en
Feedback
የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

Open in Telegram

ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።

Show more
2 620
Subscribers
+324 hours
+207 days
+3730 days
Posts Archive
#መልካም_ዜና በዛሬው እለት በሰሜን አሜሪካ ከሚገኙ የቅዱስ ሚካኤል ማኅበር ልጆች መካከል የሆኑት መልአከ ሰላም ቀሲስ እስክንድር ወ/ማርያም እና ወንድማችን ሄሎም ተስፋዬ ከባለቤቱ አርቲስት አዚዛ አህመድና ልጆቻቸው ጋር በሰንበት ት/ቤታችን ጽ/ቤት በመገኘት ለሚዲያ ክፍሉ አገልግሎት ማጠናከሪያ የሚያስፈልጉ ቁሳቁሶችን በድጋፍ አስረክበውናል። በዕለቱ የሰንበት ት/ቤታችን ሰብሳቢ መ/ር ተስፋዬ ተሾመ እና ምክትል ሰብሳቢ ወጣት ካሳሁን እሸቱ እንዲሁም ከስራ አመራር የሚዲያ ክፍሉ ሰብሳቢ ወጣት አፈወርቅ በላቸው ፣የሕጻናት ክፍል ሰብሳቢ ኢ/ር ዳዊት አበበ ፣ እና የሚዲያ ክፍል አባላት ተገኝተው ተረክበዋል።በቀጣይ ድጋፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ቃል የገቡ ሲሆን በተጨማሪም የማኅበሩ አባላት በሆሣዕና አገልግሎት ላይ ላደረጉት ከፍተኛ አስተዋጽኦም የምስጋና የምስክር ወረቀት ተሰጥቷቸዋል። በተያያዘ መልካም ዜና የሰንበት ት/ት ቤታችን አባል በሆኑት ዲያቆን ዳንኤል ተክሌ ለሚዲያ ክፍሉ ፕሮጀክተር  ገቢ ተደርጎለታል እንዲሁም በሰሜን አሜሪካ የሚገኙት የሰንበት ትምህርት ቤታችን አባል አቶ ብሩክ ገ/ሥላሴ ከነባለቤታቸው ለሚዲያ ክፍሉ ማጠናከሪያ እንዲሆን የ10,000# (አስር ሺህ ብር) ድጋፍ አድርገውልናል ። ድጋፍ ያደረጉልን ሁሉንም አምላከ ቅዱስ ሚካኤል በነፍስ በስጋ ይጠብቅልን በማለት የሰንበት ት/ቤታችን ሰብሳቢ ምስጋና አቅርበዋል። በመጨረሻም የሰንበት ትምህርት ቤታችን ሚዲያ ክፍል ራሱን ለማደራጀትና ለማሳደግ እያደረገ ላለው የስቱዲዮ ግንባታ እንቅስቃሴ ሁላችንም በገንዘብ ወይም የማቴሪያል ድጋፍ በማድረግ የድርሻችንን አበርክቶ ልንወጣ ይገባል።    የኢ/ያ ንግድ ባንክ - 1000555650594 (media/ሚዲያ) በማለት የበረከቱ ተሳታፊ ይሁኑ እግዚአብሔር ይስጥልን ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ የእግዚአብሔር ቤት በእግዚአብሔር መንገድ መመራት እንደሚኖርበት አስገነዘቡ። ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በተመረጡት ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅና የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ የአቀባበል መርሐ ግብር ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት አባታዊ መልዕክት የእግዚአብሔር ቤት በእግዚአብሔር መንገድ ብቻ መመራት ይኖርበታል ብለዋል። የእግዚአብሔር ቤት በአምልኮተ እግዚአብሔርና በጸሎት ከመራነው ሁሉም ነገር ቀና ይሆናል ዓለማዊ መንገድ ከተደባለቀበት ግን አደገኛ ነው "ጋሻና ቅል ለየቅሉ ይሰለል።" እንደሚባለው መንፈሳዊነትና ፖለቲካን ለይተን መጎዝ ይኖርብናል።ብለዋል። አያይዘውም ለአዲሶቹ አመራሮች የሁላችንም ድጋፍና ጸሎት ያስፈልጋቸዋል።ስለሆነም ሁላችንም እንደ አንድ ቃል ተናጋሪና እንደ አንድ ልብ መካሪ በመሆን በሀቅና በቅንነት ልናግዛቸው ይገባል ብለዋል።ይህችን ታላቅ ቤተክርስቲያን በእግዚአብሔራዊ መንገድ ሰርተን ካልጠበቅናት አደጋው የከፋ ይሆናል። ያሉት ቅዱስነታቸው ይህን በመገንዘብም ቤተክርስቲያናችንን በቀና መንገድና በመንፈሳዊነት መምራት ይኖርብናል ብለዋል። ሰላም የሚገኘው ከሰላማዊቷ ቤተክርስቲያን ነው ያሉት ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ ከቤተክርስቲያን ያልተገኘ ሰላም ከየት ሊገኝ ይችላል? የተሰጠን ኃላፊነት መንፈሳዊ መሆኑን ግንዛቤ ውስጥ በማስገባትም ለአገራችን ሰላም የበኩላችንን አስተዋጽኦ ለማበርከት በትጋት መስራት ይኖርብናል ብለዋል። ጥላቻ፣ዘረኝነት፣ጎጠኝነት አይጠቅምም እኛ መንፈሳዊያን ነን እግዚአብሔር ሲፈጥረን ንፁሃን አድርጎ ነው የፈጠረን እኛ በራሳችን መንገድ በመጓችን ነው ወርደን ተጠባቂዎች የሆነው። ያሉት ቅዱስነታቸው እኛ ጠባቂዎች መሆናችንን አውቀን የጠባቂነት ሚናችንን ከጥላቻና ከዘረኝነት በራቀ መንገድ በመፈጸም ለሰይጣን ሳይሆን ለእግዚአብሔር ተመችተን መገኘት አለብን ብለዋል። በመጨረሻም አሁን ለተመረጡት አባቶች እግዚአብሔር አምላክ ጽናትንና ብርታትን ይስጥልን።የአገልግሎት ጊዜአቸውን ጨርሰው የተሰናበቱትን አባቶችም እግዚአብሔር አምላክ በቸርነቱ ይጠብቅልን ሥራዎቻቸውን ሁሉ ይባርክ በማለት መርሐ ግብሩን በጸሎት አጠናቀዋል። © የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

        እንኳን ደስ ያላችሁ!! በዛሬው ዕለት በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የፍኖት መረዳጃ ዕድር በልዑል እግዚአብሔር መልካም ፈቃድ መልዓከ ሰላም ቀሲስ እስክንድር ወልደማሪያም ባሉበት ምስረታው እውን ሆኖል። በዕለቱ በርካታ  የዕድሩ መስራች አባላት ተገኝተው የመተዳደሪያ ደንብ ላይ ውይይትና ገለጻ በአቶ አንዱአምላክ ፈቃዱ ቀርቦ ውይይት ከተደረገ በኋላ እድሩን ለሁለት ዓመት የሚያገለግሉ አባላትን መርጧል ። የሰንበት ት/ቤታችን ምክትል  ሰብሳቢ የሆኑት አቶ ካሳሁን እሸቱ የዕድሩ መመስረት ለዘመናት በጉጉት ሲጠበቅ የነበረና አሁን ግን አምላከ ሚካኤል ፈቅዶ እውን በመሆኑ የተሰማቸውን ደስታ የገለጹ ሲሆን። ሰንበት ትምህርት ቤቱ አቅሙ በፈቀደ መጠን ከእድሩ ጎን እንደሚቆም ተናግረዋል በመጨረሻም የእድሩ መስራችና አባል የሆኑት መልአከ ሰላም ቀሲስ እስክንድር እድሩ በመመስረቱ የተሰማቸውን ደስታ ከገለጹ በኋላ እድሩን ለመደገፍ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንደሚያደርጉ ለአባላቱ ቃል ገብተዋል። በመጨረሻም አዲስ ለተመረጡት የዕድሩ የኮሚቴ አባላት ጸሎትና ቡራኬ በመስጠት ኮሚቴው የተጣለበትን ኃላፊነት ተግቶ እንዲወጣ አባታዊ ምክራቸውን አስተላልፈዋል። መስራች አባላትም በዕለቱ የቤተሰብ ቅጽ የተሞላ ሲሆን የእድሩን መተዳደሪያ ደንብና የዕድር ደብተር በመውሰድ ተጠናቋል!! እግዚአብሔር ቀሪውንም ያስፈጽመን🙏🙏

ግንቦት 23/2017 ዓ.ም የደብራችን ሕንጻ እና የሰ/ት/ቤታችን የአገልግሎት ሕንጻ ምርቃት በፎቶ
+9
ግንቦት 23/2017 ዓ.ም የደብራችን ሕንጻ እና የሰ/ት/ቤታችን የአገልግሎት ሕንጻ ምርቃት በፎቶ

"ስለዚህ አንድ ሥጋ ናቸው እንጂ ወደ ፊት ሁለት አይደሉም። እግዚአብሔር ያጣመረውን እንግዲህ ሰው አይለየው።" ማቴ 19 ÷6 በዛሬው እለት ግንቦት 24 /2017 ዓ.ም ጋብቻችሁን በቅድስት ቤተክርስቲ
+1
"ስለዚህ አንድ ሥጋ ናቸው እንጂ ወደ ፊት ሁለት አይደሉም። እግዚአብሔር ያጣመረውን እንግዲህ ሰው አይለየው።" ማቴ 19 ÷6 በዛሬው እለት ግንቦት 24 /2017 ዓ.ም ጋብቻችሁን በቅድስት ቤተክርስቲያን ሥርዓት የፈጸማችሁት የሰንበት ትምህርት ቤታችን የፍኖተ ብርሃን አገልጋይ ወንድማችን ማቴዎስ ወ/ገብርኤልና እና  እህታችን ተስፋነሽ ፍቅሩ የአብርሃምን እና የሳራን ጋብቻ የባረከ አምላክ ጋብቻችሁን ይባርክላችሁ።  ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል በክንፉ ከልሎ በፍቅርና በጤና ይጠብቃችሁ ዘንድ መልካም ምኞታችን ነው!      እንኳን ደስ አላችሁ  ፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

"ስለዚህ አንድ ሥጋ ናቸው እንጂ ወደ ፊት ሁለት አይደሉም። እግዚአብሔር ያጣመረውን እንግዲህ ሰው አይለየው።" ማቴ 19 ÷6 ግንቦት 24 /2017 ዓ.ም ጋብቻችሁን በቅድስት ቤተክርስቲያን ሥርዓት የፈጸማችሁት የሰንበት ትምህርት ቤታችን የፍኖተ ብርሃን አገልጋይ ወንድማችን ማቴዎስ ወ/ገብርኤልና እና  እህታችን ተስፋነሽ ፍቅሩ የአብርሃምን እና የሳራን ጋብቻ የባረከ አምላክ ጋብቻችሁን ይባርክላችሁ።  ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል በክንፉ ከልሎ በፍቅርና በጤና ይጠብቃችሁ ዘንድ መልካም ምኞታችን ነው!      እንኳን ደስ አላችሁ  ፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

"ስለዚህ አንድ ሥጋ ናቸው እንጂ ወደ ፊት ሁለት አይደሉም። እግዚአብሔር ያጣመረውን እንግዲህ ሰው አይለየው።" ማቴ /2017 ዓ.ም ጋብቻችሁን በቅድስት ቤተክርስቲያን ሥርዓት የፈጸማችሁት የሰንበት ትምህርት ቤታችን የፍኖተ ብርሃን አገልጋይ ወንድማችን ያሬድ ጥላሁን  እና  እህታችን ምሕረት የአብርሃምን እና የሳራን ጋብቻ የባረከ አምላክ ጋብቻችሁን ይባርክላችሁ።  ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል በክንፉ ከልሎ በፍቅርና በጤና ይጠብቃችሁ ዘንድ መልካም ምኞታችን ነው!      እንኳን ደስ አላችሁ  ፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

የደብራችን የጽ/ጽ/ሐ/ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል አካባቢ የተገነባው እና የሰንበት ትምህርት ቤታችን የአገልግሎት ሕንፃ በዛሬው እለት ግንቦት 23/2017 ዓ.ም ብፁዕ አቡነ ሕዝ
+9
የደብራችን የጽ/ጽ/ሐ/ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል አካባቢ የተገነባው እና የሰንበት ትምህርት ቤታችን የአገልግሎት ሕንፃ በዛሬው እለት ግንቦት 23/2017 ዓ.ም ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል የከፋ ፣ሸካና ቤንችማጂ  ሃገረ  ስብከት ሊቀ ጳጳስና የሰዋሰው መንፈሳዊ ኮሌጅ የበላይ ሊቀጳጳስ ፣አቡነ ማርቆስ የጠቅላይ ቤተክህነት የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልዕኮ መምሪያ ሊቀ ጳጳስ ፣ አቡነ እንጦንስ የምዕራብ ሐረርጌ ሃገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ አቡነ መልከጼዴቅ የጉራጌ ሃገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ መጋቤ ሃይማኖት አባ ጥዑመ ልሳን የልደታ፣ ቂርቆስና አዲስ ከተማ ክፍላተ ከተማ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ፣ መልአከ ኃይል ቆሞስ አባ ገ/ሥላሴ በላይ የደብረኃይል ቅዱስ ራጉኤል ቤ/ክ ዋና አስተዳዳሪ ፣ የደብራችን ዋና አስተዳዳሪ መልአከ ብርሃን አዕምሮ ምስጋናው እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው የቤተክህነትና የመንግስት መስሪያ ቤት ኃላፊዎችና ተወካዮች በተገኙበት በታላቅ ድምቀት ተመረቀ። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com