የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)
Open in Telegram
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
Show more2 635
Subscribers
No data24 hours
+157 days
+5530 days
Posts Archive
ብፁዕ አቡነ ሰላማ የታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያምና የመንበረ መንግሥት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን የበላይ ጠባቂ ሊቀ ጳጳስ ሥርዓተ ቀብርን አስመልክቶ የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት መግለጫ ሰጠ።
+++++++++++++++++++++++++++++++++++++++!
ብፁዕ አቡነ ሰላማ የታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያምና የመንበረ መንግሥት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን የበላይ ጠባቂ ሊቀ ጳጳስ ሥርዓተ ቀብር እሑድ መስከረም 20 ቀን 2016 ዓ.ም በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ከቀኑ 6 ሰዓት ይፈጸማል ሲሉ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ለለኢኦተቤ ቴቪ (EOTC TV) ገለጹ።
የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እና የኒውዮርክ እና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) እንደገለጹት የብፁዕ አቡነ ሰላማ የታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያምና የመንበረ መንግሥት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን የበላይ ጠባቂ ሊቀ ጳጳስ ክቡር አስክሬን ነገ ቅዳሜ መስከረም 19 ቀን 2016 ዓ.ም ከቀኑ በ 9 ሰዓት ከሀሌሉያ ሆስፒታል ወደ መንበረ ፓትርያርክ ቅድስት ማርያም ገዳም የሚመጣ ሲሆን ለሊቀ ጳጳስ በሚመጥን ሥርዓተ ጸሎተ ፍትሐት ሲፈታ አድሮ በማኅሌትና በቅዳሴ ሥርዓተ ጸሎቱ የሚከናወን ይሆናል።
እሑድ መስከረም 20 ቀን 2016 ዓ.ም ከቅዳሴ በኃላ የብፁዕነታቸው ክቡር አስክሬን ወደ በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የሚሄድ ሲሆን በዚያ አስፈላጊው መንፈሳዊ ሥርዓት ተከናውኖ ግብአተ መሬት እንደሚፈጸም የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ለለኢኦተቤ ቴቪ (EOTC TV) በሰጡት መግለጫ ገልጸዋል ዘመድ ወዳጆቻቸውና የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻቸው በመርሐ ግብሩ መሠረት ተገኝተው አባታችንን እንዲሸኙ ጥሪ ቀርቧል።
ምንጭ:- EOTC TV
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የብፁዕ አቡነ ሰላማ አጭር የሕይወት ታሪክ
********
ዜና ህይወቱ ለብፁዕ አቡነ ሰላማ (የብፁዕ አቡነ ሰላማ አጭር የሕይወት ታሪክ)
ብፁዕ አቡነ ሰላማ ከአባታቸው ከአቶ ገብረ ሥላሴ ገ/መድኀንና ከእናታቸው ከወ/ሮ ብዙነሽ ወንድሙ በትግራይ ክፍለ ሀገር በመቀሌ ከተማ ልዩ ስሙ በዓታ ለማርያም በተባለው ፲፱፴፬ ዓ/ም ተወለዱ።
ዕድሜያቸው ለትምህርት ሲደርስ በትውልድ ሀገራቸው ንባብና የቃል ትምህርት በሚገባ የተማሩ ሲሆን ለግብረ ዲቁና የሚገባውንም ትምህርት ከየኔታ ክነፈ
ርግብ ተምረዋል ፤ ዲቁና ከብፁዕ አቡነ ማርቆስ ተቀብለዋል።
ብፁዕነታቸው ለቤተክርስቲያንና ለመንፈሳዊ ዕውቀት ባላቸው ጥልቅ ፍቅር በተለያዩ አካባቢዎች በመዘዋወር የተለያዩ መንፈሳዊ ትምህርቶችን የተማሩ ሲሆን
ዜማ፡- ከየኔታ ተክለ ማርቆስ ማየ አንበሳ ገዳም (ተንቤን)
- ቅኔ፡- ከየኔታ ንጉሤ መነዌ ገዳም (ተንቤን)
- ቅኔ፡- ከየኔታ አክሊሉ ደበጋ (ጐንደር)
• ትርጓሜ መጻሕፍት- ከየኔታ ኃ/ማርያም ቀረፃ ማርያም ከምትሀባል ገዳም
ቅኔና ትርጓሜ መጻሕፍት፡- እንድባ ጊዮርጊስ ከየኔታ ልሳነ ወርቅ (ጐጃም)
● ቅኔ፡- ከየኔታ ዲበኩሉ (ጐጃም) በሚገባ ከተማሩ በኋላ ለመምህር ነት በቅተዋል፡፡
ከዚህ በኋላ በጐጃም ክ/ሀገር በፈረስ ቤት ሚካኤል፣ በጅጋ ሚካ ኤል ወንበር ዘርግተው ለ፲፪ ዓመታት ቅኔ በማስተማር አያሌ ደቀ መዛሙርትን አፍርተዋል፡
መዝገበ ቅዳሴ ከየኔታ ልዑል (ቦረራ ሚካኤል) ተምረዋል፤ በወ ቅቱ የጐጃም ሊቀ ጳጳስ ከነበሩት ከብፁዕ አቡነ ማርቆስ የቅስናና የምንኵስና መዐረግ ተቀብለዋል።
ብፁዕ አቡነ ሰላማ በ ፲፱፻፷፬ ዓ.ም ወደ አርሲ ክፍለ ሀገር በመሄድ በወቅቱ የሀ/ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ በነበሩት በብፁዕ አቡነ ሉቃስ መልካም ፈቃድ በሀገረ ስብከቱ በማስተማር፣ የአውራጃ ሰባኬ ወንጌል በመሆን፣ የወረዳ ሊቀ ካህናት በመ ሆን በተለያዩ የኃላፊነት ሥራዎች ተመድበው በመሥራት ሰፊ አገልግሎት አበርክተዋል፤ በርካታ ደቀ መዛሙርትንም አፍርተዋል፤ በዚሁ ሀገረ ስብከት ለ፳፪ ዓመታት በማስተማር ቆይተዋል፤ በዚህም ሰፊ ወቅት ብዙ ደቀ መዛሙርትን አውጥተው ለቤተ ክርስቲያን አበርክተዋል፡፡
ብፁዕነታቸው ከአርሲ ሀገረ ስብከት በ፲፱፻፹፮ ዓ.ም ወደ አዲስ አበባ ከመጡ በኋላ ውቅያኖስ በሆነው እውቀታቸውና በቅድስናቸው ቤተ ክርስቲያንንም ሆነ ምእመናንን እንደሚጠቅሙ በማሰብ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በተለያዩ ጊዜያት በቅዱሳን ፓትርያርኮች ፈቃድና ትእዛዝ እየተሾሙ፦-
⇨ በቡራዩ ፄዴንያ ማርያም፣
⇨ በመተሐራ መድኃኔ ዓለም፣
-በቃሊቲ ቅዱስ ገብርኤልና ሳሎ ቅዱስ ጊዮርጊስ፣
⇨ በሰዓሊተ ምሕረት፣
⇨ በደብረ አሚን ተክለ ሃይማኖት በአስተዳዳሪነት ተመድበው ለበር ካታ ዓመታት በማስተማር በሚያስመንነው ስብከታቸው ብዙ አማንያንን አበርክተዋል፤ ለምናኔም አብቅተዋል፤ በተሰጣቸው ሀብተ ፈውስ በጸሎታቸው አያሌ ሕሙማንን ፈውሰዋል፧ ሰበካ ጉባኤን አጠናክረዋል ስብከተ ወንጌልን አስፋፍተዋል፧ በተለይም በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ሊቀ ሥልጣናት ሆነው ለ ዓመታት ያህል በአስተዳደሩበት ጊዜ ከፈጸሟቸው ተግባራት ዋና ዋናዎቹ ምእመናን በጣዕመ ስብከታቸውና በቅድስናቸው እየተማረኩ ለካቴድራሉ በሚያደርጉት የቦታና የገንዘብ ልግስና በርካታ የሆኑ የልማት ተግባራትን አከናውነዋል።
❖ በዚህም መሠረት በትምህርታቸው በጎ አድራጊዎችንና ምእመናንን በማስተባበር በካቴድራሉ ስም የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤትና ከፍተኛ ክሊኒክ አሠርተው በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ፣ሊቀ ጳጳስ አክ ሱም፣ ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ተባርኮ አገልግሎት በመስጠት ላይ ነው፡፡
⇨ በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ለ፭ ዓመታት ካገለገሉ በኋላ በእን ጦጦ ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት ገዳም በአስተዳዳሪነት አገልግለዋል።
⇨ ብፁዕ አቡነ ሰላማ ሙሉ የቤተ ክርስቲያን ትምህርታቸውን አጠናቅቀው በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ከተመደቡበት ጊዜ ጀምሮ ከቦታ ወደ ቦታ በመዘዋወር በአብነት መምህርነታቸው በተለይም በቅኔ መምህርነታቸው በተለያዩ አህጉረ ስብከት ወንበር ዘርግተው በማስተማር እስከ ጵጵስና ደረጃ የደረሱ አያሌ ምሁራንን አፍርተው ለቤተ ክርስቲያን ያስረከቡ፣ በልዩ የስብከት ችሎታቸው የታወቁ ሰባክያነ ወንጌልን ያፈሩና አማንያንን ያበዙ፣ ቅድስናን ከሙያ ጋር አስተባብረው የያዙ፣ የቅዱሳኑ፣ የፍጹማኑ ረድኤት ያልተለያቸው፣ እንደ አባቶቻቸው ቅዱሳን ሐዋር ያት አጋንንትን የማስወጣትና ሌላውንም ደዌ ሁሉ የመፈወስ ሀብተ ፈውስ የተሰጣቸው፣ በጥላቸው ብቻ ሕሙማንን የሚፈውሱ፣ የበቁ (ፍጹም) አባት ነበሩ።
ብፁዕ አቡነ ሰላማ ከፈጣሪያቸው የተሰጣቸው ተውህቦ የተወሰነ አይደለም ሀብተ ጸጋቸው ብዙ ነው! ጣዕመ ስብከታቸው ካለ መጠገቡም በላይ በተመስጦ በአካለ ሥጋ ያሳርጋልI ቅኔያቸውም ልዩ ጣዕም አለው ከማር ከወተት ይጣ ፍጣል! ፈጣሪያቸውን ብቻ አይደ ለም የሚያከብሩት፣ ሲበዛ ሰው አክባሪ ናቸው‥ ምንም ይሁን ምን በአርአያ እግዚአብሔር የተፈጠረውን ትልቁንም ትንሹንም ሁሉ በአክብሮት የሚወዱ አባት ነበሩ።
በአጠቃላይ ብፁዕ አቡነ ሰላማ የቤተ ክርስቲያናችን ጸጋና በረከት ነበሩ።በዚህ ቅድስና ቸው፣ በቤተ ክርስቲያን ትምህርት ሙሉ ችሎታቸው፣ በአብነት መምህርነታቸው በርካታ ምሁራንን በማፍራታቸውና ለቅድስት ቤተ ክርስቲያናቸው ባበረከቱት ሰፊ የሆነ መንፈሳዊ አገልግሎታቸው ተመዝነው ብቁና ፍጹም አባት ሆነው በመገኘታቸው ሐምሌ ፱ ቀን ፲፱፻፺፯ ዓ.ም በተደረገው የጳጳሳት ምርጫ ከሌሎች ዕጩ ቆሞሳት ጋር ተወዳድረው የድምፅ ብልጫ ስለ አገኙ የአክሱምና ማዕከላዊ ዞን ሃገረ ስብከት ኤጲስ ቆጶስ ሆነው የተመደቡ ሲሆን ከታኅሣሥ ፱/ ፪ሺ፪ ዓ/ም ጀምሮ የሰሜን ምዕራብ ሽሬ እንዳሥላሴ ሀገረ ስብከትን ደርበው እየሰሩ እስከ ግንቦት ፳፰/፪ሺ፭ ዓ/ም ድረስ ሐዋርያዊ ተግባራቸውን ሲፈጽሙ ቆይተዋል።
ግንቦት ፳፰ /፪ሺ፭ ዓ/ም ከትግራይ ማዕከላዊ ዞን አክሱም ሀገረ ስብከት ወደ አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ተዛውረው የታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም ገዳም እና የመንበረ መንግሥት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም የበላይ ኃላፊ ሆነው ሲያገለግሉ ቆይተው በ ፪ሺ፮ ዓ/ም የምሥራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በመሆን ለ፮ ዓመታት በምሥራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት ከፍተኛ ሐዋርያዊ አገልግሎትን ፈጽመዋል።
ብፁዕ አቡነ ሰላማ ከህዳር ፳፻ ፲፪ዓ/ም ጀምሮ በድጋሚ የታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም ገዳም እና የመንበረ መንግሥት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም የበላይ ኃላፊ ሆነው በበአታቸው በመወሰን ሲያገለግሉ ቆይተው ባደረባቸው ሕመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው መስከረም ፲፰ቀን፳፻ ፲ወ፮ ዓ/ም ይህን ዓለም በዕረፍተ ሥጋ ተለይተው ወደ ሰማያዊው አባታቸው ተጉዘዋል።
የብፁዕ አባታችን በረከት ይደርብን።
ምንጭ:- የ/ኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
ዜና እረፍት
ጸሎተኛው አባታችን ብፁዕ አቡነ ሰላማ ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል። «ክቡር ሞቱ ለጻድቅ በቅድመ እግዚአብሔር፤የጻድቅ ሞት በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው፤» (መዝ.፻፲፭፥፭
የብጹዕነታቸው በረከት ይደርብን
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
ዜና እረፍት
ጸሎተኛው አባታችን ብፁዕ አቡነ ሰላማ ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል። «ክቡር ሞቱ ለጻድቅ በቅድመ እግዚአብሔር፤የጻድቅ ሞት በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው፤» (መዝ.፻፲፭፥፭
https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSdiexRM-y7lNQcauWdwYJrJ_d6YyQqzwlmXWka3xc8_PddMMA/viewform?usp=pp_url
መጠይቁን በመሙላት አገልግሎታችንን እንድናሰፋ እንዲያግዙን በእግዚአብሔር ስም እንጠይቃለን።
https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSdiexRM-y7lNQcauWdwYJrJ_d6YyQqzwlmXWka3xc8_PddMMA/viewform?usp=pp_url
መጠይቁን በመሙላት አገልግሎታችንን እንድናሰፋ እንዲያግዙን በእግዚአብሔር ስም እንጠይቃለን።
https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSdiexRM-y7lNQcauWdwYJrJ_d6YyQqzwlmXWka3xc8_PddMMA/viewform?usp=pp_url
መጠይቁን በመሙላት አገልግሎታችንን እንድናሰፋ እንዲያግዙን በእግዚአብሔር ስም እንጠይቃለን።
"ስለዚህ አንድ ሥጋ ናቸው እንጂ ወደ ፊት ሁለት አይደሉም። እግዚአብሔር ያጣመረውን እንግዲህ ሰው አይለየው።" ማቴ 19 ÷6
በዛሬው እለት መስከረም 13 /2016 ዓ.ም ጋብቻችሁን በቅድስት ቤተክርስቲያን ሥርዓት የፈጸማችሁት የሰንበት ትምህርት ቤታችን የፍኖተ ብርሃን አገልጋይ ወንድማችን ኢንጂነር አሸናፊ ጥበቡ እና ሔለን የአብርሃምን እና የሣራን ጋብቻ የባረከ አምላክ ጋብቻችሁን ይባርክላችሁ።
ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል በክንፉ ከልሎ በፍቅርና በጤና ይጠብቃችሁ ዘንድ መልካም ምኞታችን ነው!
እንኳን ደስ አላችሁ ፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ እና የባህር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በመስቀል አደባባይ የሚከበረውን የደመራ በዓልን አስመልክቶ መልእክት አስተላለፉ።
"""""""""""""""""""""
መስከረም ፲፪ ቀን ፳፻፲ወ፮ ዓም
*
አዲስአበባ -ኢትዮጵያ
""""""""""""""""""""
ብፁዕነታቸው በመግቢያቸው ስለ ትግስት አስፈላጊነት እና ጠቀሜታ ትምህርት የሰጡ ሲሆን በበዓሉ ላይ የሚፈትኑ ጉዳዮች ሊገጥሙን ስለሚችሉ በትዕግስት ማለፍ አለብን ብለዋለል። በማስከተልም የዕለቱን መርሐ ግብር ያስተዋወቁ ሲሆን በይበልጥም ሰዓትን ማክበር ከፍተኛ ትኩረት እንደሚሰጠው አሳስበዋል። ብፁዕነታቸው የመግቢያ ባጅ እደላው በሕግና በሥርዓት ትኩረት ተሰጥቶት የሚከናወን መሆኑን ገልጸዋል።
ሰንደቅ ዓላማን በተመለከተም የፌዴራል እና የቤተ ክርስቲያን አርማ ብቻ ይለበት መሆን እንደሚገባውና ርችት መተኮስ የቤተ ክርስቲያን ሥርዐት ባለመሆኑ እንደማይፈቀድ ገልጸዋል።
የቲሸርት አለባበስ በተመለከተም ተንኳሽ መልእክት መጠቀም አይገባም ያሉት ብፁዕነታቸው በየመንደሩና በየአጥቢያው በሚከበሩ በዓላት ላይም ጥንቃቄ ያስፈልጋል ብለዋል።
በበዓሉ ላይ የተፈቀደለት አስተናባሪ ብቻ የሚያስተናግድ ሲሆን ያልተፈቀደለት አካል ሲንቀሳቀስ ቢገኝ በወንጀል ያስጠይቃል ያሉት ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ መርሐ ግብር መሪዎች እና ተናጋሪዎች በተፈቀደላቸው ሰዓት እንዲጠቀሙ አሳስበዋል።።
በመጨረሻም ለመርሐ ግብሩ መሳካት ሁሉም የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ አባታዊ ጥሪ አስተላልፈዋል። በዕለቱ የሙስሊም ወገኖቻችን የሚያከብሩት በዓል ስላላቸው በመከባበር እና በመተባበር በዓላቱን ማክበር ይገባል ሲሉም ጨምረው አሳስበዋል።
እንደዚሁ፦ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ዶ/ር የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የኒውዮርክ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በዓሉን አስመልክተው መልእክት ያስተላለፉ ሲሆን ብፁዕነታቸው በበኩላቸው በዓሉ መንፈሳዊ ስለሆን በመንፈሳዊነት ልናከብረው ይገባል እንደዚሁም በታዛዥነት እና በእምነት በበዓሉ ላይ ልንታደም ይገባል ብለዋል።
ምንጭ EOTC TV
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
"ስለዚህ አንድ ሥጋ ናቸው እንጂ ወደ ፊት ሁለት አይደሉም። እግዚአብሔር ያጣመረውን እንግዲህ ሰው አይለየው።" ማቴ 19 ÷6
በዛሬው እለት መስከረም 12 /2016 ዓ.ም ጋብቻችሁን በቅድስት ቤተክርስቲያን ሥርዓት የፈጸማችሁት የሰንበት ትምህርት ቤታችን የፍኖተ ብርሃን አገልጋይ ወንድማችን ሰሎሞን ዘሚካኤል እና ሕይወት ወሀቤ የአብርሃምን እና የሳራን ጋብቻ የባረከ አምላክ ጋብቻችሁን ይባርክላችሁ።
ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል በክንፉ ከልሎ በፍቅርና በጤና ይጠብቃችሁ ዘንድ መልካም ምኞታችን ነው!
እንኳን ደስ አላችሁ ፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የጥቅምት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ጥሪ ተላለፈ።
መስከረም 10 ቀን 2016 (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ)
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በዓመት ሁለት ጊዜ ከሚያደርጋቸው የምልአተ ጉባኤ ስብሰባዎች አንዱ የሆነው የጥቅምት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ስብሰባ መሆኑ ይታወቃል።
የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት የዘንድሮው የጥቅምት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ስብሰባ ከጥቅምት 12 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ እንደሚካሄድ በመግለጽ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት እና ጳጳሳት ጥቅምት 11 ቀን 2016 ዓ.ም በጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ እንዲገኙ መንፈሳዊ ጥሪውን አስተላልፏል።
ከጥቅምቱ ቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ስብሰባ በፊት ባሉት ዕለታት አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ስብሰባ በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ መሪነት ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትና ጳጳሳት፣ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት የመምሪያና የድርጅት ኃላፊዎች፣የአህጉረ ስብከት የሥራ ኃላፊዎች፣ የሰበካ ጉባኤያት ምክትል ሊቃነ መናብርትና የሰንበት ትምህርት ቤቶች ተወካዮች በተገኙበት እንደሚከናወን የ/ኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ አሳውቋል።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የርቀት (የተልዕኮ)ትምህርት አላማው ዘመኑን ያማከለ የትምህርት አሰጣጥን በመከተል፤ በሥራ፣በትዳር፣ በጊዜ ማጣት፣ እንዲሁም በተለያዩ ምክንያቶች የቤተክርስቲያንን መሰረታዊ ትምህርቶች መማር ላልቻሉ ሃገር ውስጥም ከሃገር ውጭም ያሉ ምዕመናን በሙሉ ቃለ እግዚአብሔርን እንዲማሩ ማድረግ እና በጉብዝናህ ወራት ፈጣሪህን አስብ የሚለውን የአምላካችንን ትዕዛዝ ወጣቶች
እንዲፈጽሙ ማስቻል ነው፡፡ /መክ.፲፪(12)
"ስለዚህ አንድ ሥጋ ናቸው እንጂ ወደ ፊት ሁለት አይደሉም። እግዚአብሔር ያጣመረውን እንግዲህ ሰው አይለየው።" ማቴ 19 ÷6
መስከረም ፫ ፳፻፲፮ ዓ.ም. ጋብቻችኹን በቅድስት ቤተክርስቲያን ሥርዓት የፈጸማችሁት የሰንበት ትምህርት ቤታችን የፍኖተ ብርሃን አገልጋይ ወንድማችን ሙሉጌታ ሰማን እና ምሕረት ግዛው የአብርሃምን እና የሳራን ጋብቻ የባረከ አምላክ ጋብቻችሁን ይባርክላችሁ።
ቅዱስ ሚካኤል በክንፉ ከልሎ በፍቅርና በጤና ይጠብቃችሁ ዘንድ መልካም ምኞታችን ነው!
እንኳን ደስ አላችሁ
"ወትባርክ አክሊለ ዓመተ ምሕረትከ ፤ በቸርነትህ ዓመታትን ታቀዳጃለህ" መዝ፡ 65÷11
የተወደዳችሁና የተከበራችሁ ኦርቶዶክሳውያን በሙሉ ዘመንን በዘመን የሚተካ ዓመታትን እያፈራረቀ የሚለዋውጥ እርሱ ግን ዘለዓለም የማይለወጥ የዘመናት ጌታ በቸርነቱ እንኳን ከዘመነ ሉቃስ ወደ ዘመነ ዮሐንስ አሸጋገረን
መዝ.102÷25 "አቤቱ አንተ ከጥንት ምድርን መሠረትህ ሰማዮችም የእጅህ ሥራ ናቸው፤ እነርሱ ይጠፋሉ አንተ ግን ጸንተህ ትኖራለህ ሁሉም እንደ ልብስ ያረጃሉ እንደ መጎናጸፊያም ትጠቀልላቸዋለህ ይለወጡማል አንተ ግን ያው አንተ ነህ ዓመቶችህም ከቶ አያልቁም"
መጪው ዓመት ዘመነ ዮሐንስ 2016 ዓ.ም የሰላም ፣ የፍቅር ፣የጤናና የበረከት እንዲሁም በንስሃ የምንመለስበት ዓመት እንዲሆንልን የእግዚአብሔር ቅዱስ ፈቃድ ይሁንልን።
የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
Available now! Telegram Research 2025 — the year's key insights 
