የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)
Open in Telegram
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
Show more2 639
Subscribers
-224 hours
+87 days
+5630 days
Posts Archive
የተከበራችሁ የፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት አባላት በሙሉ
በሐዋርያት ሥራ 20÷28 ላይ በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ትጠብቋት ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለመንጋው ኹሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ። የሚለውን አምላካዊ ቃል በመተው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በማያውቀውና ሕገ ቤተ ክርስቲያንን ባልጠበቀ መንገድ የተሰጠውን ሕገ ወጥ "ሢመተ ኤጲስ ቆጶሳት" በማስመልከት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በአስተላለፉት ጥሪ ለሚደረገው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ዛሬ ረቡዕ ጥር 17 ቀን 2015 ዓ.ም መንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም የመክፈቻ ጸሎት በማድረግ ተጀምሯል፡፡
የጸሎት መርሐ ግብሩ ላይ ቅዱስ ፓትርያርኩ እንዲሁም ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት በመከናወን ላይ ሲሆን ለሕዝበ ክርስቲያኑ ከቅዱስ ሲኖዶስ በተላለፈው የሶስት ቀን ጸሎት አዋጅ መሰረት ሰንበት ት/ቤታችንም የሲኖዶሱን ጥሪ በመቀበል ከነገ ሐሙስ ጥር18/2015 ጀምሮ እስከ ቅዳሜ ጥር 20/2015 ዓ.ም ምሽት 12:00 እግዚአብሔር መልስ እንዲሰጠን ለቅዱስ ሲኖዶሱም መንፈስ ቅዱስ ይረዳቸው ዘንድ የጸሎት መርሐ ግብሩ የሚከናወን ስለሆነ በጸሎት መርሐ ግብሩ ላይ እንድትገኙ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት
የተከበራችሁ የፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት አባላት በሙሉ
በሐዋርያት ሥራ 20÷28 ላይ በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ትጠብቋት ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለመንጋው ኹሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ። የሚለውን አምላካዊ ቃል በመተው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በማያውቀውና ሕገ ቤተ ክርስቲያንን ባልጠበቀ መንገድ የተሰጠውን ሕገ ወጥ "ሢመተ ኤጲስ ቆጶሳት" በማስመልከት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በአስተላለፉት ጥሪ ለሚደረገው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ዛሬ ረቡዕ ጥር 17 ቀን 2015 ዓ.ም መንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም የመክፈቻ ጸሎት በማድረግ ተጀምሯል፡፡
የጸሎት መርሐ ግብሩ ላይ ቅዱስ ፓትርያርኩ እንዲሁም ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት በመከናወን ላይ ሲሆን ለሕዝበ ክርስቲያኑ ከቅዱስ ሲኖዶስ በተላለፈው የሶስት ቀን ጸሎት አዋጅ መሰረት ሰንበት ት/ቤታችንም የሲኖዶሱን ጥሪ በመቀበል ከነገ ሐሙስ ጥር18/2015 ጀምሮ እስከ ቅዳሜ ጥር 20/2015 ዓ.ም ምሽት 12:00 እግዚአብሔር መልስ እንዲሰጠን ለቅዱስ ሲኖዶሱም መንፈስ ቅዱስ ይረዳቸው ዘንድ የጸሎት መርሐ ግብሩ የሚከናወን ስለሆነ በጸሎት መርሐ ግብሩ ላይ እንድትገኙ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
የ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት
ዓ.ም ነው፡፡
ከዚህም በኋላ ባኮስ እስከ ኑብያ ድረስ ሄዶ ወንጌልን ሰብኮ ብዙዎችን አሳምኖ አጥምቋል፡፡ በዚህም ጊዜ ወንጌላዊው ቅዱስ ማቴዎስ ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ በባኮስ እየተሰጠ የነበረውን የወንጌል ብርሃን የበለጠ እንዲበራ አድርጓል፡፡ ከጃንደረባውም ጋር ሆነው በብዙ ቦታዎች አብረው ወንጌልን ሰብከው አምልኮተ ጣዖትን አጥፍተዋል፡፡
ከዚህም በኋላ ባኮስ ወደ የመን በመሄድ በዚያም ክርስትናን በማስተማር ብዙዎችን አሳምኖ ካጠመቀ በኋላ ወደ ፐርሺያ ከዚያም ወደ ሕንድ፡ በመሄድ ሐዋርያዊ አገልግሎቱን ፈጽሟል፡፡ በመጨረሻም ጥንት ታፕሮባና (taprobana)፡ ዛሬ ሲሎን በምትባለው ደሴት ወንጌልን በማስተማር ላይ እያለ በሰማዕትነት እንዳረፈ መዛግብት ያስረዳሉ፡፡ (lives of the most eminent fathers of the church, page 87) በሌላም በኩል ሐዋርያው ባኮስ (አቤላክ) ከመጠመቁ በፊት 35 ዓመት ከተጠመቀ በኋላ ደግሞ41 ዓመት ኖሮ በኢየሩሳሌምም 3ዓመት ተቀምጦ ወንጌልን ዞሮ ካስተማረ በኋላ በመጨረሻ በ79ዓመቱ ጥር 18 ቀን በሰሜን ተራራዎች ላይ ቅዱስ ያሬድ በተሰወረበት ቦታ እንደተሰወረ ሊቀ ብርሃናት መርቆሬዎስ አረጋ ጽፈዋል፡፡
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ቅዱሳት_ደናግል_ማርያ_ወማርታ (የአልዓዛር እህቶች)
በዚህችም ዕለት ከአራ ቀኖች በኋላ ጌታችን ከመቃብር ያስነሳው የአልዓዛር እህቶች የማርያ እና የማርታ መታቢያቸው ሆነ፡፡ በዘመነ ሐዋርያት በተመሳሳይ 'እንተ ዕፍረት-ባለ ሽቱ' ተብለው የሚጠሩ 2 እናቶች ነበሩ:: 2ቱም ስማቸው ማርያም ስለ ነበር ለመለየት እንዲያመች አንደኛዋን 'ማርያም ኃጥዕት ከኃጢአት የተመለሰች': 2ኛዋን ደግሞ 'ማርያም እኅተ አልዓዛር - በቢታንያ የነበረችው ብለው አበው ይጠሯቸዋል::
በሉቃስ ወንጌል ላይ የምትገኘው ከኃጢአት ሕይወት የተመለሰችው ስትሆን በዮሐንስ ወንጌል 12:1 ላይ ያለችው የአልዓዛር እህት (ድንግሊቱ) ናት:: ዛሬም የምናስባት ይህቺውን እናታችን ነው::
ቅድስት ማርያም መድኃኒታችን ክርስቶስ ወደዚህ ዓለም መጥቶ በሚያስተመርበት ዘመን በቢታንያ አካባቢ ትኖር የነበረች ድንግል ወጣት ናት:: ወላጆች ባልነበረበት ቤት ውስጥ ታላቆቿ አልዓዛርና ማርታ አሳድገዋታል::
በቤተሰብ ደረጃ እንግዳን ይቀበሉ ነበርና ጌታችን ወደዳቸው:: አልዓዛርን ከ72ቱ አርድእት: ማርያምና ማርታን ደግሞ ከ36ቱ ቅዱሳት አንስት ቆጥሯቸዋል:: ወንድማቸው አልዓዛር በታመመ ጊዜ ወደ ጌታ ልከው ነበር::
ያለ ጊዜው የማይሠራ ጌታ ባይመጣ አልዓዛር ሞተ:: በ4ኛው ቀን አምላክ ሲመጣ ቅድስት ማርያም በጌታ ፊት ሰግዳ "እግዚእየ ሶበሰ ኀሎከ ዝየ እምኢሞተ እሑየ-አንተ በዚህ በኖርክስ ወንድሜ ባልሞተ ነበር" ብላ አለቀሰች:: (ዮሐ.11)
ጌታም ስታለቅስ ባያት ጊዜ አምላክነቱ አራርቶት አለቀሰ:: ወዲያውም በስልጣነ ቃሉ አዞ አልዓዛርን አስነሳው:: ከፋሲካ (ጌታ ከመሰቀሉ 6 ቀናት) በፊትም ቅዱሳኑ ለጌታ ግብር አገቡ:: እርሱም ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ታደመላቸው:: (ዮሐ. 12:1)
በዚያም አልዓዛር ከጌታ ጐን ሲቀመጥ: ቅድስት ማርያም ከጌታ ሥር ተንበርክካ: ናርዶስ የሚሉትን የ300 ዲናር ሽቱ በጌታ ላይ አፈሰሰች:: መዓዛ መለኮቱና ሽቱው ሲገናኝ "መልዐ መዓዛሁ" እንዲል ምስጥ የሚያደርግ ሽታ ቤቱን ሞላው::
በወቅቱ ይሁዳ ቢቃወምም ጌታ ምላሹን ሰጥቶታል:: ቅድስት ማርያምንም "ማርያምሰ ኃርየት መክፈልተ ሠናየ ዘኢየኃይድዋ" ብሎ አመስግኗታል:: ያስመሰገናት ቁጭ ብላ በተመስጦ መማሯ ብቻ እንዳልሆነ አባ ሕርያቆስ መስከሯል::
ሲመክረንም "አርምሞንና ትዕግስትን እንደ ማርያም ገንዘብ እናድርግ" ብሎናል:: (ቅዳሴ ማርያም) ቅድስት ማርያም በጌታችን ክርስቶስ በኅማሙ ጊዜ: ሲቀብሩት ነበረች:: ትንሳኤውንም ዐይታለች::
ከጌታ እርገት በኋላም መንፈስ ቅዱስን ተከትላ ለወንጌል አገልግሎት ተግታለች:: ቅድስት እናታችን ማርያም እንተ ዕፍረት ዛሬ በዓሏ ከእህቷ ቅድስት ማርታ ጋር ይከበራል::
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን ።https://t.me/finotebirhan12
🔴#ስንክሳር ጥር_18
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ጥር ዐስራ ስምንት በዚች ቀን የሰማዕታት አለቃ #የቅዱስ_ጊዮርጊስ አፅሙ ተቃጥሎ ተደቁሶ የተበተነበት ነው፣ የሀገረ ንጽቢን ኤጲስቆጶስ #አባ_ያዕቆብ አረፈ፣ #የቅዱስ_አቤላክ (ባኮስ) ኢትዮጵያዊው ጃንደረባ መታሰቢያው ነው፣ የአልዓዛር እህቶች #የማርያ_እና_የማርታ መታቢያቸው ነው፡፡
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ዝርወተ_አፅሙ_ለቅዱስ_ጊዮርጊስ
ጥር ዐስራ ስምንት በዚች ቀን የሰማዕታት አለቃ የቅዱስ ጊዮርጊስ አፅሙ ተቃጥሎ ተደቁሶ የተበተነበት ነው፡፡
ይኸውም ሰባ ነገሥታት ማሰቃየት በሰለቻቸው ጊዜ ቅዱስ ጊዮርጊስ እንደ መጭመቂያ ሆኖ ከተሠራ የስቃይ መሣሪያ ላይ አውጥተው ሰውነቱን እንዲሰነጥቁት ንጉሥ ዱድያኖስ አዘዘ፡፡ አንጀቱ ሁሉ ወጥቶ ከምድር ላይ እስኪዘረግፉት ድረስ እንዲህ አደረጉበት፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከስቃይ ብዛት የተነሳ ነፍሱ ከሥጋው ተለየች ሥጋውንም በሙሉ በእሳት አቃጠሉት አመድም ሆነ፡፡
ከሐዲው ንጉሥ ዱዲያኖስ የተቃጠለውን የሥጋውን አመድ አፍሰው በቀፎ አድርገው ይድራስ ወደሚባል ተራራ ወስደው ምዕመናን ራሩን አመዱን እንኳን እንዳያገኙት በነፋስ እንዲዘሩት አዘዘ፡፡ ደብረ ይድራስ ማለት ምድረ በዳ ማለት ነው፡፡ ወታደሮቹም የሥጋውን አመድ በተራራ ላይ ነስንሰው የተመለሱበት፣ የሥጋው አመድ ያረፈበት ዕፅዋት ሁሉ ጊዮርጊስ ጊዮርጊስ ያሉበት፣ ጌታችን ከመላእክት ጋር ተገልጦ አራቱን የምድር ነፋሳትንም የቅዱስ ጊዮርጊስ የሥጋውን ትቢያ እንዲሰበስብ አዞ። "የኔ ሆይ! የመረጥኩህ ወዳጄ ጊዮርጊስ ከሞት ተነሥ አትፍራ፤ እኔ አዝዤሀለሁና" ሲል ኀያሉን ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ ጠራው። ያን ጊዜ ልዑል ንዑድ ጊዮርጊስም ከጫጉላ ቤት እንደሚወጣ ሙሽራ ምንም ሕማም ሳይኖርበት ተነሣ።
መድኃኒታችንም ባረከው። "አትፍራ፤ ይኸንን ከሀዲ ንጉሥም እስክታሳፍረው ድረስ እኔ አጸናሀለሁ። ከእንዲህስ ወዲህ አምላኩ ከእጃችን ሊያአድነው አይችሉም እንዳይሉ እነዚህን ከሐድያን ነገሥታትና የረከሱ ጣዖታቸውን ታሳፍራቸው ዘንድ ተነሣና ወደ አገር ውጣ፤ ሰላሜ ለዘለዓለም ከአንተ ጋር ይሁን" አለው፤ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይህን ተናግሮ ሳመው። በፍጹም ምስጋናም ወደ ሰማይ ዐረገ። ቅዱስ ጊዮርጊስ ከጌታችን ይህንንም ቃል ኪዳን የተቀበለበት ቀን ነው፡፡
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#አባ_ያዕቆብ_ዘንጽቢን
በዚህችም ዕለት በገድል የተጸመደ የከበረ አባት ለቅዱስ ኤፍሬምም መምህሩ የሆነ የሀገረ ንጽቢን ኤጲስቆጶስ አባ ያዕቆብ አረፈ፡፡ ይህም ቅዱስ ተወልዶ ያደገው በንጽቢን ከተማ ነው እርሱ ግን ሶርያዊ ነው ከታናሽነቱም የምንኵስና ልብስ መልበስን መረጠ ከጠጕር የተሠራ ማቅንም ለበሰ በጾም በጸሎት ተወስኖ በቀን በሌሊት በበጋ በሐሩር በክረምት ቊር የሚጋደል ሆነ ያንንም ማቅ ከቶ ከሥጋው ላይ አያወጣውም ነበር ምግቡም ቅጠላቅጠል ነው የሚጠጣውም የዝናብ ውኃ ብቻ ነው ስለዚህ ሥጋው ብሩህ ሆነ ነፍሱም እጅግ በራች።
እግዚአብሔርም ሀብተ ትንቢት ድንቆች ተአምራቶችንም የመሥራት ጸጋን ሰጠው ለሰዎችም ከመሆኑ በፊት የሚሆነውን ይነግራቸውና እንዲሁም ይሆናል። ተአምራቱም እጅግ ብዙ ነው በአንዲትም ቀን ሴቶች በውኃ ምንጭ ላይ ያለማፈር ሲጫወቱና ሲሣለቁ አያቸው የውኃውንም ምንጭ አደረቀ የራሳቸውንም ጠጒር ነጭ ሽበትን አደረገ በተጸጸቱና የውኃውን ምንጭ እንዲመልስላቸው እየሰገዱ በለመኑት ጊዜ የውኃቸውን ምንጭ መለሰላቸው እንዳይታበዩም ይገሠጹ ዘንድ የራሳቸውን ጠጒር ነጭ እንደሆነ ተወው።
በአንዲት ዕለትም በጐዳና አልፎ ሲሔድ አንዱን ሰው አስተኝተው ሰዎችን አገኛቸው መገነዣ ልብስም ይሰጣቸው ዘንድ ቅዱሱን ለመኑት እርሱ ግን በጸሎቱ ሰውዬውን ምውት አደረገው ሰዎችም ወደርሱ በተሰበሰቡ ጊዜ ሙቶ አገኙት ተጸጽተውም ሁለተኛ ያድንላቸው ዘንድ ለመኑት አዳነላቸውም። ትሩፋቱና ደግነቱም በተሰማ ጊዜ መርጠው በአገረ ንጽቢን ላይ ኤጲስቆጶስነት ሾሙት የክብር ባለቤት የክርስቶስን መንጋዎች ከአርዮሳውያ ተኵላዎች በበጎ አጠባበቅ ጠበቀ።
ንጉሥ ቈስጠንጢኖስም የሦስት መቶ ዐሥራ ስምንቱን የከበሩ አባቶች በኒቅያ ከተማ በሰበሰባቸው ጊዜ ይህ አባት አብሮ አለ ከእርሳቸውም ጋር አርዮስን አውግዞ ከክርስቲያን አንድነት ለየው የቤተ ክርስቲያንንም ሥርዓትና በሁሉ ምእመናን ዘንድ የታወቀች የሃይማኖት ጸሎትን ሠራ። ንጉሥ ቈስጠንጢኖስ በደረሰ ጊዜ የሞተውን ሰው በጉባኤው ውስጥ አስነሥቷል።
የፋርስ ንጉሥም መጥቶ አገረ ንጽቢንን በከበባት ጊዜ ይህ ቅዱስ ያዕቆብ የጭጋግ ደመና በሠራዊቱ ላይ አመጣ ትንኞችም ፈረሶቻቸውንና ጐበዛዝቶችን ነደፏቸው ፈረሶችም ማሠሪያቸውን ቆርጠው ፈረጠጡ የፋርስ ንጉሥም አይቶ ታላቅ ፍርሀትን ፈራ ተነሥቶም ሽሽቶ ወደኋላው ተመለሰ። ነፍሱን የመንጋዎቹንም ነፍስ ጽድልት ብርህት አድርጎ ገድሉንም በፈጸመ ጊዜ ዐረፈ።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ቅዱስ_አቤላክ (#ባኮስ)
የመጀመሪያው የአፍሪካ ሐዋርያ ቅዱስ አቤላክ (ባኮስ)፡- ይኽም ጃንደረባ በመጀመሪያ የኢትዮጵያ ንግሥት የሆነችው የህንደኬ የገንዘቧ ሁሉ ኃላፊና አዛዥ የነበረ ነው፡፡ ከአባቱ እብነ መላክ ከእናቱ ስሂነ ሕይወት ታኅሣሥ29 ቀን ተወለደ፡፡ ኢትዮጵያውያን ከጥንት ጀምሮ ወደ ኢየሩሳሌም በመጓዝ ለበዓለ ፋሲካ በቤተ መቅደስ ይሰግዱ እንደነበረው ሁሉ ይኽም ጃንደረባ ከ4ሺህ ማይልስ በላይ ተጉዞ ኢየሩሳሌምን ተሳልሞ በመለስ ላይ ነበረ፡፡
ከኢየሩሳሌም ወደ ኢትዮጵያ ሲመለስ የነቢዩ ኢሳይያስን መጽሐፍ በተለይም ስለ ጌታችን መከራ መስቀል በዝርዝር የሚናገረውን ክፍል 53ኛውን ምዕራፍ ያነብ ነበር ነገር ግን ጃንደረባው ስለማን እንደሚናገር አልገባውም ነበር፡፡ በዚህም ጊዜ እግዚአብሔር በአካባቢው ወንጌልን ይሰብክ የነበረውን ሐዋርያውን ቅዱስ ፊሊጶስን ላከለት፡፡ እርሱም ጃንደረባው ያነበው የነበረውን መጽሐፍ ተረጎመለት፣ የከበረች ወንጌልን ሰበከለት፣ በመጨረሻም አጠመቀው፡፡ ሐዋርያው ባጠመቀውም ጊዜ መንፈስ ቅዱስ በጃንደረባው ላይ ወረደ፡፡ ሐዋ 8፡26-40፡፡
ይህን ለእኛ ለኢትዮጵያውን እጅግ የሚያኮራን ታሪካችን ነው፡፡ ዛሬ በእጃችን ላይ በመገኘው መጽሐፍ ውስጥ ባይኖርም በቆዩ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥራዞች ላይ ግን ሐዋርያው ቅዱስ ፊሊጶስ ጃንደረባውን ባጠመቀውም ጊዜ መንፈስ ቅዱስ በኢትዮጵያው ጃንደረባ ላይ እንደወረደ ተጽፏል፡፡ (v.39.cord.alexand. in bible reg. angl-alique plures codd.mss)
ሐዋርያው ቅዱስ ፊልጶስ ጃንደረባውን ያጠመቀበት ወንዝ "ቤተ ሳሮን" በተባለችውና እስከዛሬም ድረስ ከኢየሩሳሌም 20 ማይልስ ርቀት በምትገኘው መንደር በኬብሮን መካከል ባለው ኮረብታ ሥር የሚመነጭ ነው፡፡ የቤተ ክርስቲያን የታሪክ ጸሐፊ የሆነው ሊቁ ቅዱስ ጀሮም ጃንደረባውን "የኢትዮጵያውያን ሐዋርያ" በማለት ይጠራዋል፡፡ በሰፊው ለኢትዮጵያውያን ወንጌልን የሰበከ እርሱ ነውና፡፡
ጌታችን የመረጣቸው የከበሩ ሐዋርያት እንኳን ወንጌልን በዓለም ለመስበክ ገና ከኢየሩሳሌም ባልወጡበት ወቅት በ34ዓ.ም ነው። ቅድስት አገራችን ኢትዮጵያ በክርስቶስ አምና ወንጌልን የተቀበለችው፡፡ በምድሪቱም ላይ ወንጌል መነገር የጀመረው ከዚሁ ጊዜ ጀምሮ ነው፡፡ሐዋርያው ባኮስ (አቤላክ) ከኢየሩሳሌም ወንጌልን ተምሮና ተጠምቆ ወደ አክሱም እንደተመለሰ በመጀመሪያ ያጠመቀ ንግሥቲቷ ሕንደኬን ነው፡፡ ከእርሷም በኋላ መኳንንቱና መሳፍንቱ ሁሉ አምነው በባኮ እጅ ተጠመቁ ይኸውም በ34
ሦስት አመት ያህል ወደርሱ ስለአልመጡና ስለአልጎበኙት አባታቸው አባ መቃርስ ከስራቸው የተነሳ አደነቀ ስራቸውንም ይገልጥለት ዘንድ ወደ ጌታችን ለመነና ተነስቶ ወደ ርሳቸው ሄደ እነርሱም በመምጣቱ ደስ ተሰኙበት በዚያች ሌሊትም ከርሳቸው ጋር አደረ። ለፀሎትም በተነሱ ጊዜ የእሳት ሐብል ከአፋቸው ሲወጣና ወደ ሰማይ ሲደርስ ሰይጣናትም እንደ ዝንቦች ሲከቡት የእግዚአብሔርም መልአክ በእሳት ሰይፍ ዝንቦቹን ሲያበርራቸው የከበሩ መክሲሞስንና ዱማቴዎስን አያቸው በነጋም ጊዜ አስኬማን አለብሳቸው ፀልዩልኝ ብሏቸውም ሊሄድ ተነሳ። እንርሱም ሰገዱለትና አባታችን ሆይ አንተ በእኛ ላይ ትፀልይ ዘንድ ትባርከንም ዘንድ የሚገባ ነው አሉት።
ተጋድሎአቸውንም በፈፀሙ ጊዜ እግዚአብሔር ከዚህ አለም ድካም ሊአሳርፋቸው ወደደ መክሲሞስም በፅኑ ህመም ታመመ ስጋውም እንደ እሳት ጋለ ወደርሱም ይመጣ ዘንድ ወደ አባ መቃርስ ላከ። አባ መቃርስም በመጣ ጊዜ በደዌ ሲሰቃይ አገኘው መክሲሞስም ፀልይልኝ ባርከኝም አለው። እርሱም በላዩ አማትቦ ይህ ደዌ ከአንተ ይርቃልና አይዞህ አለው መክሲሞስም አባቴ ሆይ በዚች ደዌ ከዚህ አለም እንደምወጣ እኔ አውቃለሁ ረድኤት አገኝ ዘንድ አንተ ፀልይልኝ አለው።
ይህንንም በተናገረ ጊዜ መሪር ልቅሶን አለቀሰ በዚያችም ጊዜ አባ መቃርስ የቅዱሳንን አንድነት ነቢያትን ሀዋርያትን መጥምቁ ዮሀንስን ንጉስ ቆስጠንጢኖስንም አያቸው። እነርሱም ነፍሱ በክብር እስከወጣች ድረስ በአባ መክሲሞስ ዙሪያ ነበሩ።
አባ መቃርስም አልቅሶ መክሲሞስ ሆይ የተመሰገንክ የከበርክ ነህ አለ። ዱማቴዎስም በውንዱሙ ላይ መራራ ልቅሶ በማልቀስ አባ መቃርስን የሚለምነው ሆነ ነፍሴን ይወስዳትና ወደ ወንድሜም ያደርሳት ዘንድ ስለ እኔ ወደ እግዚአብሔር ፀልይ አለው።
አባ መክሲሞስም ከተቀበረ በኃላ በሶስተኛው ቀን አባ ዱማቴዎስ ታመመ ስለርሱም ለአባ መቃርስ ነገሩት አባ መቃርስም ወደርሱ ሊሄድ ተነሳ በጉዞ ላይም ሳለ አስቀድሞ ወደ አባ መክሲሞስ የመጡትን የቅዱሳን አንድነት አየ የአባ ዱማቴዎስንም ነፍስ ተቀበለው በክብር ወደ ሰማይ አሳረጓት።
አባ መቃርስም ወደ በኣታቸው ሲደርስ ዱማቴዎስን አርፎ አገኘው ወስዶም ከወንድሙ ከመክሲሞስ ጋር በአንድ መቃብር በክብር ቀበረው። የመክሲሞስም እረፍት በዚህ ወር በአስራ አራት ነው ዳግመኛ የዱማቴዎስ እረፍት ጥር አስራ ሰባት በዚች ቀን ነው።
የከበረ አባ መቃርስም ያ ቦታ በስማቸው እንዲጣራ አዘዘ እንዲሁም ደብረ በርሞስ ተብሎ እስከ ዛሬ የሚጠራ ሆነ ለዘላለሙም መታሰቢያቸው ሆነ።
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ መክሲሞስና ዱማቴዎስ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።https://t.me/finotebirhan12
🔴#ስንክሳር ጥር_17
#ቅዱስ_መክሲሞስ እና #ቅዱስ_ዱማቴዎ
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ጥር ዐሥራ ሰባት በዚህች ዕለት ለለውንድዮስ ለሮም ንጉስ ልጆቹ የሆኑ የከበሩና የተመሰገኑ መክሲሞስና ዱማቴዎስ መታሰቢያቸው ሆነ። ይህም ንጉስ ሃይማኖቱ የቀና እግዚአብሔርንም የሚፈራ በእውነትም የቀና ፍርድን የሚፈርድ ነበር ስለዚህም እሊህን ሁለት ቅዱሳን እግዚአብሔር ሰጠው እነርሱም ከታናሽነታቸው ጀምሮ በንጽህና እንደ እግዚአብሔር መላእክት ሆኑ።
ትሕትናን ፈሪሀ እግዚአብሔርን በማስተማር አሳደጋቸው የሚጾሙና የሚፀልዩ በቀንና በሌሊትም የብሉይና የሐዲስ መጻህፍቶችን የሚያነቡ ሆኑ። ከዚህም በኋላ ይህን ዓለም ይተውት ዘንድ የመላእከትንም ልብስ ይለብሱ ዘንድ እርሷም የከበረች የምንኩስና ልብስ ናት ከዚያም ሐሳብ መጣባቸው ሃይማኖታቸው የቀና ሦስት መቶ አስራ ስምንት አባቶች ወደ ተሰበሰቡባት ወደ ኒቅያ ሂደው ይፀልዩ ዘንድ እንዲአስናብታቸው ለአባታቸው ምክንያት አቀረቡ።
ይህንንም ከርሳቸው በሰማ ጊዜ እጅግ ደስ አለው ከብዙ አገልጋዮችና ከብዙ ሰራዊት ጋር አሰናበታቸው ከኒቅያ አገርም በደረሱ ጊዜ ከከበረ ቦታ በረከትን ተቀበሉ ሰራዊቱንም ወደ ንጉስ አባታቸው ጌታችን ንጉሥ ሆይ እኛ ከዚህ ጥቂት ቀን መቆየት እንሻለን ከሚል ጽሑፍ ጋር ጽፈው ላኩ።
ከዚህም በኃላ ለአንድ ፃድቅ መነኮስ ሐሳባቸውን ገለጡ እንዲህም አሉት ከአንተ ዘንድ የምንኩስናን ልብስ እንድንለብስ እንሻለን እርሱም እኔ ከንጉስ አባታችሁ የተነሳ እፈራለሁ ነገር ግን ወደ ሶሪያ ሂዱ ስሙ አጋብዮስ የሚባል ከዚያ ሀይማኖቱ የቀና ካህን ደግ መነኮስ አለ አላቸው። ይህንንም ሲላቸው ምክሩን ተቀብለው ወደ ሶሪያ ተጉዘው ወደ ቅዱስ አባ አጋብዮስ ደርሰው ኀሳባቸውን ገለጡለት እርሱም ተቀብሎ የምንኩስና ልብስን አለበሳቸው እስከሚአርፍበትም ቀን ከእርሱ ዘንድ ኖሩ።
ከዕረፍቱም አስቀድሞ ያየውን ራእይ ነገራቸው ታላቁ አባ መቃርስ ወደርሱ እንደመጣና ልጆችህ መክሲሞስና ዱማቴዎስ ለኔ ልጆቼ ይሆኑኝ ዘንድ ወደ እኔ ወደ አስቄጥስ ገዳም እንዲመጡ ከመሞቴ በፊት እዘዛቸው አለው።
ዳግመኛም እንዲህ አላቸው ልጆቹ እኔ ይህን ሰው አባ መቃርስን በስጋው አየው ዘንድ እመኝ ነበር እነሆ በመንፈስ አየሁት እናንተም ከሞትኩ በኃላ ወደርሱ ሒዱ።
ከአረፈም በኃላ አልሄዱም በዚያ በሶሪያ አገር ኖሩ እንጂ እግዚአብሔርም ሀብተ ፈውስ ሰጥቷቸው በሽተኞችን የሚፈውሱ ሆኑ ወሬያቸውም በሀገሮች ሁሉ ተሰማ በባህርና በየብስ ከሚነግዱ ነጋዴያንም የመርከብ መዛነቢያቸውን መስራት ተምረው ከድካም ዋጋቸው በየጥቂቱ የሚመገቡና የተረፈውን ለድሆችና ለችግረኞች የሚሰጡ ሆኑ።
እግዚአብሔርም በእጆቻቸው ከሚሰራቸው ድንቆች ተአምራቶች የተነሳ የቅዱሳን መክሲሞስንና ዱማቴዎስን ስም መናፍስት ርኩሳን በሚሰሙ ጌዜ ከሰዎች ወጥተው ይሻሻሉ ሰዎቹም ያን ጊዜ በጌታ ኃይል ይድናሉ ጤነኞችም ይሆናሉ።
እጅግ ታላቅ የሆነ በጎዳና አጠገብ የሚኖር ከይሲ ነበር ብዙዎች ሰዎች ሰዎችንም አጥፍቷል የአገር ሰዎችም ወደ ከበሩ መክሶሞስና ዱማቴዎስ መጥተው ከዚያ ከይሲ ያድኗቸው ዘንድ ለመኗቸው አባ መክሲሞስም ክርታስ አንስቶ እንዲህ ብሎ ፃፈ የብፁእ መቃርዮስ አምላክ በሆነ መንፈስ ቅዱስንም በለበሰ በአባታችን በአጋብዮስ አምላክ በህያው እግዚአብሔር አካላዊ ቃል በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ይህ ደብዳቤ ከዋሻህ ደጅ ቢደርስ አንተ ወጥተህ ሙት የሰማይ ወፎችም ይብሉህ።
አንድ ሰውም ያቺን ደብደቤ ተቀበሎ ሄደ በዚያም የዘንዶ ዋሻ ደጃፍ አኖራት በዚያንም ጊዜ ዘንዶዉ ወጥቶ ሞተ የሰማይ ወፎችም በሉት ህዝቦችም ሁሉ እጅግ አደነቁ እግዚአብሄርንም አመሰገኑት የክብር ባለቤት ጌታችንም በእሊህ ቅዱሳን በመክሲሞስና በዱማቴዎስ እጆች ብዙ ድንቆች ተአምራቶችን አደረገ።
በአንዲትም ዕለት ከአባታቸው መኳንንቶች አንዱ ወደ ባህር ዳርቻ ደረሰ ከመርከቦችም በአንዱ መርከብ መዛገቢያ ላይ መክሲሞስና ዱማቴዎስ የሚል ፅሁፍ በአየ ጊዜ የመርከቡን ሹም ጠየቀው እርሱም እንዲህ አለው በፀሎታቸው ከስጥመት እግዚአብሔር ያድነኝ ዘንድ የእሊህን ሁለት ወንድማማቾች የከበሩ መነኮሳት ስማቸውን በመርከቤ ላይ ፃፍኩ መኮንኑም መልካቸው ምን ይመስላል አለው እርሱም የመልካቸውን ምልክት ነገረው የንጉሱ ልጆች እንደሆኑ አውቆ ያን ነጋዴ ወደ ንጉስ አባታቸው አደረሰው።
ንጉሡም ጠየቀው ነጋዴውም የመልካቸውን አምሳል አስረዳው ንጉሡም ልጆቹ እንደሆኑ በተረዳ ጊዜ እናታቸውንና እኅታቸውን ከብዙ ሠራዊት ጋር ወደነርሱ ላከ ደርሰውም በአዩአቸው ጊዜ ጩኸው አለቀሱ እናታቸውም ወደ ንጉስ አባታቸው ከእርሷ ጋር ይመጡ ዘንድ ለመነቻቸው።
እነርሱም ራሳችንን ስእለት አድርገን ለእግዚአብሔር ሰጥተናልና ቃል ኪዳናችንን ማፍረስ አይቻለንም ነገር ግን ሄጄ ለአንቺም ለአባታችንም ከመከራ ሁሉ እግዚአብሔር ያድናችሁ ዘንድ እንፀልይላችኋለን በዚህም አነጋገር አረጋጓት በመለየቷም ፈፅማ እያዘነች ተመለሰች።
ወደ ንጉሱም በደረሰች ጊዜ ከእነርሱ የሆነውን ነገረችው ንጉሱም ለሚስቱና ለባለሟሉቹ እንዲህ አለ በእግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ የሕይወት ድልብ ይሆኑን ዘንድ እንተዋቸው ፀሎታቸውም ይጠቅመናል በዓለም ውስጥ ያለ ክብር ሁሉ እንደ ሕልም ኃላፊ ጠፊ ነውና እነርሱ ግን የማያልፍ መንግስትን አተረፉ።
በዚያም ወራት የሮሜ ሀገር ሊቀ ጳጳሳት አረፈ ስለሚሾሙትም ሊቀ ጳጳሳት ይማከሩ ዘንድ ኤጲስቆጶሳት ጳጳሳትም ተሰበሰቡ የከበረ መክሲሞስንም አሰቡትና ሁሉም ለዚች ሹመት እርሱ በእውነት ይገባል ተባባሉ።በሽተኞችን ይፈውስ ዘንድ ብዙዎች የሆኑ ድንቆች ተአምራቶችንም ያደርግ ዘንድ እግዚአብሔር ታላቅ ፀጋ ሰጥቶታልና በእድሜውም ወጣት ቢሆን ክርስቶስ በውስጡ ወጣት ቢሆን ክርስቶስ በውስጡ ስለአደረ በዕውቀትና በበጎ ስራ በቤተ ክርስቲያንም ህግና ስርአት ሁሉ ፍፁም ነው።
ይህንንም በሰሙ ጊዜ አባቱና እናቱ ደስ አላቸው መኳንንቶችንም ላኩ የከበሩ መክሲሞስንና ዱማቴዎስን ወደ ሮሜ ይሰዳቸው ዘንድ ወደ ሶሪያ አገረ ገዢ ደብዳቤ አብረው ላኩ። እሊህም ቅዱሳን ሰምተው እጅግ አዘኑ አባታቸው አባ አጋብዮስም ያዘዛቸውን አሰቡ በዚያንም ጊዜ ተነሱ ልብሳቸውንም ለውጠው ወደ ኤርትራ ባህር ዳርቻ ተጓዙ ወደየትም እንደሚጓዙ አያውቁም ውኃን በሚጠሙ ጊዜም እግዚአብሔር መራራውን ውኃ ለውጦ ጣፋጭ አድርጎላቸው ይጠጣሉ ከዚህም በኃላ ከእርሱ ዘንድ ረድኤትን ኃይልን ላከላቸውና ከሶሪያ አገርም ተሸክማ ወደ አስቄጥስ ገዳም አደረሰቻቸው ወደ አባ መቃርስም ገብተው በእርሱ ዘንድ መኖርን እንደሚሹ ነረጉት።
እነርሱም በፀጋ የለመለሙ እንደሆኑ በአየ ጊዜ በገዳም መኖርን የማይችሉ መስለው በገዳም ያለውን ችግር ነገራቸውና በዚህ መኖር አትችሉም አላቸው እነርሱም አባታችን ሆይ ተወን ከዚህ መኖር ካልተቻለን እንሄዳለን ብለው መለሱለት።
ከዚህም በኃላ ሰሌን መስራትን አስተማራቸው ሰሌንም የሚቆርጡበትን ወንዝ አሳያቸው ማደሪያቸውንም እስከሚሰሩ ድረስ ረዳቸው የእጅ ስረቸውንም የሚሸጥና ምግባቸውን የሚያመጣላቸውን አንድ ህዝባዊ ሰው አምጥቶ አገናኛቸው። እንዲህም ሆነው ከቶ ከሰው ሳይገናኙ ሶስት አመት ኖሩ ነገር ግን በጭልታና በዝምታ ወደ ቤተ ክርስቲያን የሚገቡና ሥጋውንና ደሙን ተቀብለው ወደ ማደሪያቸው የሚመለሱ ሆኑ።
አገልግሎ በመልካም
ሽምግልና አረፈ።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ቅዱስ_አባ_ዮሐንስ
በዚህችም ዕለት የእስክንድርያ አገር ሊቀ ጳጳሳት የከበረ አባት አባ ዮሐንስ አረፈ እርሱም ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት አርባ ስምንተኛ ነው።
ይህ አባት ከታናሽነቱ በአስቄጥስ ገዳም በአባ መቃርስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ መንኲሶ ፍጹም ተጋድሎን ተጋደለ። በጾም በጸሎት በመትጋት የተጠመደ ሆነ በእግዚአብሔርም ተመርጦ በሰማዕቱ ቅዱስ ሚናስ ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳሳት አባ ሚካኤል ቅስና ሾመው የቤተ ክርስቲያኑንም ገንዘብ ሁሉ ምድሩንም በውስጧ የሚገባውን መባና ስዕላቱንም አስረከቡት መልካም አስተዳደርንም አስተዳደረ በሰላም በፍቅርም አገለገለ።
ከእርሱ አስቀድሞ የነበረ ሊቀ ጳጳሳት አባ ሚናስ በአረፈ ጊዜ የሚሾሙትን ሊቀ ጳጳሳት ይመርጡ ዘንድ ኤጲስቆጶሳቱና መምህራኑ ተሰበሰቡ ብዙዎችንም መርጠው ስማቸውን በክርታስ። ጻፉ አንድ ጻድቅ ሰውም በሰማዕት ቅዱስ ሚናስ ቤተ ክርስቲያን የተሾመውን ቀሲስ ዮሐንስን ለምን ረሳችሁት አላቸው ሁሉም በእውነት እርሱ ለዚች ሹመት የተገባ ነው አሉ።
ከዚህም በኋላ ስሙን በክርታስ ጽፈው ከእነዚያ ጋር ቀላቀሉት በመሠዊያ ላይ አድርገው ሦስት ቀኖች ሲጸልዩና ሲቀድሱ ኖሩ ከዚህም በኋላ ሕፃን አምጥተው አንዷን ክርታስ እንዲአነሣ አዘዙትና በውስጧ የዚህ ቅዱስ ስም ያለባትን አነሣ አይተውም መልሰው ከክርታሶች ጋር ቀላቀሏት።
ሌላ ሕፃንም አመጡና እርሱም ያቺን ክርታስ ደግሞ አነሣት አይተው እንደ ቀድሞው መልሰው ቀላቀሏት። ሦስተኛም ሕፃን አመጡ እርሱም የዚህ አባት ዮሐንስ ስም ያለባትን ያቺን ክርታስ አነሣ እግዚአብሔርም እንደ መረጠው ተረዱ ከዚህም በኋላ ያለ ውዴታው ይዘው በእስክንድርያ አገር ላይ ሊቀ ጵጵስና ሾሙት።
በተሾመም ጊዜ እንደ ሐዋርያት አጠባበቅ መንጋዎቹን ጠበቀ ወደ እግዚአብሔርም የሚያደርሱ መጻሕፍቶችን ያነቡላቸው ነበር በበጎ ሥራና በቀናች ሃይማኖት የሚያጸናቸው ሆነ ችግር ላለበት ሰው ሁሉ አብዝቶ የሚራራና የሚመጸውት ሆነ።
በዘመኑም አንድ መስፈሪያ ሥንዴ ዋጋው ሁለት የወርቅ ዲናር እስኪሆን በግብጽ አገር ታላቅ ረኃብ ሆነ ድኆችና ችግረኞች ከሕዝቡም ውስጥ ብዙዎቹ ወደ ቤቱ ደጃፍ ይሰበሰቡ ነበር። ረዳቱ ማርቆስንም በአብያተ ክርስቲያናት ገንዘብ ላይ ሁሉ ሾመው ጌታችንም ከሰዎች ላይ ቊጣውን እስከ አራቀ ድረስ ለችግረኞች ሁሉ በጥዋትና በማታ የሚሰጣቸው ሆነ ስለዚህም ይህ አባት ዮሐንስ መሐሪ ተብሎ ተጠራ። ከዚህም በኋላ ይህ አባት አብያተ ክርስቲያናትን ሠራ በጌጥ ሁሉ አስጌጣቸው።
ዕረፍቱም በቀረበ ጊዜ ለካህናቱ የሚያርፍባትን ቀን ነገራቸው እንዲህም አላቸው እኔ ጥር ዐሥራ ስድስት ቀን ተወለድኩ በዚችም ቀን ሊቀ ጵጵስና ተሾምኩ ደግሞ በዚች ቀን አርፋለሁ። ይህንንም ሲላቸው ኤጲስቆጶሳቱ አለቀሱና አባታችን ሆይ ከአንተ በኋላ ሊቀ ጵጵስና የሚሾም ማን ነው አሉት። እርሱም ረዳቴ ቀሲስ ማርቆስ ነው የክብር ባለቤት ጌታችን ለዚች ሹመት መርጦታልና አላቸው። በሹመቱ ሃያ ሦስት ዓመት ከኖረ በኋላ ጥር ዐሥራ ስድስት ቀን አረፈ።
በዘመኑም በእስክንድርያ ሊቀ ጵጵስና በግፍ የተሾመው ዳዊት ሞተ ዳግመኛም ከእርሱ አስቀድሞ የነበረ በእሥር ቤት ዐሥር ዓመት ከኖረ በኋላ ሌላ ጊዮርጊስ የተባለ ተሾመ። ይህም አባት አባ ዮሐንስ በተሾመ ጊዜ ስለ ቀናች ሃይማኖት መልእክትን ጻፈ ጊዮርጊስም በአረፈ ጊዜ በእርሱ ፈንታ ስሙ ኪራኮስ የሚባል ጻድቅ ሰው ተሾመ መልእክትንም ጽፎ ወደ አባ ዮሐንስ ላከ እርሱም ደስ ተሰኘበት የመልእክቱንም መልስ ጽፎ ላከለት።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ማር_ዳንኤል_ሶርያዊ
በዚህችም ዕለት ዓምድ ከሚባል አገር የሶሪያ ሰው ሊቅ ዳንኤል አረፈ የዚህም ቅዱስ አባቱ በወርቅና በብር ባለጸጋ የሆነ ነው። አባቱም በሞተ ጊዜ የሀገረ ዓምድ ጳጳስ አባ ዲዮናስዮስ ይህን ቅዱስ አሳደገው የቤተ ክርስቲያንንም ትምርት አስተማረው ከዚህም በኋላ ዲቁና ቅስና ሾመው የምንኲስና ልብስንም አለበሰው ሀብተ ፈውስም እስከተሰጠው ድረስ ከሰንበት እስከ ሰንበት ሳይበላ በጾም በጸሎት ጸንቶ ኖረ።
ከዚህም በኋላ የሴቶችን ፊት እንዳያይ ፈጽሞ ስዕለት አደረገ እናቱም ወሬውን በሰማች ጊዜ ወደርሱ መጣች ታየውም ዘንድ ላከችበት እርሱም የሴቶችን ፊት እንዳላይ ስዕለትን ተስያለሁ አላት። እርሷም እኔ እናትህ አይደለሁምን እንዴት እንደ ሌሎች ሴቶች ታስመስለኛለህ አለችው እምቢ በአላትም ጊዜ ክንብንቧን ገልጣ ሁለት ሴቶች አንድ ልብስ ለብሰው እያዩህ ሲጠቃቀሱብህ እግዚአብሔር ያሳየኝ ብላ ረገመችው።
ከጥቂት ቀንም በኋላ አንድ ምእመን ሰው ለሊቅ ዳንኤል ሦስት መቶ የወርቅ ዲናር ወሰደለት በማታም ጊዜ ከሊቅ ዳንኤል ደጃፍ ሲደርስ ከእርሱ ጋር ያለ ወዳጁ ስለ ገንዘብ ፍቅር በላዩ ተነሥቶ ገደለው። ስለ ሟቹም የዓምድ ንጉሥ በሰማ ጊዜ አባ ዳንኤልን ያቀርቡት ዘንድ አዘዘ በውሽባ ቤት ያሉ ሁለት ሴቶች የአባ ዳንኤልን መምጣት ወሬ በሰሙ ጊዜ ከችኮላቸው ብዛት የተነሣ ያዩት ዘንድ አንድ ልብስ ለብሰው ወጡ አባ ዳንኤልም እናቱ የተናገረችው ስለደረሰበት ፈገግ ብሎ ሣቀ።
ንጉሡም ስለ ሞተው ሰው አባ ዳንኤልን በመረመረው ጊዜ እኔ አልገደልሁትም ነገር ግን የገደለውን ራሱ ይናገር አለ። በዚያንም ጊዜ ሟቹ በአባ ዳንኤል ጸሎት ተነስቶ ገዳዩን ተናገረ ይህንንም ድንቅ ተአምር ንጉሡና ሕዝቡ ሁሉ አይተው በአባ ዳንኤል ፊት ሰገዱ። በቅዱሳኑ ላይ ድንቅ ሥራ የሚሠራ እግዚአብሔርንም አመሰገኑት።
ከዚህም በኋላ ለአባ ዳንኤል እጅ መንሻ ንጉሡ ብዙ ወርቅን አመጣ አባ ዳንኤልም ከርሱ መቀበልን እምቢ ባለ ጊዜ ንጉሥ ገዳምን ሠራለትና ብዙ መነኰሳት ተሰበሰቡ። ወደ መልካም ሽምግልናም በደረሰ ጊዜ ጥቂት ታመመና በሰላም አረፈ፡፡
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።https://t.me/finotebirhan12
🔴#ስንክሳር ጥር_16
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ጥር ዐሥራ ስድስት በዚህች ቀን የከበረ #ቅዱስ_ፊላታዎስ በሰማዕትነት ሞተ፣ የከበረ አባት ተጋዳይ የሆነ #ቅዱስ_ጰላድዮስ አረፈ፣ የከበረ አባት #አባ_ዮሐንስ አረፈ፣ የሶሪያ ሰው ሊቅ #ማር_ዳንኤል አረፈ፡፡
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ቅዱስ_ፊላታዎስ_ሰማዕት
ጥር ዐሥራ ስድስት በዚህች ቀን የስሙ ትርጒም የእግዚአብሔር ወዳጅ የሆነ የከበረ ፊላታዎስ በሰማዕትነት ሞተ። ይህም ቅዱስ ከአንጾኪያ ሀገር ሰዎች ወገን ነው ወላጆቹም መረግድ የሚባል ላም ያመልኩ ነበር የተፈተገና የበሰለ በሰሊጥ ቅባትና በማር የተለወሰ ስንዴ ይመግቡታል ሁል ጊዜ ሦስት ጊዜ የተወደደ የሽቶ ቅባት ይቀቡታል የወይን ጠጅም ያጠጡታል ለክረምትና ለበጋም ማደሪያ አለው በአንገቱም የወርቅ ዛንጅርና ድሪ አለ።
ይህ ቅዱስ ፊላታዎስም መልኩ እጅግ የሚአምር ነበር ዐሥር ዓመትም በሆነው ጊዜ ለዚያ በሬ ይሰግድ ዘንድ ወላጆቹ ተናገሩት ሕፃን ፊላታዎስም ቃላቸውን አልሰማም እነርሱም እርሱን ስለሚወዱት ልቡን ሊያሳዝኑት ስለአልፈለጉ አላስገደዱትም።
የከበረ ፊላታዎስም ያን ጊዜ ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን አያውቀውም ነበር ፀሐይም አምላክ ይመስለው ነበር በፀሐይም ፊት ቁሞ እንዲህ አለ አንተ ፀሐይ አምላክ ከሆንክ ታስረዳኝ ዘንድ እለምንሃለሁ አለው። በዚያንም ጊዜ ከወደላይ እንዲህ የሚል ቃል ወደርሱ መጣ እኔ አንተ ልታወቀውና ስለ ከበረ ስሙ ደምህ ይፈስ ዘንድ ያለህ አምላክ አይደለሁም።
ሕፃን ፊላታዎስም ይህን በሰማ ጊዜ ልቡ ጸና ዳግመኛም በዚያች ሰዓት ወደርሱ መልአክ ተላከ እርሱም የአምላክን ምሥጢር አስረዳው የሚነግረውንም ያስተውል ዘንድ ልቡናውን ከፈተለት ከዓለም ፍጥረት ጀምሮ የክብር ባለቤት መድኃኒታችን ክርስቶስ ሰው እስከሆነበት ድረስ የሆነውን ይነግረው ጀመረ በልቡናውም እጅግ ደስ አለው።
ከዚያችም ዕለት ወዲህ ሁል ጊዜ አብዝቶ የሚጾምና የሚጸልይ ሆነ ከብቻው እንጀራና ጨው በቀር አይበላም ለድኆችና ለምስኪኖችም ምጽዋት ይሰጣል።
ከዓመትም በኋላ ወላጆቹ አሰቡ ለልጃቸው ባልንጀሮች ምሳ አዘጋጁ ሳይበሉና ሳይጠጡ አስቀድሞ ልጃቸው ፊላታዎስ ለዚያ በሬ ዕጣን እንዲአሳርግ ፈለጉ ሕፃኑ ፊላታዎስም በበሬው ፊት ቁሞ ሰዎች የሚያመልኩህ አንተ በእውነት አምላክ ነህን አለው።
ያን ጊዜ ከበሬው እንዲህ የሚል ቃል ወጣ እኔ አምላክ አይደለሁም ሰይጣን በእኔ ላይ አድሮ ሰዎችን እንዳስት አደረገኝ እንጂ ይህንንም ብሎ ያ በሬ ተነሥቶ የቅዱስ ፊላታዎስን ወላጆች በቀንዶቹ ወግቶ ገደላቸው ፊላታዎስም ያንን በሬ ይገድሉት ዘንድ አመድ እስከሚሆንም በእሳት አቃጥለው በነፋስ ይበትኑት ዘንድ አገልጋዮቹን አዘዛቸው እርሳቸውም እንዳዘዛቸው አደረጉ።
የወላጆቹም በድኖቻቸው ወድቀው ነበር እግዚአብሔርም ጸጋውን አሳድሮበታልና ቅዱስ ፊላታዎስ በወላጆቹ በድኖች ላይ ጸለየ ነፍሳቸውም ተመልሳ በዚያን ጊዜ ተነሡ በሲዖልም ከአዩት ሥቃይ ነገሩት። ከዚህም በኋላ ቅዱስ ፊላታዎስና ወላጆቹ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም የክርስትና ጥምቀትን ተጠመቁ ሀብተ ፈውስም ተሰጥቶት በጸሎቱ በሽተኞችን የሚፈውስ ሆነ።
ወሬውም በንጉሡ ዲዮቅልጥያኖስ ዘንድ ተሰማ መልከተኞችንም ልኮ ወደርሱ አስቀረበውና ለአጵሎን ዕጣን ያሳርግ ዘንድ አዘዘው ብዙ ቃል ኪዳንም ገባለት ባልሰማውም ጊዜ በየአይነቱ በሆነ ሥቃይ ያሠቃዩት ዘንድ አዘዘ። በአላንጋዎች ገረፉት በሆዱም ላይ የሚከብዱ ደንጊያዎችን አደረጉ እርሱ ግን በክብር ባለቤት ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ኃይል የጸና ነው።
ከዚህም በኋላ ንጉሡንና የረከሱ አማልክቶችን ሊረግማቸው ጀመረ ንጉሡም አፉን ይመቱት ዘንድ ምላሱንም ይቆርጡ ጥርሶቹንም ይሰብሩ ዘንድ አዘዘ ጌታችንም ያለ ጥፋት ጤነኛ አደረገው።
ከዚህም በኋላ ንጉሡ ይሸነግለው ዘንድ መልካም ቃል ሊናገረው ጀመረ የከበረ ፊላታዎስ ግን ሲዘብትበት ለጣዖቶቹ እንደሚሠዋ ቃል ገባለት ንጉሡም እውነት ስለመሰለው ደስ አለው አጵሎንንና አገልጋዮቹን ለጠዖትም የሚገዙትን ሁሉንም እንዲአመጡአቸው አዘዘ ዳግመኛም በከተማው ውስጥ ዓዋጅ ነጋሪ ይዞር ዘንድ አዘዘ እንዲህ እያለ ሁላችሁ አሕዛብ ኑ ፊላታዎስ ለአማልክት ሲሠዋ ታዩ ዘንድ አሕዛብም ሁሉ ወደ ፍርድ አደባባይ ተሰበሰቡ።
ጣዖታቱንም በጐዳና ውስጥ ሲያመጡአቸው የከበረ ፊላታዎስ የክብር ባለቤት ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን ጣዖታቱንና አገልጋዮቻቸውን ጣዖተ አምላኪዎችንም ሁሉንም ምድር አፍዋን ከፍታ ትውጣቸው ዘንድ ለመነው ዋጠቻቸውም። በአደባባዩም ውስጥ ታላቅ ጩኸትና ሽብር ሆነ። ይህንን ድንቅ ሥራ አይተው ብዙዎች በክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ ንጉሡም ተቆጥቶ ራሳቸውን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ ቆረጡአቸውም የሰማዕትነት አክሊልንም ተቀብለው ወደ ዘላለም ሕይወት ገቡ።
የከበረ ፊላታዎስንም ማሠቃየቱን ንጉሡ በሰለቸ ጊዜ ራሱን በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘና ቆረጡት የሰማዕትነት አክሊልንም በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለ።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ቅዱስ_አባ_ዸላድዮስ_ገዳማዊ
በዚህችም ቀን የከበረ አባት ተጋዳይ የሆነ ጰላድዮስ አረፈ። ይህም ቅዱስ ከዋሻው ሳይወጣ የሴቶችን ፊት ሳያይ ሃምሳ ዓመት ኖረ ድንቆች ተአምራቶችን የማድረግና የትምቢት መናገር ሀብት ተሰጠው ዜናውም በቦታው ሁሉ ተሰማ።
በምስር አገር አንድ ነጋዴ ነበር ይነግድም ዘንድ በመርከብ ተጭኖ ሔደ ማዕበልም ተነሥቶበት ለመሥጠም ደረሰ በአባ ጰላድዮስ ጸሎት ተማጽኛለሁ ከሞት ከዳንኩ መቶ የወርቅ ዲናር ለእርሱ እሰጣለሁ ብሎ ጮኸ በዚያንም ጊዜ በመስቀሉ መርከቡን ሲቀዝፍ አባ ጰላድዮስን አየው ወደ ወደብም አደረሰው።
ከዚህም በኋላ ወደ አገር ውስጥ በደረሰ ጊዜ ያ ነጋዴ ፈረስ ተከራይቶ ያንን መቶ የወርቅ ዲናር ይዞ ወደ አባ ጰላድዮስ ሔደ በመሸም ጊዜ በአንዲት አገር በእንግዳ ማደሪያ ውስጥ አደረ። በዚያም ሞሪት የሚባል ሰው አግኝቶ በልቡ ያለውን ሁሉ ምሥጢሩን ነገረው ሞሪትም እኔ ቦታውን አውቀዋለሁና ወደርሱ አደርስሃለሁ አለው በማግሥቱም ሁለቱም ወደ አባ ጰላድዮስ ሔዱ በደረሱም ጊዜ ሰላምታ ሰጡት ነጋዴውም ያን ያመጣውን ወርቅ ሰጠው። አባ ጰላድዮስም አይቶ ባረከው እንዲህም አለው ወደዚህ ወርቅ ፍላጎት የለኝም ነገር ግን በእግዚአብሔር ፊት ጠቃሚ እንዲሆንህ ሒደህ ለድኆችና ለችግረኞች በትነው አለው ነጋዴው ግን ይቀበለው ዘንድ ከእግሩ ሥር ወድቆ ማለደው ጥቂትም ወሰደለትና እንዲህ አለው ለበረከት ይህን ተቀብየሃለሁ የቀረውን እንዳዘዝኩህ አድርገው አለው።
ነጋዴውም ወርቁን ይዞ ተመለሰ ከተራራውም ወርዶ ከወንዝ ደረሰ በዚያንም ጊዜ ሰይጣን በሞሪት ልብ አደረና ገንዘቡን ሊወስድ ወደደ በአደገኛነትም በላዩ ተወርውሮ ገደለው በሌሊትም በድኑን ተሸክሞ ወስዶ ከአባ ጰላድዮስ ደጅ ጣለው በማግሥቱም ወደ አገረ ገዥ ሒዶ ስለ ሟቹ ነገረው።
መኰንኑም ወደዚያ በደረሰ ጊዜ አባ ጰላድዮስን ይዞ ጽኑ እሥራትን አሠረውና ስለ ሞተው ሰው ሊመረምረው ጀመረ። እርሱም እኔ አልገደልኩም አለው ወደሞተውም ቀርቦ ቃሬዛውን ይዞ ረጅም ጸሎትን ጸለየ በድን ሆይ ማን እንደገደለህ ተነሥተህ ትናገር ዘንድ በእግዚአብሔር ስም አዝዝሃለሁ አለ ወዲያውኑ የሞተው ተነሥቶ ስለ ገንዘቡ ሞሪት እንደ ገደለው ተናገረ መኰንኑም ይህን ድንቅ ተአምር በአየ ጊዜ ደነገጠ ለአባ ጰላድዮስም ሰገደለት በላዩም ክፉ ስላደረገ ተጸጸተ ሞሪትንም ሊገድለው ወደደ አባ ጰላድዮስም አስተወው። ከብዙ ተጋድሎም በኋላ እግዚአብሔርን ደስ አሰኝቶ
ከዚህም በኋላ መኰንኑ እለእስክንድሮስ ቂርቆስንና እናቱን ወደ አደባባይ ያመጡአቸው ዘንድ አዘዘ ያን ጊዜ አንደበቱ ተፈትቶ ነበርና እንዲህም አለ ሕፃኑንና እናቱን ከቆዳቸው ጋር ራሳቸውን ላጩአቸውና በላያቸው የእሳት ፍሞችን ጨምሩ እርር ብለው እንዲቃጠሉ ዳግመኛም አራት ችንካሮችን ከትከሻዎቹ እስከ ተረከዙ ድረስ እንዲተክሉበት አዘዘ የእግዚአብሔርም መልአክ መጥቶ ሥቃዮችን ከርሱ አራቀ።
ዳግመኛም ከጥዋት እስከ ማታ ከሥቃይ መሣሪያዎች ውስጥ ጨምረው አዋሏቸው ግን ማሠቃየት ተሳናቸው። ከዚህም በኋላ ከማምጠቂያው ውስጥ ጨምረው መገዙአቸውና አመድ እስከሆኑ ከቅባትና ከጨው ጋር በብረት ምጣድ ውስጥ ቆሉአቸው ጌታችንም ከሞት አስነሥቶ አዳናቸው።
ወደ መኰንኑም በገቡ ጊዜ እንዲህ አላቸው በእውነት ከሙታን ተለይታችሁ የተነሣችሁ ከሆነ ይህ ጫማዬ ከእግሬ ወጥቶ እንደ ቀድሞው ሕያው እንዲሆን አድርጉ ሕፃን ቂርቆስም በጸለየ ጊዜ ያ ጫማ ታለቅ በሬ ሆነ ከአንገቱም ፍየል ወጣ።
በዚያንም ሰዓት ለዐሥራ አንድ ሽህ አራት ሰዎች በሬውንና ፍየሉን አርደው ምሳ እንዲያደርጉላቸው መኰንኑ አዘዘ እንዲህም አለ ይህ በቅቷቸው ከጠገቡ ከዚህም ሌላ ምግብ ካልፈለጉ የተሠራው ሁሉ ዕውነተኛ ነዋሪ ነው። ከዚህም በኋላ አርደው ምሳ አደረጉላቸውና ከፍየሉ ሥጋ ስድስት እንቅብ ከበሬው ሥጋ አራት እንቅብ አተረፉ መኰንኑም የተረፈውን ሥጋ አይቶ ወደ ባሕር እንዲጥሉት አዘዘ።
መኰንኑም ቢያፍር የሕፃኑን ምላስ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ ጌታችንም ምላሱን መለሰለት ዳግመኛም በታላቅ ጋን ውኃ እፍልተው ሕፃን ቂርቆስንና እናቱን ኢየሉጣን ይጨምሩአቸው ዘንድ አዘዘ እናቱም አይታ ፈረች። ልጅዋም ወደ እግዚአብሔር በጸለየላት ጊዜ አምላካዊ ኃይልን አሳደረባትና ከልጅዋ ጋር ወደ ጋኑ ገባች። እንደ ውርጭም ቀዝቀዛ ሆነ ደግሞም በውስጡ መንኰራኲር ወዳለበት የብረት ምጣድ እንዲጨምሩአቸውና ሥጋቸው እሰከሚቦጫጨቅ እንዲስቡአቸው አዘዘ የእግዚአብሔርም መልአክ በሕይወት አወጣቸው።
መኰንኑም እነርሱን ማሸነፍ በተሳነው ጌዜ ቸብቸቧቸውን በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ በዚያን ጊዜ ለስም አጠራሩ ስግደት የሚገባው የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወረደ ሕፃን ቂርቆስንም የምትሻውን ለምነኝ አለው።
ሕፃኑም ሥጋዬ በምድር አይቀበር ስሜን ለሚጠራ መታሰቢያዬን ለሚያደርግ ቤተ ክርስቲያኔን ለሚሠራ የተጋድሎዬን መጽሐፍ ለሚጽፍና ለሚያጽፍ ወይም ለሚያነበው ለቤተ ክርስቲያኔ መባ ለሚያገባ በውስጧም ለሚጸልይ ለሁሉም ፍላጎታቸውን ስጣቸው ኃጢአታቸውንም ይቅር በል ስሜም በሚጠራበት በዚያች ቦታ የከብት ዕልቂት አይምጣ በሰውም ላይ እባር ቸነፈር በእህልም ላይ ድርቅ የውኃም ማነስ አይሁን።
መድኃኒታችንም የለመንከኝን ሁሉ እሰጥሃለሁ አንተም በቀኜ ትኖራለህ ሥጋህንም ኤልያስ በዐረገበት ሠረገላ ውስጥ አኖራለሁ አለው ሕፃን ቂርቆስም በሰማ ጊዜ እጅግ ደስ ብሎት ጌታችንን አመሰገነው። ከዚህም በኋላ በሌሊቱ እኩሌታም ከእናቱ ጋር አንገቱን ተቆረጠ መድኃኒታችንም በማይጠፋ አክሊል ጋረደው ነፍሶቻቸውንም በታላቅ ክብር ከእርሱ ጋር አሳደገ።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ቅዱስ_አብድዩ_ነቢይ
በዚህች ቀን ዕውነተኛ ነብይ አብድዩ አረፈ። ይህም ነብይ የሐናንያ ልጅ ነው። በንጉሥ ኢዮሳፍጥም ዘመን ትንቢት ተናገረ እግዚአብሔርም ስለ ትንሣኤና ስለ ፍርድ ቀን በቃሉ ነገረው።
ሁለተኛም ከእስራኤል ልጆች የሚሆነውን ከአሕዛብም ለቀሩት አጸናቸው አብዝቶ መከራቸውም ገሠጻቸውም። ይህም ንጉሥ አካዝያስ ይጠሩት ዘንድ ወደ ኤልያስ ከላካቸው ሦስተኛ መስፍን ነው። ከእርሱ አስቀድመው የመጡ እነዚያን ሁለት መስፍኖች በኤልያስ ቃል እሳት ከሰማይ ወርዳ ከእነርሳቸው ጋር ካሉ ወታደሮች ጋር በላቻቸው።
ይህ ግን ወደ ኤልያስ በመጣ ጊዜ በፊቱ ተንበርክኮ ሰግዶ ተገዛለት እንዲህም አለው የእግዚአብሔር ሰው ተገዛሁልህ የእሊህ የባሮችህ ሰውነትና የኔ ሰውነት በፊትህ ትክበር በእግዚአብሔር ነቢይ ላይ ፈጽሞ አልታበየምና ነቢዩ ኤልያስም ራራለት ወርዶም ከርሱ ጋር ወደ ንጉሡ ሔደ።
ይህም አብድዩ ከምድራዊ ንጉሥ አገልግሎት የኤልያስ አገልገሎት እንደምትበልጥ የኤልያስም አገልገሎት ለሰማያዊ ንጉሥ አገልገሎት ታደርሳለችና ይህን በልቡ ዐወቀ ስለዚህ ምድራውያን ነገሥታትን ማገልገል ትቶ ነቢይ ኤልያስን ተከተሎ አገለገለው በላዩም ከእግዚአብሔር ሀብተ ትንቢት አደረበትና ትንቢትን የሚናገር ሆነ የትንቢቱም ወራት ሃያ ዓመት ነው ከጌታችን ሥጋዌ በፊት በዘጠኝ መቶ ዓመት በሰላም በፍቅር አንድነትም አረፈ።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ቅዱስ_ጎርጎርዮስ_ዘኑሲስ
በዚህችም ቀን ዳግመኛ በሶርያ አገር ያሉ የክርስቲያን ወገኖች የቅዱስ ጎርጎርዮስን የዕረፍቱን መታሰቢያ በዓል ያከብራሉ። ይህም አባት በነፍስ በሥጋ በበጎ ሥራ ሁሉ ከወላጆቹ ጋር ፍጹም ነው። እርሱ እግዚአብሔርን መፍራትንና ትምህርቶችን ተምሮ ዐውቋልና የቋንቋም ትምህርት እጅግ የሚያውቅ የዮናናውያንንም ቋንቋ የሚያነብና የሚተረጒም ለቀና ሃይማኖትም የሚቀና ሆነ በውስጡም በጎ ሥራ በጎ ጠባይ ተፈጸመለት ኑሲስ በምትባል አገርም ላይ ሳይወድ በግድ መርጠው ኤጲስቆጶስነት ሾሙት እርሷም ደሴት ናት የእግዚአብሔርንም መንጋዎች ጠበቀ በትምህርቱና በድርሰቶቹም ልቡናቸውን ብሩህ አደረገ የብሉያትንና የሐዲሳትንም መጻሕፍት ተረጐመ።
ጳጳስ ሁኖ ስለነበረው ስለ ከሀዲው መቅዶንዮስ በንጉሥ ቴዎዶስዮስ ዘመን በቊስጥንጥንያ ከተማ የመቶ ሃምሳ ኤጲስቆጶሳት የአንድነት ስብሰባ በሆነ ጊዜ ይህ ጎርጎርዮስ ከአባቶች ኤጲስቆጶሳት ጋር ሁኖ የሰባልዮስን ወገኖች መቅዶንዮስንና አቡሊናርዮስን ተከራከራቸው መልስ አሳጥቶም አሳፈራቸው። ስሕተታቸውንም ገለጠ። ይህም የካቲት አንድ ቀን ተጽፎአል የእነዚህንም ክህደት አስወገደ በቃሉ ሰይፍነትም የንባባቸውን የስሕተት ሐረግ ቆራርጦ አጠፋ ከተሰበሰቡትም ጋር በሰላም ተመለሰ እነርሱ በድል አድራጊነት እነዚያም ከሀ**ድያን በኀፍረት ሆነው ተመለሱ ።
ወደ መልካም እርጅና ደርሶ እግዚአብሔርንም ደስ አሰኝቶ አገልገሎ በሰላም አረፈ እነሆ በዚህ ወር ጥር ሃያ አንድ ቀን ከገድሉ ጥቂት ጽፈናል ይኸውም በግብጻውያን ዕረፍቱ ነው።
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።https://t.me/finotebirhan12
🔴#ስንክሳር ጥር_15
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ጥር ዐሥራ አምስት በዚህች ዕለት የከበረ ሕፃን #ቅዱስ_ቂርቆስና_ቅድስት_ኢየሉጣ በሰማዕትነት አረፉ፣ #ነብዩ_ቅዱስ_አብድዩ አረፈ፣ በሶርያ ክርስቲያን ወገኖች #የቅዱስ_ጎርጎርዮስን የዕረፍቱን መታሰቢያ በዓል ያከብራሉ።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ቅዱስ_ቂርቆስና_እናቱ_ቅድስት_ኢየሉጣ
ጥር ዐሥራ አምስት በዚህች ዕለት የከበረ ሕፃን ቂርቆስ እናቱ ብፅዕት ኢየሉጣ ዳግመኛ ለከበረ ሕፃን ቂርቆስ ማኅበር የሆኑ ዐሥራ አንድ ሺህ አራት ሰዎች በሰማዕትነት ሞቱ።
በዚያንም ወራት የክብር ባለቤት የሆነ ክርስቶስን በሚያምኑ የክርስቲያን ወገኖች ላይ ታላቅ መከራና ስደት ሆነ። ስሟ ኢየሉጣ የሚባል አንዲት ሴት ነበረች እርሷም ከታናሽነቷ ጀምራ ደግ ናት ስደትም እንደሆነ በሰማች ጊዜ መኰንኑን ከመፍራት የተነሣ ሕፃኗን ይዛ ከሮም ከተማ ተሰዳ የኪልቅያ አውራጃ ከሆነ ከጠርሴስ ደርሳ ከዚያም በሀገሮች ውስጥ እየተዘዋወረች ተቀመጠች።
ወደዚያች አገርም ያ ከእርሱ የሸሸችው መኰንን እለእስክንድሮስ መጣ ጭፍሮቹም ክርስቲያኖችን ፈለጓቸው። ይቺንም ቅድስት ኢየሉጣን አግኝተው ያዝዋትና ወደ መኰንኑ አደረሷት የክርስቲያን ወገንም እንደሆነች ነገሩት።
መኰንኑም ሴትዮ ተናገሪ ከወዴት ሕዝብ ወገን ነሽ ነገድሽ ምንድን ነው ሀገርሽስ ወዴት ነው አላት። የከበረች ኢየሉጣም እንዲህ ብላ መለሰችለት የአንጌቤን ሰው ለሆንኩ ለእኔ ወገኖቼ ለኢቆንዮን አገር አለቆች የሆኑ ኤሳውሮሳውያን ናቸው እኔም በአንተ ምክንያት ሸሽቼ ነበር እነሆ ዛሬ ግን በእጅህ ውስጥ ነኝ አለችው።
መኰንኑም በእጄ ውስጥ እንደተገኘሽ ታውቂያለሽን አላት አሁንም የሚሻልሽን ምረጪ ስምሽንም ተናገሪ እኔንም እሺ በይኝና ለአማልክት ሠዊ የከበረች ኢየሉጣም ለረከሱ አማልክት እኔ አልሰዋም አለችው መኰንኑም ስምሽን ስጪ ተናገሪ አላት እርሷም የኔ ስም ክርስቲያን መባል ነው አለችው። መኰንኑም ይህስ ስንፍና ነው የሚጠቅምሽ አይደለም እንዳትሞቺ ስምሽን ስጪ ተናገሪ አላት። የከበረች ኢየሉጣም የኔ ስም ክርስቲያን መባል እንደሆነ ነገርኩህ ሞት የሚሽረው በሰዎች ዘንድ የምጠራበትን ከፈለግህ ስሜ ኢየሉጣ ነው ብላ መለሰችለት።
መኰንኑም ጽኑ የሆኑ ሥቃዮችን በላይሽ ሳይመጣ ተነሥተሽ መሥዋዕትን ለአማልክት አቅርቢ አላት። የከበረች ኢየሉጣም ዕወነት ነገርን ለመሥራት የምትሻ ከሆነ ዕድሜው ሦስት ዓመት የሆነ ሕፃን ልጅ ይፈልጉ ዘንድ ወደ ሀገሩ መንደር ላክ ወዳንተም ያምጡትና የምንገዛለትንና የምናመልከውን እርሱ ይንገረን አለችው።
ያን ጊዜም የሦስት ዓመት ልጅ ይፈልጉ ዘንድ መኰንኑ ወታደሮችን ላከ የሀገር ሰዎችም ልጆቻቸውን ሠውረዋልና አላገኙም ከዚያም ከከተማው ቅጽር ውጭ በፀሐይ መውጫ ወዳለው በረሀ በኩል ወጡ የቅድስት ኢየሉጣንም ልጅ አገኙት ይህ ሕፃን የስንት ዓመት ልጅ ነው ብለው ስለርሱ ጠየቁ ሰዎችም ይህ ሕፃን የሦስት ዓመት ሲሆን የክርስቲያናዊት መበለት ልጅ ነው አሏቸው።
ያንንም ሕፃን ይዘው ወደ መኰንኑ ወሰዱት መኰንኑም መልኩ የሚያምርና ደም ግባት ያለው እንደሆነ በአየው ጊዜ ደስ የምትል ደስተኛ ሕፃን ሰላምታ ይገባሃል አለው። ሕፃኑም እኔን ደስተኛ ማለትህ መልካም ተናገርክ ላንተ ግን ደስታ የለህም እግዚአብሔር ለዝንጉዎች ደስታ የላቸውም ብሏልና ብሎ መለሰለት መኰንኑም ሕፃኑን ሳልጠይቅህ ይህን ያህል ትመልስልኛለህን አለው። ሕፃኑም ገና ከዚህ የሚበዛ ነገርን እመልስልሃለሁ አለው።
መኰንኑም ሕፃኑን ስምህ ማን ነው አለው ከንጹሕ ዐዘቅትና ከማይለወጥ ከማይጠፋ ውኃ የተገኘ ሕፃን ስሜ ክርስቲያን መባል ነው ብሎ መለሰለት። መኰንኑም ዳግመኛ እንዳትሞት ስምህን ንገረኝ አለው የከበረ ሕፃንም ስሜ ክርስቲያን መባል እንደሆነ ነገርኩህ ሞክሼ ስም የምትሻ ከሆነ እናቴ የሰየመችኝ ቂርቆስ ነው።
መኰንኑም ሕፃን ቂርቆስን እሺ በለኝና ለአማልክት ሠዋ በሥጋህም ስታድግ እሾምሃለሁ በብዙ ወርቅና ብርም አከብርሃለሁ አለው። ሕፃኑም የሰይጣን መልእክተኛ ለዕውነትም ጠላቷ የሆንክ ከእኔ ራቅ አለው።
መኰንኑም ሰምቶ ተቆጣ ደሙ እንደ ውኃ እስከሚፈስ ቆዳውን እንዲጨምቁትና እንዲገፉት አዘዘ። የከበረች ኢየሉጣም የልጅዋን ትዕግሥት ባየች ጊዜ እግዚአብሔርን አመሰገነችው።
ከዚህም በኋላ መኰንኑ ጨውና ሰናፍጭ አምጡ አለ የሁለቱንም አፍንጮቻቸውን ከፍተው ያንን ጨውና ሰናፍጭ እንዲጨምሩባቸው አዘዘ ያን ጊዜ ሕፃኑ ትእዛዝህ ለጕረሮዬ ጣፋጭ ሆነ ከማርና ከስኳርም ለአፌ ጣመኝ ብሎ ጮኸ።
ሁለተኛም መኰንኑ እንዲህ ብሎ አዘዘ የረዘሙና የተሳሉ በእሳትም እንደ ፍም የጋሉ ዐሥራ አራት የብረት ችንካሮች አምጡ ሰባቱን በእናቱ አካላት ውስጥ ጨምሩ በሕፃኑም ሁለት በጆሮዎቹ ሁለት በዐይኖቹ ሁለት በአፉና በአፍንጫው አንድ በልቡ ጨምሩ እንዲህ ሲጨመርበት ጆሮዎቹ እንዲአሩ ዐይኖቹም ይጠፉ ዘንድ አንደበቱም ይቃጠል ዘንድ ወደ ልቡም ጽኑ ሕማም ገብቶ እርሱ ከዚህ ዓለም በሞት እንዲለይ ለእናቱም እንዲሁ አድርጉ ችንካሮችም በቅዱሳኑ በሥጋቸው ሁሉ ተጨመሩ።
የክብር ባለቤት በሆነ በጌታችን ትእዛዝ የብረቶቹ ግለት ጠፍቶ እንደ በረዶ ቀዘቀዘ ጤነኞችም ሆኑ መኰንኑም ወደ ወህኒ ወስዳችሁ በዚያ አሥራችሁ ዝጉባቸው አለ።
ከዚህም በኋላ መኰንኑ የሥቃይ መሣሪያ ይሠራ ዘንድ አንዳዝዘው ብረትን የሚያቀልጥ ሰው አምጡልኝ አለ። በአመጡለትም ጊዜ ሰይጣኑ ወደ መኰንኑ ልብ ገብቶ አንደበቱን ዘጋውና መናገር ተሳነው ሕፃኑ ፈጥኖ አክሊልን ለመቀበል እንደሚተጋ ሰይጣን ስለ አወቀ ስለዚህ ዘጋው።
ከዚህም በኋላ ሕፃኑ ሠራተኛውን ጠርቶ እኔንና እናቴን የሚያሠቃዩበትን የሥቃይ መሣሪያ መሥራት ትችላለህን ይህ መኰንን ግን ምንም የሚያውቀው ነገር የለም አለው ሠራተኛውም እንደምትሻው በል ንገረኝ እንደምታዝዘኝ እኔ መሥራት እችላለሁ አለው።
ሕፃን ቂርቆስም ሊአዝዝ ጀመረ እንዲህም አለ ሁለት መላጫዎች ስፋታቸው አራት ክንድ የሆነ ለእኔና ለእናቴ ሥራ። ዳግመኛም የሚያስጨንቅ ራስን የሚመታና የሚሰብር አንገትንም የሚያሥር የሚዝቅም ሹካ ዐይንንም የሚያወልቅ አካልንም የሚበሳሳ አፍንጫንም የሚያጣምምና የሚሰብር ጆሮንም የሚልጥ ሕዋሳትን የሚፈታና የሚለያይ እንደ ልጓም ሁኖ ምላስን የሚቆርጥ በሰውነትም ውስጥ ገብቶ የሚንቀሳቀስ ቆላፋ ጉጠትን ጐኖችንም የሚፍቅና የሚቆለምም አስጨናቂ የሆነ ጉልበቶችንና ጭኖችን የሚሰብር ጅማቶችንም የሚቆራርጥ ሥሮችንም የሚመዝ በዚችም አስጨናቂ መሣሪያ ጅማቶችን የሚታታ አድርግ።
ዳግመኛም በላም አምሳል ሰፊ መቀመጫ ከናስ ሥራ ሦስት ቀዳዳዎችንም በዚያ መቀመጫ ውስጥ ቅደድ። በቁመቴም ልክ ሦስት ችንካሮችን ሥራ የችንካሮቹንም ራስ ከናስ አድርገህ በውስጡ ከሚጠሩት ዘንድ ፈጽሞ የማይለይ ልዩ ሦስት ብለህ ጻፍ።
ዳግመኛም ጠምዝዞ ወደ ላይ የሚያወጣ ሁለት መሣሪያ ሁለት መጋዞችን ሁለት የብረት ምጣዶችን ሥራ አሁንም አንድ ታላቅ ጋን ሠርተህ በውስጡ አንገትን የሚጠመዝዝና የሚሠነጥቅ ተሽከርካሪ መሣሪያ አድርግ።
በውስጥ የተሸሸገ የሆድ ዕቃን የሚመረምር እጅን ከብረት ሥራ እኔ የጻዕር ስቃይን የምሠቃይበት ይህ ነው አለ። ብረት ሠሪውም ሰምቶ እጅግ አደነቀ የሚረዱትንም ከሀገር ውስጥ መቶ ሠራተኞችን ሰብስቦ መሥራት ጀመረ በአርባ ቀንም ጨረሰ።
የተወደዳችሁ የሰንበት ት/ቤታችን የጥምቀት ዘማርያን የነበራችሁ በሙሉ የአገልግሎት ልብስ(ዩኒፎርሙ) ለሌላ አገልግሎት ስለሚፈለግ ከ14/05/2015 እሑድ ጀምሮ ወደ ንብረት ክፍል ተመላሽ እንድታደርጉ እናሳስባለን ሠላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን።
የከበረ አርኬሌድስም ከመምጣቱ በፊት ለአበምኔቱ መንፈስ ቅዱስ አስረድቶት ነበር ወደርሱም በደረሰ ጊዜ አበ መኔቱ ደስ አለው የከበሩ መነኮሳትን ሁሉንም ሰበሰባቸውና በቅዱስ አርከሌድስ ላይ ፀለዩ። አበ ምኔቱም የምንኩስና ልብስን አስኬማንም አለበሰው መነኮሳቱ ሁሉም በእርሱ ደሰወ አላቸው የእግዚአብሄር ፀጋ በላዩ ተገለፃለችና።
ከዚህም በኃላ የከበረ አርከሌድስ በጠባብ መንገድ ተጠመደ ፅኑ ገድልን ተጋድሏልና ሁልጊዜ በየሰባት ቀን የሚፆም ሆነ በቀንና በሌሊትም ይፀልያል እግዚአብሄርም ሀብተ ፈውስን ሰጥቶት በእምነት ወደርሱ የሚመጡትን ብዙዎች በሽተኞችን አዳነቸው።
የሴቶችንም ፊት ከቶ እንዳያይ ከጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ቃል ገባ ከእናቱ ዘንድም አስራ ሁለት አመት ያህል ወሬው መሰማቱ በዘገየ ጊዜ በእርሱም የሆነውን አላወቀችም የሞተ መስሏታልና እጅግ አዘነች።
ከዚህም በኃላ የእንግዶችና የመፃተኞች መቀቢያ የሚሆን ቤትን ሰራች መንገደኞችም እንዲአድሩበት አደረገች በአንዲትም እለት የብፁእ አርከሌድስን ዜና ሲናገሩ መንገደኞችን ሰማቻቸው እንርሱም ቅድስናውን ተጋድሎውን ምልክቶቹንም የመልኩንም ደም ግባት ሰምታ ልጅዋ እንደሆነ አወቀች ደሰግመኛም መንገደኞችን ጠየቀቻቸው ስራውን ሁሉ ነገሩዋት እርሱ ህያው እንደሆነ ተረዳች።
በዚያንም ጊዜ ተነስታ ወደ ከበረ ሮማኖስ ገዳም ሄደች ወደ ልጅዋ ወደ አርከሌድስም እንዲህ ብላ ላከች እነሆ ፊትህን አይ ዘንድ ወድጄ እኔ እናትህ መጥቻለሁ። እርሱም ከቶ የሴቶችን ፊት እንዳለሰይ ከክበር ባለቤት ከጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ቃል ገብቻለሁና ቃል ኪዳኔን ማፍረስ አይቻለኝም ብሎ መልሶ ወደርሷ ላከ ።ዳግመኛም ፊትህን ካላሳየኸኝ እኔ ወደ ዱር እሄዳለሁ አራዊትም ይበሉኛል ብላ ወደርሱ ላከች።
የከበረ አርከሌድስም እርሷ እንደማትተወው እርሱም ለእግዚአብሄር የገባውን ቃል ኪዳን ማፍረስ እንደማይቻለው በአወቀ ጊዜ ነፍሱን እንዲወስዳት ወደ ጌታችን ለመነ ከዚህም በኃላ የበሩን ጠባቂ ወደ እኔ ትገባ ዘንድ እናቴን ተዋት አለው ።በገባችም ጊዜ ሙቶ አገኘችውና በታላቅ ድምፅ በመጮህ አለቀሰች ነፍሷንም ይወስድ ዘንድ ወደ እግዚአብሄር ለመነች ልመናዋንም ተቀብሎ ነፍሷን ወሰደ።
ከዚህም በኃላ ስጋዋን ከልጅዋ ስጋ ለይተው ለብቻዋ ሊቀበሩ ወደዱ ከከበረ አርከሌድስም በድን የእናቴን ስጋ ከስጋዬ አትለዩ በህይወቷ ሳለች ታየኝ ዘንድ ልቧን ደስ አላሰኘሁምና የሚል ቃል ወጣ።ይህንንም ቃል በሰሙ ጊዜ አጅግ አደነቁ እግዚአብሄርንም አመሰገኑት ሁለቱንም በአንድ መቃብር ውስጥ ቀበሩአቸው ጌታችንም ለበሽተኞች ታላቅ ፈውስን ከስጋው ገለጠ።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ቅድስት_እምራይስ
በዚህችም እለት የከበረች እምራይስ በሰማእትነት አረፈች። ይቺም ብፅእት በክርስቶስ ሀይማኖት ለፀኑ ለከበሩ አባቶች ልጅ ናት ፈሪሀ እግዚአብሄርንም እየተማረች አደገች።በአንዲትም እለት ውኃ ልትቀዳ ወደ ወንዝ ስትወርድ ስለ ክርስቶስ የታሰሩ እስረኞችን አየች።
እንርሱም ጳጳሳት ቀሳውስትና ዲያቆናት ናቸው ከእነርሱም ጋር ስሟን ይፅፍ ዘንድ መዘጋቢውን ለመነችው መዘገባትም ወደ ከሀዲውም መኮንን ወደ ቁልቁልያኖስ አቀረባት።እርሱም ለጣኦት ትሰግድ ዘንድ በብዙ ነገር ሸነገላት እምቢ ባለችውም ጊዜ ቸብቸቦዋን ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ ከተባባሪዎቿም ጋር ምስክርነቷን ፈፀመች።
አምላከ ቅዱሳን ለቅዱሳኑ ካደለው ፍቅራቸው ለእኛም አይንሳን:: በረከታቸውንም ያብዛልን።https://t.me/finotebirhan12
🔴#ስንክሳር ጥር_14
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ጥር አሥራ አራት በዚህች ቀን #ጻድቁ_አቡነ_አረጋዊ (ዘሚካኤል) የተወለዱበት እና ወደ ደብረ ዳሞ የወጡበት ነው፣ የከበረችና የተመረጠች #ቅድስት_ምህራኤል በሰማእትነት አረፈች፣ በገድል የተጠመደ የከበረ #ቅዱስ_አባ_አርከሌድስ አረፈ፣ የከበረች #ቅድስት_እምራይስ በሰማእትነት አረፈች።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ጻድቁ_አቡነ_አረጋዊ (ዘሚካኤል)
ጥር አሥራ አራት በዚህች ቀን ታላቁና የከበረው አባታችን አቡነ አረጋዊ (ዘሚካኤል) የተወለዱበት እና ወደ ደብረ ዳሞ የወጡበት ነው።
እኚህ አባት ከ9 ቅዱሳን አባቶች አንዱ ሲሆኑ አባታቸው ይስሐቅ የሮም ንጉስ ነበሩ፡፡ እናታቸው ንግስት እደና ይባሉ ነበር፡፡ የመጀመሪያ ስማቸው ዘሚካኤል ነው፡፡ ጥበብ መንፈሳ ሲማሩ አድገው ወደ እስክንድርያ ገዳም ገቡ፡፡ አበምኔቱ አባ ጳኩሚስ በፈቃደ እግዚአብሔር የመጡ መሆናቸውን አውቀው መዓረገ ምንኩስና ሰጥተዋቸዋል፡፡
የንጉሳዊ የቅንጦት ኑሮ ንቀው ትተው ገዳም ገብተው በምንኩስና ተወስነዋል፡፡ አባታችን በተጋድሏቸውም ከአባ እንጦንስ፣ ከአባ ጳውሊ እና ከአባ መቃርስ ቀጥሎ በአራተኛ ማዕረግ አበ መነኮሳት ሆነው ተመርጠዋል።
በገዳመ ዳውናስ 7 ዓመት ከቆዩ በኋላ ወደ ሮም ተመልሰው ሲያስተምሩ የሀገራችን ኢትዮጵያን ዜና ሰምተው ለመምጣት በ480 ዓ.ም ከአባ ፍሬምናጦስ በኋላ መንገድ ጀመሩ፡፡ ቅዱስ ሚካኤልም በክንፉ ተሸክሞ አክሱም አድርሷቸዋል፡፡
ተመልሰውም ሄደው ስለ ቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ መስክረዋል፡፡ ሐዋርያ ሳይላክላት በሃይማኖት በምግባር ጸንታ ትኖራለች ብለው ለሰባቱ ዘመዶቻቸው አበው መነኮሳት ነገሯቸው፡፡ ስምንቱም ጓዛቸውን ጠቅልለው በሮም ነግሶ የነበሩ ይስሐቅን (አባ ገሪማን) ጨምረው ንጉስ አልአሜዳ በነገሰ በአምስተኛ ዓመት ማለትም በ480 ዓ.ም ወደ ኢትዮጵያ ዘጠኝ ሆነው መጥተዋል፡፡
አባ አረጋዊ እናታቸው ቅድስት እድናን ደቀ መዝሙራቸውን ማትያስን አስከትለው እግረ መንገዳቸውን እያስተማሩና ድውያንን እየፈወሱ ደብረ ዳሞ ደረሰዋል፡፡
ከእግረ ደብር ሆነው አሁን ይህን ተራራ በምን ልወጣው እችላለሁ እያሉ ሲያወጡ ሲያወርዱ በንግግሩ ሐሰት የሌለበት አምላካችን በነቢዩ ዳዊት ላይ አድሮ በመዝሙር 90/91፥11-16 ላይ “በመንገድህ ሁሉ ይጠብቁህ ዘንድ መላእክቱን ስለ አንተ ያዝዛቸዋልና፤ እግርህም በድንጋይ እንዳትሰናከል በእጆቻቸው ያነሡሃል። በተኵላና በእባብ ላይ ትጫማለህ፤ አንበሳውንና ዘንዶውን ትረግጣለህ። እንዳለው የታዘዘ ዘንዶ መጥቶ ስደሳ ክንድ በሚያህል ጅራቱ ጠምጥሞ ቅዱስ ሚካኤል ሰይፈ እሳት ይዞ እየጠበቃቸው ከተራራው አናት አድርሷቸዋል፡፡
ወዲያው ሃሌ ሉያ ለአብ ሃሌ ሉያ ለወልድ ሃሌ ሉያ ለመንፈስ ቅዱስ ብለው አመስግነዋል፡፡ ቦታውም ደብረ ሃሌ ሉያ ተብሏል፡፡ በዚያ ዕለት ግማሽ ህብስት በልተው ጠገቡ፤ ከዚያ በኋላ ግን ምድራዊ ሕብስት አልተመገቡም፡፡ በሰንበተ ክርስታያን ከቅዳሴ በኋላ ሕብስተ ሰማያዊ እያመጡላቸው ይመገቡ ነበር እንጂ፡፡ ኋላም ዜና ጽድቃቸውን ሰምተው ከስድስት ሺህ ያላነሱ ደቀ መዛሙርት ተሰብስበውላቸዋል፡፡
ዘጠና ዘጠኝ አመት ሲሞላቸው ጌታ በመንፈቀ ሌሊት ተገልጾ ምድራዊ መንግስትህን ትተህ ስላገለገልከኝ ህልፈት ሽረት የሌለባት ሰማያዊ መንግስቴን አወርሰሃለሁ ብሎ ቃልኪዳን ሰጣቸው፡፡ በስምህ የተማጸነውን እስከ አስራ አምስት ትውልድ ድረስ እምርልሃለሁ አንተም ከሞት ገጽ ትሰወራለህ ብሎ ተስፋቸውን ነገራቸው፡፡ እሳቸው መነኮሳቱን ሰብስበው ከእንግዲህ በሥጋ አታዩኝም ብለው ነግረዋቸው አበምኔት ሾመውላቸው በደብረ ዳሞ ተራራ በስተምስራቅ አቅጣጫ ተሰውረዋል፡፡
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ቅድስት_ምህራኤል
በዚህች እለት ጠምዋህ ከሚባል ሀገር ሰዎች የከበረችና የተመረጠች ምህራኤል በሰማእትነት አረፈች።
የዚችም ቅድስት ወላጆቿ እግዚአብሔርን የሚያመልኩ ክርስቲያኖች ናቸው አባቷም ስሙ ዮሐንስ የሚባል ቄስ ነው እናቷም ኢላርያ የምትባል ደግ ናት።ነገር ግን ልጅ ስለሌላቸው ስለዚህ እያዘኑ ወደ እግዚአብሔር ይለምኑ ነበር ከብዙ ዘመንም በኃላ ይህቺን የከበረች የተቀደሰች ልጅ ተሰጠቻቸው ስሟንም ምህራ ኤል ብለው ጠርዋት።
ዐስራ ሁለት ዓመትም በሆናት ጊዜ በላይዋ በአደረ በመንፈስ ቅዱስ ስጦታ ድንቆች ተአምራቶችን መስራት ጀመረች።ከዚህም በኃላ ከሀዲ ንጉስ ዲዮቅልጣኖስ በተነሳ ጊዜ ወደ ባህር ዳርቻ ወጣች መርከበም አግኝታ በላዩ ተሳፈረች ለሰማእትነት ከሚሄዱት ጋር በመሄድ ወደ እንፅና ከተማ በደረሰች ጊዜ ስሙ ፍልፍልያኖስ በሚባል መኮንን ፊት ቆመች በአያትም ጊዜ ስለታናሽነቷ ራርቶላት ሊተዋት ወደደ።
ሊተዋትም እንደወደደ አውቃ እርሱንና የረከሱ አማልክቶቹን በድፍረት ረገመች።ስለዚህም መኮንኑ ተቆጥቶ ፅኑእ የሆነ ስቃይን አሰቃያት ከቀናች ሀይማኖቷ ሸንግሎ ይመልሳት ዘንድ በተሳነው ጊዜ ጊንጦችን እፉኝቶችንና እባቦችን ሰብስበው በዳውላ ውስጥ እንዲጨምሩአቸው እርሷንም ከእነርሱ ጋር በዳውላ ውስጥ እንዲጨምሩ አጥማጆችን አዘዛቸው እነርሱም እንዲሁ አደረጉ።
ያን ጊዜ የእግዚአብሄር መልአክ ተገለፀላትና ከጌታችን ዘንድ የተሰጣትን ቃል ኪዳን አስረከባት ከዚህም በኃላ ነፍሷን አሳለፈች የምስክርነት አክሊልንም ተቀበለች ከዳውላውም ውስጥ አውጥተው በዚያች ቦታ ቀበሩዋት።
ከዚህም በኃላ አባቷና እናቷ በሰሙ ጊዜ ስጋዋ ወዳለበት ከብዙ ህዝብ ጋር መጡ ከዚያም ስጋዋን አፈለሱና ወሰዱአት በታላቅ ክብርም ገንዘው በአማረች ሳጥን ውስጥ አኖሩዋት በስውር ቦታም ያማረች ቤተ ክርስቲያን ሰሩላት ከእርሷም ድንቆች ተአምራቶች ተገለጡ።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ቅዱስ_አባ_አርከሌድስ
በዚህችም ቀን በገድል የተጠመደ የከበረ አባት አርከሌድሰ አረፈ። ይህም ቅዱስ ከሮሜ ሀገር ከታላለቆች ወገን ነው የአባቱ ስም ዮሀንስ የእናቱም ስም ሰንደሊቃ ነው ሁለቱም እውነተኞች የሆኑ በእግዚአብሄር ህግ ያለ ነቀፋ የፀኑ ናቸው።
ቅዱስ አርከሌድስም እድሜው አስራ ሁለት አመት በሆነው ጊዜ አባቱ ሞተ እናቱም ሚስት ልታጋባው አሰበች እርሱ ግን ይህን አልወደደም።
ከዚህም በኃላ ወደ ንጉስ ሄዶ የአባቱን ሹመት ይቀበል ዘንድ መከረችው ከእርሱም ጋር ሁለት አገልጋዮችን ላከች ልንጉስም እጅ መንሻ የሚሰጠውን ብዙ ገንዘብ ሰጠችው።በመርከብም ተጭኖ በባህር መካከል ሳለ ጥቅል ነፋስ በላዩ ተነሳ ማእበሉም እጅግ ከፍ ከፍ ብሎ መርከቡ ተሰበረ እርሱም በአንዲት የመርከብ ስባሪ ሰሌዳ ተንጠልጥሎ ወደ የብስ አደረሰችው።
ከባህሩም ሲወጣ ማእበል የተፋው በድን አገኘ ተቀምጦም በላዩ አለቀሰ የአለምን ኃላፊነትም አሰበ ነፍሱንም የሚገስፃትና የዚህ የኃላፊው አለም ገንዘብ ምኔ ነው ላንቺስ ምንሽ ነው ከሞትኩ በኃላ ወደ አፈር እመለሳለሁና የሚላት ሆነ።
በዚያንም ጊዜ የክብር ባለቤት ወደ ሆነ ወደ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለመነ የቀና መንገድን ይመራው ዘንድ ከዚህም በኃላ ተጓዘ በቅዱስ ሮማኖስ ስም በሶርያ አገር ወደ ተሰራ ወደ አንድ ገዳም ደረሰ። ከገንዘብም ከእርሱ ጋር የቀረውን ሁለት መቶ የወርቅ ዲናር ለአበ መኔቱ ሰጠው የምንኩስና ልብስንም እንዲያለብሰው ለመነው ።
Available now! Telegram Research 2025 — the year's key insights 
