en
Feedback
የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

Open in Telegram

ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።

Show more
2 768
Subscribers
+124 hours
+107 days
+5330 days
Posts Archive
የሰንበት ትምህርት ቤታችን ፍኖተ ብርሃን ዓመታዊ ጉዞ -  ወደ የረር በዓታ ጳጉሜ 3 /2016 ዓ.ም የጉዞ ዋጋ ለተማሪዎች 400 ብር                 ለሠራተኞች 450 ብር ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

የሰንበት ትምህርት ቤታችን ፍኖተ ብርሃን ዓመታዊ ጉዞ - ወደ የረር በዓታ ጳጉሜ 3 /2016 ዓ.ም የጉዞ ዋጋ ለተማሪዎች 400 ብር ለሠራተኞች 450 ብር ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/
+1
የሰንበት ትምህርት ቤታችን ፍኖተ ብርሃን ዓመታዊ ጉዞ -  ወደ የረር በዓታ ጳጉሜ 3 /2016 ዓ.ም የጉዞ ዋጋ ለተማሪዎች 400 ብር                 ለሠራተኞች 450 ብር ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

አሐደ ለከ ወአሐደ ለሙሴ ወአሐደ ለኤልያስ ንግበር ማኅደረ ስለዚህም ጴጥሮስም ጌታችንን አቤቱ በዚህ ትኖር ዘንድ ትወዳለህን ሦስት ሰቀላዎችን አንድ ላንተ፣ አንድ ለሙሴ፣ አንድ ለኤልያስ እንስራ። እን
አሐደ ለከ ወአሐደ ለሙሴ ወአሐደ ለኤልያስ ንግበር ማኅደረ ስለዚህም ጴጥሮስም ጌታችንን አቤቱ በዚህ ትኖር ዘንድ ትወዳለህን ሦስት ሰቀላዎችን አንድ ላንተ፣ አንድ ለሙሴ፣ አንድ ለኤልያስ እንስራ። እንኳን ለበዓለ ደብረ ታቦር በሰላም አደረሳችሁ። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

🔴#ስንክሳር ነሐሴ13 አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ነሐሴ ዐሥራ ሦስት #ጌታችን_መድኃኒታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ ብርሃነ መለኮቱን #በደብረ_ታቦር የገለጠበት ዕለት ነው፣ #የቅዱስ_ሙሴ_ሊቀ_ነቢያት ልደቱ ነው፣ ተጋዳይ #አባ_ጋልዩን አረፈ። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ደብረ_ታቦር ነሐሴ ዐሥራ ሦስት በዚች ቀን ክብር ይግባውና የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታላቅና ክቡር በዓል ነው። በዚች ቀን መድኃኒታችን ሦስቱን ደቀ መዛሙርቶቹን ጴጥሮስን፣ ያዕቆብንና ዮሐንስን ይዞ ወደ ታቦር ተራራ ላይ አወጣቸው። መልኩም በፊታቸው ተለወጠ ልብሱም እንደ በረዶ ነጭ ሆነ። ስለ እነርሱም ጌታችን የሰው ልጅ በጌትነቱ ሲመጣ እስከሚያዩት ድረስ በዚህ ከቆሙት መካከል ሞትን የማይቀምሱት አሉ አለ። ሰዎች ሁሉ እርሱ ለሙሴ ጌታውና ከሞት ያስነሣው እንደሆነ ለኤልያስም ፈጣሪው እንደሆነና ካሳረገበትም ያወረደው እርሱ እንደሆነ ያውቁ ዘንድ እነሆ ከጌታ ከኢየሱስ ጋራ እየተነጋገሩ ሙሴና ኤልያስ ወደርሱ መጡ። ስለዚህም ጴጥሮስ ጌታችንን እንዲህ አለው አቤቱ በዚህ ትኖር ዘንድ ትወዳለህን ሦስት ሰቀላዎችንም አንድ ላንተ፣ አንድ ለሙሴ፣ አንድ ለኤልያስ እንሠራ ዘንድ። በዚህም ቃል የደካማነትና የትሕትና ምልክት አለበት። ደካማነት የተባለ ጴጥሮስ ጌታችን ከሰማይ የወረደበትን ሥራ ትቶ በተራራ ላይ ይኖር ዘንድና ራሱን የሚሠውርበትን ቤት ይሠራለት ዘንድ የተናገረው ነው። ትሕትና ያልነውም ጴጥሮስ ለራሱና ለባልንጀሮቹ ሐዋርያት ቤት ይሠራ ዘንድ ስለ አላሰበ ነው። ራሱንና ባልንጀሮቹ ሐዋርያትን እንደ ባሮች ነቢያትን ደግሞ እንደ ጌቶች አድርጎ አስቧልና። ሰለ ሐዋርያትም የእውቀት ማነስ አታድንቅ በዚያን ጊዜ ፍጹማን አልሆኑምና። እንዲህም በሚልበት ጊዜ ጌታችን በሰው እጅ የተሠራ ማደሪያን የማይሻ መሆኑን ለጴጥሮስ ያሳየው ዘንድ እነሆ ደመና ጋረዳቸው። የጌታችንን ጌትነቱን የሚገልጽ በሐዋርያትም ልቡና እምነትን የሚያጸና እንዲህ የሚል ቃል ከደመና ውስጥ መጣ። ይህ የምወደው በእርሱ ደስ የሚለኝ ልጄ ይህ ነው እርሱንም ስሙት። ሙሴና ኤልያስም ከእርሱ ጋራ ሲነጋገሩ ተሰሙ ስለ ርሱ መምጣት የተናገሩትን ትንቢታቸውንም በቸርነቱ አረጋገጠ። ወደ ተራራ ላይ በመውጣቱም ነቢያትና ሐዋርያት ደስ አላቸው። ሁለተኛም የአብን ቃል በሰሙ ጊዜ ከእነርሱ ሥውር የነበረ የወልድ ዋሕድን በእውነት ሰው መሆን በዚያን ጊዜ ተረዱ ያን ጊዜ የጌትነቱ ክብር ተገልጦአልና። ሐዋርያትም ፍጹም አምላክ ፍጹም ሰው የሆነ እርሱ ሙሴን ከመቃብር ያስነሣው ኤልያስንም ያሳረገው አውርዶም ያመጣው እርሱ እንደሆነ አወቁ። ከእርሱ በቀር ማንም ማን የሙሴን መቃብር የሚያውቅ የለምና ከዐሳረገው ከእርሱ በቀር ማንም ማን ኤልያስ ያለበትን የሚያውቅ የለምና። በሰማይና በምድር ሥልጣን ካለው ከሁሉ ጌታ በቀር ሙታንን አድኖ ሊአስነሣቸው ማንም አይችልም። ደብረ ታቦርም የቤተ ክርስቲያን አምሳል ሆነች ከብሉይና ከሐዲስ በውስጧ ሰብስባለችና። የአብንም ቃል በሰሙ ጊዜ በግምባራቸው ፍግም ብለው በምድር ላይ ወደቁ እንደ ሙታንም ሆኑ። ከዓለም አስቀድሞ ከእርሱ ጋራ በህልውና እንዳለ ለልጁ አብ ምስክርን ሆነ ወዲያውኑ ሙሴ ወደ መቃብሩ ኤልያስም ወደ ቦታው ተመለሱ። ሐዋርያትንም በአነቃቸው ጊዜ ከብቻው ጌታችን በቀር ማንንም አላገኙም። ከባሕርያችን የተዋሐደና ሥጋችንን የለበሰ ፍጹም አምላክ እንደሆነ በዚህ ሐዋርያት አስተማሩ። እንግዲህ እናስተውል ሰው ካልሆነ ቅዱስ ገብርኤል እመቤታቸንን ድንግል ማርያምን በአበሠራት ጊዜ እግዚአብሔር ከአንቺ ጋራ ነው እንዴት አላት። አምላክ ካልሆነስ ለመንግሥቱ ፍጻሜ የለውም እንዴት አላት። ሰው ካልሆነ በበረት እንዴት አስተኙት። አምላክስ ካልሆነ መላእክት ከሰማይ ወርደው ለእግዚአብሔር በሰማያት ምስጋና በምድርም ሰላም ለሰውም ግዕዛኑ ሊሰጠው እያሉ እንዴት አመሰገኑ። ሰው ካልሆነ ዮሐንስ በውኃ እንዴት አጠመቀው አምላክስ ካልሆነ አልዓዛርን ከመቃብር እንዴት ሊያስነሣው ቻለ። ይህ ተቀዳሚ ተከታይ የሌለው እንድ ልጅ አካላዊ ቃል እግዚአብሔር እርሱ ያለ መለወጥ ያለ መለየት አንድ አካል አንድ ባሕርይ በመሆን ፍጹም አምላክ ፍጹም ሰው እንደሆነ እናምንበታለን። እርሱም ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋራ ሁል ጊዜ አንድ ህላዌ ነው ዛሬም ዘወትርም ለዘላለሙ አሜን። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc

በዚህ ልዩ ጉባኤ ላይ እንዲገኙ በክብር ተጋብዘዋል። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩ
በዚህ ልዩ ጉባኤ ላይ እንዲገኙ በክብር ተጋብዘዋል። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

ሰላም ለከ መልአከ ኪዳኑ ወምክሩ፣ ለእግዚአብሔር ልዑል ዘግሩም ግብሩ፣ በረድኤትከ ረዋፂ ዘአሠረ ነፋስ አሠሩ፣ ሶበ ላዕሌየ እኩየ መከሩ፣ ጉባኤ ፀርየ ሚካኤል ዝሩ። ሥራህ የሚደንቅ የልዑል እግዚአብሔ
ሰላም ለከ መልአከ ኪዳኑ ወምክሩ፣                ለእግዚአብሔር ልዑል ዘግሩም ግብሩ፣              በረድኤትከ ረዋፂ ዘአሠረ ነፋስ አሠሩ፣ ሶበ ላዕሌየ እኩየ መከሩ፣ ጉባኤ ፀርየ ሚካኤል ዝሩ። ሥራህ የሚደንቅ የልዑል እግዚአብሔር የቃል ኪዳኑ ባለሟል ቅዱስ ሚካኤል ሆይ ሰላም እልሃለሁ።ጠላቶቼ ሤራቸውን በአሤሩ ጊዜ ከነፋስ ፍጥነት ይልቅ እጅግ በፈጠነ ረድኤትህ የጠላቶቻችንን ጉባኤ በትነው። እንኳን ለቅዱስ ሚካኤል ወርሐዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ፓትርያክ ፲፪ኛ ዓመት የዕረፍተ ሥጋ የመታሰቢያ ጸሎተ ፍትሐት በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ፓትርያክ ፲፪ኛ የዕረፍተ ሥጋ የመታ
+2
የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ፓትርያክ ፲፪ኛ ዓመት የዕረፍተ ሥጋ  የመታሰቢያ ጸሎተ ፍትሐት በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል  የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ፓትርያክ ፲፪ኛ የዕረፍተ ሥጋ  የመታሰቢያ ጸሎተ ፍትሐት ብፁዕ አቡነ አብርሐም የባህርዳር ሀገረ  ስብከት ሊቀጳጳስና የጠቅላይ ቤተክህነት ስራ አስኪያጅ ፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ፣ የጠቅላይ ቤተክህነት የስራ ኃላፊዎች፣ በተገኙበት  በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል  ተከናወነ ። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

ጽንሰታ ለእግዝእትነ ማርያም ነሐሴ ሰባት በዚች ቀን እግዚአብሔር የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤልን ወደ ከበረና ከፍ ከፍ ወዳለ ጻድቅ ኢያቄም ላከው አምላክን የወለደች የእመቤታችን የድንግል ማርያምን ፅንስቷንና ልደቷን በእርሷም ለዓለሙ ሁሉ ድኅነትና ተድላ ደስታ እንደሚሆን ነገረው።  ይህ ጻድቅም ሰው ኢያቄምና የከበረች ሚስቱ ሐና ልጅ ሳይወልዱ ሸመገሉ የከበረች ሐና መካን ሁናለችና ስለዚህም እጅግ ያዝኑ ነበር የእስራኤል ልጆች ልጅ ያልወለደውን ከእግዚአብሔር በረከትን ያጣ ነው እያሉ ያቃልሉት ነበርና። እነርሱም ልጅን ይሰጣቸው ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ዘወትር ፈጽሞ ይለምኑ ነበር። ከዚህም በኋላ ወንድ ልጅን ወይም ሴት ልጅን ቢወልዱ ለእግዚአብሔር ቤት አገልጋይ ሊያደርጉ ስለትን ተሳሉ።  የከበረ ኢያቄምም በተራራ ላይ ሳለ ሲጸልይና ሲማልድ እነሆ በላዩ እንቅልፍ እንቅልፍ ብሎት አሸለበ ያን ጊዜ ከእግዚአብሔር የተላከ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል ተገለጸለት እንዲህም አለው ሚስትህ ሐና ትፀንሳለች ዓለሙ ሁሉ ደስ የሚሰኝባትን የብዙዎችም ዐይነ ልቡ ናቸው በእርሷ የሚበራላችውን በእርሷም ድኅነት የሚሆንባትን ሴት ልጅን ትወልድልሃለች።  በነቃ ጊዜም ወደ ቤቱ ሒዶ ለሚስቱ ለቅድስት ሐና ነገራት ራእይዋን እውነት እንደሆነች አመኑዋት ከዚህም በኋላ ነሐሴ ሰባት በዚች ቀን የከበረች ሐና ፀነሰች። ለዓለም ሁሉ መመኪያ የሆነች በሁለት ወገን ድንግል የሆነች የአምላክ እናት እመቤታችን ማርያም በዚህች እለት ተጸነሰች ።    የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም በረከቷ በሁላችንም ላይ ይደር። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

በሰንበት ትምህርት ቤታችን ትምህርታቸውን እየተከታተሉ የሚገኙ የሶስተኛ ዙር የተልዕኮ ት/ት ተማሪዎች የምስጢረ ጥምቀት ትምህርት በመምህር ዳንኤል በቀለ ነሐሴ 05/2016 ተሰጠ ። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ
+8
በሰንበት ትምህርት ቤታችን ትምህርታቸውን እየተከታተሉ የሚገኙ የሶስተኛ ዙር የተልዕኮ ት/ት ተማሪዎች የምስጢረ  ጥምቀት ትምህርት በመምህር ዳንኤል በቀለ  ነሐሴ 05/2016 ተሰጠ ።    ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

‛‛ከሚቀበል ይልቅ የሚሰጥ ብፁዕ ነው’’ የሰንበት ትምህርት ቤታችን በጎ አድራጎት ክፍል በየዓመቱ በምዕመናን እገዛ ለተቸገሩ ሕጻናት የትምህርት መሣሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ እንደሚያደርግ ይታወቃል። እንደ
‛‛ከሚቀበል ይልቅ የሚሰጥ ብፁዕ ነው’’ የሰንበት ትምህርት ቤታችን በጎ አድራጎት ክፍል በየዓመቱ በምዕመናን እገዛ ለተቸገሩ ሕጻናት የትምህርት መሣሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ እንደሚያደርግ ይታወቃል።  እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ በዚህ ዓመትም ይህን በጎ ስራ ለማስቀጠል ለመጪው 2017 የትምህርት ዘመን ለተማሪዎች የሚያስፈልጋቸውን የመማሪያ ቁሳቁስ በፓኬጅ አዘጋጅተን ለመስጠት አስበናል እና እርስዎም ለዚህ አገልግሎት የአቅሞትን ድጋፍ በማድረግ የበረከቱ ተካፋይ እንዲሆኑ በአምላከ ቅዱስ ሚካኤል ስም እንጠይቃለን።             የፓኬጁ ዝርዝር (1ጥቅል ፓኬጅ) 1 ደርዘን ደብተር---------600 ብር 1 ደርዘን እስክርቢቶ ------240 ብር 1 ደርዘን እርሳስ ----------120 ብር 1 ቦርሳ --------------------600ብር 1 ኮምፓስ -----------------90 ብር       በአጠቃላይ 1 ፓኬጅ--1650 ብር ለመለገስ የምትፈልጉ ለሌሎች መረጃዎችም    0912 41 97 72    09 66 25 87 38    09 31 14 44 44  በመደወል ማነጋገር ይቻላል።    የፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት በጎ አድራጎት ክፍል የቴሌግራም ቻናላችን https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

‛‛ከሚቀበል ይልቅ የሚሰጥ ብፁዕ ነው’’ የሰንበት ትምህርት ቤታችን በጎ አድራጎት ክፍል በየዓመቱ በምዕመናን እገዛ ለተቸገሩ ሕጻናት የትምህርት መሣሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ እንደሚያደርግ ይታወቃል። እንደ
‛‛ከሚቀበል ይልቅ የሚሰጥ ብፁዕ ነው’’ የሰንበት ትምህርት ቤታችን በጎ አድራጎት ክፍል በየዓመቱ በምዕመናን እገዛ ለተቸገሩ ሕጻናት የትምህርት መሣሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ እንደሚያደርግ ይታወቃል።  እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ በዚህ ዓመትም ይህን በጎ ስራ ለማስቀጠል ለመጪው 2017 የትምህርት ዘመን ለተማሪዎች የሚያስፈልጋቸውን የመማሪያ ቁሳቁስ በፓኬጅ አዘጋጅተን ለመስጠት አስበናል እና እርስዎም ለዚህ አገልግሎት የአቅሞትን ድጋፍ በማድረግ የበረከቱ ተካፋይ እንዲሆኑ በአምላከ ቅዱስ ሚካኤል ስም እንጠይቃለን።             የፓኬጁ ዝርዝር (1ጥቅል ፓኬጅ) 1 ደርዘን ደብተር---------600 ብር 1 ደርዘን እስክርቢቶ ------240 ብር 1 ደርዘን እርሳስ ----------120 ብር 1 ቦርሳ --------------------600ብር 1 ኮምፓስ -----------------90 ብር       በአጠቃላይ 1 ፓኬጅ--1650 ብር ለመለገስ የምትፈልጉ ለሌሎች መረጃዎችም    0912 41 97 72    09 66 25 87 38    09 31 14 44 44  በመደወል ማነጋገር ይቻላል።    የፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት በጎ አድራጎት ክፍል የቴሌግራም ቻናላችን https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

እንኳን ለጾመ ማርያም (ጾመ ፍልሰታ በዓል አደረሰን አደረሳችሁ መደበኛ የቅዳሜ ትምህርት (ክርስቲያናዊ ሕይወት)በሚል ርዕስ በመ/ር ያሬድ ጥላሁን ነሐሴ 4/2016 ይሰጣል አባላት ትምህርት መማሯን ማ
እንኳን ለጾመ ማርያም (ጾመ ፍልሰታ በዓል አደረሰን አደረሳችሁ መደበኛ የቅዳሜ ትምህርት (ክርስቲያናዊ ሕይወት)በሚል ርዕስ በመ/ር ያሬድ ጥላሁን ነሐሴ 4/2016 ይሰጣል አባላት ትምህርት መማሯን ማረጋገጫ ከሰ/ት/ቤቱ የሚፈልጉ ከሆነ ተከታታይ የሚሰጠውን ትምህርት ይማሩ  በጊዜ በመገኘት የድርሻችንን እንወጣ። ቦታ በጸበል ቤት አዳራሽ ሰዓት 11:30 ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc

ውድ የሰ/ት/ቤታችን አባላት በሙሉ ለ/ሰ/ት/ቤታችን አገልግሎት መስፋፋት ጉልህ አስተዋጽኦ የሚያደርጉበት ቀን ደረሰ!! ወርኃዊ መዋጮ ከነሐሴ 01 እስከ ነሐሴ10 ድረስ ይክፈሉ። አገልግሎታችንን እናሳ
ውድ የሰ/ት/ቤታችን አባላት በሙሉ   ለ/ሰ/ት/ቤታችን አገልግሎት መስፋፋት ጉልህ አስተዋጽኦ የሚያደርጉበት ቀን ደረሰ!!      ወርኃዊ መዋጮ ከነሐሴ 01 እስከ ነሐሴ10  ድረስ ይክፈሉ። አገልግሎታችንን እናሳድግ  መንፈሳዊ የአባልነት ግዴታችንን እንወጣ።  1000555650594 በአካውንታችን ሲያስገቡ (ወርሐዊ አስተዋጽኦ ) ብለው ይጻፉበት። የፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት ልማት ክፍል ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

ውድ የሰ/ት/ቤታችን አባላት በሙሉ ለ/ሰ/ት/ቤታችን አገልግሎት መስፋፋት ጉልህ አስተዋጽኦ የሚያደርጉበት ቀን ደረሰ!! ወርኃዊ መዋጮ ከነሐሴ 01 እስከ ነሐሴ10 ድረስ ይክፈሉ። አገልግሎታችንን እናሳ
ውድ የሰ/ት/ቤታችን አባላት በሙሉ   ለ/ሰ/ት/ቤታችን አገልግሎት መስፋፋት ጉልህ አስተዋጽኦ የሚያደርጉበት ቀን ደረሰ!!      ወርኃዊ መዋጮ ከነሐሴ 01 እስከ ነሐሴ10  ድረስ ይክፈሉ። አገልግሎታችንን እናሳድግ  መንፈሳዊ የአባልነት ግዴታችንን እንወጣ።  1000555650594 በአካውንታችን ሲያስገቡ (ወርሐዊ አስተዋጽኦ ) ብለው ይጻፉበት። የፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት ልማት ክፍል ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc

ጾመ ፍልሰታ አምላክን የወለደች እመቤታችን ድንግል ማርያም ከዕረፍቷ በኋላ ከእነርሱ ስለመለየቷ ሐዋርያት ፈጽሞ እያዘኑ ነበር፡፡ ከዚህም በኋላ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ተገለጠላቸው፤ እርሷን በሥጋ ያዩ ዘንድ እንዳላቸውም ተስፋ ሰጣቸው፡፡ ወንጌላዊ ዮሐንስም እስያ በሚባል አገር እያስተማረ ሳለ በነሐሴ ወር ዐሥራ ስድተኛ ቀን ተድላ ደስታ ወደአለባት ገነት በመንፈስ ቅዱስ ተነጠቀ፡፡ የክብር ባለቤት ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን የእመቤታችን ማርያም ሥጋዋ ካለበት ከዕፀ ሕይወት ዘንድ ተቀምጦ አየው፡፡ የንጽሕት እናቱንም ሥጋ ታወጣ ዘንድ ምድርን እንዲጠሩዋት ሰባቱን የመላእክት አለቆች አዘዛቸው፤ እነርሱም ”የንጽሕት እናቱን ሥጋ ታወጪ ዘንድ እግዚአብሔር አዞሻል‘ አሏት፡፡ያን ጊዜም ከዕፀ ሕይወት በታች ካለ መቃብር የእመቤታችን ማርያም ሥጋዋ ወጣ፡፡ የክብር ባለቤት ጌታችንም እንዲህ እያለ አረጋጋት፤ ”የተወደድሽ የወለድሽኝ እናቴ ሆይ ዘላለማዊ ወደ ሆነ መንግሥተ ሰማያት አሳርግሽ ዘንድ ነዪ፡፡ ያን ጊዜም በገነት ያሉ ዕፅዋት ሁሉም አዘነበሉ፤ መላእክት፤ የመላእክት አለቆች ጻድቃን ሰማዕታትም እየሰገዱላትና ፈጽሞ እያመሰገኗት አሳረጓት፡፡ አባቷ ዳዊትም ንግሥት እመቤታችን ወረቀ ዘቦ ለብሳ ደርባ ደራርባ በቀኝህ ትቀመጣለች እያለ በበገና አመሰገናት፡፡ በኪሩቤል ሠረገላ ተቀምጣ ከዐረገች በኃላ በልጆችዋና በፈጣሪዋ ቀኝ በታላቅ ክብር ተቀመጠች፡፡ ወንጌላዊ ዮሐንስም ከእርሷ በረከትን ተቀብሎ ሰግዶላት ተመልሶ ከሰማይ ወረደ፤ ሐዋርያትን ተሰብስበው ስለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሥጋ ፈጽሞ ሲያዝኑና ሲተክዙ አገኛቸው፡፡ እርሱም እንዳየ እንደሰማ ሥጋዋንም በታላቅ ክብር በምስጋና እንዳሳረጓት ነገራቸው፡፡ ሐዋርያትም በሰሙ ጊዜ ዮሐንስ እንዳየና እንደሰማ ባለማየታቸውና ባለመስማታቸው እጅግ አዘኑ፡፡ ከዚህም በኋላ እያዘኑ ሳሉ እነሆ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገለጠላቸውና ”የፍቅር የአንድነት ልጆች ሰላም ይሁንላችሁ፤ ስለ እናቴ ማርያም ሥጋ ለምን ታዝናላችሁ፡፡ እነሆ እኔ እርስዋን በሥጋ ላሳያችሁ ልባችሁም ደስ ሊለው ይገባዋል‘ አላቸው፡፡ ይህንንም ብሎ ከእርሳቸው ዘንድ ወደ ሰማይ ዐረገ፡፡ ሐዋርያትም ዓመት ሙሉ ቆዩ፤ የነሐሴም ወር በባተ ቀን ለሐዋርያት ዮሐንስ እንዲህ አላቸው፡፡ ”አምላክን የወለደች የእመቤታችንን ሥጋዋን ለማየት የተዘጋጀን አድርጎ ያሳየን ዘንድ ኑ ይህን ሁለት ሱባዔ በጾም የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን እንለምነው” በልጅዋ በወዳጅዋ ቀኝ ተቀምጣ አይተን በእርሷ ደስ እንዲለን፡፡‘ በዚያን ጊዜም ዮሐንስ እንዳላቸው በጾም በጸሎት ሱባዔ ያዙ፤ የነሐሴ ወር እንደዛሬ ዐሥራ ስድስተኛ ቀን በሆነ ጊዜ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሁሉንም ሐዋርያት ወደ ሰማይ አወጣቸው፡፡ በታላቅ ክብር በተወደደ ልጅዋ ቀኝ ተቀምጣ ከሥጋዋ ተዋሕዳ ተነሥታ እመቤታችን ማርያምን አዩዋት፡፡ እጆቿንም ዘርግታ የከበሩ ሐዋርያትን እያንዳንዳቸውን ባረከቻቸው፤ በልባቸውም እጅግ ደስ አላቸው፡፡ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም በከበረ ሥጋውና ደሙ ላይ ሠራዔ ካህን ሆነ፡፡ እስጢፋኖስም አዘጋጀ፤ ዮሐንስም ”በመፍራት ቁሙ‘ አለ፡፡ ሁሉም ሐዋርያት በመሰዊያው ዙሪያ ቆሙ፤ በዚያን ጊዜ ከቶ እንደርሱ ሆኖ የማያውቅ ታላቅ ደስታ ሆነ፡፡ ጌታችንም የቅዳሴውን ሥርዓት በፈጸመ ጊዜ ሥጋውንና ደሙን አቀበላቸው፡፡ ከዚያም በኪሩቤልና በሱራፌል ሠረገላ ተቀምጣ በምታርግ ጊዜ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እናቱን እመቤታችን ማርያምን እንዲህ ብሎ ተናገራት፡፡ ”በዚች ቀን የሆነ የዕርገትሽን መታሰቢያ በዓለም ውስጥ እንዲሰበኩ ልጆችሽ ሐዋርያትን እዘዣቸው፡፡ መታሰቢያሽን የሚያደርገውን ሁሉ ተጠብቆም በዚች ቀን ቅዱስ ቁርባን የሚቀበለውን ኃጢአቱን እደመስስለታለሁ፡፡ የእሳትን ሥቃይ ከቶ አያያትም፤ መታሰቢያሽን ለሚያደርግ ሁሉ በዚች ቀን ለድኆች በስምሽ ለሚመጸውት ቸርነቴ ትገናኘዋለች፤ ይህም ሥጋሽ ወደ ሰማይ ያረገበት ነው፡፡‘ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም ክብር ይግባውና ጌታችንን እንዲህ አለቸው፤ ”ልጄ ሆይ እነሆ በዓይኖቻቸውም አዩ፤ በጆሮዎቻቸውም ሰሙ፤ በእጆቻቸው ያዙ ሌሎችም ታላላቅ ድንቆች ሥራዎችን አዩ፡፡‘ እመቤታችንም ይህን ስትናገር ጌታችን ሰላምታ ሰጥቷቸው በታላቅ ደስታ ወደ ደብረ ዘይት ተመለሱ፡፡ የተወደዳችሁ ወንድሞች ሆይ! ይህን ጾም ልንጾምና በፍጹም ደስታ የእመቤታችንን መታሰቢያዋን እናደርግ ዘንድ ይገባናል፡፡ እርሷ ስለ እኛ ወደተወደደ ልጅዋ ሁልጊዜ ትማልዳለች፡፡ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፤ እኛንም በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት ይማረን፡፡ በረከቷም ሐዋርያት በሰበሰበዋት ከቅድስት ቤተ ክርስቲያን ልጆች ከሁላችን ጋር ይሁን፤ ለዘላለሙ አሜን፡፡   ©ማኀበረ ቅዱሳን የቴሌግራም ቻናላችን https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com