en
Feedback
ሙርሰል/አንሷር ሰይድ ጨፌ

ሙርሰል/አንሷር ሰይድ ጨፌ

Open in Telegram
1 905
Subscribers
No data24 hours
-87 days
-4330 days
Posts Archive
አድስ ዜና‼‼️ የአምባሰል ወረዳ የ01 ከነማ ቀበሌ መጅሊስ ተዋቀረ። 👉በዛሬው ዕለት ሐምሌ 13 ቀን 2015 ዓ/ል የአምባሰል ወረዳ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት የ01 ከነማ ቀበሌ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤትን በዉጫሌ ከተማ በአቡበክር መስጂድ ግቢ ዉስጥ 7 የቀበሌ መጅሊስ አመራሮችነ በማስመረጥ የተሳካና እጅግ እጅግ ሰላማዊ የሆነ ሥራ መስራቱ ታዉቋል። የአምባሰል ወረዳ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ከዛሬ 5 ወራት በፊት የካቲት 1/6/2015 በዉጫሌ ከተማ በማክስማ አዳራሽ እጂግ ሰላማዊና ፍትሀዊ በሆነ መልኩና ከበቂ በላይ የሆነ ከየቀበሌዉ የተዉጣጣ ህዝበ ሙስሊም በታደመበት በአድሱ ሪፎርም መሰረት መዋቀሩ ይታወሳል። 🤌ይሁን እንጂ የወረዳችን መጅሊስ በህጋዊ መንገድ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ በስሩ ወደሚገኙ ቀበሌዎች መዋቅሩን በቶሎ ለመዘርጋት ከፍተኛ ጥረት ሲያደርግ ቢቆይም በጣልቃ ገብ አካላትና የመንግስትን ለዉጥ እምብዛም ባልተቀበሉ ግለሰቦች አማካኝነት የተለያዩ ፈታኝ የሆኑ ተግዳሮቶች ሲያጋጥሙት ቆይቷል። በዞናችን ዉስጥ ከ29 ያላነሱ ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች ያሉ ሲሆን በአንድ እጅ ብቻ ሊቆጠሩ ከሚችሉት በስተቀር በሰላማዊ መንገድ በወረዳና በቀበሌ የመንግስት አመራሮች እጀባ እየተደረገላቸዉ መዋቅራቸዉን እስከ ቀበሌ ድረስ አዋቅረዉ እያጠናቀቁ ባሉበት በዚህ ሰአት እንደ አለመታደል ሆኖ የእኛ ወረዳ ግን ገና አንድ ቀበሌ እንኳን ሳያዋቅር ከ5 ወራት በለይ አሳልፏል። ይህ የህዝበ ሙስሊሙ ብቸኛ ተቋም እስካሁን በመንጓተቱ ልባችን ቢደማም መዋቅሩ ከዚህ በላይ መዘግየት ስለሌለበት ከዞን በተሰጠን አቅጣጫ መሰረት በአስቸኳይ በስራችን ወዳሉ ቀበሌዎች መዉረድና ማዋቀር ግድ ሆኖ በመገኘቱ በዛሬዉ እለት የወረዳዉ ዋና ከተማ ከሆነችዉ ዉጫሌ ከተማ በመጀመር አንድ ብሎ የቀበሌ መዋቅሩን በተሳካ ሁኔታ አከናዉኗል። በዚህም መሰረት 1—አቶ ሙሀመድ ተሾመን.ፕሬዝዳንት 2—ሸይኽ አሊይ ዑመርን ም/ፕሬዝዳንት 3—ሰይድ ሙሀመድ ይመርን ዋና ፀሀፊ 4—ሸይኽ ሙስጦፋን የአዉቃፍ ዘርፍ ተጠሪ 5—ሸይኽ ሁሰይን ኑርዪን የደእዋ ዘርፍ ተጠሪ 6—አቶ ጉማታዉ በላይን አደረጃጀት ዘርፍ ተጠሪ 7—አቶ አደም ሷሊህን እርቅና ሰላም ዘርፍ ተጠሪ አድርጎ ማስመረጡ ታዉቋል። አልሀምዱ ሊላህ!! 👉https://t.me/murselseid

👉ይቅር ብሎ ማለፍ የኢስላም መርህ ነዉ 👉የሙስሊሞች ዉበት የቅኖች ምርኩዝ ነዉ ـــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــ ይህ ኢትዮዽያዊ የመን ውስጥ የጥይት ተኩስ እየተለ
👉ይቅር ብሎ ማለፍ የኢስላም መርህ ነዉ 👉የሙስሊሞች ዉበት የቅኖች ምርኩዝ ነዉ ـــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــ ይህ ኢትዮዽያዊ የመን ውስጥ የጥይት ተኩስ እየተለማመደ በስህተት አንድ የመናዊ ይገድላል። ያው የመን በአለማችን በማንኛውም ሱቅ ያለምንም ፓስፖርት ጠያቂ መሳሪያ የሚሸጥበት አገር ናት። ዱላ ከረሚላ ማለት መሳሪያ ነው የመን ውስጥ፣ የሆነው ሆኖ ልጅ ልክ እንደገደለው በአካባቢው ሰዎች ቁጥጥር ስር ይውላል። ሟች ተቀብሮ እስከሚያበቃ ልጅን ደበቀው ለሸህ አስቀመጡት። የልጅ ወላጆች ተጠርተው ልጅን ምን እናድረገው ተባሉ። በሸሪአ ህግ መሰረት የገደለ ይግደል ነውና ይገደል ተባለ። የማች አባት ገዳዮን ላግኘው አሉ። ተገናኙ። አባት ለምን ልጀን ገደልከው .? አሉት። ገዳይ መተኮስ እያስለመደኝ ነበር ጥይቱ አልቋል ብየ ስስብ ደገልኩት አውቄ አደለም አለው። አንተ ምንድነህ ዜግነትህ ምንድነው ሲባል ሀበሻ ( ኢትዮዽያዊ) ነኝ አላቸው። ለምን የመን መጣህ አሉት ወደ ሳኡዲ እየሄድኩ ነው አላቸው። የሟች አባት ይሄንን ካወቁ ቡኋላ ምንም ሳይሉ ወደቤታቸው ተመለሱ።ዘመድና ቤተሰብ ሰብስበው፣ ገዳይ ስደተኛ ነው። እጅ ላይ ምንም የለውም። ቢደገልም ቤተሰቡን መጉዳት ነው። እናት ልጀ ይመጣል ስትል እሰው አገር ተቀብሯል ትባላለች እንጅ ትርፍ የለውም። ስለዚህ የሞተውን አላህ ይዘንለት ያለውን ይቅር ብለነው ወደ ቤተሰቡ ይሂድ አሉ። የሟች ወንድሞችና ዘመዶች ሁሉ ተስማሙ ይህ ልጅ ከሞት ተርፎ ዛሬ የመኖች ተገርመው ዜና እየሰሩበት ነው። ይቅርታ ብሄር ጎሳ ድንበር ዜግነት የለውም። የገዛ ወንድሙን በብሄር እየለየ ለሚገለውና ለሚዘርፈው የአገሬ ነውረኛ ፖለቲካ የየመናዊያን ከተራራ የገዘፈ ይቅር ባይነት ትልቅ መልዕክት አለው። ✍ሱሌማን አብደላ 👉https://t.me/murselseid

አሰላሙ አለይኩም ወረህመቱሏሂ ወበረካቱህ ــــــــــــــــــــــــــــــــ 👉ወደ አንድ አመት ገደማ ያስቆጠረዉና እለተ ጁሙዐህ ከመግሪብ በሗላ የሚካሄደዉ ሳምንታዊዉ የደእዋ ፕሮግራማችን ዛሬም በአሏሁ ተዓላ ፈቃድ በተለመደዉ ቦታና ሰአት ያለ በመሆኑ በሰአቱ ትታደሙ ዘንድ ለማስታወስ እንወዳለን!! 👉መልእክቱን ለሌሎችም ያድርሱ 07/11/2015 አ.ል

Repost from N/a
አካዉንት ከፍቷል‼️‼️ 🤌የአምባሰል ወረዳ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት የያዘዉን የመልካም ሥራ ጅማሮ ለማሳለጥ በማለም በዛሬዉ እለት 04/11/2015 በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በዉጫሌ ከተማ አሻሚል ቅርንጫፍ በመገኘት በመጅሊሱ ዋና ሰብሳቢ ኡስታዝ አንሷር ሰይድ፣ በፀሀፊዉ ቲቸር አደም ኢድሪስ እና በአደረጃጀት ዘርፍ ሀላፊዉ በሸይኽ ሰይድ ኢብራሂም የሚንቀሳቀስ ከወለድ ነፃ በሆነዉ አሰራር መሰረት (( የአምባሰል ወረዳ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት )) በሚል ስያሜ ጥምር ተንቀሳቃሽ አካዉንት መክፈቱ ታዉቋል። የአካዉንት ቁጥሩም 👉1000557463678 👉https://t.me/ambaselweredaeslmnagudayohce

🌸🌸【 أذكار الصباح】【 የንጋት ዚክር】🌸🌸 ــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــ 👈①قراءة آية الكرسي (1) 👈②قراءة سورة الإخلاص. (3) 👈③قراءة سورة الفلق.(3) 👈④ قرءاة سورة الناس. (3) 👈⑤ أَصْـبَحْنا وَأَصْـبَحَ المُـلْكُ لله وَالحَمدُ لله، لا إلهَ إلاّ اللّهُ وَحدَهُ لا شَريكَ لهُ، لهُ المُـلكُ ولهُ الحَمْـد، وهُوَ على كلّ شَيءٍ قدير، رَبِّ أسْـأَلُـكَ خَـيرَ ما في هـذا اليوم وَخَـيرَ ما بَعْـدَه، وَأَعـوذُ بِكَ مِنْ شَـرِّ ما في هـذا اليوم وَشَرِّ ما بَعْـدَه، رَبِّ أَعـوذُ بِكَ مِنَ الْكَسَـلِ وَسـوءِ الْكِـبَر، رَبِّ أَعـوذُ بِكَ مِنْ عَـذابٍ في النّـارِ وَعَـذابٍ في القَـبْر. (1) 👈⑥اللّهـمَّ أَنْتَ رَبِّـي لا إلهَ إلاّ أَنْتَ، خَلَقْتَنـي وَأَنا عَبْـدُك، وَأَنا عَلـى عَهْـدِكَ وَوَعْـدِكَ ما اسْتَـطَعْـتُ، أَعـوذُ بِكَ مِنْ شَـرِّ ما صَنَـعْتُ، أَبـُوءُ لَـكَ بِنِعْـمَتِـكَ عَلَـيَّ وَأَبـوءُ بِذَنْـبي فَاغْفـِرْ لي فَإِنَّـهُ لا يَغْـفِرُ الذُّنـوبَ إِلاّ أَنْتَ. (1) 👈⑦.رَضيـتُ بِاللهِ رَبَّـاً وَبِالإسْلامِ ديـناً وَبِمُحَـمَّدٍ صلّى الله عليه وسلّم نَبِيّـاً. (3). 👈⑧ اللّهُـمَّ إِنِّـي أَصْبَـحْتُ أُشْـهِدُك، وَأُشْـهِدُ حَمَلَـةَ عَـرْشِـك، وَمَلَائِكَتَكَ، وَجَمـيعَ خَلْـقِك، أَنَّـكَ أَنْـتَ اللهُ لا إلهَ إلاّ أَنْـتَ وَحْـدَكَ لا شَريكَ لَـك، وَأَنَّ مُحَمّـداً عَبْـدُكَ وَرَسـولُـك. (4) 👈⑨اللّهُـمَّ ما أَصْبَـَحَ بي مِـنْ نِعْـمَةٍ أَو بِأَحَـدٍ مِـنْ خَلْـقِك، فَمِـنْكَ وَحْـدَكَ لا شريكَ لَـك، فَلَـكَ الْحَمْـدُ وَلَـكَ الشُّكْـر. (1) 👈∅①حَسْبِـيَ اللّهُ لا إلهَ إلاّ هُوَ عَلَـيهِ تَوَكَّـلتُ وَهُوَ رَبُّ العَرْشِ العَظـيم. (7) 👈①①بِسـمِ اللهِ الذي لا يَضُـرُّ مَعَ اسمِـهِ شَيءٌ في الأرْضِ وَلا في السّمـاءِ وَهـوَ السّمـيعُ العَلـيم. (3) 👈②①اللّهُـمَّ بِكَ أَصْـبَحْنا وَبِكَ أَمْسَـيْنا، وَبِكَ نَحْـيا وَبِكَ نَمُـوتُ وَإِلَـيْكَ النُّـشُور. (1) 👈③①سُبْحـانَ اللهِ وَبِحَمْـدِهِ عَدَدَ خَلْـقِه، وَرِضـا نَفْسِـه، وَزِنَـةَ عَـرْشِـه، وَمِـدادَ كَلِمـاتِـه. (3) 👈④①اللّهُـمَّ عافِـني في بَدَنـي، اللّهُـمَّ عافِـني في سَمْـعي، اللّهُـمَّ عافِـني في بَصَـري، لا إلهَ إلاّ أَنْـتَ. (3) 👈⑤①اللّهُـمَّ إِنّـي أَعـوذُ بِكَ مِنَ الْكُـفر، وَالفَـقْر، وَأَعـوذُ بِكَ مِنْ عَذابِ القَـبْر، لا إلهَ إلاّ أَنْـتَ. (3) 👈⑥①اللّهُـمَّ إِنِّـي أسْـأَلُـكَ العَـفْوَ وَالعـافِـيةَ في الدُّنْـيا وَالآخِـرَة، اللّهُـمَّ إِنِّـي أسْـأَلُـكَ العَـفْوَ وَالعـافِـيةَ في ديني وَدُنْـيايَ وَأهْـلي وَمالـي، اللّهُـمَّ اسْتُـرْ عـوْراتي وَآمِـنْ رَوْعاتـي، اللّهُـمَّ احْفَظْـني مِن بَـينِ يَدَيَّ وَمِن خَلْفـي وَعَن يَمـيني وَعَن شِمـالي، وَمِن فَوْقـي، وَأَعـوذُ بِعَظَمَـتِكَ أَن أُغْـتالَ مِن تَحْتـي. (1) 👈⑦①يَا حَيُّ يَا قيُّومُ بِرَحْمَتِكَ أسْتَغِيثُ أصْلِحْ لِي شَأنِي كُلَّهُ وَلاَ تَكِلْنِي إلَى نَفْسِي طَـرْفَةَ عَيْنٍ. (3) 👈⑧①أَصْبَـحْـنا وَأَصْبَـحْ المُـلكُ للهِ رَبِّ العـالَمـين، اللّهُـمَّ إِنِّـي أسْـأَلُـكَ خَـيْرَ هـذا الـيَوْم، فَـتْحَهُ، وَنَصْـرَهُ، وَنـورَهُ وَبَـرَكَتَـهُ، وَهُـداهُ، وَأَعـوذُ بِـكَ مِـنْ شَـرِّ ما فـيهِ وَشَـرِّ ما بَعْـدَه. (1). 👈⑨①اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ وَبَارِكْ على نَبِيِّنَا مُحمَّد. (10) 👈∅②اللَّهُمَّ إِنَّا نَعُوذُ بِكَ مِنْ أَنْ نُشْرِكَ بِكَ شَيْئًا نَعْلَمُهُ، وَنَسْتَغْفِرُكَ لِمَا لَا نَعْلَمُهُ. (3) 👈①②اللَّهُمَّ إِنِّي أَعُوذُ بِكَ مِنْ الْهَمِّ وَالْحَزَنِ، وَأَعُوذُ بِكَ مِنْ الْعَجْزِ وَالْكَسَلِ، وَأَعُوذُ بِكَ مِنْ الْجُبْنِ وَالْبُخْلِ، وَأَعُوذُ بِكَ مِنْ غَلَبَةِ الدَّيْنِ، وَقَهْرِ الرِّجَالِ. (3) 👈②②أسْتَغْفِرُ اللهَ العَظِيمَ الَّذِي لاَ إلَهَ إلاَّ هُوَ، الحَيُّ القَيُّومُ، وَأتُوبُ إلَيهِ. (3) 👈③② اللَّهُمَّ إِنِّي أَسْأَلُكَ عِلْمًا نَافِعًا، وَرِزْقًا طَيِّبًا، وَعَمَلًا مُتَقَبَّلًا. (1) 👈④②لَا إلَه إلّا اللهُ وَحْدَهُ لَا شَرِيكَ لَهُ، لَهُ الْمُلْكُ وَلَهُ الْحَمْدُ وَهُوَ عَلَى كُلِّ شَيْءِ قَدِيرِ. (100) 👈⑤ ②سُبْحـانَ اللهِ وَبِحَمْـدِهِ. (100) 👈⑥②أسْتَغْفِرُ اللهَ وَأتُوبُ إلَيْهِ. (100). ـــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــ 👉ማሳሰቢያ!! ① ስለረዘመብኝ ዉስን ዚክሮችን ቀንሻለሁ ② የሚደረግበትን ጊዜ በተመለከተ የሱብህ ሶላት ጊዜ ከገባ ጀምሮ ፀሀይ ከፍ እስከምትል ድረስ ማድረግ ይቻላል። ③ ከ25 ደቂቃ የበለጠ አይፈጅምና በየቀኑ ፕሮግራም ይዘን ከማድረግ አደራ እንዳንዘናጋ!! ✍በሙርሰል ሰይድ ጨፌ 👉https://t.me/murselseid

👉በሱፍያዉ አለም ረጂም አመታትን ሲዋኙ የነበሩ መሻይኾች እዉነቱን ሲናገሩ እንዴትስ ደስ አይል? 👉ይህቺን የሸይኽ ሰይድ ኮምበልቻን ኹጥባ ሳልሰማት ነበር ሼር ያደረግኳት። አሁን ሰአት አግኝቼ ሙሉዋን ስሰማት ግን በጣም ነዉ ደስ ያለኝ!! እስኪ ሁላችሁም ሰአት ስጡና በጥሞና አዳምጧት ከዚያም ሼር አድርጓት!! 30 ደቂቃ ብቻ

👉በሱፍያዉ አለም ረጂም አመታትን ሲዋኙ የነበሩ መሻይኾች እዉነቱን ሲናገሩ እንዴትስ ደስ አይል? 👉ይህቺን የሸይኽ ሰይድ ኮምበልቻን ኹጥባ ሳልሰማት ነበር ሼር ያደረግኳት። አሁን ሰአት አግኝቼ ሙሉዋን ስሰማት ግን በጣም ነዉ ደስ ያለኝ!! እስኪ ሁላችሁም ሰአት ስጡና በጥሞና አዳምጧት ከዚያም ሼር አድርጓት!! 30 ደቂቃ ብቻ

ኹጥባ 👉ተውሂድ እና ሺርክ በሚል ርእስ በሙጢቆሎ መስጂደተውሂድ የተደረገ ኹጥባ 👉በአቢ ሙሀመድ ሸይኽ ሰይድ ሙጢ 👉https://t.me/murselseid

👉ዝንቦች የሚበዙበት አካባቢ ካየህ እዚያ አካባቢ መልካም ጠረን እንደሌለ ገምት 👉አህባሽ የሚበዛበት አካባቢ ደግሞ ቢድአ እንጂ የነቢዩ ሱና ደብዛዋም እንደማይገኝ እርግጠኛ ሁን። ✍ሙርሰል ሰይድ ጨፌ 29/10/15 👉https://t.me/murselseid

ከምን ደረሰ? ~ ባለፈው የዒደል ፊጥር ጊዜ የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ለእስልምና እምነት ተከታዮች ለመስገጃ የሚሆን 20 ሺህ ካሬ ሜትር ቦታ መስጠቱን አሳውቆ ነበር። የወልዲያ ከተማ አስተዳደርም እንዲሁ ለሙስሊሙ ማህበረሰብ ቦታ ሰጥቶ ለተነሺዎች ካሳ የሚሆን መዋጮ ሲጠየቅ ነበር። ጉዳዩ ከምን ደረሰ? የአካባቢው ሙስሊም ወኪሎች ኃላፊነት አለባችሁ። ቦታዎቹን ተረክባችኋል? ካልተረከባችሁ ምን ሂደት ላይ ናችሁ? ለህዝብ ማሳወቅ ይኖርባችኋል። ከተረከባችሁም እንዲሁ ማሳወቅ አለባችሁ? ወሰን የማስከበር፣ አጥር የማጠር፣ ለአገልግሎት ዝግጁ የማድረግ ስራ ሰርታችኋል? ለምን ? ሰሞኑንም በደቡብ ወሎ ዞን ወረባቦ ወረዳ ውስጥ ለሙስሊሙ ማህበረሰብ የተገባ ቃል ሲንሸራሸር ነበር። ጉዳዩን የሚከታተል፣ የአፈፃፀም ሂደቱን እየተከታተለ የሚያሳውቅ ባለቤት ተደርጎለታል ወይ? ወይስ ለአስተዳደሮች መልካም ፈቃድ ብቻ የተተወ ነው? እዚህ አገር ለሙስሊሙ ማህበረሰብ ብዙ ቃል ተገብተው የቀሩ ጉዳዮች አሉ። ከዘመናት በኋላ የተፈፀሙ ካሉም ብዙ ተቀንሰዋል። አዲስ አበባ አያት አካባቢ ለመስጂድ የተወሰነ ቦታ ቃል የተገባውን ሲሶ የማያክል ቦታ ነው በቅርቡ የፀደቀው። የከፊሎች ችግር ደግሞ ህሊና በሌላቸው የሙስሊሙ ወኪሎች የመጣ ነው። የአስኮ አወሊያ ሰፊ ቦታ ተቆርሶ ተቆርሶ በሌሎች አካሎች ብዙ ተወስዷል። የኮተቤ መቃብር እንዲሁ ብዙ ተቆርሶ ተወስዷል ወይም ተሽጧል። መሰል አሳፋሪ ሁነቶች ብዙ ናቸው። ስለዚህ ሙስሊሙ እንደማህበረሰብ ጠያቂ ሊሆን ይገባል። ያለበለዚያ ብዙ ተስፋ የተጣለባቸው ጉዳዮች ሰሞንኛ ፖለቲካ ማድመቂያ ብቻ ሆነው ያልፋሉ። ወይም ቃል ሲገባ በነበሩበት ወርድና ቁመት ሳይሆን በእጅጉ አንሰው ይፈፀማሉ። ✍በኢብኑ ሙነወር 👉https://t.me/murselseid

የኔ ጀግና! ~ ሸይኽ ሙሐመድ ብኑ ዐብዲል ወሃብ ኢስላምን ያጠለሹ፣ ሙስሊሞችን በአጉል ኮተቶች ጠፍረው ያሰሩ የሱፊያ ኮተቶችን የበጣጠሰ አንበሳ ነው። በጀሊሉ፣ በወሃቡ ፈቃድ የተሃድሶ ንቅናቄው የቀብር አምልኮትን ግንድ ከምድረ ሰዑዲያ ገንድሶታል። በመላው የሙስሊሙ አለም ያለውን የበሰበሰ የሱፊያ ሸክም አነቃንቆታል። ኧረ ክፉኛ ወዝውዞታል። በዚህ የተነሳ ሱፊዮች ዘንድ እንደሱ የተጠላ ፍጡር የለም። የተፃፈ ኹጥባ ለማንበብ ሚንበር ላይ ወጥቶ የሚንገዳገደው ሁላ እየተነሳ "ሙሐመድ ብኑ ዐብዲል ወሃብ ጃሂል ነው" ሲል የምንሰማው ያለ ምክንያት አይደለም። ይገባናል፣ የሚያስጮሃችሁ ህመማችሁ ነው። "አሶራኹ ዐላ ቀድሪል አለም" እንዲል ዐረብ። "ጩኸት በህመም ልክ ነው!" ሙሐመድ ብኑ ዐብዲል ወሃብ እንዳንተ ሶደቃ ሲያባር እድሜውን አልፈጀም። ጋርዶ ጫት የሚቀረጥፍ ቦዘኔ አልነበረም። ሁሉን እንዳመጣጡ ያስተናገደ፣ ለቆመበት አላማ ቆርጦ የተነሳ፣ ከዚያም እስከ ደም ጠብታ የታገለ ቆራጥ ነበር፣ የጀግና ጀግና! የፅናት፣ የትጋት፣ የብቃት ተምሳሌት! ዛሬ ግን ይሄ ነው የሚባል የዒልም ቅሪት የሌለው፣ ኢስላምን የግል ጥቅም መሸመቻ ያደረገ፣ ከሆዱ አሻግሮ መመልከት የማይችል ቦዘኔ ሁላ እየተነሳ "እሱ'ኮ ጃሂል ነበር" ይላል። እርሱ ጃሂል ከነበረ አንተ ጅህልና እራሱ ነህ! • "ወሃብዮች ዑለማእ አያከብሩም" የሚሉ አስመሳዮች ሁላ በሸይኹ ላይ ምላሳቸውን ሲያሾሉ ማየት በስፋት የተለመደ ነው። ግማሹ "ተ'ክ'ፊ'ር ነው" ይላል። ግማሹ "የሁዲ ነው" ይላል። ግማሹ "የእንግሊዝ ቅጥረኛ ነበር" ይላል። ሌላም ሌላም ለጆሮ የሚሰቀጥጡ ውንጀላዎች አሉ። እናንተ ናችሁ ስለ ዑለማእ ክብር የምታወሩት? በጀግኖቻችን ክብር ላይ እየተረማመዱ ከዚያ የነሱን የጥፋት ሰባኪዎች እንድናከብርላቸው ይፈልጋሉ። በሃገራችን በመውሊድ ሰበብ ስማቸው ገኖ ከሚታወቁ ቦታዎች ጋር ተቆራኝቶ ዝናቸው ከናኘ መሻይኾች ውስጥ #ብዙዎቹ የእውነት እንደሚባለው በዒልም የላቁ እንደነበሩ የሚያሳይ ማስረጃ ብትጠይቁ አስቂኝ ነገር ነው የምትሰሙት። "እስኪ ኪታባቸውን አሳዩን?" ብትሉ "የመውሊድ መንዙማ ፅፈዋል" "ማዲሕ ነበሩ። መድሕ አዘጋጅተዋል" ብለው የግጥም መድብል ይነግሯችኋል። ዒልም ማለት ግጥም መፃፍ ነው እነዚህ የዞረባቸው ዘንድ! በዚህ የግንዛቤ አቅምህ ነው ሸይኽ ሙሐመድ ብኑ ዐብዲል ወሃብን በጅህልና የምትወርፈው?! አዎ መውሊድ ያገነናቸው ብዙ ስመ ገናናዎች አሉ። ከመውሊድ ጭፈራ ባለፈ ከነ ጭራሹ በቦታው ምንም አይነት የዒልም እንቅስቃሴ የሌለባቸው ብዙ ናቸው። = ✍በ IbnuMunewor 👉https://t.me/murselseid

የሰዉ ጉልበት መሳለም ምን የሚሉት ልክፍት ነዉ? ــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــ አህባሾች 👉አብዱሏህ አልሀረሪ 👉የጀነቱ መሪ እያሉ የጀነት ከመሆኑም አልፎ ጭራሽ የጀነት መሪ መሆኑን የሚመሰክሩለት የአህባሾች መስራች ይህ ነዉ። 👉ከሞተ ወደ 13 አመት ገደማ ሆኖታል። 👉https://t.me/murselseid

አርኪ ድካም! ~ ሐጅ ውጣ ውረድ፣ ድካም፣ ልፋት አለው። የዐረፋ በረሃ አናት ያፈላል። ሙዝደሊፋ ያዝለፈልፋል። ወደ ዐቀባ የሰው ጎርፍ ካፍ እስከ ገደፉ ጢም ብሎ ሲርመሰመስ ይታያል። ጦዋፈል ኢፋዷ ትንፋሽ ያሳጣል። ሰዕዩ (በሶፋና መርዋ መሐል መመላለሱ) ተረከዝ ያቆስላል። አገር ምድሩ በተክቢራ፣ በተልቢያ ይናጣል። ከ0ረፋ ወደ ሙዝደሊፋ መልስ ላይ አንድ ሙሉ እርምጃ የመራመድ ፋታ ለማግኘት ትእግስትን የሚፈታተን ረጅም ድካም ይጠይቃል። ይህም ሁሉ ሲሆን ታዲያ ልዩ የሆነ ሐሴት አለው። ጫፍ የደረሰ የመንፈስ እርካታ። እየደከሙ መርካት፣ እየረኩ መድከም፣ ጣፋጭ ድካም! አርኪ ልፋት። ሐጅን ካላደረጉት ሰዎች ይልቅ የቀመሱት፣ ያጣጣሙት ሰዎች ይበልጥ ለድጋሚ ልባቸው ይቆማል። ሰሞኑን አንድ አባት ከሩቅ ደወሉልኝ። "አሞኛል" አሉኝ። "ህመሞት ገብቶኛል" አልኳቸው። "አዎ ገብቶሀል" አሉኝ። ህመማቸው ሐጅ ነው። የዛሬን አራት አመት ሐጅ ካደረጉ በኋላ ይሄው በየዓመቱ ሐጅ ሲደርስ ያማቸዋል። ህመሙን የሚያውቅ ያውቀዋል። (አላህ ይማራቸው፣ አሁን ሞተዋል።) ከስር በምስሉ ላይ ተሰልፈው የሚታዩት ህመምተኞችን የያዙ አምቡላንሶች ናቸው። የሐጅ ስርአት በጊዜ የተገደበ ነውና እንዳያልፋቸው ከነ ህመማቸው ከመዲና ወደ መካ እየተጓዙ ነው። አልጋ ላይ ሆነው ሐጅን ይከውናሉ። የኢማን ጣእም ከህመም ስቃይ በላይ እንደሆነ የሚያሳይ እውነታ። የኢማን ጥፍጥና የሞትን ፍርሃት ይገፍፋል። በዚህ ሁኔታ ላይ የሚሞቱ ብዙ አሉ። ግና ከነ ኢሕራም ልብሳቸው ተቀብረው ነገን "ለበይክ" እያሉ መነሳትን የሚጓጉለት ምርጥ ሞት እንጂ ከሃገሬ ወጥቼ እንዳልቀር ብለው የሚጨነቁለት መአት አይደለም። ጉዳዩ የየቂን ጉዳይ ነው፣ ከሞት በኋላ ባለው ዓለም ያለ እርግጠኝነት። = ( Ibnu Munewor ፣ ነሐሴ 27/2009 ፣ ተነካክቶ በድጋሚ የተለጠፈ) 👉https://t.me/murselseid

👉ለሀጅ ለከእባ ይኑር ሶቅሶቃ‼️‼️ 👉ነፍስያህ ትድን ዘንድ ከወንጀል ተላቃ ــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــ 👉ከሰኡዲ አረቢያ ቻናሎች በአንዱ አንድት ሴት ወደ ሸይኽ ኡሰይሚን ደወለችና፣ 👉የሆነ ህልም አይቻለሁ። (ህልሙን) ፍቱልኝ አለቻቸዉ። 👉ምን አየሽ? አሏት 👉የሆነ ሰዉ በከእባ ዙሪያ ምንም ልብስ ሳይለብስ ራቁቱን ሁኖ ጠዋፍ ሲያደርግ አየሁት አለች። 👉(በህልምሽ) ያየሺዉን ሰዉ ታዉቂዋለሽ? አሏት። 👉አዎ አለቻቸዉ። 👉ኢልምና መልካምነት አለዉ? አሏት። 👉እርሱ ራሱ እዉቀትና ደግነት ነዉ አለቻቸዉ። {እርሱ ራሱ እዉቀትና ደግነት ነዉ ማለቷ ማጋነኗ ነዉ} 👉አሏህ ወንጀሎቹን (ሁሉ) እንደማረዉና ልክ እናቱ እንደወለድችበት ቀን የነፃ መሆኑን አበስሪዉ አሏት። 👉ላበስረዉ? አለቻቸዉ። 👉አዎ አበስሪዉ አትፍሪ አሏት። 👉ያ ያየሁት ሰዉየ አንተ ነህ አለቻቸዉ። 👉በጣም ከባድ ለቅሶ አለቀሱ። ምክኒያቱም ባላሰቡት መንገድ እራሳቸዉን ስላወደሱ። አሏህ ይዘንላቸዉ!! ــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــ 👌እነዚህ ናቸዉ የሱና ኡለሞች‼️‼️ ــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــ ከተኮረጀ አረበኛ የተተረጎመ ــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــ ✍በሙርሰል ሰይድ ጨፌ 19/10/15 👉https://t.me/murselseid

👉አሏህ ከአርሽ በላይ መሆኑ በቁርአን፣ በሀድስ፣ በኢጅማእም በአቅልም የተረጋገጠ ኢስላማዊ እዉታ እንጂ አህባሾች እንደሚሉት፣ 👉ወደላይም የለም፣ 👉ወደታችም የለም፣ 👉ወደ ቀኝም የለም፣ 👉ወደግራም የለም፣ 👉ወደ ፊትም የለም፣ 👉ወደ ሗላም የለም፣ 👉በጥቅሉ ከስድስቱም አቅጣጫ የጠራ ነዉ የሚለዉ አሏህን ከናካቴዉ ወደ ማጥፋት ያንዣበበ አድስ መጤ አስተሳሰብና ቅዠት የፍልስፍና እምነት ነዉና ልንርቀዉ ይገባል!!! 👉https://t.me/murselseid

✋አሰላሙ አለይኩም ወረህመቱሏሂ ወበረካቱህ . 👉ይህ የአምባሰል ወረዳ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ቻናል ነዉ። ጆይን እያሉ ከምክር ቤቱ በየጊዜዉ የሚለቀቁትን መረጃዎችና ጥቆማዎች ይከታተሉ። 👉ሊንኩን ለሌሎች ሼር በማድረግም ይተባበሩን!! 👉https://t.me/ambaselweredaeslmnagudayohce