! @WAS143 @WAS143

"ንቀት" ንፋስ ቤቱን ሞላው ተንሳፈፍን እንደደላው:: ጥጋብ ፍሙን አፋፋምነው እሳት ትተን "ሰውን" ምስኪን አጠፋነው:: ተሳለቅን በየተራ ለቅሶ ድንኳን አፈረሰን "ነፍስ ይማርን" አሳነስን:: ዕንባ ላይ ደነስን:: እዚህ ሀገር “እውቀት” ነኝ እያለ “እምነት” ነኝ እያለ “ክብር” ነኝ እያለ “ዝና” ነኝ እያለ “ስልጣን” ነኝ እያለ በየሰው ጀርባ የተጠቀለለ የዕንባ : ንቀት : አለ:: @WAS143 @WAS143

"ስለሌለሽ አይደል?" ኤልያስ ሽታኹን ~ ~ ~ ~ ሌሊት ስድስት ሰዓት የመናፈቅ መዓት በድቅድቅ ጨለማ እቅፍሽ የለማ ቢኖርማ ኖሮ የማንም ድሪቶ ባልመጣ ከኔ በር ንፋስ ጌታ ሆኖ ባላዘዘኝ ነበር ስለሌለሽ አይደል? እንዲህ ባልነበርኩኝ የፌስታል ሽወታ ደጄ ድረስ መጥቶ እንዴት ቤቴ ገባ ውርጭ አቅም አጊንቶ? ስለሌለሽ አይደል? ነፍሴን ብቸኝነት አልምዶ ቢያፀናኝ የሴተኛ አዳሪ ጩኸት ባላስቀናኝ:: ስለሌለሽ አይደል? @WAS143 @WAS143

"አልወድሽም" ኤልያስ ሽታኹን ~ ~ ~ ~ "ቋ ቀጭ ቋ ቀጭ" ህይወት መጣች ሳቋን ይዛ አልቆየችም እንደ ጤዛ ... እቅፍ ሳም አንገቴ ስር ለወጠችኝ በቀይ ምስር .... ተሸጥኩላት ባገኘችው ተሞኘሁኝ እንዳለችው.... (አልወድሽም) ቋ ቀጭ ቋ ቀጭ ጫማዋን አወለቅች ልብሷን አወለቀች አብራኝ ተኛች አወላልቃ እኔ ከፋኝ እርሷ ስቃ (አልወድሽም) ህልሟ እንደጠፋባት እንደልጃገርድ ወዴት ለመሄድ ነው ከአልጋዬ የምወርድ? ወዴት ? ህይወት ራሷ ናት አንገቴን ብትቀላ በሰው ተመስላ:: ህይወት ራሷ ናት ውሸት ብታሰላ ሞቴን ያስመኝችኝ ፍቅር አስመስላ:: ህይወት ውሸት አሞኝችኝ ገላ ነፍሴን ቀደድችኝ አጎነበስኩ እንደስንዴ ይወጋኛል ዕንባ ቀንዴ "ህይወት በቃኝ" ስል ሰማችኝ ሳቀችብኝ እያየችኝ:: (አልወድሽም) እጠጋበት ባጣም እተኛበት ባጣም እሞትበት ባጣም እስቅበት ባጣም አለቅስበት ባጣም እናቅበት ባጣም እንደወደድ ባጣም እደርስበት ባጣም ከእቅፍሽ ባልወጣም ወዴትም ባልሸሽም ማርያም ምስክሬ ህይወት አልወድሽም:: አልወድሽም አልወድሽም አልወድሽም @WAS143 @WAS143

🍀🍀🍀 መርጌታ አለሙ የባህል ህክምና 0928934812 ትክክለኛዉን እና የቀደምት ሊቃውንት የአባቶቻችንን ጥበብ ይሻሉ ወይም ይፈልጋሉ ??0928934812 0928934812 እንግዲያውስ ከምንሰጣቸው የጥበብ አገልግሎት በትንሹ ከታች ተዘርዝረዋል 1  🍀🍀ለሀበት 2  🍀🍀ለመፈትሄ ስራ 3  🍀ለመስተፋቅር 4  🍀🍀ለስንፈተ ወሲብ 5  🍀🍀ለበረከት 6  🍀🍀 ለገቢያ 7  🍀🍀 ለትዳር እንቢ ላላቹሁ 8  🍀🍀 ለአይነ ጥላ 9  🍀🍀ለስልጣን 10🍀🍀ገንዘብ አልበረክት ላላችሁ 11🍀🍀ለግርማ ሞገስ 12🍀🍀ገንዘባቹሁን የተወሰደባቹሁ እንዲመለስላቹሁ የሚያደርግ 13🍀🍀አፍዝ አደንግዝ 14🍀🍀ለትዳር የሚሆን ኮኮብ ቆጠራ 15🍀ለሁሉ መስተፍቅር 16🍀🍀ለድምፅ 17🍀🍀ለብልት 18🍀🍀ለውጭ እድል 19🍀🍀 ወንድ ልጅ ብቻ እየወለዱ ሴት ልጅ መዉለድ ለተሳናቸዉ 20🍀🍀ለደም ግፊት 21🍀🍀ለመካንነት 22🍀🍀 ለህመም 23🍀🍀ኢቃማ ሳይኖራቹሁ ለምትንቀሳቀሱ እንዳትያዙ የሚያደርግ 24🍀🍀ሴት ልጅ ብቻ እየወለዱ ወንድ ልጅ መዉለድ ለተሳናቸዉ 25🍀🍀ለጥይት መከላከያ ወይም ጥይት እዳይመታ የሚያደርግ 26🍀እፀ መሰዉር 27🍀🍀ኤች አቪ ኤዲስን የሚያስወግድ ለሁለት ወር የሚወሰድ መድሀኒት ከምንሰጣቸዉ በትንሹ  ይህን ይመስላል     🍀 🍀በአካል መምጣት ለማትችሉ ወይም መዳኒቱን ለምትፈልጉ ከአገር  ውጭም  ሆነ  ከአገር ውስጥ  መዳኒቱን ባሉበት ቦታ እናደርሳለን   🍀🍀ልብ ይበሉ አንዳንድ ግለሰቦች በሀሰተኛ ግለሰቦች እየተጭበረበሩ  እደሆነ ደዉለዉ አሳዉቀዉናል እናም  ትክክለኛዉን የባህል መዳህኒት ለማግኘት እኛጋ ይምጡ 🍀🍀ለጥያቄ ይደውሉልን 🇪🇹 0928934812 0928934812

(ኤልያስ ሽታሁን) ከመኖሬ ዛፍ ስር የሰው ጥላ አያለሁ ማንም ስለሌለ የኔ ነው እላለሁ... ውሸት.... ከንጋቴ ረፋድ ከቁጭት ስጋደም ጥላዬን መራገም፡፡ እውነት... ጥላ.... ጥላህ ይርገፍ ዘላለም ህልምን ለመሬት አቀርቅር አትደግ....ባጭር ቅር፡፡ እረግምሀለሁኝ... ጥላዬን በፀሀይ ያቀለምከው ኬላ አብቅል አሜኬላ፡፡ እረግምሀለሁኝ.... የተውኩዋትን እሷ መቆሜን አሳብቦ ጥላ 'ሚያስታውሰኝ መከዳቴን ከብቦ ጥላ ጥላህ ይርገፍ አካሌን ስትስል ህልምክ ይጨናገፍ፡፡ እረግመሀለሁኝ.... እጄም ቅርፅ ሰራ ፀሀይን ተውሶ እግሬም ቅርፅ ሰራ ፀሀይን ተውሶ ልቤ ግና ሞቷል ከጥላው ስር ምሶ፡፡ እረግምሀለሁኝ .... ፀሀይን ሰደባለሁ መሬትን ሰድባለሁ አካሌን ረግማለው አካሏን........?እላለሁ:: ካንተ መኖር ቀድሞ በዚህ ትንሽ መሬት የርሷን ጥላ ነበር የማውቀው ተጋድሞ፡፡ ጥላዬ ጥላዋን ሲዘምር በቀትር ሲዘክር በመንፈስ ቀን እገባ ጀመር በተዘጋ መቅደስ በክርችሙ ታዛ አንዳንዱ መውደድህ ከዕድልህ ሲያድፍ ስትሞት የሚሞት ነው ትዝታ 'ሚያስታቅፍ፡፡ ካልሞትኩኝ የማይሞት ትናንቴ ይቆጣል ...መውደዴ ይቀጣል ታዲያንስ ወዳጄ የአካሌን ክፋይ ጥላዬን የት ልጣል? ፡ ፡ ፡ ነይልኝ ጠላቴ በጥላዬ ስለት ነፍሴ አይታረድ ነይልኝ ወዳጄ የምንረሳውን ትዝታን እንውለድ፡፡   @WAS143 @WAS143

ጉልበት ቆጥቢያለሁ (በእውቀቱ ስዩም) እንደ ልጅነቴ አክሮባት አልሰራ ልክ እንደታች አምናው ፥ ብረት አልጠመዝዝ ጠማማን አልገራ፥ ክንድ አልለካካ ፥ ከጎበዞች ጋራ እግሬ አጭር ተራምዶ፥ በረጅሙ አረፈ እግዜር እድሜ አይጨምር፥ አቅምን ካልሸረፈ : : ልቦናሽ ታውኳል? ‘የፈራው ደረሰ አቅሙ ተቀነሰ ይስለመለም ጀመር፥ እንደ ቁራጭ ሻማ፥ በነፋስ ክንፍ ፊት እንደተለኮሰ ‘ የሚል ፍርሀት ይዞሽ እንግድያውስ አይዞሽ! የሌለን ቢመስልም፥ ሀይልና ወኔ አለን፥ የምናስቀምጠው፥ ለክፉ ቀን ብለን :: ሲያምርሽ አፋፍሼሽ ፥ እስካልጋየ ድንበር ሲያምሽ ተሸክሜሽ ፥ እስካምቡላንሱ በር የምራመድበት ጉልበት ቆጥቢያለሁ፥ ከቁንጮ እስከ ሽበት @WAS143 @WAS143

ሰሞንኛ! (በእውቀቱ ስዩም) በቀደም የአባቶች ቀን ሲከበር ከሰባት አመት በፊት “ ለአባቴ “ ጽፌ በማለዳ ድባብ ውስጥ የታተመ ውዳሴ ግጥም እዚህ ግድም ሲዘዋወር ዋለ፤ በረከት ገበሬዋ የተባለች የተሳካላት ሴት ግጥሙን አነብንባ ለቀቀችው፤ በረከትን በስኬትዋ የሚቀኑባት፥ ወይም በግላቸው ምክንያት የጠመዷት ሰዎች ከግጥሙ ውስጥ አንዲት ቃል መዝዘው ዘመቱባት ፤ በረከት በምትችለው አስረድታለች፤ አሁን የኔ የባለቤቱ ተራ ነው፤ ላባቴ የጻፍኩት ግጥም ላይ “ሉሲፈር “ እሚል ቃል ተጠቅሚያለሁ፤ ትርጉሙ አሻሚ ለሆን እንደሚችል በመገመት በግርጌ ማስታወሻ ላይ ቃሉን የተጠቀምኩበትን አግባብ ማስቀመጥ አልረሳሁም፤ ሉሲፈር የሚለው ቃል መሰረቱ ሮማይስጥ ወይም ላቲን ነው ፤ የንጋት ኮከብ ወይም ያጥቢያ ኮከብ “ በሚል ይተረጎማል፤ ቬነስ የተባለቸው አንጸባራቂ ፕላኔት በዚህ ስም ስትጠራ ቆይታለች፤ በዚህ ረገድ፥ መጽሀፍ ቅዱስ ውስጥ የሚገኘው ትንቢተ ኢሳያስ የባቢሎን ንጉስ ሲናገር እንዲህ ይላል፤ “ አንተ የንጋት ልጅ ፤ አጥቢያ ኮከብ ሆይ! እንዴት ከሰማይ ወደቅህ ! አህዛብንም ያዋረድህ አንተ ሆይ እንዴት እስከምድር ድረስ ተቆረጥህ “ እያለ ይቀጥላል፤ አማርኛው የንጋት ልጅ ወይም ያጥቢያ ኮከብ እሚለውን የላቲኑ ትርጉም ሉሲፈር ይለዋል፤ የባቢሎኑ ንጉስ በቅጽል ስሙ “ ያጥቢያ ኮኮብ ወይም የንጋት ልጅ “ ተብሎ ይጠራ ነበር ፤ ባገራችንም ነገስታት “ ጸሀዩ ንጉስ “ ተብለው ይሞገሱ ነበር ፤ ለእቴጌ ምንትዋብ በነገሱ ጊዜ “ አሁን ወጣች ጀንበር ፤ ተሸሽጋ ነበር “ ተብሎ ተዘፍኗል ፤ ሀዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ በሁለተኛው መልክቱ ኢየሱስን ለመግለጽ ይሄንን ቃል ተጠቅሟል “ ምድርም እስኪጠባ ድረስ ፥ የንጋትም ኮከብ በልባችሁ እስኪወጣ ድረስ ፥ሰው በጨለማ የሚያበራን መብራት እንደሚጠነቀቅ ይህንን ቃል እየተጠነቀቃችሁ መልካም ታደርጋላችሁ” (ምእራፍ 1፤ 19) በሌላ በኩል፥ የካቶሊክ የስነመለኮት እና ባለቅኔዎች በሁዋለኛው ዘመን ኢሳያስ ስለ ባቢሎን ንጉስ የተናገረውን በመተርጎም ሉሲፈር የሰይጣን የቀድሞ ስም ነው የሚል ትረካ አስተዋውቀዋል፤ በርግጥ፥ ማርቲን ሉተርን ጨምሮ ታላላቅ የፕሮቴስታን አባቶች ይህንን ትርጓሜ አልተቀበሉትም፤ እኔ ባህላዊ እውቀቴን ባገኘሁበት የኢትዮጵያ አርቶዶክስ ተዋህዶ አስተምህሮ፥ የክፋት አውራ እንደሆነ እሚታመነው ፍጡር፤ ልዩልዩ ስሞች ይሰጡታል፤ ካልተሳሳትኩ ሄዋንን ያሳታት ሰይጣን” ተመን “ ይባላል፤ መጽሀፈ ሄኖክ የልዩልዩ አጋንንትን ስሞችን ሲዘረዝር ሉሲፈር እሚል አልጠቀሰም፤ ሰይጣን፤ ሳጥናኤል፤ ቢልዘቡል፤ ጸላኤ ሰናይ፥ እሚል አውቃለሁ፤ እኔ ገጣሚ ስለሆንኩ እያንዳንዷን ቃልና ዘይቤ በጥንቃቄ ለመምረጥ እሞክራለሁ፤ “ላባቴ” በተሰኘው ግጥሜ ላይ “ሉሲፈር “እሚለው ቃል “የንጋት ኮከብ “ የሚለውን እንዲገልጽ ተጠቅሜበታለሁ፤ ባንጻሩ ስለ ክፋት (evil) መጻፍ በፈለግሁበት ጊዜ ‘ሰይጣን” እና “ዲያብሎስ “የሚሉ ቃላትን ተገልግየባቸዋለሁ ፤ ለዚህ ማሳያ እዚያው የማለዳ ድባብ ውስጥ “ አባ ይፍቱኝ “ እሚለውን ግጥሜን እጠቅሳለሁ፥ “ አባ ይፍቱኝ ሰይጣን ብሎ ነገር ፥ የተጭበረበረ ዋዛ ነው ቧልት ነው ፥ ብየ አስብ ነበረ ይሄው እውነት ሆኖ ዋዛና ተረቱ ዲያብሎስን አየሁት፤በሸሚዝ ዘንጦ እልፍ ግዳይ ጥሎ፥ ቸብቸቦ ጨብጦ” (የማለዳ ድባብ ፥ ገጽ 75) ዛሬ ዛሬ፥ ሚድያ ከፍተው ከሞላ ጎደል ለአገሪቱ በጎ አስተዋጽኦ ያደረጉ ሰዎችን ስም በማጥፋትና ባልዋሉበት በመወንጀል የሚተዳደሩ ሰዎች አሉ፤ የግል ውድቀታቸውን ፤ ክፋታቸውን በሀየማኖት እና በሀገር ፍቅር ካባ ስለሚሸፍኑት የሚያዳምጣቸውና የሚከተላቸው አላጡም ፤ “ ዲያብሎስን አየነው በሸሚዝ ዘንጦ” እሚለው ሀረግ ደና አድርጎ ይገልጻቸዋል፤ የሚባንንባቸው ትውልድ እስኪመጣ ድረስ በቅደስና ስም ክፋትን እየነገዱ ይቆያሉ:: @WAS143 @WAS143

የወንድ ዱላ የሴት መላ (በእውቀቱ ስዩም) ስለ ጠለፋ በተነሳ ቁጥር ብልጭ እምትልብኝ ታሪክ አለች፤ የባለቅኔ መንግስቱ ለማ አባት አለቃ ለማ ተርከዋታል፤ ጊዜው በዘመነ መሳፍንት ሳይሆን አይቀርም፤ ከመንግስት የታዘዘ ጦር ከበጌምድር ወደ የጁ እየተመመ ነው፤ ሰራዊቱ ዋድላ ላይ ሲደርስ የሰራዊቱ መሪ አይናቸው አንድ ነገር ላይ አረፈ : : አንዲት ትንሽ ልጅ ከጓደኞቿ ጋራ ከገበያ ትመለሳለች፤ የጦሩ መሪ ሲያይዋት አለቅጥ ጎመዡ፤ አሸከራቸውን “ ያዝና ጫንልኝ “ ብለው አዘዙት፤ አሸከርየው እየጋለበ ደረሰባትና ብድግ አድርጎ ፈረሱ ላይ አፈናጠጣት ፤ ጓደኞቿ አካባቢውን በጩኸታቸው አቀለጡት : : እድለቢሷ ብላቴና ከደብረታቦር በታች ወደ ሚገኝ አገር ተወሰደች፤ የበጌምድሩ መኮንን ልጆችን አስወለዳት፤ በጥንቱ ልማድ ተጠላፊዋ ሀይለኛ ዘመድ ካላት በጠላፊ ላይ ይዘምታል፤ በዚህ ምክንያት ድንብን ያለ ጦርነት ሊቀሰቀስ ይችላል ፤ የዚች ልጅ አባት ግን ለውጤ ሀይሉ የተባሉ አንድ የዋድላ ደብተራ ነበሩ፤ አቅማቸውን ገምተው ዝም ያሉ ይመስላል፤ ተጠላፊዋ ባለችበት ሆና አገርዋን ልጅነቱዋን እና ቤተሰቧን ስትናፍቅ ኖረች፤ አንዳንድ ጊዜ የሆነ የቆሎ ተማሪ ደጇ ላይ ቆሞ “ በእንተ ማርያም ‘ብሎ ሲለምን ትሰማለች፤ እንጀራ ይዛ ትወጣና፥ “ከየት አገር ነው የመጣህ?” “ ከመቄት" “ለውጤ ሀይሉ የሚባል ሰው ታውቃለህ?" “ እሳቸውን ማን እማያውቅ አለ! እንደ ወንድማችን ናቸው “ “አባቴ ነው፤ ስታገኘው መጥተህ አትወስደኝም ወይ በልልኝ ! “ አባትየው ግን ገስግሰው መጥተው አልወሰዷትም፤ ተራኪው ከላይ በራሴ አማርኛ ያቀረብሁትን ታሪክ ሲደመድሙ እንዲህ በሚል ልብ ሰባሪ ቃል ነው፤ “’ እንዲህ እንደ ለፈለፈች ሞተች” 2 ታሪካችን ባያሌው የጦርነት ነው ፤ በጦርነት ያሸነፈው የተሸናፊውን ንብረት እና ሚስት ይማርካል፤ ዳግማይ ቴዎድሮስ በሀያልነታቸው አነጋግ ላይ የሸዋን ግዛት በጦር አስገበሩ፤ ያጤ ምኒክን አባት የሸዋው ንጉስ ሀይለመለኮት የድል አድራጊውን ፊት ከማየታቸው በፊት ታመው አረፉ: : ቴዎድሮስ በተሸናፊው ቤት ሰተት ብለው ገቡ፤ ሀይለመለኮት ሁለት ሚስቶች ጥለው ሄደዋል ፤ የመጀመርያዋ የምኒልክ እናት ወይዘሮ እጅጋየሁ ሲሆኑ ሁለተኛይቱ ወይዘሮ ትደነቂያለሽ የተባሉት ወይዘሮ ናቸው ፤ ትደነቂያለሽ እጅግ ውብ ነበሩ ይባላል፤ ቴዎድሮስ ባልየውን ሊማርኩ መጥተው በሚስቲቱ ተማረኩ፤ ግን ፍቅር አለዝቧቸው፥ አሽከራቸውን “ ያዝና ጫናት “ ለማለት ሳይደፍሩ ቀሩ፤ “ እቴጌ! በጌምድር አብረን እንሂድ” ብለው ጋበዟቸው፤ ሴት ያልፈለገችውን ሀይለኛ ወንድ የምታመልጥበት መሳርያ አላት፤ ያ መሳርያ መላ ወይም በሾፐንሀወር አገላለጽ “ ማታለል “ሊሆን ይችላል፤ ወይዘሮ ትደነቂያለሽ የአሸናፊውን ንጉስ ልብ በሚያቀልጥ ፈገግታ የታጀበ መልስ ሰጡ፤“ደስ ይለኛል ፤ ግን ከዛ በፊት ኢየሩሳሌምን ተሳልሜ ለመመለስ አስቢያለሁ፤ ይፍቀዱልኝ “ ንጉሱ ስንቅ ሰጥተው፥ አጃቢ ጨምረው ወደ እየሩሳሌም ሸኗቸው፤ ውቢተን ሸኝተው ወደ ቤታቸው ሲመለሱ የሀይለመለኮት እናት ወይዘሮ በዛብሽ ፤ “ሸዋ እንዲገብር እርዳታ አድርጊያለሁና ሹመት ይስጡኝ “ ብለው ጠየቁ፤ በዚህ ጊዜ ነበር አሸናፊው ንጉስ ከወደ ኢየሩሳሌም መርዶ የሚያክል ዜና የመጣላቸው፤ "ወይዘሮ ትደነቂያለሽ “ከሀይለመለኮት ወድያ አለም አልሻም ብለው መንነዋል “ ይህንን ሲሰሙ ቴዎድሮስ ይቺን ግጥም ወደ ታሪክ ወረወሩ፤ “አወይ ጉድ ሚስቱ መናኝ እናቱ ሹመት ለማኝ “ ታሪክ መዝጋቢው ዘንግቶት ይሆናል እንጂ ግጥሙ “ እኔን ብሎ ሰው አማኝ “ ብሎ የሚደመደም ይመስለኛል : : @WAS143 @WAS143

የእሁድ ጨዋታ (በእውቀቱ ስዩም) በቀደም “ የመጨረሻው ጥይት “ የተባለውን መጽሀፌን ጽፌ ጨረስኩ፤ ወዳጆቼን የማሳተምያ አዋጡ ስላቸው “ ዛሬ ማን መጽሀፍ ያነባል? ይልቅ! በድምጽህ ተርከውና በሰዋስው ይለቀቅ” ብለው ማበረታቻ አይሉት መጎተቻ ሀሳብ ሰጡኝ ፤ ለጊዜው የህትመቱን ነገር እርግፍ አድርጌ ትቼ፥ ለቤት ኪራይ የሚሆን ስራ እንዲያሰሩኝ ከዘፋኞች ጋራ መዋል ጀመርኩ:: ታድያ ባለፈው ሰብሰብ ብለን ስናወጋ አንድ የማደንቀውን የዜማ ደራሲ የሚከተለውን ጠየቅሁት፤ “ ስማ! ሹፌሮች ሲራራ ነጋዴዎችና አርቲስቶች ባንድ ሴት አይወሰኑም ይባላል፤ ርግጥ ነው፥ በድርሰቱ አለም ከኔና ከሀዲስ አለማየሁ በቀር በጭምትነት የሚኖር ያለ አይመስለኝም፤ ከዘፋኞች ውስጥ ሴት እማያተራምስ ማን ነው ?” ወዳጄ ትንሽ አሰበና ፥ “ እንጃ ! ምናልባት ታምራት ሞላ! “ የዚያን ቀን ምሽት ከምኡዝ ጋር ተገኛኝተን ስናወጋ ይህንን ዘገብኩለት፤ “ እስቲ ከታምራት ዘፈኖች ውስጥ የተወሰኑትን አስታውሰኝ “ አለኝ:: እኔ ታምሜ ተኝቼ ትናንትና ሌሊት በልሜ መጥተሽብኝ አይኔ ሲንከራተት ከእንቅልፌ ነቅቼ ፊቴን ብዳብሰው እንባየን በሙሉ ትራሴን አራሰው " 2 "ስንዋደድ አሀ ከልባችን መሞት ኑሩዋል መሀላችን " 3 እምባየ አልቆም አለ፥ ፍጹም አጣሁ ተስፋ ልበደል አላዝንም፥ መለየትሽ ከፋ 4 ማን ነበረ ቆንጆ ማን ነበረ አይናማ ታድያ ምናረጋል መሞት አይቀርማ ምእዝ ይህንን ሰማና እንዲህ አለ; “ ጋሽ ታምሜ እንዲህ አይነት “ሆረር “ ሲዘፍን ኖሮ አንዲት ሴት ማግኘት መቻሉ ራሱ ተመስገን ነው ! " ምኡዝ በአንባ የሚማረኩ ሴቶች መኖራቸውን ሳያውቅ ቀርቶ ነው? ድምጻዊ አበበ ተካ ተወዳጅ ዘፈኑን ያወጣ ጊዜ አስታውሳለሁ፤ አቤ ከድምጻዊነቱ በላይ ጥላው የሄደች ፍቅረኛውን እያሰበ በየመድረኩ ማንባቱ እጅግ ዝነኛ አድርጎት ነበር ፤ ትዝ እንደሚለኝ ካሴቱን ያወጣበት ዘመን የደስታ ዘመን ነበር፤ እና በጊዜው የሚያለቅስ ሰው ሲገኝ እንደ ብርቅ እንስሳ ይጎበኝ ነበር፤ አቤ ባነባ ቁጥር ሊያጽናኑኑት የተዘጋጁ ብዙ ሴቶች የክለቡን አዳራሸ ያጨናንቁታል፤ ይህንን ያስተዋሉት ድምጻዊ ይርጋ ዱባለ አንድ ቀን ወደ አቤ ሄደው እንዲህ አሉት፤ “ አቤ! ታንተ ጋራ አንድ ላይ የመድረክ ስራ ልሰራ ወስኛለሁ፤ ምን ታስባለህ? አንተ’ ሰው ጥሩ ሰው ጥሩ” እያልህ እያለቃቀስክ ፥ እኔ ጥራኝ ዱሩ እያልኩ እየፎካከርኩ ድፍን ጦቢያን በንብርክክ እናስኬደዋለን “ “ ለግብዣው አመሰግናለሁ! ግን እኔ እንኳን ብቻየን መስራት ነው የምፈልገው” አለ አቤ ቢለምኑት፥ ቢለምኑት ፍንክች አልል አለ፤ በመጨረሻ ጋሽ ይርጋ ተናደዱና እንዲህ አሉ፥ “ ይሁን ግዴለም! ይቺ እምባ እንደ ጥይት ስታልቅ እንተያያለን” @WAS143 @WAS143

የቱ ጋ ነው ጫፉ? (በእውቀቱ ስዩም) አየሩን ሲሞላው፤ ድቀት እና ሽንፈት እንኳን ባጭር ታጥቆ፥ ዱር ጥሶ መሸፈት ጉልበት ይፈትናል ፤ አይንን ከድኖ መክፈት :: በውሀካታው መሀል፥ አንቀላፋን ቆመን ሳንለፋ ደከመን፤ የት ጋ ነው ምእራፉ የቱ ጋ ነው ጫፉ ? -ይሄ ዳገት ዘመን :: @WAS143 @WAS143

ደላላው (በእውቀቱ ስዩም) “ እድሜና ደንቁርና ለራስ አይታይም “ የሚል ጥቅስ ፥ የሆነ ጊዜ ላይ፥ ወደ ወይራ ሰፈር የሚሄድ ባቡር ውስጥ ማየቴ ትዝ ይለኛል ፤ ባለፈው አራት ኪሎ ግድግዳ ላይ “ ሹገር ማሚ እና ሹገር ዳዲ አገናኝ “ እሚል ማስታወቂያ አየሁ፤ ባሁኑ ጊዜ የጽሁፍ ስራ አስተማማኝ ስላልሆነ ይህንን ነገር፥ የኑሮ መደጎምያ አድርጌ ልጠቀምበት እችላለሁ ብየ አሰብኩ የደላላውን ስልክ መዘገብኩት! በቀን ሁለቴ ሮጥኩ፤ ፑሽ አፕ ሰራሁ፤ ጢሜን ተቆረጥኩት፤ ጸጉሬን በቅባት አስተኛሁት ፤ ከዚያ በማበጠርያ ቀሰቀስኩት ! በመስታውት ፊት ቆምኩ፤ መልኬ ለክፉ አይሰጥም! በርግጥ ለበጎም አይሰጥም! ሹገሬን በሀሳቤ ሳልኳቸው! ደርባባ ወይዘሮ! ከሁለት ብልቃጥ ሜክ አፕ በላይ እማይቀቡ፥ ዘንጠው ከቤት ሲወጡ፥ ሽቷቸው ሙሉ ክፍለከተማውን የሚያውድ፤ ስማቸው ተናኘወርቅ ወይ ሌንሳ፥ ወይ አበረኸት ቢሆን ይመረጣል፤ ተገናኝተን አልጋውን ካተራመስነው በሁዋላ የሳር ትራስ የመሰለ ደረቴ ላይ ድፍት ብለው፥ የደረቴን ጸጉሮች እየቆነጠሩ “ ትንሽ ትንፋሽ ውሰድና ወደ ሰባተኛው ዙር እንሸጋገራለን “ ሲሉኝ “ እርስዎ ግን እኔን ይወዱኛል ! ?” ብየ ስመልስላቸው፥ “ እንዲህ ተግተህ ከኮተኮትከኝ ፤ ቱሉ ዲምቱ ላይ የማይፈርስ ባለ አራት ክፍል ቪላ አለኝ ፤ እሱን በደመወዝህ ላይ እመርቅልሀለሁ “ ሲሉኝ ፥ወዘተ ባይነህሊናየ ይመጣብኛል :: ከጥቂት ቀናት በሁዋላ አገናኙ ደላላ ጋር ተቀጣጥሬ ተገናኘሁ:: ገና ወንበር ከመያዜ ፥ደላላው፥ “ በሹገር ዳዲነት የስንት አመት ልምድ አለዎት?” @WAS143 @WAS143

ሰሞንኛ (በእውቀቱ ስዩም) የአብማይቱ ማርያም ያለህ! አፍሪካ ውስጥ መኖር መረገም ነው፤ ኢትዮጵያስ መቸም አንዴ በቃየን ድንጋይ ላይ የተመሰረተች አገር ናት፤ አሁን ሱዳንን የመሰለ ነባይ (ደግ) ሕዝብ” ፈጥኖ ደራሽ እና” ልክ በሰአቱ ደራሽ “ በሚል ተከፋፍሎ መገዳደል ነበረበት? ደሞ እሚገርመው ደሞ የተኩስ አቁም ስምምነት የሚፈራረሙት መሳርያ እጥረት ሲገጥማቸው መሆኑ ነው፤ “ ስማ” ይላል አንደኛው የመፈረምያ እስኪብርቶውን እያወጣ “ ከግብጽ ኦንላይን የሸመትኩት ሞርታር እስኪደርስ ነው እምታገስህ! ሞርታሩ በጄ ሲገባ አርህን ነው ማበላህ” ወድያኛው ደግሞ “ ወላሂ ታንኩን ካስበየድሁት በሁዋላ በስምምነቱ አልታሰርም! “ የሚባባሉ ነው እሚመስለኝ :: አድምጡኝማ! ባለፈው አንድ የልጅነት ባልንጀራየ ካስመራ መጥቶ ተገናኘን፤ እና ለጥቂት ቀናት ያክል ራስን የመከላከል ብቃት አስተማረኝ፤” አቡነ አሮን አያድርጉትና ፥ ማጅራት ሞቺዎች ከሁዋላህ ሞጥተው እዚች ጋ ኮቆሎፉህ እንዲህ አድርገህ ትፎታዋለህ “ እያለ የገዛ አንገቴን እየቆለመመ አሰለጠነኝ፤ ትናንት ፥ እዚህ አትላስ አካባቢ የታወቀ Bloom እሚባል ቁርስ ቤት ወሰድኩት፤” በሎም” ብሎ አነበበው ፤ የቁርስ ቤቱ አስተናጋጆች፥ ከምግብ ውጭ፥ የተለያየ ቅጠልና ፍራፍሬ የተደባለቀበት Detox የሚባል ውሀ ያቀርባሉ፤ እየበላን እያለ አስተናጋጂቱ መጣችና ፥ “ የሚጠጣ ምን ላምጣላችሁ?” “ ውሀ” አለ አብርሀ “ ዲቶከስ?” አብርሀ ቀና ብሎ ገላመጣትና “የምን ቶክስ? “ አኔ እምለው ጌታቸው ረዳ ፈረንጅ አገር ጫማ መደብር ገብቶ፥ ጫማ ሲገዛ ታየ ብላችሁ እሪ እምትሉ ሰዎች ግን ችግር አለባችሁ? ወይስ ራሳችሁ ስጋ -ለበስ ችግር ናችሁ? ሰውየው እንዳበበ ቢቂላ በቸርኬ እንዲሰግር ነው የፈለጋችሁ ወይስ ወደ አቻሬ ጫማ ጎራ ብሎ ከተረከዙ እስከ አውራጣቱ አስለክቶ እንዲያሰራ ነው የተመኛችሁለት? Give him a break ! ይላል ፈረንጅ ! አቦ ተውታ ይላል የሀረር ሰው! ጌች ማለት የተወረወረበትን ድሮን እንደ ቅዝምዝም ሽል ብሎ ያመለጠ ጅግና ነው! ጫማም ጮማም ተፈቅዶለታል! በነገራችን ላይ የጫማ ነገር ሲነሳ አንድ ነገር ትዝ አለኝ! የሆነ ጊዜ ያገራችንን ሰለብሪቲዎች ቤት እና ኑሮ የሚያስጎበኝ ፕሮግራም ነበር፤ አንድ ቀን። የሰራዊት ፍቅሬን ቤት አሳየን ! ሰራዊት ለጫማዎቹ ማስቀመጫ ብቻ አንድ ራሱን የቻለ ክፍል አለው፤ እኔ ደግሞ ልብስ በየሶስት ወሩ ብቀያይርም፥ ምቹ ጫማ ካገኘሁ ላመት አልፋታውም፤ ታድያ አንድ ቀን ግማሽ ፊቴን በማስክ ጋርጄ፥ በግሬ ስወዘወዝ መንገድ ላይ የሆነች ጠንበለል ልጅ " በዉቄ " ብላ ተመጠመችብኝ: : “ እኔ መሆኔን እንዴት አወቅሽ ?” ስላት የመለሰችው መልስ እከዛሬ ያስተክዘኛል ፤ “ ይሄን ጫማ ሚድያ ላይ ደጋግሜ አይቸዋለሁ” @WAS143 @WAS143

በመንገዳችን ላይ (በእውቀቱ ስዩም) በዚያ ሰሞን፥ በቦሌ መድሀኒያለም ጀርባ የተሰመረችውን ጎዳና ይዤ በእግሬ እወዘወዛለሁ፤ ብዙ ሳልርቅ፥ የእግረኞች መንገድ ላይ ሶስት የጎዳና አዳሪዎች ጎንለጎን ተደርድረው በጀርባቸው ተንዘራግተው እንቅልፍ ወስዷቸው ተመለከትኩ፤ አንድ በእድሜና በአካል የሚልቅ ብጢያቸው አጠገባቸው ቁጭ ብሏል፤ ሌላ አንድ ጎረምሳ ከ “ጽጌ” ሽሮ አቅጣጫ አንድ ፌስታል ሙሉ ፍርፋሪ ይዞ ደረሰ፤ ቁጢጥ ብሎ የፌስታሉን አፍ ለመክፈት ሲቃጣ ጠና ያለው ልጅ ወደ ተኙት ብላቴኖች በአገጩ እየጠቆመ እንዲህ ሲል አዘዘው፤ “ መጀመርያ እነሱን ቀስቅሳቸው !“ ደነቀኝ! ለምን ደነቀኝ? ሞልቶ ተርፎት ከማካፈል መድፋት የሚመርጥ ብዙ ሰው ያለበት አለም ውስጥ ነው እምንኖረው፤ ብዙዎቻችን በዚህ ጎረምሳ ቦታ ብንሆን ምንድነው የምናረገው? ነቅተው ሳይሻሙን እንበላ እንደምንል እገምታለሁ፤ ያንዳንድን ሰው ቸርነት እጦት እና ድሀነት አያከስመውም፤ በኔ ግምት ጠና ያለው ጎዳና አዳሪ ያንን ያደረገው ለታይታ አይደለም፤ የቲክቶክ ካሜራ እንዳላነጣጠረበት ያውቃል፤ ከተኙት ልጆች ደቃቃነት አንጻር ወጠምሻ እሚባል አይነት ነው፤ እና ብቻውን ቢበላ ፥ ቀጭም ሆነ ተቆጭ ያለበት አይመስልም፤ እንደመታደል ሆኖ፥ በመናመን ላይ ያለው የሰው ልጅ ህሊና እዚህ ልጅ ላይ ጨርሶ አልጠፋም፤ እንዲህ አይነቱ ትእይንት በሰው ልጅ ተስፋ እንዳትቆርጪ ያደርግሻል:: በአለማችን ሩህሩህ ሰዎች ብርቅ ናቸው፤ ርህራሄም ደረጃ አለው፤ ብዙ ሰው ፥ ለራሱ እና ለቤተሰቦቹ ብቻ ይራራል፤ ያንዳንዱ ሰው ደግነት ደግሞ ለጎረቤቱ ለወዳጆቹ ለዘመዶቹ ብቻ ተወስኖ ይቀራል ፤ ከሁሉ የላቀ መንፈስ ያላቸው ጥቂት ሰዎች ፥ ለሰው ዝርያ ብቻ ሳይሆን ለአራዊት አዋፋት ለነፍሳት ሳይቀር ቸርነታቸውን ያሳያሉ:: ሰዎች ሆድ የሚባል ጉድ የተገጠመልን ፍጡሮቸ ነን፤ ቢቸግረን ዶሮ ፥ በግ ፍየል በሬ አርደን እንበላለን፤ ግን ሳይቸግረን በእብሪት ወይም በግዴለሽነት ተነሳስተን የምናደርገው ጭካኔስ ምን ይባላል? ባለፈው እዚህ አክሱም ሆቴል ፊትለፊት ባለው መንገድ ላይ አንዱ አህያ እየነዳ ይሄዳል፤ አህያዋ በፍጥነት ትራመዳለች፤ ነጂው ግን በጎማ ዱላ እያከታተለ ይወግራታል፤ ለግማበት ነው እንዳልል በምትችለው አቅም እየተጣደፈች ነው፥ ሰውየው ከጭካኔ የተሻለ መዝናኛ ያለው አይመስልም፤ ወይም ደሀነቱ የፈጠረበትን ብስጭት እሚወጣው አገልጋዩን በመደብደብ ይሆናል፤ እስቲ ወደ ባለቤት አልባ ውሾች ተመልከቱ! አንድ አይኑ ያልጠፋ፥ ወይም እግሩ ያልተቀለጠመ ውሻ ማግኘት ይከብዳል! ከሩቅ ምስራቃውያን የመነጨ አንድ ፍልስፍና ሀሳብ እንዲህ ይላል፤ እኛ ሰዎች በዚህ አለም መኖር የምንፈልገውን ያህል አራዊት አእዋፍ እና ነፍሳት መኖር ይፈልጋሉ፤ ስለዚህ ሌሎች ፍጡራን ያንተ ብጤ ናቸው፥ ባንተ ልክ ተንከባከባቸው! ጋዜጠኛ ገነት አየለ ሸጋ አድርጋ፥ የተረጎመችውን የሚካኤል ዳባዲ ማስታወሻ ሳነብ ያገኘሁት አንድ ውብ አንቀጽ የድብርት መዳኒት ነው፤ ላጋራውና ልሰናበት፤ ደአባዲ የተባለ የፈረንሳይ አሳሽ የዛሬ ሁለት መቶ አመት ገደማ ጎጃም ሳርምድር ውስጥ አደን ለማደን ይሰማራል፤ ድንገት በለስ ቀንቶት አንድ አጋዘን ያይና አነጣጥሮ ሊኩስበት ሲዘጋጅ፥ በከፊል የተራቆተ ሰውየ ብቅ ይልና ተኩሱን ያደናቅፍበታል ፤ሰውየው በዳባዲ አጃቢዎች ተይዞ ሲመጣ በበረሀ የሚኖር ባህታዊ መሆኑ ይገለጣል፤ ባህታዊው አደኑን በማደናቀፉ ይቅርታ ከጠየቀ በሁዋላ እንዲህ አለ፤ “ይህ አጋዘን የከፋው(የተከፋ) እንስሳ ነው፤ በአቅራቢያ እያገሱ ያሉት ብዙ አንበሶች በጣም ያስጨንቁት ነበረ፤ ለኔ እንደ ባለንጀራየ ነው፤ አንዳንዴ በበረሀ አቁዋርጨ ስጓዝ ቀኑን ሙሉ እየተከተለኝ አብሮኝ ይሄዳል፤ አሁን በኔ ምክንያት ህይወቱ ድኖ ከሆነ ደስ ይለኛል “ @WAS143 @WAS143

የበልግ መባቻ ሀሳብ (በእውቀቱ ስዩም) ፈረቃው ፈርሶ ዘመን ተፋልሶ - -ካውራ መንገዱ ፥ ግንቦት ዶፍ ጣለ፥ ያለ ልማዱ የማይሆን ሆነ ዝናቡ ነግሶ፥ ዝንቡ መነነ:: ያንቺም መጭ እድል፥ ለሟርት አይመች በትናንትሽ ልክ፥ የማትገመች ለክስመት ሲያጩሽ፥ ለማበብ ቆየሽ አረጠች ሲሉሽ፥ አፍርተሽ ታየሽ :: ሊያነዱህ ሽተው፥ እየፈለጡ ወደቀ ብለው፥ ምሳር ሲቃጡ ዱር ሆነህ አድረህ ፥ ተራራ ሸፈንህ ሀመልማል ለብሰህ፥ በሁሉም ሰፈንህ:: @WAS143 @WAS143

ብቻ ናፍቀሽኛል እንደ ህፃን ልጅ ሳቅ ሳይገባኝ የህይወት ጣ'ም ሽርፍራፊ ደስታ ፊቴ ላይ ባላጣም እንደ አባት ፈገግታ እንደ እናቴ እቅፍ ናፍቀሽኛል ብዙ ናፍቀሽኛል እጥፍ አይኔ አንቺን ተራበ ሰው ፈለኩኝ እርሜን ናፍቀሽኛል ለጉድ እንጃ አከራረሜን እንጃ... እጠብቅሻለሁ ተዘገጃጅቼ ጊዜ መቁጠር ትቼ ሰዓት ማየት ትቼ አመቱን እረስቼ እጠብቅሻለሁ ያልኩሽ ቃል ሳይጎድል ትመጫለሽ አይደል ? ብቻ ናፍቀሽኛል:: (ኤፊ ማክ) @WAS143 @WAS143

ይህ ቀዥቃዣ ዝናብ ገላሽን ይንካና ወዮለት ሰማዩ ወዮለት ደመና ። ወፍ አይዘምርልሽ ዛፍ አያስጠልልሽ በቃ እኔ አለሁልሽ ። ደግሞ ይሄን እወቂ ሆዴ እንደሚበላኝ ካለ እኔ ስትስቂ እንቅልፍ እንደማጣ በፀሐይ ስትፈኪ ምራቄ እንደሚመር በእግዜር ስትመኪ ። እኔ ጠባቂሽ እኔ ነኝ ደስታሽ እኔ ነኝ ፈገግታሽ ሁሉንም የምሆን እግዜር አላህ ሰማይ ንፋስ ውሃ ድንጋይ ያንቺ ብቻ አገልጋይ ያንቺ ብቻ ታጋይ ። ክነፍ በዪኝ ልክነፍ እረፍ በዪኝ ልረፍ ብቻ ደስታሽ ሁሉ በእኔ በኩል ይለፍ ። @WAS143 @WAS143