የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)
Open in Telegram
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
Show more2 639
Subscribers
-224 hours
+37 days
+5630 days
Posts Archive
🔴ስንክሳር #መጋቢት_15
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
መጋቢት ዐሥራ አምስት በዚች ቀን የከበረች ተጋዳይ መነኰሳዪት #ቅድስት_ሣራ አረፈች፣ #ቅዱስ_ሰለፍኮስ በሰማዕትነት አረፈ።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#መነኰሳዪት_ቅድስት_ሣራ
መጋቢት ዐሥራ አምስት በዚች ቀን የከበረች ተጋዳይ መነኰሳዪት ሣራ አረፈች። ይቺም ቅድስት ከላይኛው ግብጽ ናት ወላጆቿም የክብር ባለቤት ክርስቶስን የሚያመልኩ ክርስቲያን ናቸው። እጅግም ባለጸጎች ነበሩ ነገር ግን ከእርስዋ በቀር ልጆች የሏቸውም በመልካም አስተዳደግም አሳደጓት ለክርስቲያን የሚገባ ትምህርትን ሁሉ አስተማሩዋት ደግሞም ጽሕፈትን አስተማሩዋት ሁልጊዜም የቤተ ክርስቲያንን መጻሕፍት ታነባለች ይልቁንም የመነኰሳትን ዜና ታነብ ነበር።
መጻሕፍትንም አዘውትራ ስለምታነብ የምንኲስና ልብስ ለመልበስ ፈለገች በላይኛው ግብጽ ከሚገኙ ገዳማትም ወደ አንዱ ገዳም ሒዳ ገባች ብዙ ዘመናትም ደናግልን እያገለገለች ኖረች።
ከዚህም በኋላ የምንኲስና ልብስን ለበሰች ሰይጣንን ድል እስከ አደረገችው ድረስ ሰይጣን የሚያመጣውን ሥጋዊ ፍትወት እየታገለች ዐሥራ ሦስት ዓመት ኖረች። ንጽሕናን ከመውደዷ ጽናት በተሸነፈ ጊዜ በትዕቢት ሊጥላት ወዶ በቤት መዛነቢያ ልትጸልይ ቁማ ሳለች ተገልጦ ሣራ ሆይ ሰይጣንን ድል አድርገሽዋልና ደስ ይበልሽ አላት እርሷም መልሳ እኔ ደካማ ሴት ነኝ ከክብር ባለቤት ከጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ በቀር ድል አድርጌ ላበረው አልችልም አለችው።
ይህችም ቅድስት አብረዋት ላሉ ደናግል ጥቅም ያላቸውን ብዙ ትምህርቶችን ታስተምራቸው ነበር እንዲህም ትላቸዋለች ከቀን ብዛት ጠላት እንዳያስተኝ እኔ እንደምሞት አስቀድሜ ሳላስብ እግሬን ከአንዱ መወጣጫ ደረጃ ወደ ሁለተኛም አውጥቼ አላኖራትም።
ዳግመኛም ለሰው ርኅራኄ ማድረግ በተሻለው ነበር ይህንንም በሚያደርግ ጊዜ የኋላ ኋላ በእግዚአብሔር ፈቃድ ውስጥ ይኖራል በዜና አረጋውያን መነኰሳት መጽሐፍ ውስጥ የተጻፈ ሌሎች ብዙ ቃሎችንም ተናግራለች።
ታላቅ ተጋድሎም እየተጋደለች በዓቷም በባሕር ዳርቻ ሁኖ ሰባት ዓመት ኖረች አንዲት ቀን እንኳ ከሰው አንዱም አላያትም እርሷ ግን ሁሉን ታይ ነበር። ሸምግላ እስከ ሰማንያ ዓመት በደረሰች ጊዜ ከዚህ ዓለም የሕይወት ማሠሪያ ተፈትታ የዘላለም ተድላ ደስታ ወደሚገኝበት ሔደች።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ቅዱስ_ሰለፍኮስ
በዚችም ቀን ዳግመኛ የቅድስት አስጠራጦኒቃ እጮኛዋ ቅዱስ ሰለፍኮስ በሰማዕትነት አረፈ።
የዚህን ቅዱስ ዜና ክርስቲያን እንደሆነ ከሀዲ ንጉሥ በሰማ ጊዜ ያመጡት ዘንድ አዘዘ ወደርሱም ሲቀርብ የአስጠራጦኒቃ እጮኛዋ ሰለፍኮስ የተባልክ አንተ ነህን አለው አዎን ነኝ አለ። ዳግመኛም ማንን ታመልካለህ አለው እርሱም እኔ የክብር ባለቤት የሆነ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን አመልከዋለሁ ብሎ መለሰ። ንጉሡም መርዝ ያላቸው እባቦች ወዳሉበት እንዲጨምሩት አዘዘ እግዚአብሔርም አዳነው።
ከዚህም በኋላ ራሱን በሰይፍ እንዲቆርጡት አዝዞ ቆረጡት በመንግሥተ ሰማያትም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበለ።
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ለዘለዓለሙ ይሁን አሜን፡፡
(#ስንክሳር_ዘወርኀ_መጋቢት)https://t.me/finotebirhan12
ማሠቃየቱንም በሰለቸ ጊዜ ራሱን በሰይፍ ቆርጠው ለውሾች እንዲጥሉት አዘዘ ውሾች ግን ፈጽሞ አልቀረቡትም ሌሊትም ሲሆን ምእመናን መጥተው ሥጋውን ወሰዱ በአዳዲሶች ልብሶችና በጣፋጭ ሽቶዎች ገነዙት በሣጥንም አድርገው ቀበሩት።ከሥጋውም ብዙዎች አስደናቂዎች ተአምራቶች ተደረጉ።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ቅዱሳን_አጋንዮስ_አውንድርዮስና_ብንድዮስ
በዚህችም ቀን ደግም የከበሩ አጋንዮስ አውንድርዮስና ብንድዮስ በሰማዕትነት አረፉ። እሊህም ቅዱሳን ከአባቶቻቸው ጀምሮ ክርስቲያኖች ናቸው አምላካዊ ትምህርትንም ሁሉየተማሩ ናቸው።
በእግዚአብሔርም ሕግ ጸንተው ሲኖሩ የኢየሩሳሌም ሊቀ ጳጳሳት ቅዱስ አርሞስ መርጦ ኤጲስቆጶሳት አድርጎ ሾማቸው ግን በታወቁ ቦታዎች ላይ አይደለም በብዙዎች አገሮች ውስጥ እንዲሰብኩ ላካቸው እንጂ። በሀገሮችም ያሉ ከሀዲያን ያዙአቸው ያለርኀራኄም አብዝተው ገረፉአቸው በደንጊያም ወገሩአቸው ነፍሳቸውንም በጌታችን እጅ ሰጡ።
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ለዘለዓለሙ ይሁን አሜን፡፡
(#ስንክሳር_ዘወርኀ_መጋቢት)https://t.me/finotebirhan12
🔴ስንክሳር #መጋቢት_14
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
መጋቢት ዐሥራ አራት በዚህችም ቀን #ቅዱስ_ቶማስ ሐዋርያ በአንዲት ሴት ላይ ተአምራትን አደረገ፣ የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት #የቅዱስ_ቄርሎስ የዕረፍቱ መታሰቢያ ሆነ፣ ከአረጋውያን ፍጹማን መነኰሳት ውስጥ አንዱ #ቅዱስ_አባ_ባጥል አረፈ፣ #ቅዱስ_አባት_አባ_ሲኖዳ በሰማዕትነት አረፈ፣ የከበሩ #ቅዱሳን_አጋንዮስ_አውንድርዮስና_ብንድዮስ በሰማዕትነት አረፉ፡፡
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ቅዱስ_ቶማስ_ሐዋርያ
መጋቢት ዐሥራ አራት በዚህችም ቀን ቅዱስ ቶማስ ሐዋርያ ሰባት ዓመት ያህል የጋኔን ግንኙነት በአስቸገራት በአንዲት ሴት ላይ ተአምራትን አደረገ። ሐዋርያ ቶማስንም የችው ጊዜ የክርስቶስ ሐዋርያው ሆይ እጅግ ከሚያሠቃየኝ ጠላት አድነኝ ብላ ወደርሱ ጮኸች።
እርሱም በምን ምክንያት አገኘሽ አላት እርሷም ከመታጠቢያ ከውሽባ ቤት ስወጣ እንደ ሰው ድው ድው እያደረገ በመታወክ መጣ ድምጡም ሰላላና ቀጪን ነው በሴትና በወንድ ሥራ ሁሉ ነይ እርስበርሳችን አንድ እንሁን አለኝ በተኛሁም ጊዜ በሌሊት መጥቶ ከእኔ ጋራ አንድ ሆነ ብሸሽም አይተወኝም መጥቶ ያሠቃየኛል እንጂ እኔም ከጸሎትህ የተነሣ አጋንንት እንደሚንቀጠቀጡ አውቃለሁና ጸልይልኝ አድነኝም አለችው።
ሐዋርያ ቶማስም ሰምቶ ጸለየ ጋኔኑንም ከእርሷ እንዲወጣ አዘዘው ያንጊዜም በእሳትና በጢስ አምሳል ከሴቲቱ ላይ ወጥቶ ተበተነ ከዚህ በኃላ በክርስቶስ መስቀል በላይዋ አማተበ ሥጋውንና ደሙንም አቀበላት ወደ ዘመዶቿም አሰናበታት።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#የቅዱስ_ቄርሎስ
በዚህች ቀን በእስክንድርያ ለተሾሙ አባቶች ሰባ አምስተኛ የሆነ የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት የቅዱስ ቄርሎስ የዕረፍቱ መታሰቢያ ሆነ። እርሱም በምግባሩ ፍጹም ዐዋቂ ሆነ ሀገሩም ፍዩም ይባላል በእርሷም ቅስና ተሹሞባት ነበር።
ከዚያም ለቆ ወደ አባ ፊቅጦር ገዳም ደረሰ እርሱም ከምስር ከተማ ውጭ የኢትዮጵያውያን ዐዘቅት የዐባይ ግድብ በአለበት ነው። በዚያም ታላቅ ገድልን እየተጋደለ ብዙ ዘመናትን ኖረ። ብዙ መጻሕፍትንም ተምሮ ትርጓሜያቸውንና ምሥጢራቸውን ጠንቅቆ ዐወቀ።
አሸናፊ ወደሚባለውም ንጉሥ አደባባይ ቀርቦ የእስላሞች ታላላቅ ሊቃውንቶቻቸውና ከምሁራኖቻቸው ውስጥ መምህሮቻቸው ተከራከሩት። ጠቃሚ የሆነ ዕውቀት የተመላበትን መልስ አገኙ የሚጠይቁትንም ሁሉ በመልካም አመላለስ ነገራቸው።
ከዚህ በኃላ የዕውቀቱና የቅድስናው ዜና በተሰማ ጊዜ ያለ ፈቃዱ ይዘው በእስክንድርያ ሊቀ ጵጵስና ሾሙት መንጋውንም ጠበቀ በጸሎትና በቅዳሴ ያገለግሉ ዘንድ ለካህናት ሥርዓትንና መመሪያን ሠራ። ይህም አባት በሊቀ ጵጵስናው ሰባት ዓመታት ከዘጠኝ ወር ከዐሥር ቀኖች ኖረ። ከቀኑም በሦስት ሰዓት አረፈ በምስክርነት አደባባይም ተቀበረ፡፡
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ቅዱስ_አባ_ባጥል
በዚህችም ዕለት ከአረጋውያን ፍጹማን መነኰሳት ውስጥ አንዱ አባ ባጥል አረፈ። ይህም ቅዱስ ሰው አባ ዮሐኒ የተባለ አበምኔት በመነኰሳት ላይ ነገረ ሠሪን እንደ ሚቀበል በሰማ ጊዜ በዓቱን ትቶ ወደ እስክንድርያ መጥቶ የሴት አዳሪዎችንና የአመንዝራዎችን ሁሉ ስማቸውን ጻፈ።
ከኪራይ ሠራተኞችም ጋራ ሲሠራ ይውላል። ደመወዙን በተቀበለ ጊዜ የሽንብራ ቂጣ ግዝቶ ይበላል የቀረውንም ገንዘብ ይዞ ወደ አንዲቱ ሒዶ ይሰጣታል በዚች ቀን ከአንቺ ጋራ አድራለሁና ራስሽን ለእኔ አዘጋጂ ይላታል። ከኃጢአትም ሊጠብቃት ከእርስዋ ዘንድ ያድራል ሌሊቱን ሁሉ ተነሥቶ ሲጸልይና ሲሰግድ እግዚአብሔርንም ሲለምን ያድራል ሲነጋም ሥራውን ለማንም እንዳትገልጥ አምሏት ወደ ተግባሩ ይሔዳል።
በየዕለቱም ወደ አመንዝራዎቹ እየሔደ እንዲህ ያደርግ ነበር አንዲቱም ሴት ምሥጢሩን ገለጠች ጋኔንም ይዞ አሳበዳት። ሰዎችም ስለዚህ ክፉ ሽማግሌ ክፉ ሥራ የለበትም ብላ ዋሽታለችና እግዚአብሔር መልካም አደረገባት ተባባሉ። እርሷም እንዳናመነዝር ገንዘብ በመስጠት ከኃጢአት ይጠብቀናል እንጂ ነውር የለበትም ብላ ነበርና።
የቀሩት አመንዝራዎች በእርሷ ላይ የሆነውን በአዩ ጊዜ ደነገጡ እንደርሷም እንዳያብዱ እውነቷን ነው ማለትን ፈሩ። እርሱም ይችስ በእገሌ ዕለት ትጠብቀኛለች ይል ጀመረ ሰዎችም ሁሉ ያሙት ጀመር እርሱም እንደ ሰው ሁሉ ሥጋ የለኝምን ወይስ እግዚአብሔር መነኰሳትን ተቆጥቶ በፍትወት ተቃጥለው እንዲሞቱ ትቷቸዋልን አላቸው።
እነርሱም ልብስህን ለውጠህ ሚስት አግባ ይህ ይሻልሃልና አሉት። እርሱም አዎን ብወድ በሚስቴ እጠነቀቃለሁ በዚህም በክፉ አኗኗር እኖራለሁ እናንተ ግን ከእኔ ዘንድ ሒዱ ምን ትሻላችሁ በእኔ ላይ እግዚአብሔር ፈራጆች አድርጓችኃልን ይልቁንስ እናንተ እንዳይፈረድባችሁ ለራሳችሁ አስቡ ፈራጅ አንድ ነውና ዕለቲቱም አንዲት ናትና አላቸው ይህም ቅዱስ በእግዚአብሔር ዘንድ ተቀባይነትን አገኘ በሰው ዘንድ ግን የተናቀ ሁኖ ኖረ።
ከእርሱ ጥቅም የአገኙ አመንዝራዎችም ዝሙታቸውን ተው። ከእርሳቸውም ሕራዊ ጋብቻ ተጋብቶ የኖረ አለ ወደ ገዳምም ገብቶ መንኵሶ በጾም በጸሎት ተወስኖ የኖረ አለ። በአንዲት ዕለትም ከአንዲት አመንዝራ ቤት ሲወጣ ያቺን ሴት አስቀድሞ የለመዳት አንድ ሰው አገኘውና ይህ ሽማግሌ እስከ መቼ ድረስ በዚህ በክፉ ሥራ ይኖራል ብሎ ፊቱን በጥፊመታው።
ከዚህም በኃላ በአንዲት ቀን በበዓቱ ውስጥ ሰግዶ ነፍሱንም በእግዚአብሔር እጅ ውስጥ ሰጥቶ በቤቱም መድረክ የዚች አገር ሰዎች ጊዜው ሳይደርስ በማንም ላይ አትፍረዱ እንዳይፈረድባችሁ የሚልም ጽሑፍ ተጽፎ ተገኘ።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ቅዱስ_አባት_አባ_ሲኖዳ
በዚህችም ቀን ደግሞ ቅዱስ አባት አባ ሲኖዳ በሰማዕትነት አረፈ። እርሱም በግብጽ አገር ከብሕንሳ ከተማ ነው ወደ መክስምያኖስም ክርስቲያናዊ ሲኖዳ አማልክትን የማያመልክ ነው ብለው ነገር ሠሩበት። እርሱም አስቀርቦ ስለ ሃይማኖቱ ጠየቀው በንጉሡም ፊት በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታመነ እርሱም ዕውነተኛ አምላክ እንደ ሆነም መሰከረ፡፡ መክስምያኖስም ይህን የከበረ አባ ሲኖዳን በምድር ላይ ዘርግተው በበትሮች እንዲደበድቡት አዘዘ። ዐጥንቶቹ እስቲሠነጠቁ ደሙም በምድር ላይ እንደ ውኃ እስቲፈስ እንዲሁ አደረጉበት።
ከዚህም በኃላ እግሩን ይዘው ጎትተው ወስደው ሽታው በሚከረፋ በጨለማ ወህኒ ቤት ጣሉት የእግዚአብሔርም መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ተገለጠለት። ቊስሎቹንም አድኖ ጤነኛ አደረገው አበረታውም በርታ አትፍራ ስለ መከራህም የክብር አክሊል ተዘጋጅቶልሃልና ደግሞም በጽኑዕ ሥቃይ ትሠቃይ ዘንድ አለህ እግዚአብሔር እንዳዘዘኝ እኔም ከአንተ ጋራ እኖራለሁ አለው ከዚያም ከእርሱ ተሠወረ።
በነጋ ጊዜም የነገሥታትን ትእዛዝ የሚተላለፍ ያንን ዐመፀኛ ሒዳችሁ እዩት ሙቶም ከሆነ ለውሾች ጣሉት ብሎ መክስምያኖስ ወታደሮቹን አዘዘ። ወደርሱም በደረሱ ጊዜ ቁሞ ሲጸልይ አግኝተውት ያለምንም ጥፋት ጤነኛ እንደሆነና በሥጋውም ውስጥ የሕማም ምልክት እንደሌለ እርሱም ከቶ ምንም ሥቃይ እንዳላገኘው እንደ ጤነኛና ደስ እንዳለው ሰው ተግቶ እንደሚጸልይ ስለርሱ ለንጉሡ ነገሩት።
ንጉሡም ወደርሱ አስመጣው ከሕይወቱም የተነሣ አደነቀ ልብሶቹንም አስወልቆ ያለጉዳት ጤነኛ እንደሆነ ሥጋውን አየ ደንግጦም ይህ ያየሁት ሥራይ ታላቅ ነው አለ። ከዚያም ዘቅዝቀው ሰቅለው ከበታቹ እሳትን እንዲአነዱ አዘዘ ይህንንም አደረጉበት ደግሞ በመንኰራኩር አሠቃዩት በአለንጋዎችም አብዝተው ገረፉት ደበደቡትም።
ዳግመኛም ጌታችን አባ መቃርስን መሥዋዕቱን ተሸክሞ በመሠዊያ ላይ ይቀድስ ዘንድ አዘዘው አባ መቃርስም ጌታችንን የሐዋርያት አለቃ አባታችን ጴጥሮስን እንዲቀድስ እዘዘው ይኽቺ ዕለት በከበረ ስምህ በዚች ደሴት ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ መሥዋዕት የተሠዋባት ናትና አለው።
ጌታም ላንተ ይገባል አንተ በዚች ደሴት ዘርተሃልና እኔም አሳደግሁ በደቀ መዝ ሙሬ በጳውሎስ አድሬ የተናገርኩትን አላስተዋልክምን የዘራና የደከመ እርሱ አስቀድሞ ፍሬውን ይብላ ያልሁትን አለው።
አባት መቃርስም የቅዳሴውን ሥርዓት ከጌታ ተባርኮ በጀመረ ጊዜ ከእስክንድርያዊ መቃርዮስ ጋራ ይራዱት ዘንድ ጴጥሮስ በቀኙ ማርቆስ በግራው ሁሉም ሐዋርያት በዙሪያው ቆሙ።ጳውሎስና ዮሐንስም የየራሳቸውን መልእክት አነበቡ ሉቃስም የሐዋርያትን ሥራ አነበበ ዳዊትም መዝሙሩን ዘመረ ለስም አጠራሩ ምስጋና ገንዘቡ የሆነ ጌታችንም ወንጌሉን አነበበ።በነጭ ርግብ አምሳልም መንፈስ ቅዱስ በኅብስቱና በውይኑ ላይ ወርዶ የጌታችን ክርስቶስን ሥጋና ደም ወደመሆን ለወጣቸው።
አባት መቃርስም ወደ ጽዋው ጣቱን በአስገባ ጊዜ ጣቱ በደም ታለለ።የመላእክት ሠራዊት ሁሉ በመሠዊያው ላይ ክንፋቸውን ዘርግተው ይራዱት ነበር ሚካኤልና ገብርኤልም መጡ የመላእክት አንድነት ሁሉም በእርሱ በአባት መቃርስ አምሳል ሁነው እየተራዱት ለሕዝቡ የከበረ ሥጋውንና ደሙን አቀበለ። ከቁርባን ሥርዓት ፍጻሜ በኃላ ጌታችን ፈጣሪያችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመቃርስ አምሳል ሁኖ ወንጌል በሚነበብበት አትሮንስ ላይ ተቀመጠ ፊቱም እንደ ፀሐይ ይበራ ነበር ለሕዝቡም ቡራኬ ሰጥቶ ወደ መሠዊያው ተመለሰ ሐዋርያትም ከርሱጋራ።
ዳግመኛም ከሰባት ቀኖች በኃላ አባታችን መቃርስ ስለ ቤተ ክርስቲያን የሹመት ማዕርግ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ የክብር ባለቤት እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስም ተገልጦ በእኔ ዘንድ ለዚህ ታላቅ ክብር የምትገባ አንተ ነህና አለው።
ሽማግሌውም ሰምቶ አለቀሰ በእግዚአብሔርም ፊት ሰገደ አቤቱ በሲሐት ገዳም ወዳሉ መነኰሳት ልጆችህ ጊዜው ሲደርስ እመልስሃለሁ ከዚህ ከሥጋህ ሳትለይ ያልከኝን አስብ።ይህ ካልሆነ መቃራ የምንኲስናውን ሥራ ትቶ ፓትርያርክ ሆነ ይላሉ አለ። ጌታችንም የመረጥኩህ መቃርስ ሆይ እኔ የልብህን ፍላጎት ሁሉ እፍጽምልሃለሁ ግን ፓትርያርክ ትሾም ዘንድ ከልጆችህ የመረጥከውን አንድ አቅርብ አለው። ቅዱስ መቃርስም አቤቱ አንተ ልብ ያሰበውን የምታውቅ ነህ እኔ ግን ወደዚህ አንጥረኛ ሽማግሌ ሰው ተመለከትኩ። እርሱ በቀናች ሃይማኖት የጸና ከሴቶችም ጋር ግንኙነት የማያውቅ ነው አለው ጌታችንም አንተ እንዳልክ ደግ ነው አለ። ቅዱስ መቃርስም ያንን አንጠረኛ ጠርቶ ወደ ታቦተ ሕጉ አቀረበው ያን ጊዜም ወንጌላዊው ማርቆስ መጣ እጁንም በአንጠረኛው ራስ ላይ ጭኖ ዲቁና ሾመው። ደግሞ ቅስና ሾመው ከዚያም የሊቀ ጵጵስና ሹመት እስከ ሚፈጽም በየመዐርጉ ሾመው ስሙንም ዮሐንስ አለው የሰማይ ሠራዊትም ሁሉም የወንጌላዊ ማርቆስ አዲስ ተክል የሆነ ለመቃርስ ልጅ ለዮሐንስ ሊቀ ጵጵስና ይገባዋል ይገባዋል ይገባዋል እያሉ ሦስት ጊዜ ጮኹ በዚያ ያሉ ሕዝብም እሊህን ቃሎች ይሰሙ ነበር።
ጌታችንም የሊቀ ጳጳሳት የዮሐንስን ዓይነ ልቡናውን ገልጦለት በሚቻለው መጠን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን አየው።ብዙ ቃላትንም ተናገረ ደግሞ ረቂቃን በሆኑ በሰማይ ሠራዊት ቤተ መቅደሱ ተመልቶ አየ የከበሩ ነቢያትና ሐዋርያትም በዚያ አሉ።
ከዚህም በኋላ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታላቁ አባ መቃራንና የእስክንድርያውን አባ መቃራን ጠራቸው እንዲህም አላቸው በምድር ሳሉ መታሰቢያችሁን የሚያደርጉ ሰዎች የተመሰገኑ ናቸው የዘላለም ሕይወትን ይወርሳሉና በራሴ እምላለሁ ስለ ስሜ የተቀበላችሁትን መከራ በትጋት የሚአስበውና የሚጽፈው የሚሰማው ሁሉ ያመሰግነኝ ዘንድ በቤተ ክርስቲያን የሚያነበው እኔ በጎ ነገርን ሁሉ እሰጠዋለሁ። ከበጎ ነገርም ምንም አላሳጣውም ከመከራውም ሁሉ አድነዋለሁ ኃጢአቱንም ሁሉ አስተሠርይለታለሁ። ከዚህ ዓለምም በሚለይለት ጊዜ ነፍሱን ወደ ዘላለም ተድላ ደስታ ይወስዱ ዘንድ እናንተ ወደም ታስቡትም መንግሥቴ ሊአስገቡት የምሕረት መላእክትን እልካለሁ።
በገዳም ወይም በኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ወይም በአገር ውስጥ ይህ ዜናችሁ በሚነበብበት እኔ አድራለሁ በረከቴንና ሰላሜንም እስከ ዓለም ፍጻሜ በውስጥዋ አደርጋለሁ። ለዚህ ለስደታችሁ ዜና ተቃራኒ የሚሆን ባልተወለደ በተሻለው ነበር። በእውነት እነግራችኋላሁ በሰው ፊት እንደአመናችሁብኝ በሰማያት በአለው አባቴ ፊትና በከበሩ መላእክቶቼ ፊት አምንባችኋለሁ። አሁን ግን ወደ ሀገራችሁ የምትመለሱበት ጊዜ ደረሰ ይህንንም ብሎ ሰላምታ ሰጥቷቸው ወደ ሰማይ በክብር ዐረገ።
ከዚህ በኋላ ሕዝቡን ሁሉ ንጉሡንም ሰበሰቧቸው ወደ አገራቸውም እንደሚመለሱ ነገሩአቸው የክርስቶስንም ሕጉን ሁሉ እንዲጠብቁ ለሊቀ ጳጳሳቱ ዮሐንስም እንዲታዘዙ አዘዙአቸው።ከቀናች ሃይማኖት ወደ ቀኝም ቢሆን ወደ ግራም ፈቀቅ እንዳይሉ በብዙ አማፀኑአቸው አስጠነቀቋቸውም። ሕዝቡም ሰምተው ደነገጡ መሪር ልቅሶንም አለቀሱ ቅዱሳን አባቶቻችንም ከእሳቸው ጋራ በአንድነት አለቀሱ ከእዚህም በኋላ እየአንዳንዳቸውን ባረኳቸውና ተሰናበቷቸው።
ያን ጊዜም ከኪሩቤል ወገን የሆነ መልአክ መጣ አውጥቶም በክንፎቹ ተሸከማቸው ወደ እስክንድርያም አድርሶ በሊቀ ጳጳሳቱ ደጅ እሑድ ጥዋት አወረዳቸው።ሊቀ ጳጳሳቱ አባ ጢሞቴዎስም ሰምቶ እጅግ ደስ አለው።ሁለተኛም በአያቸው ጊዜ አለቀሰ ሰገደላቸውም እነርሱም ሰገዱለት እርስ በርሳቸውም እጅ ተነሣሥተው ሰላምታ ተለዋወጡ። ጤንነታቸውንም ተነጋገሩ ደግሞም ልዩ የነበሩ የአሕዛብን ወደ እግዚአብሔር ስለመመለሳቸውና ስለ ተደረጉት ድንቆች ተአምራት ነገሩአቸው።ሊቀ ጳጳሳቱ አባ ጢሞቴዎስና ይህን የሰሙ ሁሉም ሕዝብ አደነቁ እግዚአብሔርንም አመሰገኑት አባቶቻቸንም በዚያ ስምንት ቀን ተቀመጡ።
ከዚህም በኋላ ያ መልአክ ተገልጦ በክንፎቹ ደግሞ ተሸከማቸው ወደ ደብረ ሲሐትም አደረሳቸው አንዱ ኪሩብም ከአየር ሁኖ የአባት መቃርስ ልጆች ሆይ አባታችሁ የመንፈስ ቅዱስን ፍሬዎች ተሸክሞ ከስደት ተመልሶ መጥቷልና ወጥታችሁ ተቀበሉ እያለ ጮኸ፡፡ ይህንንም በሰሙ ጊዜ ከታላላቆች እስከ ታናናሾች ወጡ ቁጥራቸውም አምሳ ሺህ መነኰሳት ሆኑ። ከውስጣቸውም በዚያን ጊዜ አባ ዮሐንስ ሐፂርና አባ ብሶይ አሉ የደረሰባቸውንም ሥቃይ በነገራቸው ጊዜ እጆቹንና እግሮቹን እየሳሙ መሪር ዕንባ አለቀሱ። ደግሞ ፊቱን ስለአዩ ደስ አላቸው እርሱም በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ባረካቸው።
የክርስቶስ ወገን የሆናችሁ በዓለሙ ሁሉ የምትገኙ ምእመናን ሆይ በዘመናት ሁሉ በዓል እያደረጋችኋት በዚች ዕለት ደስ ሊላችሁ ይገባል።ይህም ለአምላካችን ክርስቶስ ስለ ስሙ ደማቸውን እንዳፈሰሱ እንደ ጴጥሮስና እንደ ጳውሎስ መታሰቢያ ለእሊህ ታጋዮች አባቶች ለመከራቸው መታሰቢያ እንዲሆን።
እሊህም ታላቁ አባ መቃርስና ባልንጀራው የእስክንድርያው አባ መቃርስ ናቸው በዚች በመጋቢት ወር በዐሥራ ሦስተኛ ቀን ሉክዮስ ከእስክንድርያ አስቀድመን ወደ አወሳናት ደሴት አጋዛቸው ደግሞ በዚሁ ቀን ተመልሰው ወደ እስክንድርያ ደረሱ ።https://t.me/finotebirhan12
🔴ስንክሳር #መጋቢት_13
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
መጋቢት ዐሥራ ሦስት በዚህችም ቀን የታላቁ አባት #የቅዱስ_መቃርስ እና #የቅዱስ_መቃርዮስ_ዘእስክንድርያ የስደታቸውን መታሰቢያ ነው፣ የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት #ቅዱስ_ዲዮናስዮስ አረፈ፣ የከበሩ #ቅዱሳን_አርባ_ሐራ ሰማይ በሰማዕትነት አረፉ፡፡
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ታላቁ_ቅዱስ_መቃርስ እና #ቅዱስ_መቃርዮስ_እስክንድርያዊ
መጋቢት ዐሥራ ሦስት በዚህችም ቀን ኦርቶዶክሳውያን ሰዎች የታላቁ አባት የመቃርስን የእስክንድርያው የመቃርዮስን የስደታቸውን መታሰቢያ ያከብራሉ። ይህም በሮም መንግሥት ከወንድሙ ከዋልጥስ በኋላ በነገሠ ጊዜ በኦርቶዶክሳውያን ምእመናን ላይ ስደትንና መከራን አመጣ።የረከሰ የማኒንና የከሀዲው አርዮስን እምነት ስለሚከተል ነው ለእስክንድርያም ሉክዮስን ሊቀ ጳጳሳት አድርጎ ሹሞ ሐዋርያዊ አትናቴዎስን አሳደደው።
ይህም ከሀዲ ሉክዮስ ታላቁን አባት አባ መቃሪን እስክንድርያዊውን አባት መቃርዮስን ፈልጎ በንጉሥ ትእዛዝ ወደርሱ ከገዳማቸው አስመጣቸው። ወደርሱም በደረሱ ጊዜ ለያይቶ በለሰለሰ አንደበት በመሸንገል ወደረከሰ የአርዮስ ሃይማኖት ይገቡ ዘንድ አግባባቸው። እነርሱ ግን ወደ ነገሩ አልተመለሱም ሳይፈሩትም መለሱለት በቅንነትና በትዕግሥትም መከሩት ገሠጹት እንጂ የአርዮስንም ሃይማኖት ብላሽነት የባህሉንም አስከፊነት ከቅዱሳት መጻሕፍት ለይተው አስረዱት።
በዚያን ጊዜም ተቆጣ ከቊስጥንጥንያ መካከል ወደምትርቅ ደሴት አጋዛቸው ከእስክንድርያም መርከብን የሚጠብቋቸውንም ወታደሮችን በእነርሱ ላይ በሚያደርጉት ሥራ ሁሉ አጫንቀው በብረት አሥረው ይወስዱአቸው ዘንድ አዘጋጁ። ወደዚች ደሴት በደረሱ ጊዜ በደሴቱ ንጉሥ ፊት አቆሙአቸው ንጉሡም ሰይጣንን የሚያመልክ የከፋ ሰው ነበር የደሴቱም ሰዎች አምላክ ነው ብለው እስቲ አምልኩትና እስቲሰግዱለት ድረስ በሥራዩ አስቷቸው ነበር።
እሊህ አባቶቻችንም ከስሕተቱ እንዲመለስ አስተማሩት ለመኑትም አልሰማቸውም ከብዙ ሥቃይ ጋር በወህኒ ቤት ዘጋባቸው እንጂ በጽኑዕ ሥቃይም አሠቃያቸው ጌታችንም ተገልጦ የሚያጸናቸውና የሚያስታግሣቸው ሆነላቸው። የክብር ባለቤት ጌታችንም ጽድቃቸውንና ትሩፋታቸውን ሊገልጥ በወደደ ጊዜ የንጉሡን ልጅ ሰይጣን ያዛት። አባትና እናቷም በታላቅ ኀዘን ላይ እስቲሆኑ አብዝቶ አሠቃያት በከተማ ውስጥም ሰይጣናት ተገልጠው መቃርስና ባልንጀራው ሆይ እኛ ከእናንተ እናንተ ከኛ ምን አላችሁ ከአገራችሁ ያሰደዳችሁን እያሉ ተገልጠው ይጮኹ ጀመር።በንጉሡ ልጅ ያደረውም ሰይጣን ንጉሥ ሆይ መቃርስና ባልንጀራው ካልመጡ ከልጅህ ላይ አልወጣም ብሎ ጮኸ ንጉሡና አብረውት ያሉ አደነቁ ወደ ንጉሡም ቅዱሳንን አመጡአቸው።
እሊህ ቅዱሳን መቃርስና ባልንጀራው ወደ ንጉሥ በደረሱ ጊዜ በንጉሡ ልጅ ያደረ ሰይጣን እንዳያሠቃዩት ለመነ። ንጉሡና አብረውት ያሉትም ስለ ሥራቸው ቅዱሳንን መረመሩአቸው፡፡ እነርሱም የሆነውን ሁሉ ነገሩአቸው ስለ ንጉሡም ልጅ ያድኑዋት ዘንድ ለመኑዋቸው። እነርሱም ንጉሡን ገሠጹት እንዲህም አሉት አንተ ሰው ስትሆን ለምን ራስህን አምላክ ታደርጋለህ ዓለምን የፈጠረ አምላክ ከሆንክ ራስህንና ልጅህን ማዳን ይገባህ ነበር። ያን ጊዜም ወደ ክብር ባለቤት ጌታችን ጸልየው ጋኔኑም በወጣ ጊዜ ስለ ክፉ ሥራቸው ንጉሡንና የዚያችን ደሴት ሰዎች ዘለፋቸው።
ንጉሡና በዚያ የተሰበሰቡት ይህን አይተው በእሊህ ቅዱሳን አምላክ እናምናለን ከእሊህ ቅዱሳን አምላክ ከእግዚአብሔር በቀር በሰማይና በምድር ሌላ አምላክ እንደሌለ ተረድተናልና እያሉ ጮኹ። የከበሩ አባቶቻችንም በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ማመንን አሰተማሩአቸው እነርሱም በሽተኞቻቸውን ሁሉ ሰበሰቡ አባቶቻችንም በዘይት ላይ ጸልየው በመስቀል ምልክት አማትበው ቀብተው በሽተኞችን ሁሉ አጋንንት ያደሩባቸውንም ሁሉንም አዳኑአቸው እንዲሁም እያደረጉ እያስተማሩዋቸውም ብዙ ቀን ኖሩ።
ከዚህም በኋላ የሀገሩን ምኵራብ አስፈርሰው ቦታውን አጸዱ አነፁ ቦታውም እጅግ ስፋት ያለው መልካም ስለሆነ ቤተ ክርስቲያን አሳነፁ ንጉሡም ስፍር ቁጥር የሌለው ወርቅና ብር የሐር ልብሶችንም ለእግዚአብሔር መቅደስ ለሚአሻውም ሁሉ አመጣ። የከበሩ አባቶቻችንም ጥበብ ያላቸው አንጣሪዎችን ሚዛኑ ለየአንዳንዱ ዘጠኝ ልጥር የሚሆን አሥራ ሁለት ጻህሎችን ሠርተው የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስንና የእመቤታችን የድንግል ማርያምን ሥዕል የሁለቱንም የመላእክት አለቆች የሚካኤልንና የገብርኤልን ሥዕል በውስጡ እንዲሥሉ ደግሞ አሥራ ሁለት መንበሮችን ለመሠዊያ የሚፈለገውንም ሁሉ አሥራ ሁለት ጽዋዎችና አሥራ ሁለት ዕርፈ መስቀልም እያንዳንዱ ሦስት ሦስት ልጥር የሆኑ ሃያ አራት መስቀሎችን እንዲሠሩ ሦስቱንም የመቅደስ ግድግዳ እንዲሥሉ አዘዙ።
የቤተ ክርስቲያኒቱ የሕንፃዋ ሥራ ተፈጸመ። የተረፈውንም ገንዘብ ለድኆችና ለችግረኞች በተኑ። ጌታችን የተጠመቀባት ጥር ዐሥራ አንድ ቀን በሆነች ጊዜ ወደ ባሕር አጠገብ እንዲወርዱና እንዲሰበሰቡ የአገሩን ሰዎች አዘዙዋቸው። ከእስክንድርያም በተሰደዱ ጊዜ እግረ መንገዳቸውን የያዙትን የከበረ ሜሮንን አመጡ። ይህም ከሐዋርያዊ አትናቴዎስ ጊዜ ጀምሮ የተጠበቀ ሉክዮስም ያላገኘው ጌታችንም በዘመናት ሁሉ የጠበቀው ጥፋት ያላገኘው ነው።ይህ በመንፈስ ቅዱስ ትእዛዝ ሆኖአልና።
በዚያንም ጊዜ አባት መቃሪ በከበረ ሜሮን በጥልቁ ባሕር ላይ ባረከ ባሕሩም ከእሳት ኃይል የተነሣ በድስት እንደሚያፈሉት ውኃ የሚፈላ ሆነ ዘይቱና ሜሮኑም በውኃው ላይ ተንሳፈው እንደሚያበሩ ከዋክብት ሆኑ ከእርሳቸውም እንደ ፀሐይ የሆነ ታላቅ ብርሃን ታየ። ንጉሡና የተሰበሰቡት ሕዝብ አይተው ፈሩ። የክብር ባለቤት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገለጠ። አጥማቂው ዮሐንስና ቅዱሳን መላእክትም ውኃው በመከብርበትና በሚለወጥበት ጊዜ ተገለጡ። ሕዝቡም ሁሉ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ተጠመቁ ያንጊዜ ከሽቱ ሁሉ መዓዛው የሚጣፍጥ ሽታ ሸተተ።
በዚያን ጊዜም የከበሩ አባቶቻችን ይህን አይተው በምድር ላይ ወድቀው ሰገዱ በስግደታቸው እዚያው ዘገዩ። አባት መቃርስም ሰግዶ ሳለ ጌታችንን እንዲህ ሲል ለመነው። ጌታዬ እለምንሃለሁ ቸርነትህ ትድረሰኝ የዚች ታቦትና ንዋየ ቅድሳቷ ቡራኬ በአምላካዊት እጅህ እንዲሆን አለው።ጌታም እሺ በጎ ብሎ ሜሮኑን ከአባ መቃሪ እጅ ተቀብሎ ታቦቱንና ንዋየ ቅዱሳቱን አከበረ።
ከዚያም በኋላ አባት መቃርስን ሦስቱን ደርብ ትባርክ ዘንድ እኔ አዝሃለሁ እኔም ካንተ ጋራ አለሁ ይህንንም ንጹሕና ክቡር የሆነ አገልግሎት ባልንጀራህ አብሮህ ያገልግል። በመጀመሪያም የመካከለኛውን ደርብ በሥጋ በወለደችኝ በድንግል ማርያም ስም ለይተህ አክብር ደግሞ በቀኝ በኩል ያለውን በከበረ መስቀል ስም ለይተህ አክብር በግራ በኩል ያለውን ደርብ በስምህ ለይተህ አክብር በከሀዲ ሉክዮስ እጅ ስለ ስሜ በዚች ደሴት ውስጥ ደምህን አፍሰሃልና አለው።
እሊህም የተባረኩ አባቶች ጌታችን እንደ አዘዘ ሊሠሩ በጀመሩ ጊዜ ንጉሥ ዳዊት በመዝሙር ሊያመሰግን ጀመረ መላእክትም በመልካም ቃላት በቋንቋቸው ያመሰግኑ ጀመር ሕዝቡም አድንቀው እግዚአብሔርን አመሰገኑ።
፳፯_ሥነ_ፍጥረት_ቁ_፫_መጋቤ_ስብሐት_አለሙ_አጋ.mp33.59 MB
፳፮_ሥነ_ፍጥረት_ቁ_፪መጋቤ_ስብሐት_አለሙ_አጋ.mp323.56 MB
፳፭_ሥነ_ፍጥረት_ቁ_፩_መጋቤ_ስብሐት_አለሙ_አጋ.mp35.20 MB
አባ ዮልያኖስም በአረፈ ጊዜ በወንጌላዊ ማርቆስ ወንበር ላይ ሊቀ ጳጳሳት አድርገው ሾሙት በወንጌላዊ ማርቆስ ወንበር ከእርሱ በቀር ሚስት ኑራው የተሾመ የለም። ሰይጣንም በሰዎች ልቡና አደረ። በእርሱ ላይም በመናገር የሚአሙት ሆኑ።
ስለዚህም ነገር ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ ለቅዱስ ድሜጥሮስ ተገልጦ እንዲህ አለው ከሕዝቡ የሚአሙህ አሉና ከልባቸው ጥርጥርን ልታርቅ ይገባሃል። ከሚስትህም ጋር ያለውን የገድልህን ምሥጢር ልትገልጥላቸው ይገባሃል አንተ ራስህን አድነህ በአንተ ምክንያት ሌሎች ይጠፉ ዘንድ አይገባህም ቸር ጠባቂ ከሆንክስ ወገኖችህን ለማዳን ታገል።
ማግስት በሆነ ጊዜም ይህም መጋቢት ዐሥራ ሁለት ቀን ነው የቍርባንን ቅዳሴ ቀደሰ፡፡ ሕዝቡንም እንዲጠብቁ እንጂ ከቤተ ክርስቲያን እንዳይወጡ አዘዛቸው። ደግሞ እሳትን እንዲአነዱ አዘዛቸው ወደ ሴቶች መቆሚያም ልኮ ሚስቱን አስመጣት ከሥራው የተነሣ ሕዝቡ ያደንቁ ነበር ምን ሊሠራ እንደፈለገ ሕዝቡ አላወቁምና ።
ከዚህም በኋላ ቅዱስ ድሜጥሮስ ተነሥቶ ተንቀሳቀሰ ከእሳቱ መካከል ገብቶ በመቆም እሳቱ እየነደደ በውስጡ ጸለየ ከእሳቱም ፍም በእጁ ዘግኖ በልብሰ ተክህኖው ላይ አኖረ በእሳቱ ውስጥም ቁሞ ለረጅም ጊዜ ጸለየ በልብሰ ተክህኖው ውስጥ ያለ እሳትም አይቀጣጠልም።
ከዚህም በኋላ ሚስቱን ጠርቶ ያንን እሳት በመጐናጸፊያዋ ውስጥ ጨመረ ረጅም ጸሎትም ጸለየ እሳቱም ከልብሶቻቸው ምንም ምን አላቃጠለም። ሕዝቡም አድንቀው እግዚአብሔርን አመሰገኑ። ሕዝቡም ይህን ሥራ በምን ምክንያት እንደሠራ ያስረዳቸው ዘንድ የከበረ ድሜጥሮስን ለመኑት።
እርሱም ከሚስቱ ጋራ ያለውን ገድሉን ገለጠላቸው ያለውዴታው እርሷም ጋብቻን ሳትሻ እንዳጋቡት እንዲህም አለ እነሆ በአንድነት እኛ ሠላሳ ስምንት ዓመት ስንኖር በጋብቻ ሥርዓት ከተገናኘንበት ጊዜ ጀምሮ በአንድ አልጋ አንድ ልብስ ለብሰን እንተኛለን። ግን ወንዶች ሴቶችን በግብር እንደሚአውቋቸው ሴት እንደሆነች አላውቃትም።
በዚህ ሁሉ ዘመን በየሌሊቱ የእግዚአብሔር መልአክ ከሰማይ እየወረደ በክንፎቹ ይሸፍነናል። ይህንንም በዚህ ሁሉ ዘመን ከሰው ወገን ለማንም ከቶ አልገለጥኩም። ልገልጠውም ከቶ አልሻምና ግን እናንተ ከበደል ትድኑ ዘንድ እርሱ እግዚአብሔር አዘዘኝ እንጂ አላቸው። ከአዩትና ከሰሙት የተነሣ ሕዝቡ እጅግ አደነቁ እግዚአብሔርንም አመሰገኑት እርሱን ስለማማታቸውም የበደሉትን በደል ይቅር ይላቸው ዘንድ እያለቀሱ ቅዱስ ድሜጥሮስን ለመኑት።
እርሱም ስሕተታቸውን ይቅር ብሎ በጎ ሥራን ከሚጠላ ከሰይጣን እንጂ ከእናንተ አይደለምና አትዘኑ አላቸው። ከዚህም በኋላ ባረካቸው ወደ ቤታቸውም ይገቡ ዘንድ በሰላም በፍቅር አሰናበታቸው ከሊቀ ጳጳሳቱ ከቅዱስ ድሜጥሮስ ከአዩት ተአምራት የተነሣ እግዚአብሔርን እያመሰገኑ ወደ ቤታቸው ገቡ።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#አቡነ_ተስፋ_ጽዮን
ዳግመኛም በዚህች እለት አቡነ ተስፋ ጽዮን እረፍታቸው ነው፡፡ ጻድቁ ሀገራቸው ሸዋ ሲሆን የንጉሡ የዐፄ ዳዊት ልጅና የዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ ወንድም ናቸው፡፡ ስንክሳሩ ‹‹መናኔ መንግሥት ወብእስት›› በማለት ይጠራቸዋል፡፡ አቡነ ተስፋ ጽዮን በመጀመሪያ ‹‹በዓለም ነግሦ መኖርን አልፈልግም›› በማለት የዓለምን ጣዕም ንቀው በመተው ገዳም ገብተዋል፡፡ በታላቅ ተጋድሎ እየኖሩ አጠቃላይ የመርሐ ቤቴ ገዳማትን ሲመሩና ሲያስተዳድሩ ነበር፡፡
ጻድቁ በመስቀላቸው በመባረክ በሐምሌ ወር የዠማን ወንዝ አቆመው የተሻገሩ ታላቅ አባት ናቸው፡፡ ብዙ ሙታንን በማስነሣትና ታላላቅ ተአምራትን በማድረግ ነው ወንጌልን ሲሰብኩ የነበረው፡፡ አበታችን ከመላእክት ጋር በማዕድ አብረው ይቀመጡ የነበሩ ናቸው፡፡ በተለያየ ሀገር የሚኖሩ ቢሆኑም ከወለቃው አቡነ ዘአማኑኤል ጋር በመንፈስ ቅዱስ መሪነት እየተገናኙ ስለ ገዳማት ይወያዩ ነበር፡፡ አቡነ ተስፋ ጽዮን በትግራይ ትልቅ ገዳም ያላቸው ሲሆን በደብረ በግዕና በዜና ማርቆስ ገዳም ደግሞ ቅዱስ ገድላቸው ይገኛል፡፡ ጻድቁ ከብዙ ተጋድሎ በኋላ ጌታችን ተገልጦላቸው ታላቅ ቃልኪዳን ሰጥቷቸው በዛሬዋ ዕለት መጋቢት 12 በታላቅ ክብር ዐርፈዋል፡፡
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ለዘለዓለሙ ይሁን አሜን፡፡
(#ስንክሳር_ዘወርኀ_መጋቢት፣ #ኦሪት_ዘኁልቁ_ምዕራፍ_22 እና #ከገድላት_አንደበት)https://t.me/finotebirhan12
🛑ስንክሳር #መጋቢት_12
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
መጋቢት ዐሥራ ሁለት በዚች ዕለት እግዚአብሔር #ቅዱስ_ሚካኤልን ወደ ጠንቋዩ በለዓም ላከው፣ የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት #ቅዱስ_ድሜጥሮስ ድንግልናው የተገለጠበት ነው፣ ኢትዮጵያዊው ጻድቅ #አቡነ_ተስፋ_ጽዮን እረፍታቸው ነው፡፡
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ቅዱስ_ሚካኤል
መጋቢት ዐሥራ ሁለት በዚች ዕለት እግዚአብሔር ቅዱስ ሚካኤልን ወደ ጠንቋዩ በለዓም ላከው።
"የእስራኤልም ልጆች ተጓዙ፥ በኢያሪኮ ፊት ለፊት በዮርዳኖስ ማዶ ባለው በሞዓብ ሜዳ ሰፈሩ። የሴፎር ልጅ ባላቅ እስራኤል በአሞራውያን ላይ ያደረገውን ሁሉ አየ። ብዙም ነበረና ሞዓብ ከሕዝቡ እጅግ ፈራ፤ ከእስራኤልም ልጆች የተነሣ ሞዓብ ደነገጠ። ሞዓብም የምድያምን ሽማግሌዎች። በሬ የለመለመውን ሣር እንደሚጨርስ ይህ ጭፍራ በዙሪያችን ያለውን ሁሉ ይጨርሳል አላቸው። በዚያን ጊዜም የሴፎር ልጅ ባላቅ የሞዓብ ንጉሥ ነበረ።
በወንዙ አጠገብ ባለችው በሕዝቡ ልጆች ምድር በፋቱራ ወደ ተቀመጠው ወደ ቢዖር ልጅ ወደ በለዓም። እነሆ፥ ከግብፅ የወጣ ሕዝብ አለ፤ እነሆም፥ የምድሩን ሁሉ ፊት ሸፈነ በአቅራቢያችንም ተቀምጦአል፤ አሁንም ይህ ሕዝብ ከእኔ ይበልጣልና ልወጋቸውና ከምድሪቱ ላሳድዳቸው እችል እንደ ሆነ፥ እባክህ፥ ና ርገምልኝ፤ አንተ የመረቅኸው ምሩቅ የረገምኸውም ርጉም እንደ ሆነ አውቃለሁና ብሎ ይጠሩት ዘንድ መልእክተኞቹን ላከ። የሞዓብ ሽማግሌዎችና የምድያም ሽማግሌዎችም የምዋርቱን ዋጋ በእጃቸው ይዘው ሄዱ፤ ወደ በለዓምም መጡ፥ የባላቅንም ቃል ነገሩት። እርሱም። ዛሬ ሌሊት በዚህ እደሩ፥ እግዚአብሔርም እንደሚነግረኝ እመልስላችኋለሁ አላቸው፤ የሞዓብም አለቆች በበለዓም ዘንድ ተቀመጡ። እግዚአብሔርም ወደ በለዓም መጥቶ። እነዚህ በአንተ ዘንድ ያሉ ሰዎች እነማን ናቸው? አለው። በለዓምም እግዚአብሔርን። የሞዓብ ንጉሥ የሴፎር ልጅ ባላቅ። እነሆ፥ ከግብፅ የወጣ ሕዝብ የምድርን ፊት ሸፈነ፥ አሁንም ና እርሱንም ርገምልኝ፤ ምናልባት እወጋው አሳድደውም ዘንድ እችል እንደ ሆነ ብሎ ወደ እኔ ልኮአል አለው።
እግዚአብሔርም በለዓምን። ከእነርሱ ጋር አትሂድ፤ የተባረከ ነውና ሕዝቡን አትረግምም አለው። በለዓምም ሲነጋ ተነሥቶ የባላቅን አለቆች። ከእናንተ ጋር እሄድ ዘንድ እግዚአብሔር አልፈቀደምና ወደ ምድራችሁ ሂዱ አላቸው። የሞዓብ አለቆች ተነሡ፥ ወደ ባላቅም መጥተው። በለዓም ከእኛ ጋር ይመጣ ዘንድ አልፈቀደም አሉት። ባላቅም ደግሞ ከፊተኞች የበዙና የከበሩ ሌሎችን አለቆች ሰደደ። ወደ በለዓምም መጥተው። የሴፎር ልጅ ባላቅ። ክብርህን እጅግ ታላቅ አደርገዋለሁና፥ የተናገርኸውንም ሁሉ አደርግልሃለሁና እባክህ፥ ወደ እኔ ትመጣ ዘንድ ምንም አይከልክልህ፤ እባክህ፥ ና፥ ይህን ሕዝብ ርገምልኝ አለ ብለው ነገሩት። በለዓምም መልሶ የባላቅን ባሪያዎች። ባላቅ በቤቱ የሞላውን ወርቅና ብር ቢሰጠኝ፥ በትንሹ ወይም በትልቁ ቢሆን የአምላኬን የእግዚአብሔርን ቃል እተላለፍ ዘንድ አይቻለኝም፤ አሁንም እግዚአብሔር ደግሞ የሚነግረኝን አውቅ ዘንድ፥ እባካችሁ፥ ዛሬ ሌሊት ደግሞ በዚህ እደሩ አላቸው። እግዚአብሔርም ወደ በለዓም በሌሊት መጥቶ። ሰዎቹ ይጠሩህ ዘንድ መጥተው እንደ ሆነ፥ ተነሣ ከእነርሱም ጋር ሂድ፤ ነገር ግን የምነግርህን ቃል ብቻ ታደርጋለህ አለው።
በለዓምም ሲነጋ ተነሣ፥ አህያይቱንም ጭኖ ከሞዓብ አለቆች ጋር ሄደ። እርሱም ስለ ሄደ እግዚአብሔር ተቈጣ፤ የእግዚአብሔርም መልአክ ሊቋቋመው በመንገድ ላይ ቆመ። እርሱም በአህያይቱ ላይ፥ ሁለቱም ሎሌዎቹ ከእርሱ ጋር ነበሩ።
አህያይቱም የእግዚአብሔርን መልአክ በመንገድ ላይ ቆሞ የተመዘዘም ሰይፍ በእጁ ይዞ አየች፤ ከመንገዱም ፈቀቅ ብላ ወደ እርሻው ውስጥ ገባች፤ በለዓምም ወደ መንገድ ይመልሳት ዘንድ አህያይቱን መታት። የእግዚአብሔርም መልአክ ከወይኑ ቦታዎች መካከል በወዲያና በወዲህ ወገን ግንብ በነበረበት በጠባብ መንገድ ላይ ቆመ። አህያይቱም የእግዚአብሔርን መልአክ አየች፥ ከበለዓምም በታች ተኛች፤ በለዓምም እጅግ ተቈጣ፥ አህያይቱንም በበትሩ ደበደባት። እግዚአብሔርም የአህያይቱን አፍ ከፈተ፥ በለዓምንም። ሦስት ጊዜ የመታኸኝ ምን አድርጌብህ ነው? አለችው። በለዓምም አህያይቱን። ስላላገጥሽብኝ ነው፤ በእጄስ ሰይፍ ቢኖር አሁን በገደልሁሽ ነበር አላት።
አህያይቱም በለዓምን። ከብዙ ዘመን ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ የምትቀመጥብኝ አህያህ አይደለሁምን? በውኑ እንዲህ አደርግ ዘንድ ልማዴ ነበረን? አለችው። እርሱም። እንዲህ አላደረግሽብኝም አላት። እግዚአብሔርም የበለዓምን ዓይኖች ከፈተ፤ የእግዚአብሔርን መልአክ በመንገድ ላይ ቆሞ የተመዘዘም ሰይፍ በእጁ ይዞ አየ፤ ሰገደም፥ በግምባሩም ወደቀ። የእግዚአብሔርም መልአክ። አህያህን ሦስት ጊዜ ለምን መታህ? እነሆ፥ መንገድህ በፊቴ ጠማማ ነውና እቋቋምህ ዘንድ ወጥቼአለሁ፤ አህያይቱም አይታኝ ከፊቴ ሦስት ጊዜ ፈቀቅ አለች፤ ከፊቴስ ፈቀቅ ባላለች በእውነት አሁን አንተን በገደልሁህ፥ እርስዋንም ባዳንኋት ነበር አለው። በለዓምም የእግዚአብሔርን መልአክ። በድያለሁ፤ አንተ በመንገድ ላይ በፊቴ እንደቆምህብኝ አላወቅሁም፤ እንግዲህም አሁን አትወድድ እንደ ሆነ እመለሳለሁ አለው።
የእግዚአብሔርም መልአክ በለዓምን። ከሰዎቹ ጋር ሂድ፥ ነገር ግን የምናገርህን ቃል ብቻ ትናገራለህ አለው። በለዓምም ከባላቅ አለቆች ጋር ሄደ። ባላቅም በለዓም እንደ መጣ በሰማ ጊዜ በአርኖን ዳር ዳርቻ በመጨረሻ ወዳለችው ወደ ሞዓብ ከተማ ሊገናኘው ወጣ። ባላቅም በለዓምን። በውኑ አንተን ለመጥራት አልላክሁብህምን? ለምንስ ወደ እኔ አልመጣህም? በውኑ አንተን ለማክበር እኔ አልችልምን? አለው። በለዓምም ባላቅን። እነሆ፥ ወደ አንተ መጥቼአለሁ፤ በውኑ አሁን አንዳችን ነገር እናገር ዘንድ እችላለሁን? እግዚአብሔር በአፌ የሚያደርገውን ቃል እርሱን እናገራለሁ አለው። በለዓምም ከባላቅ ጋር ሄደ፥ ወደ ቂርያት ሐጾትም መጡ። ባላቅም በሬዎችንና በጎችን አርዶ ወደ በለዓም ከእርሱም ጋር ወዳሉት አለቆች ላከ። በነጋውም ባላቅ በለዓምን ይዞ ወደ በኣል ኮረብታ መስገጃ አወጣው፤ በዚያም ሆኖ የሕዝቡን ዳርቻ አየ።
..... በለዓምም መርገሙን ወደ በረከት መለሰው።
(ሙሉ ታሪኩን ለማንበብ ኦሪት ዘኁልቁ ምዕራፍ ፳፪፣ ፳፫፣ ፳፬ እስከ ፍጻሜ)
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ቅዱስ_ድሜጥሮስ_ሊቀ_ዻዻሳት
በዚህችም ዕለት የከበረና የተመሰገነ የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ዐሥራ ሁለተኛ ተሿሚ የሆነ የድሜጥሮስ ድንግልናው የተገለጠበት ሆነ።
የመገለጡ ምክንያትም እንዲህ ነው ከእርሱ በፊት ሊቀ ጳጳሳት ለነበረው ለቅዱስ ዮልያኖስ መንፈቀ ሌሊት በሆነ ጊዜ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ ተገልጦለት አንተ ወደ ክብር ባለቤት ወደ ክርስቶስ ትሔዳለህ የወይን ዘለላ ይዞ ነገ ወደ አንተ የሚገባ ሰው ከአንተ በኋላ ሊቀ ጳጳስ ሊሆን የሚገባው እርሱ ነው አለው።
ማግስት በሆነ ጊዜም የከበረና የተመሰገነ ድሜጥሮስ የወይን ዘለላ ይዞ ወደ ከበረ ዮልያኖስ ዘንድ ገባ ቅዱስ ዮልያኖስም ያዘው ከእኔ በኋላ ሊቀ ጳጳሳታችሁ እነሆ ብሎ ለሕዝብ አስረከባቸው ስለእርሱም የእግዚአብሔር መልአክ እንደተገለጠለት ነገራቸው።
🔴 ዛሬ መጋቢት 11 የሰንበት ት/ቤታችን ወርኅዊ ጸሎት
ክፍዎች ሰዎችም ቀንተውበት በጠላትነት ተነሡበት በክርስቶስ ከማያምኑ ጋራ ተሰባስበው ወደ ሸንጓቸውም አደረሱት ይህን ቅዱስ ባስሊዖስን ታላቅ ግርፋትን ገረፉት ነፍሱንም በጌታችን እጅ እስከሰጠ ድረስ እያሠቃዩ በዚያች አገር አዋሉት።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ቅዱስ_ቴዎቄጤኖስ
በዚህች ቀን በንጉሥ መክስምያኖስ ዘመን ቅዱስ ቴዎቄጤኖስ በሰማዕትነት አረፈ። ይህ ቅዱስ አስቀድሞ ወታደር ነበር ትጥቁን በንጉሡን ፊት ጥሎ በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታመነ ከርሱም ጋራ ብፅዕት እስክንድራ አለች።
ንጉሡም ሰምቶ ተቆጣ ልብሱን አስወለቀው የሴቶች ልብስ አልብሰው ከሚፈትሉ ሴቶች ጋራ እንዲጨምሩት። ከዚያም የጋለ የብረት መንኰራኲር በላዩ አድርገው ዘቅዝቀው ቊልቊል እንዲሰቅሉት አዘዘ።
ሁለተኛም እንዲህ ብሎ አዘዘ የፈላ ቅጥራን የተመላ ወጭት አምጥታችሁ ወደ ጆሮው እስቲደርስ በራሱ ላይ ድፉበት ደግሞ ከተሰቀለበት አውርደው ከእሥረኛዋ እስክንድራ ጋር በፊቱ እንዲአቆሙት አዘዘ።
ከዚህም በኋላ ምላሱን እንዲቆርጡ አዘዘ በእሊህ ቅዱሳን በአንገቶቻቸው የሚካበዱ ደንጊያዎችን አሥረው በኤፍራጥስ ወንዝ ውስጥ እንዲጥሉአቸው አዘዘ። በዚያም ተጋድሎአቸውንና ምስክርነታቸውን ፈጸሙ ሥጋቸውንም ምእመናን አግኝተው በሥውር ቦታ ቀበሩት፡፡
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ለዘለዓለሙ ይሁን አሜን፡፡
(#ስንክሳር_ዘወርኀ_መጋቢት እና #ከገድላት_አንደበት)https://t.me/finotebirhan12
🛑ስንክሳር #መጋቢት_11
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
መጋቢት ዐሥራ አንድ በዚህች ዕለት ከተሰዓቱ ቅዱሳን አንዱ #አባ_አሌፍ አረፈ፣ ተጋዳይ የሆነ ኤጲስቆጶስ #አባ_ባስሊዖስ በማዕትነት አረፈ፣ በንጉሥ መክስምያኖስ ዘመን #ቅዱስ_ቴዎቄጤኖስ በሰማዕትነት አረፈ።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#አባ_አሌፍ
መጋቢት ዐሥራ አንድ በዚህች ዕለት ከተሰዓቱ ቅዱሳን አንዱ አባ አሌፍ አረፈ፡፡ ተሰዓቱ ቅዱሳን በፈቃደ እግዚአብሔር ተሰባስበው በአንድ ላይ አገልግሎታቸውን ይፈጽሙ እንጂ ከተለያዩ ሀገራት የተውጣጡ ናቸው፡፡ እነርሱም የቁስጥንጥንያው አባ ሊቃኖስ፣ የሀገረ ቁስያው (ኢጣሊያ) አባ ይምአታ፣ የአንጾኪያው (ሶሪያ) አባ ጽሕማ፣ የቂልቅያው (ግሪክ) አባ ጉባ፣ የእስያው አባ አፍጼ፣ የሮምያው ጰንጠሌዎን፣ የቂሣርያው አባ አሌፍ ናቸው፡፡
ሁሉም የነገሥታት ልጆች ቢሆኑም ዓለምን ፍጹም ንቀው በአባ ጳኩሚስ እጅ ከመነኮሱ በኋላ ሮምን ወደ ቀናች ሃይማኖት መልሰዋት ነበር፡፡ በሮም ሣሉ በምድረ አዜብ ብሔረ ኢትዮጵያ ስለሚኖሩ ሰዎች ዝና ስለ ነገሥታቶቻቸውም ቅድስናና ሀገሪቱም የእመቤታችን አሥራት መሆኗን ከመጻሕፍት ተረዱ፡፡ አባ ዘሚካኤልም ከሁለቱ ደቀ መዛሙርቶቹ ጋር በሌሊት ወጥቶ ወደ ኢትዮጵያ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል እየመራው መጥቶ አክሱም ደረሰ፡፡ በዚያም ጥቂት ጊዜ በመቀመጥ ተመልሶ ወደ ሮምያ ሄዶ ስለ ኢትዮጵያ ያየውንና የሰማውን በሙሉ ሁሉ ለሌሎቹ ቅዱሳን ሲነግራቸው እነርሱም ‹‹ይህችን ሄደን ማየት አለብን›› ተባበብለው ያላቸውን ሁሉ ይዘው ታቦቶቻቸውን፣ ካህናቶቻቸውን፣ ንዋየ ቅድሳቶቻቸውን፣ መጻሕፍቶቻቸውን ሁሉ ይዘው በዘሚካኤል መሪነት በመምጣት በ460 ዓ.ም ጳጳሱና ንጉሡ ካሉበት አክሱም ከተማ ገቡ፡፡
ተሰዓቱ ቅዱሳን ከአብርሃ ወአጽብሐ 6ኛ ንጉሥ በሚሆን በአልሜዳ ዘመነ መንግሥት ከአውሮፓና ከእስያ ወደ ኢትዮጵያ መጥተው አክሱም ከተማ ካረፉ በኋላ ሀገረ ስብከታቸውን ተከፋፍለው ገዳም እየገደሙ፣ በዓት እያበጁ፣ ከሣቴ ብርሃን አባ ሰላማ የመሠረተውን የክርስትና ሃይማኖት በከፍተኛ ሁኔታ አስፋፍተዋል፡፡ ገዳማትን አስፋፍተው የወንጌልን ብርሃን በሀገራችን ላይ አብርተዋል፡፡
ተሰዓቱ ቅዱሳን የነገሥታት ወገን ስለሆኑ በሮም ነግሦ የሚገኘውን ወንድማቸውን ይስሐቅን ላኩበት፡፡ ንጉሡ ይስሐቅ ለአባ ዘሚካኤል የእኅት ልጅ ነው፡፡ እርሱም መልእክቱ እንደደረሰው 7 ዓመት በሮም ከነገሠ በኋላ መንግሥቱን ትቶ በሌሊት ተነሥቶ በመውጣት ወደ ሀገራችን በመልአኩ ቅዱስ ገብርኤል መሪነት መጣና ከወንድሞቹ ጋር ተቀላቀለ፡፡ እነርሱም አመነኮሱትና ስሙን ገሪማ አሉት፡፡ ሁሉም በአንዲት የጸሎት ቤት በምንም ሳይለያዩ በአንድነት እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ፣ እንደ አንድ ልብ መካሪ ሆነው ለጸሎት ቆመው ውለው ያድሩ ነበር፡፡ እነዚህም እጅግ የከበሩ ቅዱሳን ድውያንን እየፈወሱና ሙታንን እያስነሱ እጅግ በጣም አስገራሚ የሆኑ ድንቅ ድንቅ ብዙ ተአምራትን ያደርጉ ነበር፡፡ ከሰንበት በቀር እህል የሚባል ነገር የማይቀምሱት እነዚህ ቅዱሳን ኢትዮጵያን በኪደተ እግራቸው ባርከዋታል፣ ጌጦቿ ሆነውላታል፣ በትምህርታቸው የእምነቷን መሠረት አጽንተውታል፣ የልዕልናዋንም ታሪክ ለዓለም መስክረውላታል፡፡
ለ12 ዓመታትም በፍጹም አንድነት አብረው ከተቀመጡ በኋላ ‹‹እርስ በራሳችን እየተያየን ብንኖር ተድላ ደስታ ይሆንብናልና ተለያይተን እንቀመጥ›› ብለው ተማከረው በተለያየ በዓት አባ ሊቃኖስ በደብረ ቁናጽል፣ አባ ጰንጠሌዎንም በእርሱ ትይዩ በሆነ ቦታ፣ አባ ገሪማ በደብረ መደራ፣ አባ ጽሕማ በደብረ ጸድያ፣ አባ ይምአታ በደብረ ገረዓልታ፣ አባ አፍጼ በደብረ ይሐ፣ አባ አሌፍ በደብረ አኅድአ፣ አባ አረጋዊ በደብረ ዳሞ መኖር ጀመሩ፡፡ በዋሻና በፍርኩታ ውስጥ በተራራም ላይ መኖር ጀመሩ፡፡ እናንተ የከበራችሁ ቅዱሳን ሆይ! የነገሥታት ልጆች ስትሆኑ ላባችሁን እያንጠፈጠፋችሁ በዱር በገደል መንከራተታችሁ፣ በቀበሮም ጉድጓድ መቀመጣችሁ፣ የምትለብሱት ሳታጡ በበርድ በቁር መራቆታችሁ ምንኛ ድንቅ ነው!? የምትበሉት የምትጠጡት ሳታጡ የነገሥታት ልጆች ስትሆኑ መራብ መጠማታችሁስ እንደምን ያለ ነው!?
አቡነ አሌፍ ኤርትራ ጠረፍ አካባቢ ወደሚገኘው በዓታቸው ወደ ደብረ አኅድአ በሄዱ ጊዜ በቦታው ላይ ታላቅ ዘንዶ ሰፍሮ ይኖር ነበር፡፡ ይህንንም ታላቅ ዘንዶ ቦታውን አስለቅቀው በዋሻ ውስጥ ገብተው ብዙ ተጋድሎ አድርገዋል፡፡ ብዙ ድንቅ ድንቅ ተአምራትን በማድረግ ሕዝቡንም የከበረች ወንጌልን እያስተማሩ በተአምራት ከደዌ እየፈወሱ በጸሎታቸውም አጋንንትን እያስወጡ፣ ድውያንን እየፈወሱ፣ ዕውራንን እያበሩ፣ ሙታንን እያስነሡ ብዙ ሐዋርያዊ አገልግሎት ፈጽመዋል፡፡ መላእክትም ዘወትር ባለመለየት አባ አሌፍን ይጎበኙዋቸው ነበር፡፡ ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስም ዘወትር እየተገለጠላቸው ይባርካቸውና ቃልኪዳን ይሰጣቸው ነበር፡፡
የአቡነ አሌፍ ገዳማቸው ከአዱዋ በስተሰሜን አቅጣጫ ወደ ኤርትራ ጠረፍ አቅራቢ ልዩ ስሙ ብህዛ በሚባለው ተራራማ ቦታ ላይ ይገኛል፡፡ የአባታችን በዓለ ዕረፍታቸው መጋቢት 11 ነው፡፡ ነገር ግን ቀደምት ቅዱሳን አባቶቻችን በደነገጉት መሠረት ይህ ወቅት ዐቢይ ጾም ላይ ስለሚውል በዚህ ወቅትም ምንም ዓይነት በዓል ማክበር ሥርዓት ስላልሆነ በጻድቁ ገዳም ውስጥ የአባታችን በዓላቸው በስፋት የሚከበረው ታህሳስ 11 ነው፡፡
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#አባ_ባስሊዖስ
በዚህችም ዕለት ደግሞ ተጋዳይ የሆነ ኤጲስቆጶስ አባ ባስሊዖስ በማዕትነት አረፈ። ይህንንም ቅዱስ የኢየሩሳሌሙ ሊቀ ጳጳሳት አባ አርሞን ከሌሎች ኤጲስቆጶሳት ጋራ ሾመው። በታወቀና በተወሰነ ቦታ ላይ አይደለም። እምነት በሌላቸው በአረማውያን አገር ይሰብክ ዘንድ ላከው እንጂ።
ይህም ቅዱስ ወደ ከሀድያን አገር ገብቶ የከበረ ወንጌልን ሰበከ። እነርሱም እየደበደቡ በአገራቸው ሁሉ አዞሩት። ደግሞ ወደ ሠርዑና አገሮች ገብቶ የከበረ የወንጌል ትምህርትን ስተማረ። እኩሌቶቹ በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ።
ያላመኑት እኩሌቶቹ ከሀድያን ግን አሳደዱት ከከተማው ውጭ ወጥቶ በዋሻ ውስጥ ተቀመጠ። የዚያች አገር ሰዎች እግዚአብሔርን ወደ ማወቅ ይመለሱ ዘንድ በአንድ ልጁም ያምኑ ዘንድ ስለዚያች አገር ሰዎች አዘውትሮ እግዚአብሔርን ማለደ።
በዚያንም ሰሞን ለእርሱ ለአባቱ አንድ ብቻውን የሆነ የመኰንኑ ልጅ ሞተ። አባቱም ታላቅ ኀዘንን አዘነ መኰንኑ አባቱም በሕልሙ ልጁን አየው። እርሱም በፊቱ ቁሞ አባቴ ሆይ እነሆ እኔ በታላቅ ጨለማ ውስጥ ነኝና ወደ ክርስቶስ ስለ እኔ ይጸልይ ዘንድ ኤጲስቆጶሱ አባ ባስሊዖስን ጠርተህ ለምነው ሲለው ነበር።
ከእንቅልፉም በነቃ ጊዜ ደንግጦ ተነሣ ከእርሱም ጋራ የአገር ታላላቆችን ይዞ ወደ ቅዱስ ባስሊዖስ በዓት ሔደ። ከእርሱ ጋራም ወደ ከተማ ገብቶ ስለ ልጁ እንዲጸልይ ለመነው።
እርሱም ልመናውን ተቀብሎ ወደ ከተማ ገባ በመኰንኑ ልጅ መቃብር ላይም ጸለየ ያንጊዜም የመኰንኑ ልጅ ድኖ በሕዝብ ሁሉ ፊት ተነሣ መኰንኑ ሕዝቡም ሁሉ በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ።
ከአገርም ሰዎች ብዙዎች አምነው የክርስትና ጥምቀትን በቅዱስ ባስሊዖስ እጅ ተጠመቁ በዚያቺም አገር ታላቅ የክርስቲያኖች ጉባኤ ሆነ።
🛑.........መጻጒዕ........
አራተኛው የዐቢይ ጾም ሳምንት ‹መጻጒዕ› ይባላል፡፡ ስያሜው በዮሐንስ ወንጌል ፭፥፩ ላይ ከሚገኘው ኃይለ ቃል የተወሰደ ነው፡፡ በዚህ የወንጌል ክፍል ጌታችን በቤተ ሳይዳ ሕሙማንን እንደፈወሰ ተነግሮአል፡፡
ብዙ ሕሙማን ፈውስ ሽተው አንዲት የመጠመቂያ ሥፍራን ከበው ይኖሩ ነበር በዚያች ሥፍራ ቀድሞ የወረደ እና የተጠመቀ አንድ በሽተኛ ብቻ ይፈወስ ነበር ጌታችን በዚህ ሥፍራ ተገኝቶ በሽተኞችን ጐብኝቷል በዚያም ልዩ ልዩ ደዌ ያለባቸው አምስት ዓይነት ሕሙማን እንደነበሩ ተገልጧል፤ እነዚህም፡- ሰውነታቸው የደረቀ፣ የሰለለና ያበጠ፤ እንደዚሁም ዕውራን እና ሐንካሳን ነበሩ፡፡
ከዚህ አምስት የተለያየ ዓይነት በሽታ ከተያዙ ሰዎች መካከል ደዌው የጸናበት፣ ለሠላሳ ስምንት ዓመታት በደዌ ዳኛ፣ ባልጋ ቍራኛ ተይዞ የኖረው፤ ከደዌው ጽናት የተነሣ ‹መጻጒዕ› ተብሎ የተጠራው በሽተኛ አንዱ ነበር መጻጒዕ ስም አይደለም ደዌ የጸናበት በሽተኛ ሕመምተኛ ማለት ነው እንጂ ሰውየው ከበሽታው ጽናት የተነሣ ስሙ ጠፍቶ በበሽታው ሲጠራ የነበረ ነው፡፡
አምላካችን ይህን ሰው ‹‹አልጋህን ተሸክመህ ሒድ›› ብሎ ሠላሳ ስምንት ዘመን የተኛበትን አልጋ ተሸክሞ ወደ ቤቱ እንዲገባ ማድረጉ የሚነገርበት ወቅት በመኾኑ ሳምንቱ ‹መጻጒዕ› ተብሎ በተፈወሰው በሽተኛ ስም ተሰይሟል (ሙሉ ታሪኩን በዮሐንስ ወንጌል ፭፥፩-፲፯ ይመልከቱ) ዛሬም ቢኾን በሰዎች ላይ ልዩ ልዩ ደዌያት አሉ፤ የሥጋውን ደዌ ሐኪሞች ያውቁታል ከዚህ የከፉ የነፍስ ደዌያት እጅግ ብዙዎች ናቸው፡፡ በኃጢአት ብዛት ልባቸው የደረቀና ያበጠ፤ ሰውነታቸው የሰለለ፤ ዓይነ ሕሊናቸው የታወረ፤ እግረ ልቡናቸው የተሰበረ ብዙዎች ሕሙማን አሁንም አሉ ፈውስን ይሻሉ፤ ድኅነትን ይፈልጋሉ እንደ መጻጕዕ ቦታቸውን ሳይለቁ እግዚአብሔርን በተስፋ ቢጠብቁት አንድ ቀን ይፈወሳሉ፡፡
🔴ስንክሳር #መጋቢት_10
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
መጋቢት አስር በዚች እለት የክብር ባለቤት ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበት #ቅዱስ_ስመስቀል የተገለጠበትና የተገኘበት ነው፣ ኢትዮጵያዊው ጻድቅ ታላቁን ዲማ ጊዮርጊስን የመሠረቱ #የአቡነ_ተከስተ_ብርሃን የዕረፍታቸው መታሰቢያ ነው፡
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ቅዱስ_ዕፀመስቀል
መጋቢት አስር በዚች እለት የክብር ባለቤት ጌታችን አምላካችንና መድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበት መስቀል የተገለጠበትና የተገኘበት ነው። የዚህም የከበረ ዕፀ መስቀል መገለጡና መገኘቱ ሁለት ጊዜ ሆኗል።መጀመሪያ የፃድቁ ንጉስ የቆስጠንጢኖስ እናት በሆነች በንግስት ዕሌኒ እጅ ነው።
«እርሷ ለእግዚአብሄር ተስላ ነበርና ልጇ ቆስጠንጢኖስ ወደ ክርስቲያን ሀይማኖት ቢገባ ወደ ኢየሩሳሌም ሄዳ መስቀሉን እስከ አገኘችው ድረስ ልትፈልግው በኢየሩሳሌም ያሉ ቅዱሳት መካናትንና አብያተ ክርስቲያናትን ልታንፃቸው ነው።
ከዚህ በኃላ ልጇ አምኖ የክርስትና ጥምቀትን በተጠበቀ ጊዜ እሌኒ ቅድስት ወደ ኢየሩሳሌም ሄደች ከእረሷ ጋርም ብዙ ሰራዊት ነበር ደርሳም ስለ ከበረ መስቀል መረመረች የሚያስረዳት አላገኘችም የአይሁድ ወገን የሆነ አንድ ሽማግሌ ሰው አስራ በርሀብና በጥማት አስጨነቀችው።
በተጨነቀም ጊዜ ለንግስት እሌኒ የጉልጎታን ኮረብታ አስጠርጊ ብሎ ነገራት እርሷም ይጠርጉ ዘንድ አይሁድን አዘዘቻቸው።
ቤቱን የሚጠርግ ሰው ሁሉ ጥራጊውን በውስጡ የከበረ መስቀል በአለበት በጌታችን መቃብር ላይ እንዲጥል አይሁድ አስቀድመው አዝዘው ነበርና ንግስት እሌኒ እስከ ደረሰችበት ጊዜ ከሁለት መቶ አመት በላይ ጥራጊያቸውን ሲጥሉበት ኖሩ ኮረብታም ሆነ። አይሁድም በጠረጉ ጊዜ ሶስት መስቀሎች ተገለጡ የክብር ባለቤት ክርስቶስ የተሰቀለበት የትኛው እንደሆነ አላወቁም። የሞተ ሰውም አግኝተው አመጡ።
አንዱንም መስቀል አምጥተው በሞተው ሰው ላይ አኖሩት አልተነሳም ደግሞ ሌላውን መስቀል አምጥተው በሙቱ ላይ አኖሩ አሁንም አልተነሳም ከዚህም በኃላ ሶስተኛውን መስቀል አምጥተው በሙቱ ላይ አደረጉት ያንጊዜ የሞተው ሰው ተነሳ እሌኒም የክርስቶስ መስቀል እንደሆነ አውቃ ሰገደችለት የክርስቲያንም ወገኖች ሁሉ ሰገዱለት።
ለልጅዋ የላከችው ይህ መስቀል ነው የሚል በሌላ መፅሀፍ ይገኛል የቀረው ግን ግንዱ በውስጡ ተተክሎበት የነበረው ከእርሱም እኩሌታውን ከቅንዋቱ ጋራ ወደ ልጅዋ የላከችው ነው።
ከዚህም በኃላ ስራአታቸውና የህንፃቸው ነገር በመስከረም ወር በአስራ ሰባት ተፅፎ የሚገኝ አብያተ ክርስቲያናትንና የከበሩ ቦታዎችን አነፀች። ሁለተኛው በሮሙ ንጉስ በህርቃል ዘመን የሆነው ሲሆን የፋርስ ሰዎች በግብፅ አገር ሳሉ ወደ አገራቸው ሊመለሱ ወደዱ። ከሹማምንቶቻቸው አንዱ የጦር መኰንን ተነጥሎ ወደ ኢየሩሳሌም አልፎ ደረሰ ወደ ከበረ መስቀል ቤተ ክርስቲያንም ገባ። መስቀሉም በላዮ በተተከለበት ግንድ ፊት ታላቅ ብርሀን ሲበራ አይቶ ሊያነሳው እጁን ዘረጋ። እሳትም ወጥታ እጁን አቃጠለችው።
ከክርስቲያን በቀር ማንም ሊነካው እንደማይችል የመስቀልን የክብሩን ነገር ሰዎች ነገሩት። ሁለት ዲያቆናትንም ይዞ የከበረ መስቀልን እንዲሸከሙ አዘዛቸወወ ከኢየሩሳሌምም ብዙ ሰዎችን ማርኮ ወደ አገሩ ተመለሰ።
የፋርስ ሰዎች ኢየሩሳሌምን እንዳጠፏት ብዙዎች ሰዎችንም እነድ ማረኩና የከበረ የክርስቶስንም መስቀሉን እንደ ወስዱ የሮም ንጉስ ህርቃል በሰማ ጊዜ እጅግ አዘነ። ስለርሱም እንዲፆሙ ምእመናንን አዝዞ ወደፋርስ ዘምቶ ወጋቸው ብዙዎችንም ገደላቸው የከበረ እፀ መስቀልንም እየፈለገ በሀገራቸው ሁሉ ዞረ ግን አላገኘውም።
ያ ዲያቆናቱና መስቀሉን የወሰደ መኰንን ከቦታዎች በቤቱ አነፃር ባለ በአንድ ቦታ ላይ ወስዷቸው ጥልቅ ጉድጓድእንዲቆፍሩ አዝዞ በዚያ የከበረ መስቀልን አስቀበረ እነዚያንም ዲያቆናት ገደላቸው።
ነገር ግን ያ መኰንን የማረካት የካህናት ወገን የሆነች በእርሱ ቤት የምትኖር አንዲት ብላቴና ነበረች። እርሷም የከበረ መስቀልን ሲያስቀብርና ሁለቱን ዲያቆናት ሲገድላቸው በቤቱ ውስጥ ሁና በመስኮት ትመለከት ነበር ወደ ንጉስ ሀርቃልም ሂዳ መኰንኑ ያደረገውን ሁሉ ነገረችው።
ይህንንም ንጉስ ሰምቶ እጅግ ደስ አለው ያቺ ብላቴናም መራችው ከእርሱም ጋራ ብዙ ሰራዊት ሆኖ ኤጲስቆጶሳትና ካህናትም ነበሩ ።ወደ ቦታውም እስከምታደርሳቸው ያቺን ልጅ ተከተሏት ቅፍረውም የከበረ እፀ መስቀልን አገኙት ከአዘቅቱም አወጡት ንጉሱና ሰራዊቱም ሰገዱለት።
በልብሰ መንግስቱም አጐናፀፈው ታላቀወ ክብርንም አከበረው እጅግም ደስ አለው ከሰራዊቱ ጋር። የዚህም መስቀል ሁለተኛ የተገለጠበትና የተገኘበት በዚች ቀን በመጋቢት አስር ነው፡፡ ከዚህ በኃላ ንጉሱ የከበረ እፀ መስቀልን ተሸክሞ ወደ ቁስጥንጥንያ ከተማ ወሰደው፡፡
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#አቡነ_ተከስተ_ብርሃን
በዚህች ቀን ለኢትዮጵያ ጻድቅ ታላቁን ዲማ ጊዮርጊስን የመሠረቱ አቡነ ተከስተ ብርሃን ዘደብረ ድማኅ የዕረፍታቸው መታሰቢያ ነው፡፡ ጻድቁ አባታቸው መልከ ጼድቅ እና እናታቸው ድል በኢየሱስ ይባላሉ፡፡ አባ ተከስተ ብርሃን ከዲማ ዋሻ በመነሳት እየተዘዋወሩ ወንጌልን አስተምረዋል። ከዕለታት አንድ ቀን ከጎጃም አውራጃ ይኸውም እነብሴ በሚገኘው ነድ አጹራ ማርያም በሚባለው ቦታ ያሉ ሰዎች የእጃቸውን ተዓምራት የቃላቸውን ትምህርት ሰምተው ከማመናቸው የተነሳ በአንድ ቀን ዘጠኝ መቶ ዘጠና ዘጠኝ ህዝብ በማጥመቃቸውና ቀኑ መሽቶ ስለነበረ ብርሃን ስለወረደላቸው አባ ተከስተ ብርሃን የሚል ስም ሰጥቷቸዋል፤ የቀድሞ ስማቸው አባ በኪሞስ ነበርና።
አባ ተከስተ ብርሃን እንዲህ ባለ መንፈሳዊ አግልግሎት ደብረ ድማኅንና እግዚአብሔርን ሲያገለግሉ ኖረዉ በበአታቸው በዲማ በመቀመጥ ለ15 ዓመታት ለገዳሙ መምህር በመሆን ገዳሙን አጠናክረዋል። አባታችንም የሴትና የወንድ ገዳም አቋቁመው ሴቶችን በምሥራቅ ወንዶችን በምዕራብ መኖሪያቸው አድርገው በአንድ በር እየገቡ በአንድ አዳራሽ እየተሰበሰቡ እንደማዕረጋቸው በቆብና በአስኬማ እየተቀመጡ ሰርከ ህብስታቸው እንዲመገቡ አድርገው ከቆዩ በኋላ መጋቢት 10 ቀን ዐርፈው በዋሻው ውስጥ ተቀብረዋል። በስማቸው በፈለቀ ጠበል በሽተኞች በተለይ በመውለድ የሚሰቃዩት ይፈወሳሉ። ከአቡነ ተከስተ ብርሃን ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
የመድኃኒታችን የመስቀሉ በረከት ከሁላችን የክርስቲያን ወገኖች ጋራ ይኑር ለዘላለሙ አሜን።
(#ስንክሳር_ዘወርኀ_መጋቢት እና #ገድለ_ቅዱሳን)https://t.me/finotebirhan12
🔴ሳምንታዊ የአርብ የሰንበት ትምህርት ቤታችን ጸሎት 11:30 ይጀምራል።
Available now! Telegram Research 2025 — the year's key insights 
