የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)
Open in Telegram
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
Show more2 761
Subscribers
+324 hours
+87 days
+4830 days
Posts Archive
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
ጉዳዩ፡ የጥምቀት ዘማርያንን ስለማሳወቅ
በቅድሚያ መንፈሳዊ ሰላምታችንን እያቀረብን ከዚህ በታች በስም የተዘረዘሩ አባላት የ2017 ዓ/ም የጥምቀት አገልግሎት ላይ ዘማሪያን መሆናቸውን በአክብሮት እናሳውቃለን፡፡
1. መምህር ተስፋዬ ተሾመ
2. አቶ ካሳሁን እሸቱ
3. ወ/ሮ ቤተልሔም ገነነው
4. መ/ር ወንደሰን መኮንን
5. ኢ/ር ዳዊት አበበ
6. ዮሴፍ አምሐ
7. አቶ እንግዳወርቅ አረፋይኔ
8. አቶ አፈወርቅ በላቸው
9. መ/ር ስለሺ ይርጋ
10. ወ/ሮ ሰላማዊት ይልማ
11. አቶ አሸናፊ ኀ/ጊዮርጊስ
12. አቶ አበራ መላኩ
13. አቶ ሙሉጌታ ሰማን
14. ምእራፍ እንዳሉ
15. ሰላማዊት በላይ
16. ቤተልሔም ታደለ
17. ቤተልሔም ይልፋሽዋ
18. አብርሀም ተመስገን
19. ከተማ ደገፉ
20. እንቁ ታደሰ
21. አቶ ኢሳይያስ ባደግ
22. ሮቤል አሰፋ
23. አዲስ ሀይሉ
24. ዳንኤል ታደሰ
25.ጌታቸው ከበደ
26. አቶ ዳንኤል ጌታቸው
27. ዮሴፍ ከበደ
28. ሚኬኤሌ ዘብሬ
29. ወ/ሮ ትዕግስት አማረ
30. ዲ/ን ዘላለም ታከለ
31. አ/ቶ ወርቅነህ ባህሩ
32. ቤተልሔም በኃይሉ
33. ሜሮን ብርሃኑ
34. ናትናኤል ቴዎድሮስ
35.ዲ/ን ቡሩክ ይብራህ
36 ይርጋለም አስፋ
37. አበባ አሸናፊ
38. ሚኬኤሌ ፍቅረማርያም
39. ብርሐኑ ንጉሴ
40. አየለች ደጉ
41. ፀሐይ አምላኩ
42. በቀለች ማሞ
43. ካሰች ግደይ
44. እቴነሽ መኮንን
45. የዚች አለም ሲሳይ
46. አሰገደች ታደሰ
47. ቢኒያም ሰይፉ
48 ሙሉነሽ ፀጋዬ
49 ሔለን ማሙሽ
50 ኤደን ጥበቡ
51 ምትኩ አሰፋ
52 ሳራ ፍቅሩ
53 ያዕቆብ ተስፋዬ
54 መ/ር ፈቃዱ ኪሮስ
55 ተስፋዬ በዙ
56 አለም ንጉሴ
57 ቆንጂት ወ/ሰንበት
58 ገነት መስቀሉ
59 ገነት ጉተማ
60 ነአምን ኤልያስ
61የአብስራ አክሊሉ
62 ሚኪያስ ተስፋዬ
63 መሠረት አሰፋ
64 ኤልያስ አስፋው
65ፋንታዬ አለሙ
66 ትንሳዬ ደመቀ
67 አዲስ ሀይሉ በቀለ
68 ተስፋለም ጣዕሙ
69 ሚኪያስ ፍቅሩ
70 ውቢት ሽታነህ
71ሜሮን ተክላይ
72 ዮሃንስ ደመቀ
73 አብርሐም አስራት
74 ገነት መኮንን
75 ማስረሻ ፈንታው
76 መስፍን መኮንን
77 ረድኤት ኃይሉ
78 ሃብታሙ ኤቢሳ
79 እጸገነተ ፍቅሬ
80 መሰረት አለሙ
81 ማትያስ ወ/ገብርኤል
82 ዲ/ን ዘካሪያስ ኩሙሳ
83 ናሆም ርዕሶም
84 ዲ/ን ብሩክ ሲሳይ
85 ቢኒያም ተስፋዬ
86 ኃ/ሚካኤል ገ/አሳይ
87 ሰለሞን ክብረት
88 ተመስገን ታምራት
89 ኤርሚያስ በድሉ
90 ቤዛ አሰግድ
91 እስጢፋኖስ ኪሮስ
92 አይናለም ደጀኔ
93 ናታን ቴዎድሮስ
94 ብሩክ ተ/ሀይማኖት
95 ስመኝ ጸጋዬ
96 ዳዊት ፍቅሬ
97 ያዕቆብ ግሩም
98 ሰላማዊት ገ/ሚካኤል
99 መዓዛ ንጉሴ
100 ዲ/ን ብሩክ አበበ
101 ሰናይት ዜናዊ
102 ማርታ ናስር
103 ዲ/ን አቤኔዘር አየለ
104 ዲ/ን ዳዊት ይመስል
105 ራሄል ህሸ
106 ዲ/ን ሸዋንግዛው ሀብቴ
107 ጽዬን ሀብቴ
108 ራህዋ ሙላው
109 ረድኤት ከድር
110 ብርሀኑ ዘሪሁን
111 ፋሲካ መላ
112 ሳምሶን አብዩ
113 አበበች በቀለ
114 ሔለን ምስጋናው
115 አስናቁ አበበ
116 ጥላሁን እሸቱ
117 አዲስ ጌታቸው
118 የኔነሽ ታከለ
119 ቸሩ ባይሳ
120 አርሴማ እንየው
121ትዕግስት ከበደ
122 ሀብታሟ ተኮላ
123 አበረ እሸቴ
124 ፀጋዬ ጌታሁን
125 ዘሪቱ ብርሃኑ
126 ሳራ አብዱልቀኒ
127 ዳናይት ገ/መድህን
128 ሄለን ገ/እግዚአብሔር
129 ሰላማዊት ተፈራ
130 ሰላም ታደለ
131 ፍቅርተ ካሳሁን
132 ዮርዳኖስ አለማየሁ
133 ሰላም ወርቁ
134 አቤል ተስፋዬ
135 ታምሩ ማሬ
136 ሔዋን አብርሀም
137 ልድያ አሰፋ
138 ዳግም መሰረት
139 ሰለሞን መብራቱ
140 ትዕግስት ደረጄ
141 ዮሐንስ ትዳሩ
142 መስታወት እያዩ
143 መስከረም ሀይሌ
144 ፍጹም ወልዴ
145 አቤል ወ/ጻዲቅ
146 መክሊት ወንድማገኝ
147 ብሩክ ብርሐኑ
148 ዲ/ን አልአዛር ፍቅሩ
149 ደሊና ፍቅሩ
150 ትዝታ ወንድሙ
151 ሠላምነህ ገሠሠ
152 ዲ/ን ዳግም በላይ
153 ሜሮን አየለ
154 አቤኔዘር ልደቴ
155 ፊሊሞን አብርሐ
156 ቤተልሔም ቀለመወርቅ
157 ሻምበል ወ/ኪሮስ
158 ቤተልሔም ጸጋዪ
159 ሠላማዊት ሸዋንግዛው
160 ብሌን ተስፋዬ
161 ዓለምፀሐይ ለገሰ
162 እንዳለ መኳንንት
163 እዮብ ታደለ
164 ማራማዊት ሽፈራው
165 ምንተስኖት አሠፋ
166 ትዕግስት ከበደ
167 ናትናኤል ካሳሁን
168 ፀሐይ ተክሌ
169 ሲ/ር ውቢት ተሾመ
170 ቤተልሔም ዳዊት
171 ዲ/ን በሐይሉ ተፈራ
172 አለምሰገድ ወልዴ
172 አርሴማ ሙሴ
174 ዮናታን ብርሃኑ
175 ሰገን ሐድጉ
176 ናትናኤል ሩዳን
177 ቤተልሔም ፈቀደ
178 እመቤት ባይሳ
179 ዝናሽ ቶላ
180 ሔርሜላ አወጣኽኝ
181 ቃልኪዳን አሸብር
በቃና ዘገሊላ ዕለት የሚያገለግሉ ተጨማሪ አባላት
1 ካሳሁን ሞገስ
2 ቤተልሔም ንጉሴ
3 ዩሴፍ ግርማሜ
4 ብርቱካን ሽፈራው
5 ዘላለም ነጋሽ
6 ስምረት ኃብተየስ
7 ሰለሞን ዘሚካኤል
8 ሕይወት ወ/ፀጋ
9 ኤፍሬም ዱላ
እግዚአብሔር አገልግሎታችን ይባርክ!!!
የወጣት አባላት ጉዳይ ክፍል
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
ለውድ የሰ/ት/ቤታችን አባላት
እንኳን ለብርሃነ ልደቱ ወጥምቀቱ አደረሳችሁ እያልን የበዓለ ጥምቀት ዘማርያን የሆናችሁ አባላት በሙሉ የበዓሉ የመጨረሻ የጥምቀት ጥናት ዕለታት የፊታችን ቅዳሜ ጥር 03 እና ጥር 04/2017 እንዲሁም ማክሰኞ ጥር 06/2017 ዓ.ም ከምክሐ ደናግል ወጣቶች መንፈሳዊ ሰ/ት/ቤት ጋር በጋራ የምናጠና
በመሆኑ በእነዚህ የጥናት እለታት እንድትገኙ እናሳስባለን።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
እንኳን ለጌታችን ለመድሐኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል አደረሰን አደረሳችሁ የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ እያተከታተላችሁ እንደሆነ እናምናለን ንባብ ከተጀመረበት ጊዜ አንሰቶ ሳናቋረጥ ያነበበን የሉቃስ ወንጌልን አበቃን።አሁንም ደግሞ የዮሐንስ ወንጌልን ማንበባችንን እንቀጥል መልካም የንባብ ጊዜ
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት ዕለት በሰ/ት/ቤታችን የነበረው የምስጋና መርሐግብር ዝማሬ
እንኳን አደረሳችሁ
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
#መልእክተ_ቅዱስ_ፓትርያርክ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡
በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ የምትኖሩ፤
ከሀገር ውጭ በተለያዩ አህጉር የምትገኙ፤
የሀገራችንን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረፉ የቆማችሁ፤
በሕመም ምክንያት በየፀበሉና በየሆስፒታሉ ያላችሁ፤
እንዲሁም የሕግ ታራሚዎች ሆናችሁ በየማረሚያ ቤቱ የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያት በሙሉ፤
በምሉእ ፍቅሩ ሰውን ከባርነት ወደ ነጻነት ለመመለስ በሥጋ ሰብእ የተወለደው ጌታችን ኣምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንኳን ለሁለት ሺሕ ዐሥራ ሰባት ዓመተ ምሕረት የልደት በዓል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ፡፡
“ስብሐት ለእግዚአብሔር በሰማያት ወሰላም በምድር ለዘሠምሮ ለሰብእ፤ ክብር በሰማያት ለእግዚአብሔር ይሁን›› በምድርም እጅግ ለወደደው የሰው ልጅ ሰላም ይሁን” (ሉቃ ፪÷፲፬)
ይህ ቃለ ሰላም በጌታችን ዕለተ ልደት የተነገረ ነው፣ ቃሉ የተነገረው እንዲሁ እንደ ተራ ነገር ሳይሆን በቃለ መዝሙር እየተደጋገመ ነው፡፡ የተዘመረውም በምድራውያን ደራሲዎች ሳይሆን በሰማያውያን መላእክተ እግዚአብሔር ነው፣ የያዘው መልእክትም ሰማያውያንና ምድራውያንን ሁሉ ያካለለ ነው፡፡ የመልእክቱ ገዢ ሓሳብም አምላክ ከሰውነታችን ጋር ባለመለያየት፣ ባለመጠፋፋት፣ ባለመቀላቀል፣ ባለመዋዋጥ፣ ባለመለዋወጥና ያለባዕድና አንድ አካል፣ አንድ ክዋኔ፣ አንድ ጠባይ ሆኖ በተዋሕዶ ተገልጾኣልና እግዚአብሔር ይክብር ይመስገን፡፡ የተዋሕዶውም ምስጢር ሰላምን ያሰፍናልና እግዚአብሔር ሰውን በእጅጉ መውደዱ ከዚህ ተዋሕዶ ዓውቀናል የሚል ነው፡፡
በእርግጥም እግዚአብሔር ሰውን ለመውደዱ ከዚህ የበለጠ ማሳያ ወይም ማስረጃ የለም፤ እንከን የለሽ ንጹህ አምላክ የእኛን ኃጢአተኛ ሰውነት አካሉ አድርጎ ተወለደ ሲባል ላስተዋለው ሰው ምንኛ ቢወደን ነው የሚለው ጥልቅ አድናቆትን ያጭራልና ነው፡፡ይህ ብቻም አይደለም በዚህ ነገረ ተዋሕዶ ምክንያት ሰውነታችን አምላክ ሆኖ በመንበረ ጸባኦት እንዲቀመጥ መብቃቱ የድኅነታችንና የክብራችን ከፍታ ምን ያህል አስተማማኝ ደረጃ ላይ እንደደረሰ መንፈሳችን በአንክሮ ይረዳዋል፡፡ድምር ውጤቱም በእግዚአብሔርና በሰው መካከል ፍጹምና አስተማማኝ ሰላም መፈጠሩን ያስረዳናል፤ ሰማያውያኑ መላእክተ እግዚአብሔር በመዝሙራቸው ያበሰሩን ይህንን የምስራች ነው፡፡
የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት!
እኛ ክርስቲያኖች እግዚአብሔር ፍቅር ነው፣ እግዚአብሔር በእጅጉ ይወደናል ስንል እንዲሁ ከሜዳ ተነሥተን ኣይደለም፡፡ በበደላችንና በኃጢአታችን ሳይጸየፈን ሰውነታችንን በረድኤት ወይም በኅድረት ያይደለ በኩነት ተዋሕዶ ወደ አምላክነት ደረጃ ከፍ ስላደረገው ነው እንጂ፡፡ እግዚአብሔር በዚህ ፍጹምና ምሉእ ፍቅሩ ሰውነታችንን በመበረ ጸባኦት ኣስቀምጦ መላእክት ሳይቀሩ ፍጥረታትን በሙሉ እንድንገዛ አድርጎናል፤ ምክንያቱም መላእክት በዕለተ ልደት የዘመሩለት በተዋሕዶ አምላክም ሰውም ለሆነ ለቤተ ልሔሙ ሕፃን እንጂ ለመለኮት ብቻ ኣይደለምና ነው፡፡ የዕለተ ልደት መዝሙር ዛሬም በሰማያትም ሆነ በምድር በተዋሕዶ ሰውም ኣምላክም የሆነ አንዱ ኢየሱስ ክርስቶስ ይመለክበታል፣ ይመሰገንበታል፡፡የሰማዩና የምድሩ ዕርቅ ወደ ኋላ ላይመለስ ላንዴና ለመጨረሻ ጊዜ በዚህ ተከናውኖኣል፣ የእግዚአብሔር ፈቃድ የሰውም አዋጭ ምርጫ ይህ ዕርቅ ተጠብቆ እንዲኖር ነው፣ ያለ ዕርቅ ሰላም ሕይወት የለውምና፡፡
የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት!
የእግዚአብሔር ክብርና ሰላም በእጅጉ የተሳሰሩና የተቆራኙ ናቸው፤ እኛ እግዚአብሔርን ካከበርነው፣ ካዳመጥነው፣ ከታዘዝነውና ከተከተልነው ሰላም አለ ማለት ነው፡፡ ለሱ ካልታዘዝንና እሱን ካላከበርን ግን ዘላቂ ሰላምን ማግኘት ፈጽሞ የማይታሰብ ነው፤ ምክንያቱም ሰላምን ጨምሮ መልካም ነገር ሁሉ ያለው በእግዚአብሔር እጅ ነውና፡፡ ዛሬ በሁሉም የዓለማችን ማዕዘን የሚታየው የሰላም መደፍረስ እግዚአብሔርን ካለማክበራችንና ለሱ ካለመታዘዛችን የተነሣ እንደሆነ መዘንጋት የለብንም፡፡ ዓለም ከእግዚአብሔር ቃል ርቃ ለመሄድ በእጅጉ እየኳተነች ነው፤ በዚህ እኩይ ተግባርዋ ደግሞ እግዚአብሔር ለስጋትና ለጉስቁልና አሳልፎ እየሰጣት ነው፡፡ እግዚአብሔር በምስጢረ ሥጋዌው ቢታረቃትም ዕርቁን ማክበር አቅቶአታል፤ ይህንን የእግዚአብሔር ጸጋ ቸል ብላ የምታደርገው ሩጫ የትም ሊያደርሳት እንደማይችል ብታውቅና በንስሓ ብትመለስ እግጅ ተጠቃሚ ትሆናለች፡፡
የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት!
የእግዚአብሔር ቃል “እናንተስ ከማይጠፋ ዘር ተወለዳችሁ” ብሎ ተስፋውን እንደነገረን ምድባችን ከማይጠፋ ዘር እንዲሆን ክርስቲያኖች የሆን ሁላችን በአእምሮ ጐልብተን፣ በሥነ-ምግባር ኣምረን፣ ጤናማ ሕይወትን ልንመራ ይገባናል፡፡
የአምላካችንን በዓለ ልደት ስናከብር ነገረ እግዚአብሔርን፣ ነገረ ፍቅርን፣ ነገረ ዕርቅንና ነገረ ሰላምን በማኅበረሰባችን የማሥረጽ አጀንዳ ይዘን ልናከብር ይገባል፡፡
ጠቡ ፣ ጥላቻው፣ መለያየቱ፣ መጠፋፋቱ፣ ለወንድሜ ከማለት ይልቅ ለኔ ለኔ ማለቱ ሲጎዳን እንጂ ሲጠቅመን ኣላየንም፡፡ አሁንም ወደ ልባችን እንመለስና በፍቅር፣ በዕርቅና በእኩልነት፣ በስምምነትና በወንድምነት ወደሚገኝ አንድነት እንምጣ፤ የልደቱ መዝሙር ያስተማረን ይህና ይህ ብቻ ነውና፡፡ በሌሎቹ ክፍለ ዓለማት እንደሆነው ሁሉ በሀገራችን የተከሠተው አላስፈላጊ ግጭት ብዙዎችን አሳጥቶናል፤ ብዙዎችንም ከቤት ንብረታቸው አፈናቅሎ ሜዳ ላይ ፈሰው የሰቆቃ ኑሮ እንዲገፉ አድርጎብናል፡፡ የሀገር ሀብት እንዲወድም ሆኖአል፤ ልጆቻችን ምናለ ከእንግዲህ ወዲህ ቢበቃንና ምድሪቱን የሰላም አየር እንድትተነፍስ ብንፈቅድላት፤ ይህ የወቅቱ የቤተክርስቲያናችን ዋነኛ መልእክትና ጥሪ ነው፡፡
በመጨረሻም፡-
በዓለ ልደት የእግዚአብሔር በዓል ነውና፣ እግዚአብሔር በምድራችን ሰላምን ያወርድ ዘንድ ካለን ከፍለን ለተፈናቃዮች፣ ለነዳያን እና ለአካል ጉዳተኞች በመለገስ በዓሉን በመንፈሳዊ ደስታና በሰላም እንድናከብር አባታዊ መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን፤
መልካም በዓለ ልደት ያድርግልን፡፡
እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ
ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን!
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ
ተክለሃይማኖት
ታኅሣሥ ፳፱ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
ልደተ ክርስቶስ
ታኅሣሥ ሃያ ዘጠኝ በዚህች ቀን የከበረና የተመሰገነ ታላቅ የልደት በዓል ሆነ የጌታችንና የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም የተወለደባት ዕለት ናት።
የቤተ ክርስቲያን መምህራን አባቶቻችን የከበረ የልደትን በዓል በሁለት ቀኖች ያከብሩ ዘንድ በምክራቸው ተስማሙ ከወደኋላ ባለ በሃያ ስምንት ሌሊቱ የልደት በዓል ነው በሃያ ዘጠኝ መዓልቱ ጳጉሜን ስድስት በሆነ ጊዜ በዚያች ዓመት የልደት በዓል በሃያ ስምንት በመዓልት ይከበራል። ጳጉሜን አምስት ከሆነ ግን በሃያ ዘጠኝ ይሆናል ስለዚህ የበዓላት ሁሉ ራስ የሆነ የከበረ የልደት በዓል በሁለቱ ቀኖች እንዲከበር አዘዙ ወሠኑ።
የበዓላት ራስ ስለሆነ ስለ ከበረ የልደት በዓል የከበረ ወንጌል እንዲህ አለ። በንጉሡ በኄሮድስ ዘመን በይሁዳ ዕፃ በቤተልሔም ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በተወለደ ጊዜ እነሆ የፍልስፍና ሰዎች ከምሥራቅ መጥተው ወደ ኢየሩሳሌም ደረሱ። ኮከቡን በምሥራቅ አይተን እንሰግድለት ዘንድ መጥተናልና የተወለደው የአይሁድ ንጉሥ ወዴት ነው እያሉ።
እሊህ ፈላስፎች ከበለዓም ወገን ናቸው እነርሱም በከዋክብት የሚፈላሰፉ ናቸው በመጽሐፋቸው በበለዓም መጽሐፍም የአይሁድ ንጉሥ ሊወለድ እንዳለው ተጽፎአል እርሱ በለዓም ከያዕቆብ ኮከብ ይወጣል ከእስራኤልም ንጉሥ ብሎ ነበርና።
ይቅር ባይ እግዚአብሔርም በረቀቀ ጥበቡ በሚያምኑበትም ሳባቸው እነርሱ ከዋክብትን በመጠባበቅ የሚፈላሰፉ ናቸውና ይህንንም ኮከብ ገለጠላቸው በአዩትም ጊዜ ደስ አላቸው መልኩ በብዙ አይነት ልውጥ ነውና። ሕፃን የታቀፈች ድንግል ብላቴናን ይመስላል እርሱም በቀን ይጓዛል በሌሊትም ይሠወራል ከሰውም ሲገናኙ ይሠወርና ሲቆሙ በሌላ አንጻር ይገለጥላቸዋል።
እነርሱም ወደ ኢየሩሳሌም ሲደርሱ ያ ኮከብ ተሠወራቸው እጅግ አዘኑ የሚያደርጉትንም አላወቁም ከዚህም በኋላ ወደ ኢየሩሳሌም ከተማ ገብተው ስለተወለደው ንጉሥ ጠየቁ።
ንጉሡ ኄሮድስም በሰማ ጊዜ ደነገጠ ኢየሩሳሌምም በመላዋ ከእርሱ ጋር ደነገጠች። የካህናት አለቆችና የሕዝቡን ጸሐፊዎች ሁሉ ሰብስቦ ክርስቶስ በየት ይወለዳል ብሎ ጠየቃቸው። በይሁዳ ዕፃ በቤተልሔም ነው አሉት በነቢይ እንዲህ ተብሎ ተጽፏልና።
የኤፍራታ ዕፃ ቤተልሔም አንቺም ከይሁዳ ነገሥታት አታንሺም ወገኖቼ እስራኤልን የሚጠብቅ ንጉሥ ካንቺ ይወለዳልና። ከዚህም በኋላ ኄሮድስ ሰብአ ሰገልን በጭልታ ጠርቶ ኮከቡ የታየበትን ዘመን ከነሱ ተረዳ።
ሒዳችሁ የዚያን ሕፃን ነገር እርግጡን መርምሩ ያገኛችሁትም እንደሆነ እኔም መጥቼ እሰግድለት ዘንድ በኔ በኩል ተመልሳችሁ ንገሩኝ ብሎ ወደ ቤተልሔም ሰደዳቸው። የነገራቸውንም ሰምተው ከንጉሡ ሔዱ እነሆ በምሥራቅ ያዩት ከከብ ወደ ቤተልሔም እስኪያደርሳቸው ይመራቸው ነበር ሕፃኑ ካለበትም ዋሻ ላይ ደርሶ ቆመ።
ኮከቡንም ባዩ ጊዜ እጅግ ደስ አላቸው ወደ ቤትም በገቡ ጊዜ ሕፃኑን ከእናቱ ከድንግል ማርያም ጋር አገኙት ወድቀውም ሰገዱለት ሣጥናቸውንም ከፍተው ወርቅ ከርቤ ዕጣን እጅ መንሻ አቀረቡለት።
በእግዚአብሔርም ፈቃድ ዮሴፍ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሕፃኑ ጌታ ኢየሱስም በዚያች ዕለት ወደ ቤተልሔም መጡ ስለዚህም ሰብአ ሰገል አገኙአቸው የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያለ ናዝሬት በሌላ ቦታ አላደገምና ከተወለደም ዕድሜው ሁለት ዓመት ሆኖት ነበር።
አምላክ ነውና ስለ መንግሥቱ ወርቅን ገበሩለት ክህነትም ገንዘቡ ነውና ዕጣንን ገብሩለት ማሕየዊ ለሆነ ሞቱ ምልክትም ከርቤን ገበሩለት። ወደ ኄሮድስም እንዳይመለሱ በሕልም ነገራቸው በሌላ መንገድም ወደ አገራቸው ተመልሰው ገቡ። አምላክ በሥጋ ስለመገለጡ ዓዋጅ ነጋሪዎችና ሰባኪዎች ሆኑ።
ይችም ዕለት ነቢዩ ኢሳይያስ ትንቢት ስለርሷ የተናገረላት ናት እንዲህ ብሎ እነሆ ድንግል ፀንሳ ወንድ ልጅን ትወልዳለች ስሙንም ዐማኑኤል ትለዋለች ትርጓሜውም እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ማለት ነው።
ዳግመኛም ኢሳይያስ እግዚአብሔር እንደ እኔ የሥጋ መጋረጃ በመጋረድ ተገለጸልኝ አለ። አሁንም ደግሞ አዲስ ሰማይ አዲስ ምድር እሠራ ዘንድ አለኝ አለ ሁለተኛም ከዕሴይ ሥር በትር ትወጣለች ከእርሷም ጽጌ አበባ ይወጣል አለ። ዳግመኛም ሕፃን ተወልዶልናልና ወንድ ልጅም ተሰጥቶልናልና ይኸውም ሥልጣን በጫንቃው የሆነ ክርስቶስ ነው። ስሙም ድንቅ መካር የዘላዓለም አባት የሰላም አለቃ ይባላል አለ።
ዳዊትም በመዝሙሩ እንዲህ አለ እግዚአብሔር አንተ ልጄ ነህ ዛሬም በተዋሕዶ ወለድኩህ አለኝ። ለምነኝ አሕዛብን ርስት አድርጌ እሰጥሃለሁ ግዛትህም በመላው ዓለም ነው። ዳግመኛም አብ አለ ቀዳማዊ ወልድ በኃይል ቀን ካንተ ጋራ ሳለሁ ከአጥቢያ ኮከብ በፊት ከሆድ ወለድኩህ እንደ መልከጼዴቅ ሥርዓት አንተ የዓለሙ አገልጋይ ካህን ነህ ብሎ እግዚአብሔር ማለ ከማለም አይጸጸትም።
ቤዛ ይስሐቅ በግዕ ከኅቱም ዕፀ ሳቤቅ እንደተገኘ ለእስራኤልም በበረሀ ውስጥ ከኅቱም አለት ውኃ እንደ ፈለቀ የደነቀች የአሮን በትርም እንደለመለመችና እንደ አፈራች። በሶምሶንም እጅ ውስጥ ከአህያ መንጋጋ አጥንት ውኃ እንደ ፈሰሰ።
እንዲሁ የጌታችን ልደት በኅቱም ድንግልና ሆነ። በዕፀ ጳጦስ ውስጥ እሳት እንደ ነደደች ዕፂቱም እንዳልተቃጠለች እንዲሁ የመለኮቱ እሳት ድንግልን አላቃጠላትም።
እንኳን ለብርሃነ ልደቱ በሰላም አደረሳችሁ።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
ውድ የጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚ/ቤ/ክ የፍኖተ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት አባላት እና ወዳጆች
የ2017 ዓ.ም. የገና(የልደት) በዓል ሥጦታን ለምታሰሩት ህንጻ ማጠናቀቂያ የሚሳተፉበት ዘመቻን እስከ ገና ድረስ እናደርጋለን። እነሆ ለሰንበት ትምህርት ቤታችን ፍቅራችንን ለመግለጽ ጊዜው አሁን ነው። ሰብአ ሰገል ለተወለደው ንጉስ አምሐን(ሥጦታን) እንዳበረከቱለት እናንተም የጌታችንን ልደት ምክንያት በማድረግ ለሰ/ት/ቤታችን ሕንጻ ማስፈጸሚያ የሚሆን ሥጦታችሁን
የወርቅ ሥጦታ - 1500- 2000 ና ከዚያ በላይ
የዕጣን ሥጦታ - ከ1000- 1500 ብር
የከርቤ ሥጦታ - ከ500-1000 ብር
እንድታስገቡ (እንድትለግሱ)በተወለደው አምላክ ስም ጥሪያችንን እናቀርባለን::
አምሐ ብላችሁ በመጻፍ
1000375969533
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
51281930205011
ዳሽን ባንክ
የፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት ሕንጻ አሰሪ
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
እንኳን ለብርሃነ ልደቱ በሰላም አደረሳችሁ!
"ዮም ሰማያዊ በጎል ሰከበ ለዘተወልደ እምቅድስት ድንግል ርእይዎ ኖሎት አእኰትዎ መላእክት፤
እነሆ ዛሬ ሰማያዊውን በበረት የተኛውንና ከቅድስት ድንግል ማርያም የተወለደውን እረኞች አዩት መላእክትም አመሰገኑት።"
እነሆ አራቱም ክፍላት
📌ሕፃናት ክፍል
📌ማዕከላውያን ክፍል
📌ወጣት ክፍል
📌ባለ ትዳር ክፍል የሚገኙበት
ልዩ የዝማሬ ቀን
በልደተ ክርስቶስ
ታኅሣሥ 29/2017 ዓ.ም
ቦታ፦ በስብከተ ወንጌል አዳራሽ
ሰዓት፦ ከ 10-12 ሰዓት
ይህንንም የመዳኛችን መጀመሪያ ቀን ሁላችንም በበዓሉ ቀን በቤተክርስትያን በመገኘት አምላካችንን በማመስገን እናክብረው።
ሲመጡ 2 ጧፍ አንዱ መባችን ይሆንና ሌላኛውን እናበራው ዘንድ ይዛችሁ ተገኙ።
ማስታወሻ፦ ከርቀት ቦታ የሚመጡ አባላት ስለሚኖሩና ሲመለሱ ትራንስፖርት ሊቸገሩ ስለሚችሉ በተባለው ሰዓት እንጀምር ዘንድ ሰዓት አክብረን እንምጣ።
የመዝሙር አገልግሎት እና የዜማ
ትምህርቶች ሥልጠና ክፍል
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
+6
የሰንበት ት/ቤታችን ሕጻናት ክፍል የጌታችን የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን የልደት በዓል ምክንያት በማድረግ በጎጆ የሕሙማን ማረፊያ በመገኘት የእንኳን አደረሳችሁ መርሐግብር አካሂደዋል።
እንኳን ለብርሃነ ልደቱ በሰላም አደረሳችሁ።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
