የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)
Open in Telegram
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
Show more2 620
Subscribers
+324 hours
+207 days
+3730 days
Posts Archive
"ስለዚህ አንድ ሥጋ ናቸው እንጂ ወደ ፊት ሁለት አይደሉም። እግዚአብሔር ያጣመረውን እንግዲህ ሰው አይለየው።" ማቴ 19 ÷6
ሚያዝያ26 /2017 ዓ.ም ጋብቻችሁን በቅድስት ቤተክርስቲያን ሥርዓት የፈጸማችሁት የሰንበት ትምህርት ቤታችን የፍኖተ ብርሃን አገልጋይ ወንድማችን ያሬድ ጥላሁን እና እህታችን ምሕረት የአብርሃምን እና የሳራን ጋብቻ የባረከ አምላክ ጋብቻችሁን ይባርክላችሁ።
ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል በክንፉ ከልሎ በፍቅርና በጤና ይጠብቃችሁ ዘንድ መልካም ምኞታችን ነው!
እንኳን ደስ አላችሁ ፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን
https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com
''ዕቅበተ እምነት''
ክፍል አንድ
በመ/ር ዲ/ን ዳንኤል ታደለ
የቅዳሜ የትምህርት መርሐግብር
የፊታችን ቅዳሜ ግንቦት 02/2017 ዓ.ም ከምሽቱ 11:45 ሰዓት ላይ ቀጠሮዎትን በጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ ያድርጉ ይምጡ ይማሩ በብዙ ያተርፋሉ እንዳይቀሩ።
የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
ለገዳማዊያን አበምኔቶች እና እመምኔቶች
ሲሰጥ የቆየው የስልጠና ተጠናቀቀ።
በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት በገዳማት አስተዳደር መምሪያ አዘጋጅነት ለሁለት ቀናት ለገዳማዊያን አበምኔቶችና እመምኔቶች ሀገር አቀፍ የገዳማት ወቅታዊ ሁኔታ፣ የገዳማውያን ሕይወት እና አገልግሎትን የሚዳስሰው የሥልጠናና የምክክር መርሐ ግብር ዛሬ ቅዱስ ፓትርያርኩ በተገኙበት ባለ 12 ነጥብ መግለጫ በማውጣት ተጠናቀቀ።
በመርሐ ግብሩ ላይ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የተገኙ ሲሆን ቃለ ምዕዳን ቡራኬና ትምህርተ ወንጌል ሰጥተዋል።
የገዳማት አስተዳደር መምሪያ ለገዳማውያን አበምኔቶች እና እመምኔቶች ሲሰጥ በሰነበተው የስልጠና መርሐ ግብር በበርካታ ሊቃውንት ሰፊ ጥናታዊ እና ትምህርታዊ ጽሑፎችን አቅርበው ውይይቶች ተደርጎባቸዋል። በመጨረሻም የአቋም መግለጫ በማውጣት መርሐ ግብሩ ተጠናቋል።
የአቋም መግለጫው ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ይነበባል።
የአቋም መግለጫ
1. ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በመጀመሪያው የገዳማት ጉባኤ ላይ የሰጡትን አባታዊ መመሪያና በየጊዜው በተለያዩ መድረኮች ገዳማትን በተመለከተ የሰጡትን እና የሚሰጡትን አባታዊ መመሪያ ለመተግበር ቃል እንገባለን፡፡
2. ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፤ የባሕርዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በጉባኤው መክፈቻ ያስተላለፉትን አባታዊ መመሪያ በየመጣንበት ገዳማት ለመተግበር ቃል እንገባለን፡፡
3. በሦስቱም የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት በቀረቡት ጥናታዊ ጽሑፎች በጥናታዊ ጽሑፍ የቀረቡት ገዳውያኑን የሚመለከቱትን መልእክቶች ለመፈጸም ቃል እንገባለን፡፡
4. ገዳማት የትምህርት የሥርዓት ምንጭ በመሆን ቀደምት አባቶቻችን ገዳማቱን በማጠናከር ለሀገር ግንባታና ለቤተ ክርስቲያን አንድነት ያበረከቱት ተጋድሎ ታሪክ የሚዘክረው ነው፡፡ በመሆኑም እኛም ከየገዳማቱ የመጣን መነኮሳትና መነኮሳይያት የአባቶቻችንን ፈለግ በመከተል ገዳማቱ ለሀገርና ለቤተ ክርስቲያን አንድነት መወጣት ያለባቸውን ተግባር በተሰጠን ኃላፊነት በትጋት ለመሥራት ቃል እንገባለን።
5. አዳዲስ ገዳማት ሲገደሙ በሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ጥብቅ ክትትል ተደርጎ በገዳሙ ለሚቀመጡ አበው መተዳደሪያቸው ጭምር ታስቦበት እንዲገደም እንጠይቃለን፤
6. ሁለተኛ መነኮሳትና መነኮሳይያት ለተልእኮ ወደ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ሲመጡ ማረፊያ እንዲዘጋጅላቸው በተደጋጋሚ ተጠይቆ መልስ አልተሰጠውም ትልቁ ቤታችን የመጨረሻ ራስ ቤተ ክርስቲያን የሆነው መንበረ ፓትርያርክ ነው ፡፡ ስለሆነም ለተልዕኮ ገዳም የሚመጡ አባቶችና እናቶች ማረፊያ አጥተው በየከተማው ዘመድና ማረፊያ ፍለጋ መንከራተታቸው ከምናኔ ሕይወታቸው ጋር የማይሄድ መሆኑን ታሳቢ በማድረግ ቅዱስ ሲኖዶስ ማረፊያ እንዲያመቻችልን ዝቅ ብለን እንጠይቃለን፣
7. ምንኩስና የሚሰጥበት ቦታና ሰጪው አካል ተለይቶ ታውቆ የማያዳግም ውሳኔ እንዲሰጥበት በአጽንዎ እንጠይቃለን፣
8.ሁሉም ገዳማት ታይተው ችግራቸው ተለይቶ የጎደላቸው ተሟልቶ እንዲጠናከሩ እንጠይቃለን፡፡
9. የመነኮሳትን ፍልሰት ለማቆም አድራሻ የሌለው መነኩሴ አድራሻ የሌለውን ቄስ አድራሻ የሌለውን ዲያቆን በጥብቅ ቁጥጥር ተለይቶ ለመነኮሳቱም ለቀሳውስቱም ራሱን የቻለ የጠቅላይ ቤተ ክህነት አርማ ያለውና ለቁጥጥር አመቺ የሆነ መለያ ቁጥር ያለው ዲጂታል መታወቂያ ተዘጋጅቶ በሥራ ላይ እንዲውል እንጠይቃለን፡፡
10. በየገዳማቱ አብነት ት/ቤቶች ተከፍተው መነኮሳቱና የአካባቢውን ልጆች በተገባ መንገድ የማብቃት ሥራ እንዲሠራ እንጠይቃለን፡፡
11. በየገዳማቱ ማሠልጠኛ ኑሮ ከማሠልጠኛው በቅተው የሚወጡ መነኮሳት ብቻ የሚማሩበትና የመነኮሳት ኮሌጅ እንዲከፈትልን እንጠይቃለን፡፡
12. ይህ የገዳማውያን አባቶችና እናቶች የውይይትና የምክክር መርሐ ግብር በየዓመቱ ከርክበ ካህናት በፊት እንዲቀጥል ተደርጎ የገዳማቱ አባቶችና እናቶች የየገዳማቸውን ጠንካራና ደካማ ጎን በሪፖርት ለመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የገዳማት መምሪያ ተልኮ መመምሪያው መርምሮ በገዳማቱ የአንድነት ጉባኤ ከታየ በኋላ በቅዱስ ሲኖዶስ የርክበ ካህናት ምልዓተ ጉባኤ ግብአት ስለሚሆን በቅዱስ ሲኖዶስ በየዓመቱ የሚደረገውን የገዳማውያን አንድነት ጉባኤ እንዲያጸድቅልን በታላቅ ትህትና እንጠይቃለን፡፡
በመጨረሻ ቅዱስ ሲኖዶስ የሁሉም አባትና እናት እንደመሆኑ እዚህ ያለነው የኢትዮጵያ ገዳማት አባቶችና እናቶች ስንሰባሰብ የቀሩ የታላላቅ ገዳማት አበምኔቶችና እመምኔቶች አሉ ለዚህም ቅዱስ ሲኖዶስ ለቤተ ክርስቲያን አንድነት ቅደሚያ በመስጠት በመካል ያለውን ችግር ከሚመለከታቸው ሁሉ ጋር ተቀራርቦ በመነጋገር ያለውን ልዩነት ፈትቶ አንድነትን እንዲፈጥርልን እኛ ገዳማውያን በመጣንባቸው ቅዱሳንና ጸድቃን ስም ዝቅ ብለን በአጽኖት እንጠይቃለን፡፡
ብፁዕ ወቅዱስ አባታችን በጉባኤያችን ላይ በመገኘት አባታዊ መመሪያና ቡራኬ ስለሰጡን ከልብ በማመስገን ቡራኬዎ አይለየን እንላለን፡፡ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የባሕርዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ጉባኤው እንዲዘጋጅ በማድረግና በጉባኤው በመገኘት አባታዊ መመሪያና ቡራኬ ስለሰጡን ከልብ እናመሰግናለን፡፡ገዳማውያኑ በዚህ መልክ ተገናኝተን ስለሁለንተናው የቤተ ክርስቲያናችን ሁኔታና ስለገዳማቶቻችን እንድንወያይ መድረኩን የገዳማት መምሪያ ኃላፊዎችንና ሠራተኞችንና በአጠቃላይ ለመርሐግብሩ መሳካት አስተዋጽኦ ያደረጉትን አካላት እናመሰግናለን።
ወስብሐት ለእግዚኣብሔር፤የቅዱስነትዎ ቡራኬ ይድረሰን!!
ሚያዚያ 29 ቀን 2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
©ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
የሰንበት ትምህርት ቤታችን በዘንድሮው የ2017ዓ.ም አዘጋጅ በነበረባቸው በበዓለ ሆሳዕና ዝግጅት እና በገብረ ሰላም ዝግጅት ላይ በተለያዩ ነገሮች ተሣትፎ ያደረጉ አካላትን የምስጋና መርሐግብር በማዘጋጀት በመርሐግብሩ ላይ የደብራችን አስተዳዳሪ መልአከ ብርሃናት አዕምሮ ምስጋናው ፣ የደብራችን ዋና ጸሐፊ ሊቀ ትጉሃን ይሄይስ፣ የማኀበራት ተወካዮችና ተሣታፊዎች በተገኙበት የምስጋና መርሐ ግብሩ ተከናውኗል።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን
https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com
የሰንበት ትምህርት ቤታችን በዘንድሮው የ2017ዓ.ም አዘጋጅ በነበረባቸው በበዓለ ሆሳዕና ዝግጅት እና በገብረ ሰላም ዝግጅት ላይ በተለያዩ ነገሮች ተሣትፎ ያደረጉ አካላትን የምስጋና መርሐግብር በማዘጋጀት በመርሐግብሩ ላይ የደብራችን አስተዳዳሪ መልአከ ብርሃናት አዕምሮ ምስጋናው ፣ የደብራችን ዋና ጸሐፊ ሊቀ ትጉሃን ይሄይስ፣ የማኀበራት ተወካዮችና ተሣታፊዎች በተገኙበት የምስጋና መርሐ ግብሩ ተከናውኗል።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን
https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com
የሐዘን መግለጫ
የሰንበት ት/ቤታችን አባል የሆነው የወንድማችን አቶ መስፍስ ታደሰ የባለቤቱ እናት አርፈው ሥርዓተ ቀብራቸው ተፈጽሟል። ስለዚህ መኖሪያ ቤታቸው ቂርቆስ ቤ/ክ ጀርባ አካባቢ በመገኘት እንድናጽናናቸው ይሁን። የእናታችንን ነፍስ ይማርልን ።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን
https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com
መጽሐፍ ቅዱስን እስከምን ድረስ አንብበዋል?
Available now! Telegram Research 2025 — the year's key insights 
