en
Feedback
አጫጭር የፍቅር ልብ ወለዶች️

አጫጭር የፍቅር ልብ ወለዶች️

Open in Telegram

አንብብ ባታነብ የሚቀርብህ ድንቁርና ብቻ ነው!!! # ማሳሰቢያ # ቻናሉ የተከፈተው ለአንባቢዎች ብቻ ነው አንባቢዎች joined @achachr

Show more
The country is not specifiedThe category is not specified
1 876
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
🌀✅ #የምንጊዜም_የህይወት_ህጎች ✅🌀 ✳ ከመናገርህ በፊት→አስብ፣ ✳ ከመፈረምህ በፊት→አንብብ፣ ✳ ከማስተማርህ በፊት→ተማር፣ ✳ ከመምከርህ በፊት→ተግብር፣ ✳ ከመቁረጥህ በፊት→ለካ፣ ✴ ከማጉደልህ በፊት→ተካ፣ ✴ ከመዋጥህ በፊት→አላምጥ፣ ✴ ከመገንዘብህ በፊት→አድምጥ፣ ✴ ከማመንህ በፊት→አረጋግጥ፣ ✴ ከመረከብህ በፊት→ቁጠር፣ 💠 ከመወሰንህ በፊት→መርምር፣ 💠 ከመስራትህ በፊት→አቅድ፣ 💠 በትጋት ሳይሆን በብልሃት ስራ፣ 💠 ከመተኮስህ በፊት→አልም፣ 💠 ከመተቸትህ በፊት→አጣራ፣ ✅ ከመብላትህ በፊት→ስራ፣ ✅ ከመሞትህ በፊት→ንሰሃ ግባ፣ ✅ ከመሄድህ በፊት→ተስፋ ሰንቅ፣ ✅ ስትወያይ→ሁን አስተዋይ፣ ✅ ስትናደድ→ቶሎ ብረድ፣ 🚺 ስትናገር→በቁምነገር፣ 🚺 ስትቸገር→መላ ፍጠር፣ 🚹 ስትቀመጥ→ቦታ ምረጥ፣ 🚹 ስትወስን→ቆራጥ ሁን!! #ስለ ሁሉም አምላክ ማስተዋሉን ያብዛልን!(አአሜን join👇👇 @achachr @achachr

❤️ፍቅር ገደብ የለውም ያፈቀረ ሠው ሁሌም ተስፋ በመቁረጥም መሃል ሆኖ ይጠብቃል😘 ❤️ስው ወደደኝ 😏ጠላኝ አማኝ ብዬ አልጨነቅም ስጭም ነሽም ጠባቂም ህወትንም ቀያሪ ፈጣሪ ብቻ ነው፡፡ 😍ንፁህ ፍቅርና የሌሊት ጨረቃ አንድ ናቸው ሁለቱም ልብ ላይ ደስታን ይፈጥራሉ፡፡❤️ @achachr

ብዙ ሰዎች በህይወትህ ውስጥ ይመጣሉ ይሄዳሉ።ካንተ ጋር የሚቆዩት ግን እውነተኞች ብቻ ናቸው። @achachr

🍃🌹🍃....✍ ❤️. . .እውነተኛ ፍቅር አንድ ሰሞን ላይ አላስቆም አላስቀምጥ ብሎ መልሶ የሚጠፋ ሳይሆን በእውቀት እየዳበረ እና በእርግጠኝነት እየታጀበ ወደ ሙላቱ እንደሚፈስ ወንዝ ሁለቱንም ጥንዶች ወደ አንድ ዘላቂ ቁም ነገር አያይዞ የሚነዳ የህይወት ዘመን ማሰሪያ ገመድ ነው፡፡❤️@achachr🌹🍃🌸🍃🌹🍃,,,,,,,,,,,

〰〰〰 ዘመዶቹ 〰〰〰 ማታ ላይ ለአቶ ባል መልዕክት ይደርሰዋል፤ በስልክ፡፡ : ባልም ለወይዘሮ ሚስት “ነገኮ ዘመዶቼ እንመጣለን አሉኝ …” ብሎ የሰማውን ያጋራል፡፡ . ሚስትም ተበሳጭታ፦ “ቆይ ለምንድነው የሚመጡት …” . ባል፦“እሱንማ እኔ ምን አውቃለሁ … ጉዳይ ይኖራቸው ይሆናላ፤ ብቻ በሰላም ነው ብለውኛል …” . ሚስት፦ “ስንት ሆነው ነው የሚመጡት?” . ባል፦“እሱንስ አልጠየኳቸውም … እንዲሁ እንመጣለን ሲሉ እሺ አልኩ እንጂ …” . ሚስት፦“ታዲያ የመጡ እንደሆነሳ?” . ባል፦“አይ! … እንድንዘጋጅ ብዬ ነው፡፡ መቼስ እንግዳ ሲመጣ ዝም አይባል …” . ሚስት፦“እኔ ምንም የማዘጋጀው የለኝም … ቤቱን እንደሆነ ያውቁታል … አዲስ አይደሉም … ” . ባል፦“የሚገዛም ነገር ካስፈለገም ልገዛዛና ሰርተን እንጠብቃቸው እንጂ” . ሚስት፦“ምንም አያስፈልግም … ያለውን ይቀምሳሉ” . ባል፦“ምን አለ …” . ሚስት፦ “ውሃስ ቢሆን … ሌላ የማዘጋጀው የለኝም!” . ባል፦“ኧረ ተይ … ሰው አለን ብለው አይደል ወደኛ መምጣታቸው … እንደገቡ እንኳ የሚቀማምሱት ብናዘጋጅ አይሻልም …” . ሚስት፦“ይምጡና ያለውን አቀርብላቸዋለሁ" . . ይችኑ እንደተባባሉ ነጋ፡፡ ባልም በማለዳ ተነስቶ የቤቱን ሁኔታ ሲያይ ምንም የለም … ቁርስም የለም … ጭጭ … ጭጭ … ሚስትም ለጥ ብላ እንደተኛች አረፈደች፡፡ ባል ሹልክ ብሎ ወጣ፡፡ ወዲያው የሚስት እናት፣ አባት እና ሌሎችም ተሰባስበው ከተፍ አሉ፡፡ ደንግጣ ተነስታ ተቀበለቻቸውና ወደ ባል ደወለች … . ሚስት፦“ለምንድነው ዘመዶችሽ ይመጣሉ ብለህ ያልነገርከኝ” . ባል፦“እንዴ! ነገሬሽ …” . ሚስት፦ “ዘመዶቼ ይመጣሉ ነውኮ ያልከኝ!” . ባል፦“አዎ! ያው ያንቺ ዘመዶችስ የኔ ማለት አይደሉ እንዴ!” . ሚስት፦“እሺ አሁን ምን ላድርጋቸው” . ባል፦“ሌላ ምን ታደርጊያቸዋለች አስተናግጃቸው እንጂ” . ሚስት፦“የተዘጋጀ ደህና ነገር የለማ” . ባል፦“ታዲያ ምን ይሻላል?” . ሚስት“በቃ … ከምግብ ቤትም ቢሆን የሚበላ ነገር ገዛዝተህ ና እንጂ …” . ባል፦“እኔ እንኳ አሁን መምጣት አልችልም፤ እቆያለሁ … አንቺን ምን አስጨነቀሽ … ለቤቱ እንደሆነ አዲስ አይደሉ … ያለውን ነገር ስጫቸው” . ሚስት፦“ምንም ነገር የለምኮ!” . ባል፦“ … ውሃም ቢሆን ስጫቸው … ባይሆን ቁልፉን ለጎረቤት ሰጥተሽልኝ አብረሻቸው ሂጂ፡፡” @achachr

ንዴ? አላዉቅም። ፍዝዝ ስልባት "ሀቢብ ይህን ሁሉ የማደርገዉ አንተ በጣም ጨለማ ዉስጥ ያለህ ሰዉ ስለሆንክ በአንዴ ወደ ብርሀኑ ሲወረዉሩህ ጨረሩ በዝቶ እንዳይጎዳህ ብዬ ነዉ። ህይወትህን እንደልብህ ስትሆን እንዳሳለፍክ አዉቃለሁ። አሁን መታፈኑ እንዳይከብድህ ትንሽ ማስተንፈሻ እያመቻቸሁልህ ነዉ።" አለችኝ። "ልክ ነሽ!" አልኳት ብስለቷ ግርም እያለኝ። ቆይ ግን ስለኔ ህይወት እንዴት እንደዚህ በድፍረት ልትናገር ቻለች? ዋናዉ ግን ያቀረበችዉ ሀሳብ መልካም መሆኑ ነዉ። . በነጋታዉ ጠዋት ላይ በሀጂ መኪና ወደ ትምህርት ቤቱ ሄድን። ከአምሪያ እንደተነጠልኩ ሳስብ በጣም ሆድ ባሰኝ። ሀጂን ገፍቼ የራሴን መንገድ ለመከተል አሰብኩ። ደሞ የእናቴ አደራ ትዝ ሲለኝ እንደምንም ለመጋፈጥ ወሰንኩ። ግቢዉ ዉስጥ ገብተን ከመኪናዉ እንደወረድኩ አንድ ሰዉዬ መጥቶ ከሀጂ ጋር ትንሽ አወራና ሀጂን ተሰናብቶ "ኡስታዝ ሰዒድ እባላለሁ ተከተለኝ።" ብሎኝ ከፊት ከፊቴ መራመድ ጀመረ። ሀጂን ተሰናብቼ ሰዉየዉን ተከተልኩት። አምሪያ እንዳለችዉ ግን ፍተሻ አልተደረገብኝም። ስገምት ሀጂ ስላስገቡኝ ነዉ። ስልኬን አምሪ ወደ ማታ ልታቀብለኝ ተቀጣጥረናል። ኡስታዙ ወደ ቢሮዉ አስገብቶኝ አንዳንድ ጥያቄዎችን ከጠየቀኝ በኋላ የትምህርት ቤቱን ህጎች መናገር ጀመረ። "እዚህ እስካለህ ድረስ የመኝታ እና የትምህርት ሰዓቶችን ማክበር አለብህ።" አለኝ እና ከተማሪዎች ጋር ሊኖረኝ ስለሚገባዉ ግንኙነት አብራራልኝ። አዉርተን ስንጨርስ የምተኛበትን ክፍል አሳየኝ። ተደራራቢ አልጋዎች ያሉበት ሰፊ ክፍል ነዉ። ሻንጣዬን አልጋዬ ላይ ካስቀመጥኩ በኋላ የአንድ ክፍል በር እያሳየኝ "አሁን አንድ ልጅ ቁርዓን ሸምድዶ ስለጨረሰ የእንኳን ደስ አለህ ዝግጅት ተዘጋጅቶ ሁሉም እዛ ናቸዉ። ሂድ ግባ!" አለኝ። ወደ ክፍሉ ልገባ በሩን በትንሹ ከፍቼ ሳይ ትንሽዬ መድረክ ላይ አንድ ነጭ ጀለቢያ የለበሰ ሰዉ ቆሞ ያወራል። ተማሪዎቹ ሁሉም ነጭ ጀለቢያ ለብሰዉ እግራቸዉን አጠላልፈዉ በሰልፍ ተቀምጠዋል። ጀለቢያ የሚባለዉ ወንድ ሙስሊሞች የሚለብሱት ቀሚስ ነዉ። ተማሪዎቹ እንዳለ ልጆች መሆናቸዉን ሳይ በጣም ተበሳጨሁ። አሁን ከነዚህ ጋር ማነዉ ሚዛዛገዉ? ከከሪሜ የሚበልጥ አንድ ልጅ ብቻ ነዉ ያለዉ። በጣም ተበሳጨሁ። እቅዴ ከቻልኩ ዛሬ ለመባረር ነዉ። በሩን ከፍቼ ስገባ መድረኩ ላይ ያለዉ ሰዉዬ "አላህ ማንንም አይበድልም። በጣም ፍትሀዊ ነዉ። ሁላችንም የተሰጠንን ፀጋ ብንቆጥረዉ የጎደለን የለም!" አለ። ድምፄን ከፍ አድርጌ "አትዋሽ ፍትሀዊ አይደለም! ከፊሉን እያሰቃየ አንተን ስላስደሰተህ ፍትሀዊ ነዉ አትበል!" አልኩ። ተማሪዎቹ ዞር ብለዉ አዩኝና አጎንብሰዉ ሳቁ። ኡስታዙ አየኝና "ስምህ ማነዉ?" አለኝ። በንቀት እያየሁት "ሀቢብ" አልኩት። "አዲስ ተማሪ ነህ መሰለኝ። በኋላ ቢሮ እፈልግሀለሁ።" አለኝ። ሊያባረኝ ሊሆን ይችላል ብዬ በጣም ደስ አለኝ። . ማታዉን አምሪ መጥታ አስጠራችኝ። ኡስታዙ የሀጂ ልጅ ስለሆነች እንደልቧ እንድትገባ ይፈቅድላታል። በእጇ ፌስታል ይዛለች። "ጀለቢያ አቢ ገዝቶልሀል። አድርሺለት ብሎኝ ነዉ።" አለችና ፌስታሉን ሰጥታኝ ሄደች። ኡስታዙ አጠገባችን ቆሞ ስለነበር ምንም ማዉራት አልቻልንም። እንደሄደች ጀለቢያዎቹን እያወጣሁ ስመለከታቸዉ የአንዱ ኪስ ዉስጥ ስልኬን አገኘሁት። የአምሪ ጥበብ ገረመኝ። ከልጆቹ ተደብቄ ለአምሪ እንዳገኘሁት የሚገልፅ መልዕክት በሚሴጅ ላኩላት። . ለሊት ዘጠኝ ሰዓት ሲል አንዱ ኡስታዝ መጥቶ ቀሰቀሰኝ። በጣም ተበሳጭቼ "ምን ፈለግክ?" ስለዉ ዉሀ እየረጨ ከተኛሁበት አስነሳኝ። አሀ ለካ የመኝታ ህግ የተባለዉ ይሄ ነዉ? ለሊት ዘጠኝ ሰዓት ተነስቶ መማር? ሰዉ አይደሉም እንዴ? በጣም ቀፈፉኝ። . ይቀጥላል... . ተጨማሪ ልብወለዶችን ለማንበብ ቻናሉን ይቀላቀሉ! 👇 @achachr

የማይፋቅ ስህተት ክፍል 14 (ፉአድ ሙና) . ከአምሪ ጋር ምንጣፉን አጥበን እንደጨረስን ፀሀይ እንዲያገኘዉ ከግቢ ዉጪ አሰጣነዉ። አምሪ ግቢዉን ጠርጋ ስትጨርስ "ያዉ ዝናብ ከዘነበ ምንጣፉን ብቻዬን ማስገባት ስለማልችል ዛሬ የትም መሄድ አትችልም!" አለችኝ። ማዕቀብ ቢመስልም ደስ በሚል ሰዉ የተጣለ ደስ የሚል ማዕቀብ ስለሆነ ወድጄዋለሁ። አምሪ የግቢዉን በር ዘጋችና በረንዳዉ ላይ ከአጠገቤ እየተቀመጠች "ሀቢቤ ታዉቃለህ አንዳንዴ በህይወትህ ዉስጥ አንዴ ተሳስተህ የምትሰራዉ ስራ ህይወትህን ምስቅልቅል ሊያደርገዉ ይችላል።" አለችኝ። አንገቴን አቀርቅሬ "ምን ተሳስተሽ ነዉ?" አልኳት። መልስ ሳትሰጠኝ "ከሱ የሚከፋዉ ደግሞ ያንተ መልካም ያልሆነ ምግባር ለሌላዉ ህይወት መበላሸት ምክንያት ሲሆን ነዉ!" አለችኝ። ልትነግረኝ የፈለገችዉን ነገር ከመተንፈስ በዘለለ ለማብራራት እንዳልፈለገች ስለተረዳሁ ላስጨንቃት አልፈለግኩም። ዝም ብዬ "ልክ ነሽ!" አልኳት። ሳቀች። ምን አሳቃት? እኔንጃ አልጠየቅኳትም። ከአምሪ ጋር እየተጨዋወትን ሚኪያስ ደወለ። እየሳቀ "ሀቢብ ራህመቶ!" አለኝ። ሰሞኑን ሙድ መያዣ አድርገዉኛል። ዛሬ ከሄለን ጋር ኦፊስ ስለሚያሳልፉ ወደ ኦፊስ ድርሽ እንዳልል ሊያስጠነቅቀኝ ነዉ የደወለዉ። እኔ እንኳ ሲጀመርም ቆንጆ እስር ላይ ነኝ። አምሪ በወሬያችን መሀል "ሀቢቤ ግን እኔና አንተ አብረን እንዲህ ረዥም ሰዓት ስንቀመጥ ቢያዩ ኡሚም አቢም እንደሚቆጡ ታዉቃለህ?" አለችኝ። ዛሬ ወ/ሮ ለይላ ከሀጂ ራህመቶ ጋር በጠዋቱ ወጥተዋል። ግርም እያለኝ "ለምን?" አልኳት። "ሀይማኖታችን አይፈቅደዉም!" አለችኝ። "ይገርማል ታዲያ ለምን አብረሽኝ ተቀመጥሽ?" አልኳት። "እኔ እንኳን..." አለችና በረዥሙ እየተነፈሰች "ይለፈኝ!" አለችኝ። እኔ ሰዉ ማስጨነቅ ብዙም አይመቸኝም። አለፍኳት። ደስ የሚለዉ ምንም ክረምት ቢሆንም ዛሬ ጠዋት ምንጣፉን ከማጠባችን በፊት የዘነበ ቀኑን ሙሉ አልዘነበም። ከአምሪ ጋር ባዶ ቤት ብቻችንን መሆናችንን ሳስብ ስለሷ የሚሰማኝን ስሜት ልነግራት አሰብኩ። ደሞ ነግሬያት ቢደብራት ወዳጅነታችንም ሊቀር ይችላል ብዬ ስለፈራሁ ተዉኩት። . እነአምሪያ ቤት እየኖርኩ ትንሽ እንደቆየሁ የኛ ቤት የቤት እቃዎች በሙሉ ተሸጡ። ትናንሽ የቤት ዉስጥ መገልገያዎችን ሰፈራችን ላለች አንድ ሴትዮ ሰጠናቸዉ። ቤቱም ተከራየ። አዲስ ባለትዳሮች ናቸዉ ቤታችንን የተከራዩት። የአስራሁለተኛ ክፍል መልቀቂያ ዉጤት ወጣ። አምሪ አምስት መቶ ዘጠና ሁለት አመጣች። ወንድሞቿ በሽልማት አንበሸበሿት። እኔም ከአረብ ሀገሯ ታላቢዬ ከተሚማ ባጨድኩት ብር የእንግሊዘኛዉ ኤ መሀሉ ላይ የተንጠለጠለበት የብር የአንገት ሀብል ስጦታ ሰጠኋት። አምሪ ስጦታዬን በጣም ወዳዋለች። . ክረምቱ እያለቀ ሲሄድ ከአምሪያ ጋር ያለን ቅርርብ በጣም እየጠበቀ ሄደ። ፈጣሪ ይባርካት በህይወቴ በልቼ የማላዉቀዉን በርገር የሚባል ምግብ ሱስ አስያዘችኝ። ብር እኔም ሀጂ ስለሚሰጡኝ እሷም ከወንድሞቿ እና ከሀጂ ስለሚሰጣት አንዳንዴ ካልሆነ አጥተን አናዉቅም። ወጣ ብላ ስትመለስ ለኔ ገዝታ ይዛልኝ ትመጣለች። እኔ አስራአንደኛ ክፍልን እንደምንም ባልፍም ላለመማር ወስኛለሁ። ሀጂ ሀይማኖታዊ ትምህርት በግድ ሊያስተምሩኝ ወስነዋል። እኔም የእማዬ አደራ ሆኖብኝ ሳልወድ በግዴ እሺ ብያቸዋለሁ። እነሚኪያስ ትምህርት እንደማልቀጥል ስነግራቸዉ በጣም ተበሳጩ። ሀጂ ነፃነቴን እንደገፈፉኝ ተሰማቸዉ። በርግጥ ሀጂ ሀይማኖታዊ ትምህርት እንድማር እንጂ አለማዊ ትምህርት እንዳቋርጥ አላስገደዱኝም። መማር እንደማልፈልግ ስላወቁ ነዉ ይህን የፈረዱብኝ። ፌቪ ቢያንስ በሳምንት ሶስት ቀን ኦፊስ ዉስጥ አብራኝ ታሳልፋለች። እነሀጂ ቤት መኖር መጀመሬን አልወደደችዉም። አንዳንዴ ትምህርታችንን ትተን የሆነ ነገር እየሰራን አብረን እንኑር ትለኝ ነበር። በጣም የሚገርመኝ ቀን ከሌት የሚለፉላት እና የሚያንቀባርሯትን ቤተሰቦቿን ከቁብም ሳትቆጥር እነሱን ትታ ከኔ ጋር ለመኖር ማለሟ ነዉ። ሴት ልጅ ከወደደች፣ ከተያዘ ነፍሷ፣ የቤተሰብ ክብር ፣ ጨዋታ ነዉ ለሷ። አይደል የሚባለዉ። ይሄን ግጥም ፌስቡክ ላይ አንዷ ለጥፋዉ ነዉ ያነበብኩት። የማን እንደሆነ አላዉቅም። ከስሩ ግን ከበደ ሚካኤል የሚል ፅሁፍ ያየሁ መሰለኝ። ግጥሙ ፌቪን በደንብ ይገልፅልኛል። ክረምቱ ተጠናቆ አዲስ አመት ተበሰረ። የነአምሪ የዩኒቨርሲቲ ምድብ ወጣ። አምሪ ክፍለሀገር ቢደርሳት በጣም ሊደብረኝ እንደሚችል ይሰማኝ ነበር። ግን ቢደርሰኝም እዚሁ የግል ዩኒቨርሲቲ እማራለሁ ስላለችኝ ተረጋጋሁ። ደስ የሚለዉ ምድብ ሲወጣ ህክምና አዲስአበባ ዩኒቨርሲቲ ደረሳት። ሁላችንም በጣም ደስ አለን። . ዛሬ የአዲስ አመቱ ፀሀይ ፈገግ ያለ ይመስላል። በጠዋቱ ተነስቼ ግቢዉ ዉስጥ ፑሽአፕ እየሰራሁ ነዉ። ሀጂ የንጋት ስግደት እንድሰግድ ሲቀሰቅሱኝ እሺ ብዬ መብራቱን አበራና ሲሄዱ አጠፋዋለሁ። ያዉ ግን ስለለመደብኝ አስራሁለት ሰዓት ላይ ቻት ማድረግ እጀምራለሁ። ሀጂ ለቁርስ ሊጠሩኝ ሲመጡ ነቃ ብዬ ስልክ ስጎረጉር ስለሚያዩኝ የሰገድኩ ይመስላቸዋል። ዛሬ ፑሽአፕ ስሰራ አምሪ መጥታ ሀጂ እየጠሩኝ እንደሆነ ነገረችኝ። ስሄድ ፈገግ ብለዉ ተቀበሉኝና "ሀቢቤ ነገ ወደ መርከዙ ትሄዳለህ። ልብስህን አምሪያ ታዘገጃጅልሀለች።" አሉኝ። መርከዝ ያሉት የሀይማኖት ትምህርት ቤት ማለታቸዉ ይመስለኛል። "ልብስ ምን ያደርግልኛል?" አልኳቸዉ። ሀጂ ፈገግ እንዳሉ "አዳሪ ነዉ እኮ ትምህርቱ!" አሉኝ። ዉስጤ ንዴት ቅጥልጥል ሲል ይሰማኛል። እንዴት ነዉ እንደዚህ አይነት ህይወት የማሳልፈዉ? አዳሪ ይላሉ እንዴ? ምርር እያለኝ "አዳሪ ማለት?" አልኳቸዉ። "ያዉ አዳሪ ማለት ትምህርቱ እስኪያልቅ አዳርህም እዛዉ ነዉ ማለት ነዋ!" አሉኝ። የሆነ ስሜት ዉስጤ ላይ ጥፋ ጥፋ ሲለኝ ይሰማኛል። የእናቴን ቃል ከምጥስ ትምህርት ቤቱን ብጥብጥ አድርጌዉ ለመባረር ወሰንኩ። ሀጂ ከሄዱ በኋላ ለአምሪ ያሉኝን ነገርኳት። "ባክህ ልብሱን አስተካክይለት ብሎ ነግሮኛል።" አለችኝ። ሳላስበዉ "አምሪ ትናፍቂኛለሽ እኮ!" አልኳት። ፈገግ ብላ አየችኝና "ሀቢቤ አትጨነቅ መድረሳዉ የአቢ ነዉ። እኔም እሁድ እሁድ ስለምማር እየመጣሁ አገኝሀለሁ።" አለችኝ። የሆነ ትልቅ ሸክም የወረደልኝ ያክል ቅልል አለኝ። አምሪ እንዲህ አቅልላ ያየችዉ እዛ ያለዉን ህይወት ስለምታዉቀዉ ይመስለኛል። ከልቤ ፈገግ እንዳልኩ "እሺ!" አልኳት። . ወደ ማታ ከነሚኪያስ ጋር ተገናኝቼ የተፈረደብኝን ነገርኳቸዉ። በጣም አዘኑ። ሚኪ "ያዉ አንተ እንደምንም እያመቻቸህ ትወጣና ኦፊስ ትከሰታለህ። እኛ ፌቪን አመቻችተን እንጠብቅሀለን። አትጨነቅ!" አለኝ። በርግጥ እኔን ያስጨነቀኝ ነፃነቴ እንጂ የፌቪ ጉዳይ አይደለም። ወደ ቤት ስመለስ አምሪን መኝታ ክፍሌ ዉስጥ ልብሴን በሻንጣ ስታስተካክል አገኘኋት። "ሀቢብ እስከምጨርስ ሳሎን ሁን!" አለችኝ። አሳሳች ቦታዎች ላይ ብቻችንን ስንሆን በጣም ትጠነቀቃለች። ዛሬ እንኳ እናቷም ነበሩ። አስተካክላልኝ ስትጨርስ ዉጪ በረንዳዉ ጋር ሆና ጠራችኝ። ስሄድ "ስማ ሀቢብ እዛ ስልክ መጠቀም አይፈቅዱልህም። ስለዚህ መላ መፈለግ አለብህ። ስትገባ ይፈትሹሀል። እኔ ከፈተሹህ በኋላ ላቀብልህ እሞክራለሁ። በፍፁም ግን እንዳይታወቅብህ!" አለችኝ። ፀጉሬን እየጠቀለልኩ "ኧረ አምሪ ስራዬ ነዉ አትጨነቂ! ብቻ ስልኩ ይግባ!" አልኳት። "ደሞ ለካርዱ አታስብ እኔ እልክልሀለሁ። የምመጣ ቀን ደግሞ አስቀድሜ እነግርሀለሁ።" አለችኝ። ይህን ሁሉ ለምን ታደርግልኛለች? እሷም እንደኔ እናፍቃት ይሆን እ

ክፍሌ ገብቼ ሳዑዲ የምትኖር ብዙ ጊዜ ብር የምትልክልኝን ተሚማ የምትባል ሚስኪን ታላቢዬን መጀንጀን ጀመርኩ። በመሀል ፌቪ እንደለመደችዉ ደዉላ ረዥም ሰዓት አወራችኝ። ክፍሉ አስተማማኝ ስለሆነ እንደልብ ለመጀናጀን ይመቻል። . ሊነጋጋ ሲል ሀጂ ራህመቶ የንጋት ስግደት እንድሰግድ በሩን አንኳክተዉ ለመቀስቀስ ሞከሩ። እንቅልፍ ብዙም ባይዘኝም ላለመስገድ ብዬ ባልሰማ ተኛሁ። አስራሁለት ሰዓት ሲል እንደለመድኩት ቻት ላይ ተጥጄ ከፌቪ እና ከተሚማ ጋር መጀናጀን ጀመርኩ። ተሚማ ፎቶዋን ልካልኛለች። አሪፍ ነገር ናት። በድምፅ የምንላላካቸዉ መልዕክቶች ልብስ ያስወልቃሉ። ትንሽ እየተፃፃፍኩ እንደቆየሁ አምሪያ የመኝታ ቤቴን በር አንኳኳችና " ሀቢቤ ተነስ ቁርስ ብላ!" አለችኝ። እዚህ ቤት ከአስራአንድ ሰዓት በኋላ እንቅልፍ የለም። ተነስቼ ልብሴን ቀያየርኩና ተጣጥቤ ወደ ሳሎን ሄድኩ። ቤቱ ፏ ብሏል። ደስ ይላል። ሀጂ ቁርስ እንድንበላ እየጠበቁኝ ነበር። አጠገባቸዉ ስቀመጥ "እንቅልፎ ሰገድክ?" አሉኝ። ፈገግ ብዬ "አዎ!" አልኳቸዉ። አለመስገዴን ማን ያዉቃል? ማንም! ፈጣሪ ነዉ እሱ እንደሆነ ይበለዉ። በልተን እንደጨረስን "ሀቢቤ ማታ መማር እንደማትፈልግ ተናግረሀል። እኔ ከልጆቼ ጋር መክሬበት መስከረም ሲመጣ የሀይማኖት ትምህርት እንድትጀምር ወስኛለሁ። እኔ ሀይማኖታዊ ትምህርት ቤት ስላለኝ እዛ ትገባለህ።" አሉኝ። በህይወቴ ከዚህ በላይ የምጠላዉ ነገር ያለ አይመስለኝም። ሀጂ ደግሞ እሺ እሺ ስላቸዉ የሌለ አበዙት። ምርር እያለኝ "ሀጂ ግን ስራ ብጀምር አይሻልም?" አልኳቸዉ። "ሀቢብ ይሄ ለድርድር የሚቀርብ ጉዳይ አይደለም! ትማራለህ! የእናትህን አደራ አትርሳ!!" አሉኝ። በእናቴ ስም ይነግዳሉ እንዴ ብሽቅ ነገር ናቸዉ። በልተን ስንጨርስ ሀጂ የወጪ ብለዉ መቶ ብር ሰጡኝ። ባይሆን ይሄ ሙዳቸዉ የሌለ መስጦኛል። ዛሬም ከፌቪ ጋር ተገናኝቼ በእናቴ ህመም ምክንያት ያላገኘኋትን ለማካከስ አሰብኩ። አዲስ ሴት እስከማሰምጥ ከሷዉ ጋር ልዛዛግ! . ሀጂ እንደወጡ አምሪ ፈገግ ብላ "ዛሬ ምንጣፍ አጥባለሁ አታግዘኝም?" አለችኝ። ቀይ ምንጣፍ ላይ ህዝብ ተሰብስቦ እያጨበጨበልህ ትራመዳለህ ያለችኝ ያህል ደስ አለኝ። ፈገግ ብዬ "በጣም ደስ ይለኛል!!" አልኳት። እነአምሪ ቤት ሰራተኛ አለመኖሩ ግርም ይለኛል። አንዴ አምሪን ጠይቄያት "ሁለት ሴት ያለበት ቤት ለሶስት ሰዉ ተብሎ ሰራተኛ እንዴት ይቀጠራል?" ብላኛለች። እኛ ለስራዉ አናንስም አይነት ነገር! ምንጣፉን አዉጥቼ ግቢ ዉስጥ ዘረጋሁት። አምሪ ምንጣፉ ላይ ወጥታ በጎማ ዉሀ እያፈሰሰች በብሩሽ ማሸት ጀመረች። ጫማዬን አዉልቄ አምሪ በሰጠችኝ ብሩሽ ልክ እንደሷዉ ማሸት ጀመርኩ። ሁሉ ነገሯ ልቤን ይዞታል። እንደሌላዉ ሴት እንኳ ለማስመጥ ክብድ ብላኛለች። ምንጣፉን እያየሁ "አምሪ" አልኳት። ቀና ብላ አይታኝ ፈገግ አለችና በከንፈሮቿ ጥርሷን ያጠረዉን ሽቦ እየሸፈነች "አርፈህ እሽ!" አለችኝ። እየገባት ነዉ ልበል? እኔንጃ! ፈገግ እያልኩ "ምኑን?" አልኳት። ሳቋን መቆጣጠር አቅቷት እርጥቡ ምንጣፍ ላይ እየተቀመጠች "አመዳም ምንጣፉን ነዋ!" ብላ ብሩሿን ወረወረችብኝ። እየሳቅኩ የወረወረችብኝን ብሩሽ መልሼ አቀብያት እሷ እንደምትቦርሸዉ ምንጣፉን መቦረሽ ጀመርኩ። . ይቀጥላል... . ተጨማሪ ልብወለዶችን ለማንበብ ቻናሉን ይቀላቀሉ! 👇 @achachr

የማይፋቅ ስህተት ክፍል 13 (ፉአድ ሙና) . ዝም ብዬ እስቃለሁ። ከዛም አለቅሳለሁ። ቆይ ለምን? ፈጣሪን ምን አደረግኩት? ለሌላዉ ሀብትም ጤናም ሰጥቶ ቤተሰቦቹንም ይጠብቅለታል። እኔን ምነዉ ድሀ መሆኔ ሳያንስ ቤተሰብ አልባ አደረገኝ? ይሁና! መች ሀይ ባይ አለዉ!? እንደልቡ ይሁን!! ቆይ ለኔ ምን ሰጠኝ? ጠይም መልክ? ረዥም ቁመት? ሉጫ ፀጉር? ጉልበት? ምላስ? ይሄ ኮተት ለኔ ምን ያደርግልኛል? ሰዉ ከጎኔ ሳይኖር መልክ ፣ ቁመት ወላ ጉልበት ለኔ ምኔ ነዉ? ለነገሩ መች ከሳሽ አለዉና! እንዳሻዉ ይሁን! . እማዬ ከተቀበረች ሳምንት ሞላት። ሚኪ ሁሌም አብሮኝ ያድራል። ፌቪ ሰሞኑን ከጓደኞቿ ጋር አብራ እየመጣች ታዳብረኛለች። አምሪ ለቅሶ ለመድረስ የሚመጣዉን ሰዉ በማስተናገድ ተጠምዳለች። ዘመድ ባይኖረኝም ጎረቤትና ጓደኛ ሞልቷል። ለአምሪያ ለየት ያለ ስሜት ዉስጤ ላይ እየተፈጠረ ነዉ። ማታ ላይ ሁሉም ሰዉ ወደቤቱ እንደተበተነ አምሪ እኔና ሚኪ ወዳለንበት ክፍል መጣችና "ሀቢቤ በቃ ቤት ልገባ ነዉ። ደህና እደሩ!" አለችኝ። ልትወጣ ስትል ተከተልኳት። የዉጪዉ በር ጋር ስትደርስ "አምሪ ለምን እዚህ አታድሪም?" አልኳት። አምሪ ቀልዴን መስሏት "አዝግ!" ብላኝ ልትወጣ ስትል እጇን ያዝኳት። እንደመቆጣት እያለች "ሀቢብ!" አለችኝ። ለምን እንደያዝኳት እኔ ራሱ አላዉቅም። ቀስ ብዬ እጇን ለቀቅኳት። በቃ የሆነ ለማንም ሴት ተሰምቶኝ የማያዉቅ አይነት ስሜት ለሷ ልቤ ዉስጥ እየተቀጣጠለ ነዉ። አምሪ ፈገግ እንደማለት አለችና "ደህና እደር ሀቢቤ!" ብላኝ ወጥታ በሩን ዘጋችዉ። በረዥሙ ተነፈስኩና እዛዉ ቁጢጥ አልኩ። ሚኪ ሳሎን ቤት ሆኖ መስታወቱን አንኳኳዉ። ስዞር ሚኪ የሳሎን ቤቱን በር መስታወት መጋረጃ ገልጦ የማደርገዉን እየታዘበ ነበር። ተነስቼ ወደ ቤት ገባሁ። ሚኪ ዝም ብሎ አየኝና "ሀቢቤ ልጅቷ ጎረቤት ነህ ብላ እንዲህ መልፋቷ አይበቃም? አተርፋለሁ ብለህ እንዳትከስራት!" አለኝ። "ሚኪ እኔ ራሴን ማዘዝ አልቻልኩም። እሷ ስትሄድ በጣም ነዉ የሚጨንቀኝ።" አልኩት። ሚኪ ሳቀና "እና ፎንቃ አስጨመድዳታለሁ ብለህ ዝተህ የነበርከዉ ልጅ ፎንቃዋ ጨምድዶህ አረፍከዋ!?" አለኝ። እየሳቅኩ ተቀመጥኩ። ሚኪ እየሳቀ ለአብነት እና ለከሪም ደዉሎ ነገራቸዉ። ምንም አላልኩትም እንደዉም ደስ አለኝ። ከፈለገ ለምን አምሪያን አፈቀረ ብሎ በየፖሉ አይለጥፍም፤ እንኳን በሷ በስንቱ ታምቻለሁ። . በነጋታዉ ሀጂ ደዉለዉ ወደ ቤታቸዉ ጠሩኝ። አምሪ እጇን ስለያዝኳት ተናዳ ነግራቸዉ ከሆነ ብዬ በጣም ፈራሁ። ቤታቸዉ ስሄድ አምሪ ፈገግ ብላ ስትቀበለኝ በሷ ምክንያት እንዳልሆነ ገመትኩና ቀለል አለኝ። ሀጂን ሰላም ብያቸዉ ተቀመጥኩ። ትንሽ ከተጨዋወትን በኋላ "ሀቢቤ ከዚህ በኋላ እንደአባትህ እየኝ! ያዉ እናትህ ባስገባችኝ ቃል መሰረት ላንተ መልካም ያልኩትን አደርጋለሁ። አሁን የናንተ ቤት እየተከራየ ገንዘቡ ባንክ እንዲቀመጥ ብናደርግ፤አንተ ደግሞ እኛ ቤት ብትኖር ምን ይመስልሀል?" አሉኝ። ሳስበዉ ትንሽ ነፃነቴን የሚጋፋኝ መሰለኝ። ደግሞ ከአምሪያ ጋር አብሮ መኖር ልጀምር መሆኑ ጥሩ ነዉ። አይሆንም ለማለት የማቀርበዉ ምንም አይነት ምክንያት ስላልነበረኝ ፈገግ አልኩና "ጥሩ ሀሳብ ነዉ።" አልኳቸዉ። "በቃ ከተስማማን ጥሩ! አምሪያዬ ክፍልህን ታሳይሀለች። ልብሶችህን ታመጣቸዋለህ። የቤቱን እቃም ተከራይ ሲገኝ የሚሸጠዉ ይሸጣል።" አሉኝ። ተስማማሁ። . እነሀጂ ቤት የተሰጠኝ ክፍል ደስ ይላል። ልብሴን አምጥቼ ክፍሌ አስቀመጥኩት። አምሪ ቆንጆ አድርጋ ቁምሳጥኑ ዉስጥ አስተካክላ አስቀመጠችልኝ። . ሀዘኑ ቀለል ሲልልኝ ወደ ቀደመዉ ህይወቴ ተመለስኩ። ኦፊሳችን ስሄድ እነ አብነት የሌለ አሳብደዉታል። ትልቅ ፍራሽ፣ ገራሚ ትራሶች ምናምን ቤቱን ሞልተዉታል። የአዲስ ጎጆ ወጪ ቤት ይመስላል። ፌቪን ቀጥሬ ነበር የመጣሁት። እንደተቀመጥኩ ፌቨን መጣች። ሁለታችንም ምን እንደምንፈልግ ተግባብተናል። አብሮ መተኛት! በሩን ዘግተነዉ ሰላም እንኳ ሳንባባል የልባችንን ወደ ማርካቱ ሄድን። የምንግባባበት ዋናዉ ጉዳይ ይሄዉ ነዉ። አላፈቅራትም፤ለሷ ምንም ስሜት የለኝም። አሁን ከዚህ በላይ ከፌቪ ጋር መዛዛግ ስለደበረኝ ላሰናብታት ፈልጌያለሁ። እሷን ከማሰናበቴ በፊት ግን ሌላኛዋን ማዘጋጀት ይኖርብኛል። አምሪያን ማስመጡ እንደዚህ ቀላል አይሆንም። ለምን አምሪያ ጋር ስደርስ አቅም እንደማጣ ፣ ለምን ከሌሎች ሴቶች ተለይታ ክብድ እንደምትለኝ አላዉቅም። አጠገቧ ተቀምጬ ሳያት ብዉል አይቆጨኝም። ከፌቪ ጋር ያነፋፈቀንን የስጋችንን ጥሪ ምላሽ ከሰጠን በኋላ ወደ ቤቷ ሸኘኋት። ልንለያይ ስንል አይኖቿን አይኖቼ ላይ እያቁለጨለጨች "ሀቢቤ ላርግዝልህ?" አለችኝ። የሆነ እብደት የተጠናወታት መስሎኝ በግርምት እያየኋት "ፌቪ ግን ደህና ነሽ?" አልኳት። ፈገግ ለማለት እየሞከረች "ሀቢቤ የእናትህ ሞት የብቸኝነት ስሜት ከፈጠረብህ የኔ የምትለዉ አንድ የስጋ ዘመድ ይኑርህ ብዬ እኮ ነዉ።" አለችኝ። ግርም እያለችኝ "ሀሳብሽ ጥሩ ነዉ ግን ያንቺ ህይወት ላይ የሚፈጥረዉ ቀዉስ አልታየሽም?" አልኳት። ፊቷ ላይ እልኋን እያስነበበችኝ "ዲቃላ ወለደች ይላሉ። አለቀ! አንተን ካስደሰተህ ምንም አደርጋለሁ።" አለችኝ። ቆይ ምንድነዉ ልቧን እንደዚህ የሰቀለዉ? መተት አሰራሁባት እንዴ? ራሴን መጠርጠር ጀምሬያለሁ። "ፌቪ ስላሰብሽልኝ አመሰግናለሁ። በዚህ ሰዓት ልጅ መዉለዱ ግን ለኔም ላንቺም ስለማይጠቅም ደግመሽ እንዳትጠይቂኝ!" አልኳት። ፈገግ አለች! ምንም የተጋነነ ዉበት ባይኖራትም የደስ ደስ አላት። ፈገግ እንዳለች "ካልክ እሺ!" አለችኝ። ተሰናብቼያት ወደ አዲሱ ቤቴ ወደነአምሪያ ቤት ሄድኩ። . ዛሬ ወንድሞቿ መጥተዉ ቤቱ ደመቅመቅ ብሏል። ኢስማኢል የሚባለዉ ታላቅ ወንድሟ ገና ስገባ ፈገግ ብሎ ተቀበለኝ። ለቅሶ መጥቶ ጠይቆኝ ነበር። ሁለቱ ሰላሀዲን እና ረመዳን ይባላሉ። ለቅሶ አልመጡም ነበር። ገብቼ ትንሽ እንደቆየሁ ሁለት ሰዓት ሊሆን አካባቢ የ"ኢሻ" ሰላት ለመስገድ ሁሉም ብድግ አሉ። እኔ ብቻ ቁጭ አልኩ። ታላቅ ወንድማቸዉ ኢስማኢል "ሀቢቤ ዉዱዕ የለህም መሰለኝ። እንጠብቅህ ሂደህ አድርገህ ና!!" አለኝ። ዉዱዕ ከስግደት በፊት የሚደረግ ትጥበት ነዉ። ሽክክ አለኝ። አልሰግድም ማለቱ ደግሞ አሳፈረኝ። ተነስቼ ተጣጥቤ ተከተልኳቸዉ። ስግደት ላይ የሚባሉት ዉዳሴዎች ብዙዎቹ ጠፍተዉኛል። ልጅ ሆኜ አባቴ ሳይሞት ከሰገድኩ እስከዛሬ ሰግጄ አላዉቅም። ይኸዉ ነፃነቴን መጋፋት ጀመሩ። የእናቴ ቃል ሆኖብኝ እና የሀጂ ራህመቶ ዉለታ ባይዘኝ አብሬያቸዉ አልኖርም ነበር። ሰግደን እንደጨረስን አምሪያ ምግብ አቀረበች። ምግቡን እያቀራረበች ፈገግ ብላ ታየኛለች። ስሰግድ ስላየች ሙድ እየያዘች መሆኑ ገባኝ። ቆይ ይሂዱ ብቻ የሆነች ተምች የሆነች ልጅ! ምግቡን በልተን እንዳበቃን የኢስማኢል ታናሽ ሰላሀዲን "ሀቢቤ ትምህርትህ ላይ እንዴት ነህ?" አለኝ። ምን ልበለዉ ግራ ገባኝ። ግራ ስጋባ አየኝና "በትምህርትህ የመቀጠል ህልም አለህ ወይስ ሰዉ ስለሚማር ነዉ የምትማረዉ?" አለኝ። የመጣዉ ይምጣ አልኩና "እስከዛሬ የተማርኩት እናቴን ደስ እንዲላት ነበር። ከዚህ በኋላ ባልማር ደስ ይለኛል።" አልኩት። ረመዳን የሚባለዉ ታናሽ ወንድማቸዉ ፈገግ አለና "ካልተመቸህ ካሁኑ የሚጠቅምህ ህይወት ላይ ትኩረት አድርግ።" አለኝ። ከረመዳን ጋር ትንሽ ሙዳችን እየገጠመ ሳይመጣ አልቀረም። ትንሽ ከተጫወቱ በኋላ ሶስቱም ተያይዘዉ ወደየቤታቸዉ ሄዱ። እኔም ከአምሪያ መኝታ ክፍል ጎን ወዳለዉ መኝታ

Watch "ጂጂ ባለ ዋሽንቱ Balewashentu Ejigayehu Shibabaw GiGi እጅጋየሁ ሽባባው" on YouTube https://youtu.be/yB47_0icRgE

🍃🌹🍃....✍ ❤️. . .ፍቅር. . .❤️ ፍቅር ይታገሣል፥ ቸርነትንም ያደርጋል፤ ፍቅር አይቀናም፤ ፍቅር አይመካም፥ አይታበይም፤ : የማይገባውን አያደርግም፥ የራሱንም አይፈልግም፥ አይበሳጭም፥ በደልን አይቆጥርም፤ : ከእውነት ጋር ደስ ይለዋል እንጂ ስለ ዓመፃ ደስ አይለውም፤ : ሁሉን ይታገሣል፥ ሁሉን ያምናል፥ ሁሉን ተስፋ ያደርጋል፥ በሁሉ ይጸናል። : ፍቅር ለዘወትር አይወድቅም፤ ትንቢት ቢሆን ግን ይሻራል፤ ልሳኖች ቢሆኑ ይቀራሉ፤ እውቀትም ቢሆን ይሻራል። ~~~~~~~~~~~~~~~~~~ Join 👉👉👉@achachr

መጥታ አቀፈችኝና ተቀመጠች። ተርባኝ የነበር ይመስላል። እኔ ግን ብዙም ትዝ አላለችኝም። . በነጋታዉ እሮብ እማዬ ድክም አለች። አስሬ መጣራት ጀመረች። መጨረሻ ላይ ድምጿም እየጠፋ መጣ። እኔናአምሪ ከአጠገቧ አንጠፋም። ዛሬ ወ/ሮ ለይላም አብረዉን ናቸዉ። እማዬ ደክማለች። ሀሙስ ጠዋቱን ወደ ሁለት ሰዓት ገደማ እማዬ ፊቷ በላብ ጥምቅ ማለት ጀመረ። እግሮቿ ይፋተጋሉ። ወ/ሮ ለይላና አምሪ ቁርስ አምጥተዉልኝ ከአጠገቧ ተቀምጠዋል። አይናችን እያየ ሰዉነቷ ቀዘቀዘ። አይኖቿ ፈጠጡ። ወ/ሮ ለይላ በእጆቿ የእማዬን አይኖች ከደነቻቸዉ። እንባዬ ልብሴን አጠበዉ። ፈጣሪ ጨካኝ እንደሆነ ተሰማኝ። እንዴት ምድር ላይ ያለ አንዳች ዘመድ ብቻዬን ያስቀረኛል? እንዴት? አምሪያ ወንበሩ ላይ ተቀምጣ ታነባለች። ሀጂ ተደዉሎላቸዉ መጡ። እናቴ ታጥባ በከፈን ተጠቀለለች። ወደ ሰባት ሰዓት ገደማ ተሰግዶባት ተቀበረች። እማዬን ቀብረን ስንመለስ በጣሙን ተስፋ ቆረጥኩ። ፈጣሪን የከለከላቸዉን ነገሮች ሁሉ በመዳፈር ልበቀለዉ ወሰንኩ። እነሚኪ ቤት ተቀምጠዉ ጠበቁኝ። ትንሽ ደስታ የሚሰማኝ እነሱን ሳይ ነዉ። ገና እንዳየኋቸዉ እንባዬ ይባሱን መዉረድ ጀመረ። ወይኔ ሀቢብ! . ይቀጥላል... . ተጨማሪ ልብወለዶችን ለማንበብ ቻናሉን ይቀላቀሉ! 👇 @achachr

የማይፋቅ ስህተት ክፍል12 (ፉአድ ሙና) . እማዬን ከሆስፒታል አዉጥተን ቤት እንዳስተኛናት ሌሎች ጎረቤቶቻችንም እየተመላለሱ መጠየቅ ጀመሩ። ሆስፒታልም መጥተዉ ጠይቀዋል። እኔ ግን ሲጠይቋት አልነበርኩም። ሲጀመርም አባቴ ከሞተ በኋላ ብዙም ከጎረቤቶቻችን ጋር አንቀራረብም። አጥራቸዉን አስረዝመዉ ከመኖር በዘለለ ጉርብትናን በቅጡ የሚረዱ አይደሉም። እድሜ ለነሀጂ እማዬም ቆንጆ ዘመድ አገኘች። እማዬ ቅዳሜ ከሆስፒታል ከወጣች ይኸዉ ዛሬ ማክሰኞ አራተኛዋ ቀን ሆነ። . አምሪያ ሰሞኑን ከኛ ቤት አትጠፋም። ቤቱን ማፅዳት እና ለእማዬ የሚያስፈልጋትን ነገር ማቀራረብ የዘወትር ስራዋ ሆኗል። ዛሬ እንዲህ መድሀኒቴ ልትሆን ነገር ትናንት ለአምሪያ እንጨት እየተማረርኩ የፈለጥኩበት ጊዜ አበሳጨኝ። ዛሬም መኝታ ክፍል እማዬ ከተኛችበት አልጋ ጎን ተቀምጣለች። ሰማያዊ ሂጃብ ጠምጥማለች። ፈገግታዋ ደስ ይላል። ቀኝ እግሯን ግራ እግሯ ላይ ሰቅላዋለች። "ሀቢቤ!" አለችኝ። ድምጿ ደስ ይላል። "ወዬ?" አልኳት። እማዬ እስከአሁን ምግብ በደንብ መብላት ስላልቻለች ከጭንቀቴ የተነሳ ድምፄ ርቆኛል። አምሪያ ትክ ብላ እያየችኝ "ልብስህን ከቀየርከዉ ቆየህ እንዴ? ቆሽሿል እኮ!" አለችኝ። "አዎ ባክሽ ደሞ ሸሚዞቼ እንዳለ ቆሽሸዋል።" አልኳት። ከመቀመጫዋ ብድግ እያለች "በቃ ስጠኝ ልጠባቸዉ!" አለችኝ። "ኧረ አምሪ አይነፋም! ሹራብ ነገር እለብሳለሁ ተይዉ።" አልኳት። ዉለታዋ ሲበዛ ከብዶኛል። ልታዳምጠኝ ፈቃደኛ አልሆነችም። "ባክህ አታካብድ ብዙ አይደለም እኮ!" አለችና ቆሻሻ ልብሶቼን አልጋዉ አጠገብ ያለዉን ቁምሳጥን እየከፈተች መፈለግ ጀመረች። "በቃ እሺ እዛ ዉስጥ ነዉ።" አልኳት የኔ ልብስ ወዳለበት እጄን እየጠቆምኳት። ልብሶቹን እያወጣች ቁምሳጥኑ ጥግ ላይ የተቀመጡትን ፎቶዎች አነሳችና "እነዚህ ደሞ እነማን ናቸዉ?" አለችኝ። ቀና ብዬ ሳይ ፎቶዎቹ የሰላም፣ የሜሮን ፣ የሰሚራ እና የፌቨን ነበሩ። ምላሴ እየተሳሰረ "የትምሮ ቤት ልጆች ናቸዉ።" አልኳት። ቆይ ምን አስደነገጠኝ? አምሪን ለምን ፈራኋት? የሰላምን ፎቶ እያሳየችኝ "ስንት ትምህርት ቤት ነዉ የተማርከዉ? ማለቴ የዚች ልጅ ዩኒፎርምና ያንተ ዩኒፎርም ይለያያል።" አለችኝ። የፈጣሪ ያለህ በጣም አስጨነቀችኝ። ዝም ስላት ልብሶቹን ይዛ ለማጠብ ወጣች። አምሪ እንደወጣች እማዬ በደከመ ድምፅ "ሌላ እናት አገኘህ አይደል?" አለችኝ። አምሪያን ማለቷ ነዉ። ፈገግ ብዬ ዝም አልኳት። . እማዬ አምሪያ ወጥታ ትንሽ እንደቆየች በደከመ ድምፅ ሀጂን እንድጠራላት ጠየቀችኝ። ስራ ስለሆኑ ማታ ቢመጡ እንደሚሻል ብነግራትም አሁን ካልሆነ ብላ ተቆጣች። ከመኝታ ክፍል ወጥቼ ለአምሪያ ነገርኳት። ግቢ ዉስጥ ልብሶቼን እያለቀለቀች ነበር። በረንዳዉ ላይ የተቀመጠዉን ስልኳን እያሳየችኝ "አቢ የሚል ፈልግና ደዉለህ አገናኘኝ።" አለችኝ። አባቷን አቢ ነዉ የምትላቸዉ። ደወልኩና ሲጠራ ጆሮዋ ጋር አስጠግቼ ያዝኩላት። እጇ አረፋ ስለነበር ስልኩን እንዳይነካዉ መሆኑ ነዉ። ስልኩን ይዤላት ስታወራ በትኩረት አያታለሁ። ደስ ስትል። አለ አይደል የሆነ እርጋታዋ፣ የአይኖቿ እንቅስቃሴ ፣ ፈገግታዋ የሆነ ያዝ ሲያደርገኝ ተሰማኝ። ምን እየሆንኩ ነዉ? አምሪያ "አንተ እብድ ልጠብበት አታዝገኝ።" አለችኝ። ለካ እሷ አዉርታ ጨርሳለች። እኔ ስልኩን ጆሮዋ ላይ ለጥፌ ይዤ ፈዝዣለሁ። ደነገጥኩና ስልኩን ከጆሮዋ ላይ እያነሳሁ "እና ምን አሉ?" አልኳት። "አሁን ይመጣል። የሚገርምህ ደሞ ለምሳ እየመጣ ነበር።" አለችኝ። ላግዛት መዘፍዘፊያዉን ወደራሴ ስስበዉ "በአላህ አታዝግ ሂድና ማዘርን አጫዉታቸዉ።" አለችኝ። ለምን እንደሆነ ባላዉቅም አጠገቧ መቀመጥ ፈልጌያለሁ። "ስማ ሂድ! ማዘርን አታስደብራቸዉ!" ብላ ስትኮሳተር ተነስቼ ወደ እማዬ ክፍል ሄድኩ። ወደ እማዬ ክፍል ስገባ በር ተንኳኳ። አምሪ እጇ ላይ ዉሀ አፍስሳ ልትከፍት ስትሄድ የመስኮቱን መጋረጃ ገልጬ አያታለሁ። ከፈተችዉ። እነሚኪ ነበሩ። ሶስቱም እንደሀብታም ልጅ የመዓት ኮተት ምናምን በፌስታል ይዘዉ ገቡ። አብነት አምሪያ ላይ ዉሀ ረጭቶባት አለፈ። አናደደኝ። ለምን ተናደድኩ? "ኧረ ሀቢቤ ተረጋጋ ሲቀልድ እኮ ነዉ!" አልኩት ለራሴ! . ቤት እንደገቡ የያዙትን ኮተት ሳሎን አስገብተዉ ቤቱን ፏ ማድረግ ጀመሩ። ሀቢብ ብለዉ እንኳ አልተጣሩም። ድፍረታቸዉ አንደኛ ደረጃ ነዉ። ከመኝታ ቤት ወጥቼ ወደ ሳሎን ገባሁ። የጁስ መዓት ብስኩቶች ቸኮሌት እና ምግብ ለመስራት የሚያስፈልጉ ነገሮችን ሳይቀር ይዘዉ መጥተዋል። "አራስ ምትጠይቁ መሰላችሁ እንዴ ብስኩት፣ ቸኮሌት ምናምን? ላደጉት ልጆች ነዉ?" አልኳቸዉ። ሚኪ ፈገግ ብሎ እያቀፈኝ "የሸመጠጥካቸዉ ልጆችህ አያታቸዉን ሊጠይቁ ከመጡ ብለን እኮ ነዉ።" አለኝ። እኔ እኮ የሚገርመኝ የሚኪ መልስ ነዉ። ምላሱ ጫፍ ላይ ተቀባብላ የተቀመጠች ነዉ የሚመስለዉ። ትንሽ እንደቆየን አምሪ ልብሶቹን አጥባ ጨርሳ ወደ ቤት መጣች። ካመጡት ቸኮሌት ትልቁን አንስቼ ሰጠኋት። ተቀብላኝ ወደ መኝታ ክፍል ሄደች። ከኔ ጋር ሲሆን ነዉ እንጂ ወንድ ሲበዛ አብራ መቀመጥ አትወድም። የቤቱ በር ሲንኳኳ ልከፍት ወጣሁ። ሀጂ ነበሩ። ሰላም ብለዉኝ ወደቤት ገባን። ሀጂ እነሚኪ እንዲህ ተሰብስበዉ ቤቱን ሲያደምቁት ሲያዩ ደስ አላቸዉ። አብረን ወደ መኝታ ክፍል ገባን። እማዬ ሀጂን ስታያቸዉ ፈገግ እንደማለት አለችና "አምሪ እና ሀቢቤ አንዴ ዉጪ ቆዩ!" አለችን። እኔና አምሪ ተያይተን ፈገግ አልንና ወደ ሳሎን ሄድን። እነሚኪ ያመጡትን ኩኪስ ብስኩት ምናምን ፈትተዉ እያመቻቹ ነዉ። አምሪ ወከባ መፍጠራቸዉ ገርሟት "ማን ሊመጣ ነዉ?" አለችኝ። አብነት ከሪምን እያየ "ዛሬ ልደቱ ነዉ።" ብሎ ሳቀና "ስቀልድ ነዉ የትምሮ ቤት ልጆች ሊጠይቁ ሊመጡ ነዉ። ለዛ ነዉ የምንሯሯጠዉ!" አላት። አምሪ ፈገግ አለችና "ኦኬ ፎቶዉ ላይ ያሉት ልጆች?" አለች። ነገር ትበላለች። ሳቅኩና ፈገግ ብዬ "ኧረ በቃ አምሪ ፍቺ!" አልኳት። . ሀጂ ራህመቶ ከእማዬ ጋር አዉርተዉ ጨረሱ መሰለኝ ጠሩኝ። እኔን መኝታ ክፍል አስገብተዉ በሩን ዘጉት። እማዬ አየችኝና እያቃሰተች "ሀቢቤ ዛሬ በደንብ አዳምጠኝ!" አለችኝ። ዝም ብዬ አያታለሁ። ቀጠለች "ሀቢቤ እኔ አዝዤህ አንድም ቀን እንቢ ብለኸኝ አታዉቅም። እንዳከበርከኝ አላህ ክብር ያድርግህ። አሁን ግን እኔ ባልኖር ሀጂ እንደ አባትህ ናቸዉ። እኔን እንደምትታዘዘዉ ታዘዛቸዉ። ገደል ግባ ቢሉህ እንኳ እሺ በል። ያኔ እኔ እደሰታለሁ።" አለችኝ። ንግግሯ የስንብት ይመስላል። እንባ ከአይኖቼ ያለማቋረጥ ፈሰሰ። መንሰቅሰቅ ጀመርኩ። ሀጂ አቅፈዉ አባበሉኝ። ስረጋጋ የእማዬን እጅ ጭምቅ አድርጌ ይዤ "እማዬ አንቺ አዘሽኝ የማልቀበለዉ የለም።" አልኳት። እማዬ ፈገግ አለች። ፈገግታ ደስታ ነዉ? ፈገግታ ምንድነዉ? ፈገግታ ስንብት ይሆን እንዴ? ጨነቀኝ። ከመኝታ ቤት እንደወጣን ሀጂ ፈገግ ብለዉ ከቀረበዉ ላይ አንድ ብስኩት አንስተዉ እየበሉ ከቤት ወጡ። ልክ ሀጂ እንደወጡ አብነት እየተገረመ "ባለአጥሯ ግን አባትሽ ሙድ አላቸዉ።" አለ። ባለአጥሯ የሚላት አምሪያ ጥርሷ በሽቦ ስለታጠረ ነዉ። ሀጂ ወጥተዉ ትንሽ እንደቆየን ፌቪ ከጓደኞቿ ጋር ሆና መጣች። መኝታ ቤት ገብተዉ እማዬን ጠይቀዋት ሳሎን ተቀመጡ። ለካ ሚኪ የትምሮ ቤት ልጆች ያለዉ ላለማስጠቆር ብሎ ነዉ። አምሪ ፌቨንን አየቻትና "ፎቶ ላይ ያየኋት ናት አይደል?" አለችኝ። ፈገግ ብዬ "አዎ" አልኳት። እኛን ሳሎን ትታን ወደ መኝታ ክፍል ገባች። ፌቪ ልክ አምሪያ ስትወጣ

🌼መስቀል በዐል ስጦታ ከ ፈረስ ትራንስፖርት 🌼 እስከመስከረም 17 የሚቆይ ለ ቴሌግራም ቻናላችን ተከታይዎች! ባልነው መሰረት የያጋሩና ይሸለሙ ውድድር አሸናፊዎቻችን በአስገራሚ ስጦታዎች ለመሸለም
🌼መስቀል በዐል ስጦታ ከ ፈረስ ትራንስፖርት 🌼 እስከመስከረም 17 የሚቆይ ለ ቴሌግራም ቻናላችን ተከታይዎች! ባልነው መሰረት የያጋሩና ይሸለሙ ውድድር አሸናፊዎቻችን በአስገራሚ ስጦታዎች ለመሸለም ተዘጋጅተናል! የእንኳን ደስ አላችሁ ፈረስ ትራንስፖርት 🐎🐎 ያስተውሉ ዕጩ ለመሆን መጀመርያ በጥንቃቄ ያንብቡ ‼️ለመሸለም ይህንን መንገድ ተከተሉ 1.መጀመርያ ከታች ባለው ማስፈንጠርያ የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇👇 https://t.me/joinchat/AAAAAFM40mvWLXZ9U-nbUg 🌻1ኛ ሽልማት ለ500 ወዳጅ ዘመድዎ ይህን መልክት ሼር ካረጉ 50,0000 ብር አሸናፊ ይሆናሉ!!👇👇 https://t.me/joinchat/AAAAAFM40mvWLXZ9U-nbUg 🌻2ኛ ሽልማት ለ200 ወዳጅ ዘመድዎ ይህን መልክት ሼር ካረጉ 30,0000 ብር አሸናፊ ይሆናሉ!!👇👇👇 https://t.me/joinchat/AAAAAFM40mvWLXZ9U-nbUg 🌻3ኛ ሽልማት ለ100 ወዳጅ ዘመድዎ ይህን መልክት ሼር ካረጉ 20,0000ብር አሸናፊ ይሆናሉ 👇👇👇👇👇👇https://t.me/joinchat/AAAAAFM40mvWLXZ9U-nbUg 🌻4ኛ ሽልማት ለ50 ወዳጅ ዘመድዎ ይህን መልክት ሼር ካረጉ 10,0000 ብር አሸናፊ ይሆናሉ!!👇👇 https://t.me/joinchat/AAAAAFM40mvWLXZ9U-nbUg 🌻5ኛ ሽልማት ለ25 ወዳጅ ዘመድዎ ይህን መልክት ሼር ካረጉ 50000 ብር አሸናፊ https://t.me/joinchat/AAAAAFM40mvWLXZ9U-nbUg ቤቶ በመሆን ሀብታም ይሁኑ ለ ወዳጅ ዘመድዎ ይህን መልክት ሼር በማረግ የገንዘብ ተሸላሚ ይሁኑ!!!!👇👇 @feresappse https://t.me/joinchat/AAAAAFM40mvWLXZ9U-nbUg ፈረስ ያደርሳል!🐎

ሁን እደዉልለታለሁ።" አለቻት። ሀጂን አንተ ስትላቸዉ ልደነግጥ አልኩና ትዝ ሲለኝ ለካ አባቷ ናቸዉ። ዶ/ር ቀመሪያ ስልኳን አየችና "አሁን ኦሬዲ ኢትስ ኤይት በቃ ቴን ሰርቲ ላይ ቢሮ ይምጡ!" አለች። ምናልባት ከክፍያ ጋር የተያያዘ ከሆነ ስምንትሺህ ብሩን ሀጂ አልቀበልም ስላሉን እግረመንገዴን ለመክፈል በማሰብ "ምነዉ ግዴታ እሳቸዉ የሚያስፈልጉበት ነዉ? እኔ መምጣት አልችልም?" አልኳት። ከነርሷ ጋር ሆነዉ ከክፍሉ እየወጡ "ኖ እሳቸዉን ፐርፐዝሊ ስለፈለግኳቸዉ ነዉ።" አለች። አምሪ ለሀጂ ደዉላ ነገረቻቸዉ። አስር ከሩብ አካባቢ መጡ። ከሪሜ ዛሬ አብሮኝ ስለሚያድር ቤት ልብስ ቀይሮ ሊመጣ ሄደ። ሀጂ ዶክተሯ ቢሮ ቆይተዉ ከመጡ በኋላ ፈገግ ብለዉ "ኢንሻአላህ ነገ ወደ ቤት እንወስዳቸዋለን።" አሉኝ። ደስ አለኝ። ቢያንስ የእነ ሀጂ እንግልት ይቀንሳል። ለእማዬም ቤት መሆኗ ይሻላታል። ቢያንስ እንደተሻላት ይሰማታል። . በነጋታዉ ጠዋቱን ከከሪሜና አብነት ጋር ተቀምጠን እያወራን ፌቪ ሶደሬ አብረን ከሄድናቸዉ ጓደኞቿ ጋር ሆና መጣች። ገብተዉ እናቴን ጠይቀዋት እንደወጣን ጓደኞቿ ቀደም ብለዉን ሲሄዱ ፌቪ ጥምጥም አለችብኝና ከንፈሬን ሳመችኝ። እኔ እንኳ ለእንደዚህ አይነት ነገር ያለኝ ስሜት ወርዷል። ግን እንዳይደብራት በሚል በወጉ አስተናገድኳት። ሆስፒታል ዉስጥ የተሳሳሙ ብቸኛ እብዶች ሳንሆን አንቀርም። አይን አይኔን እያየች "ሀቢቤ ሁሉም ይስተካከላል አይዞን እሺ!" አለችኝ። . እነፌቪ ሄደዉ ትንሽ እንደቆየን ሀጂ እና ወ/ሮ ለይላ መጡ። ዶ/ር እስከምትገባ ትንሽ ጠበቅንና ያለዉን ነገር ጨራርሰን እማዬን ወደቤት ይዘናት ሄድን። እማዬ ዉሀ ነገር ካለዉ ከረጢት በመርፌ ወደ ሰዉነቷ እንደተሰካላት ነዉ። ዶ/ር ቀመሪያ አየችኝና "ሀቢቤ ችግር ካለ ደዉልልኝ" ብላ ስልኳን ሰጠችኝ። እማዬን ወደቤት እየወሰድናት ሚኪ ደወለልኝ። "ሀቢቤ እናትህ ይሻላቸዉ እንጂ ሀብታም ሆነናል።" አለኝ። ያዉ የፈረደበት ከአረብ ሀገር ሴቶች የተነጨ ብር ተገኝቶ ነዉ። በልቤ "እማ ይሻላት እንጂማ የኔዎቹንም አልባቸዋለሁ" አልኩ። እነሀጂ እንዳይገባቸዉ እየተጠነቀቅኩ "ቆይ ስንት ታዝኖ ነዉ?" አልኩት። "በኔ በኩል አምስት ሺ በከሪሜ ደሞ ሰባት ሺህ!" አለኝ። ተሰናብቼዉ ስልኩን ዘጋሁት። ይሄ ቢዝነስ እያጓጓኝ ነዉ። ቆይ ብቻ እማዬ ይሻላት። ቤት ስንደርስ አምሪ ቤታችንን ፏ አድርጋዉ እየጠበቀችን ነበር። ፈጣሪ መልዓክ ማዉረድ አይጠበቅበትም እኮ! የሰዉ መልአክ ምድር ላይ አለ። ደስ ሲሉ የሚያስቀና ቤተሰብ! . ይቀጥላል... . @achachr

የማይፋቅ ስህተት ክፍል 11 (ፉአድ ሙና) . በህይወት ዉስጥ ምንም አይነት መደነቃቀፍ ባይኖር ኖሮ የሰዉ ልጅ አምላክ መሆኑን የሚጠረጥር ይመስለኛል። አንድም ቀን እንደዚህ ይጨንቀኛል ብዬ ገምቼ አላዉቅም። እናቴ ሁሉንም ቀዳዳዎቼን ሸፍና አንደላቃኝ ነበር። ዛሬ ግን እናቴ መተማመኛ እንደማትሆነኝ ሊያሳየኝ ሲፈልግ ንቁዋ እናቴን ድንዝዝ አድርጎ ከአልጋ አጋደማት። አሁን ከእናቴ ዉጪ ዞር ብዬ አይቼዉ የማላዉቀዉን ጌታ እየተማፀንኩት ነዉ። ችግር ሲጨመድደን ትናንት ዞር ብለን ያላየነዉን አምላክ ከመማፀን በቀር ምን አማራጭ አለ? ምንም! . ማክሰኞ ጠዋቱን እማዬን ከተኛችበት የሆስፒታል አልጋ ላይ እንደተጋደመች ክፍሉ ዉስጥ ካለዉ የኦክስጅን ሳጥን ጎን ተቀምጬ አያታለሁ። እማዬ ፊቷ ሙሉ ለሙሉ ወደ ቢጫነት ተቀይሯል። ፈጣሪ ግን ምነዉ አለ? ያለአባት በመከራ ያሳደገችኝን እናቴን ለምን ያሰቃይብኛል? ለነገሩ ጉልበተኛ ነኝ አይደል የሚለዉ እንዳሻዉ! ብቻ ዝም ብዬ እናቴን አያታለሁ። ያላደላት ሚስኪን ፍጡር! አብነት እንቅልፍ በዘጋዉ ጎርናና ድምፅ "ስማ ቁርስ አያመጡልንም እንዴ?" አለ። ማታ አብረን ያደርነዉ እኔናአብነት ነበርን። ቀና ብዬ የተቀመጠበትን ነጭ ባለስፖንጅ ወንበር የእጅ መደገፊያ እያየሁ "አንተ አስታዉሰኸዉ እነሱ የሚረሱት ይመስልሀል?" አልኩት። አብነት ሳቁን ለቀቀዉና "ኧረ ባክህ? ፈጣሪህን ይህን ያህል ብታምነዉ ወርቅ ከሰማይ ያዘንብልህ ነበር።" አለኝ። ዉስጤ ላይ ብሶቴ እየተቀጣጠለ "ባክህ እሱ መከራ ያዝንብ ተወዉ!" አልኩ። እኔና አብነት እየተጨዋወትን ብዙም ሳንቆይ አምሪያ የክፍሉን በር ከፍታ ገባች። በእጇ ሰማያዊ ዘንቢል አንጠልጥላለች። አብነትን ዞር ብዬ አየሁትና ሳቅኩ። አምሪያ በሩን ዘግታ ወደኛ እየዞረች "ምን ያስቅሀል? ለነገሩ ሲጀማምር እንደዚህ እኮ ነዉ።" አለች። አብነት ወዲያዉ ዘንቢሉን ተቀብሎ ምግቡን ማቀራረብ ጀመረ። እንደሆዱ የሚያፈቅረዉ ነገር ያለ አይመስለኝም። አምሪያ ከእማዬ አጠገብ ያለዉ ወንበር ላይ እየተቀመጠች "ሀቢቤ አሁንም ምግብ መዉሰድ አልጀመሩም?" አለችኝ። "አዎ ባክሽ ግልኮስ ነዉ የያዛት! ምንም አላማረኝም።" አልኳት። እማዬ በሲቃ በታጀበ ድምፅ "ተዉ ሀቢቤ እንደሱ አይባልም። ፈጣሪ አለ።" አለችኝ። እማዬ መናገር ተራራ ከመግፋት እየከበዳት መጥቷል። እንደዉም ዛሬ ትንሽ አነጋገሯም ተስተካክሏል። አይ እማዬ ፈጣሪ አለ ነዉ ያለችዉ? ፈጣሪማ ለማሰቃየት ሲሆን መች ይጠፋል!? አብነት ምግቡን አቀራርቦ ሲጨርስ አምሪያን "ባለአጥሯ ነይ እንብላ!" አላት። ሳቅኩኝና ወደ አብነት ተጠጋሁ። አምሪን በአንገቴ ነይ ስላት ወንበሯን ይዛ ከኛ ጋር ተቀመጠች። አብነት ገና እጁን ወደ ምግቡ ሲሰነዝር አምሪያ "ወይኔ ስጋ ነዉ እንደዛኛዉ ልጅ ነህ አይደብርህም አይደል?" አለች። እንደዛኛዉ ልጅ ያለችዉ ሚኪያስን ነዉ። አብነት የጠቀለለዉን እየጎረሰ "በፈጣሪ ስም ነዉ የታረደዉ አይደል እንዴ? በእግዚአብሔር ይሁን በአላህ እነሱ ይስማሙበት። የኔ ሀላፊነት መብላት ነዉ።" አለ። እኛ አንድም ቀን የሙስሊም የክርስቲያን ስጋ ብለን ለይተን በልተን አናዉቅም። ያገኘነዉን ማተራመስ ነዉ። አምሪያ የአብነት ንግግር ስቅጥጥ እያላት "አይ እምነት እንኳ እንዲህ ድንበር የሚታለፍበት ጉዳይ አይደለም። ማንነትህን በደንብ የምትረዳዉ ስታከብረዉ ነዉ።" አለች። አየር ስለያዙብኝ እየበሸቅኩ "ይቅርታ እንብላበት!" አልኩ። "እሺ እጃችሁን አትታጠቡም? ከመድሀኒት ጋር አድራችሁ?" አለች። "አምሪ ኧረ ምንም አንሆንም ይኸዉ ሀያ አመት ሊሞላኝ ነዉ አንድም ቀን ታጥቤ አላዉቅም። ምን ሆንኩ?" አልኳት። ካልታጠባችሁ አልበላም ብላ ስታሸማቀን ተነስተን ታጠብንና መብላት ጀመርን። አብነት የአምሪያን ፊት የሚያክል ጉርሻ ጠቅልሎ ላጉርስሽ ሲላት ከአይኗ እንባ እስከሚፈስ ድረስ ሳቀች። በመሀል እማዬ እያየችን ፈገግ ስትል አየኋት። ወደሷ ስዞር "ሀቢቤ ለሴት ልጅ የሚሆን ጉርሻ በመጠኑ አጉርሳት!" አለችኝ። እማዬ ብላኝ እንቢ ብዬ አላዉቅም። አጎረስኳት። አምሪ መጉረስ አልፈለገችም ነበር ግን እማዬን ላለማስከፋት ብላ ጎርሳልኝ ፈገግ አለች። . አምሪያ ከሄደች በኋላ የክፍል ተማሪዎች እየተንጋጉ ሆስፒታሉን ወረሩት። የኢምባሲ በር ጋር ተቃዉሞ የወጡ እንጂ በሽተኛ ሊጠይቁ የመጡ አይመስሉም። እየመሯቸዉ የመጡት ሚኪያስናከሪሜ ናቸዉ። አምስት አምስት እየሆኑ እየገቡ እናቴን አይተዋት ወጡ። እኔም እናቴም በጣም ደስ ብሎናል። ሆስፒታሉ ዉስጥ ግርግር ላለመፍጠር ብለን ግቢዉ ዉስጥ ወርደን ማዉራት ጀመርን። ሀብታሙ እንባ እየተናነቀዉ "ሀቢቤ አብሽር እሺ ለፈተና እንዳታስብ እኔ አለሁልህ።" አለኝ። ሀብታሙ እና እኔ እኮ በወጉ እንኳ ክፍል ወስጥ አዉርተን አናዉቅም። ብቻ ሀበሻ በችግር ሰዓት መልዓክ ካልሆንኩ የሚል ሚስኪን ፍጡር ይመስለኛል። ፈገግ ብዬ አየሁት። ሴቶቹ በየተራ ምግብ ካላመላለስን አሉ። እኔ ግን ምንም የምግብ ችግር ስለሌለ እንዳይለፉ ነገርኳቸዉ። ብቻ ብቅ እያሉ እንደሚጠይቁ ነግረዉን ነገ ለፈተና እንዳላረፍድ አስጠንቅቀዉኝ ሄዱ። ሰብስበዉ የሰጡኝን ብር ደስ እንዲላቸዉ ብዬ ተቀብያቸዋለሁ። . ማታዉን ወ/ሮ ለይላ መጥተዉ እማዬን በደንብ ፈታ አደረጓት። ሀጂ ቀጣዩን ሶስት ቀን ፈተና መሆኔን ስለተረዱ ለሊት ስድስት ሰዓት ድረስ እየተኙ የቀረዉን ለሊት አምሪያን ሆስፒታል አድርሰዉ እኛን ወደቤት መልሰዉን ከአምሪያ ጋር እማዬን ሲጠብቁ ለማደር አሰቡና አማከሩን። ምንም ቢከብደንም አማራጭ ስላልነበረን ተቀበልነዉ። ፈተናዉ ተጀመረ። የረቡዕ እለትን ሙሉ ፈተና የሰራልኝ ሀብታሙ ነበር። ትምህርት ብቻ ሳይሆን ማስኮረጅም አንደኛ ነዉ። ሀሙስ ጠዋት ወደ ፈተና ልገባ ስል ሁለት ሀይማኖተኛ ሀይማኖተኛ የሚሰራራቸዉ የግቢያችን ልጆች አገኙኝና "ሀቢብ አሁንስ የትም ብትዘል የማታመልጠዉ አምላክ መኖሩ ገባህ?" አሉኝ። ሸምድደዉት የመጡ እስከሚመስለኝ ድረስ ሁለቱም ደጋገሙልኝ። ዉስጤ በጣም ቆስሏል። ሌላ ጊዜ ቢሆን አንስቼ አፈርጣቸዉ ነበር። አሁን ግን ቅስሜ ስብር ስላለ ትቻቸዉ ሄድኩ። ምን ራሳቸዉን የፈጣሪ መልአክተኛ ያስመስላሉ? የሆኑ አመዳሞች። . እማዬ ከሆስፒታል መዉጣት የነበረባት እነሚኪ በነገሩኝ መሰረት ከሆነ ማክሰኞ ወይም ረቡዕ ነበር። ግን ምግብ ስለማትወስድ ትንሽ ትቆይ ብለዉ እስከአሁን አልወጣችም። ፌቪዬ በቀን ከአስሬ በላይ የምትደዉልበት ጊዜ ሁሉ አለ። እማዬን ለማሳየት ምቹ ጊዜ አላገኘሁላትም እንጂ አስጎበኛት ነበር። ወይ እንደክፍል ልጆች ሰብሰብ ብለዉ ቢመጡ ያመች ነበር። ለነገሩ ነግሬያት ቅዳሜ ትምህርት ቀርተዉ ከጓደኞቿ ጋር እንደሚመጡ ነግራኛለች። የግል ስለምትማር ቅዳሜም ቀኑን ሙሉ ትምህርት አላቸዉ። ቀኑ እየቆጠረ ሄዶ አርብ ደረሰና ፈተና ጨረስን። እኔ እኮ ባልማርም ግድ የለኝም። የምማረዉ እማዬን ደስ እንዲላት ብዬ ነዉ። . አርብ ከፈተና መልስ አራታችንም ተሰብስበን ወደ ሆስፒታል ሄድን። ልክ ስንደርስ እናቴ የተኛችበት አልጋ አጠገብ ዶክተሯ እና አምሪያ አብረዉ ቆመዋል። ነርሷ በተቃራኒ አቅጣጫ በኩል ቆማ ዶክተሯ የምትነግራትን ትመዘግባለች። እንደገባን ዶ/ር ቀመሪያ ፈገግ እያለች "ሄይ ሀቢብ" አለች። እየሳቅኩ "እሺ ዶ/ር አለሽ ግን?" አልኳት። "አለሁ ባክህ አንተ መች ትገኝና ነዉ ሰሞኑን ኤግዛም ቢዚ አድርጎሀል አሉ።" አለችኝ። ስታወራኝ የታካሚዋ ልጅ ሳልሆን ጓደኛዋ ነዉ የምመስለዉ። እማዬን አይታ ስትጨርስ "ሀጂ መች ነዉ ሚመጡት?" አለችኝ። አምሪያ "ከፈለግሽዉ አ

🌼መስቀል በዐል ስጦታ ከ ፈረስ ትራንስፖርት 🌼 እስከመስከረም 17 የሚቆይ ለ ቴሌግራም ቻናላችን ተከታይዎች! ባልነው መሰረት የያጋሩና ይሸለሙ ውድድር አሸናፊዎቻችን በአስገራሚ ስጦታዎች ለመሸለም
🌼መስቀል በዐል ስጦታ ከ ፈረስ ትራንስፖርት 🌼 እስከመስከረም 17 የሚቆይ ለ ቴሌግራም ቻናላችን ተከታይዎች! ባልነው መሰረት የያጋሩና ይሸለሙ ውድድር አሸናፊዎቻችን በአስገራሚ ስጦታዎች ለመሸለም ተዘጋጅተናል! የእንኳን ደስ አላችሁ ፈረስ ትራንስፖርት 🐎🐎 ያስተውሉ ዕጩ ለመሆን መጀመርያ በጥንቃቄ ያንብቡ ‼️ለመሸለም ይህንን መንገድ ተከተሉ 1.መጀመርያ ከታች ባለው ማስፈንጠርያ የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇👇 https://t.me/joinchat/AAAAAFM40mvWLXZ9U-nbUg 🌻1ኛ ሽልማት ለ500 ወዳጅ ዘመድዎ ይህን መልክት ሼር ካረጉ 50,0000 ብር አሸናፊ ይሆናሉ!!👇👇 https://t.me/joinchat/AAAAAFM40mvWLXZ9U-nbUg 🌻2ኛ ሽልማት ለ200 ወዳጅ ዘመድዎ ይህን መልክት ሼር ካረጉ 30,0000 ብር አሸናፊ ይሆናሉ!!👇👇👇 https://t.me/joinchat/AAAAAFM40mvWLXZ9U-nbUg 🌻3ኛ ሽልማት ለ100 ወዳጅ ዘመድዎ ይህን መልክት ሼር ካረጉ 20,0000ብር አሸናፊ ይሆናሉ 👇👇👇👇👇👇https://t.me/joinchat/AAAAAFM40mvWLXZ9U-nbUg 🌻4ኛ ሽልማት ለ50 ወዳጅ ዘመድዎ ይህን መልክት ሼር ካረጉ 10,0000 ብር አሸናፊ ይሆናሉ!!👇👇 https://t.me/joinchat/AAAAAFM40mvWLXZ9U-nbUg 🌻5ኛ ሽልማት ለ25 ወዳጅ ዘመድዎ ይህን መልክት ሼር ካረጉ 50000 ብር አሸናፊ https://t.me/joinchat/AAAAAFM40mvWLXZ9U-nbUg ቤቶ በመሆን ሀብታም ይሁኑ ለ ወዳጅ ዘመድዎ ይህን መልክት ሼር በማረግ የገንዘብ ተሸላሚ ይሁኑ!!!!👇👇 @feresappse https://t.me/joinchat/AAAAAFM40mvWLXZ9U-nbUg ፈረስ ያደርሳል!🐎

​​​​. ♥️✿የማይፋቅ ስህተት✿♥️ ♥️ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ♥️ ●▬ተከታታይ ልቦለድ▬● #ክፍል_10 ...🖍ግን ሀቢቤ ስደዉል ስልክ አንሳልኝ እሺ!" አለችኝ። እሺ ብያት ተሰነባበትን። . ሆስፒታል ስደርስ ሀጂ እና ሚኪ እማዬ የተኛችበት ክፍል ዉስጥ ተቀምጠዋል። እማዬ ነቅታለች። የሆነ የሆነ ነገር ተሰካክቶላት ተጋድማለች። መናገር ምናምን ግን አልጀመረችም። ሳያት የማላዉቀዉ ስሜት ዉርር አደረገኝ። ወዲያዉ ግንባሯን ሳምኩና ከነሚኪ ጋር ተቀመጥኩ። ወዲያዉ ሀጂ ፈገግ ብለዉ "ዶክተሯ ነገ ይወጣሉ ብላለች።" አሉኝ። በጣም ደስ አለኝ። እማዬ እንደዚህ በአጭር ቀን ከሆስፒታል ትወጣለች ብዬ አልገመትኩም ነበር። "እና ዉጤቷን ነገሯችሁ?" አልኩ በጉጉት የሚሉትን ለመስማት እየጠበቅኩ። ሚኪ ወዲያዉ ፈጠን ብሎ "አዎ ነገሩን ደህና ናት ነገ በጣም ከበዛ ከነገ ወዲያ ወደ ቤት እንወስዳቸዋለን።" አለኝ። ሚኪ ደግሞ ሌላ አንድ ቀን ልትቆይ እንደምትችል አረዳኝ። ቢሆንም ጠብቄዉ ከነበረዉ የተሻለ ነገር ነበር። . ከከሰዓቱን አብነት እና ከሪም ወደ ሆስፒታል መጡ። ስገምት ሚኪ ነግሯቸዉ መሆን አለበት። አብነት እያቀፈኝ "አብሽር ሀቢባችን ይሻላቸዋል እሺ!" አለኝ። ከሪሜ አይኔን ማየት እየከበደ ዉ ሰላም አለኝ። እናቴን አይተዋት ካለችበት ክፍል እየወጣን አብነት "ሀቢቤ መላ ከየት አግኝተህ ነዉ እዚህ ያስተኛሀቸዉ?" አለኝ። ሚኪ ፀጉሩን እየጠቀለለ "ባክህ አንድ መልዓክ የሆኑ ሰዉዬ ናቸዉ የተሯሯጡለት አሁን ስራ ቦታቸዉ ላይ አንድ አንድ ነገሮችን ለማስተካከል ሄደዉ ነዉ።" አለ። አይን አይኔን እያየ "እግዚአብሔር ይጠብቃቸዉ። የእዉነት በጣም ጥሩ ሰዉ ናቸዉ። ግን ማናቸዉ?" አለኝ። ከሪሜ ዝም ማለቱ ገርሞኝ እያየሁት "የአምሪያ ፋዘር ናቸዉ። ያቺ ጎረቤታችን" አልኩ። ሚኪ ከሪምን እያየዉ "አንተ ደሞ ምናባህ ነዉ የምትቆዝመዉ?" አለዉ። ከሪሜ ፈገግ ለማለት እየሞከረ "ኧረ አልቆዘምኩም!" አለ። የሆነ ጭንቀታም ነገር ነዉ። በኔ ቦታ ቢሆን ምን ሊሆን እንደሚችል አስቤ ገረመኝ። ወዲያዉ አብነት ከኪሱ ዉስጥ መቶ መቶ ብሮችን አዉጥቶ እየሰጠኝ "ይኸዉ ሀቢቤ ሰዉየዉን ብዙ ብር ከምናስወጣቸዉ ቢያንስ ልጅቷ የላከችልኝን ስምንት ሺህ ብር እናግዛቸዉ።" አለኝ። ወዲያዉ ምን ብሎ ልጅቷን ብር እንዳስላካት ትዝ ብሎኝ እየበሸቅኩ "ስማ አንተ ጀዝባ ያንተ ሟርት ነዉ ይኸዉ እናቴን ቀዶ ጥገና ላሰራበት ብለህ ብር አስልከህ እናቴን ቀዶ ጥገና አስገባሀት። ወደዛ ዉሰድልኝ አልፈልገዉም!" አልኩት። አብነት እንደመለማመጥ እያደረገዉ "ሀቢቤ ታዉቃለህ እኔ ጋር ከሆነ ለረባ ነገር አንጠቀምበትም ስለዚህ ልጅቷም ትፅደቅበት ደሞ ጓደኝነታችን ለመቼ ነዉ?" አለ። ሚኪ ብሩን እየተቀበለዉ "ዝም በለዉ ባክህ!" አለና ወደኔ እየዞረ "ሰዉየዉ አባትህ መሰለህ እንዴ? ቢያንስ ይህቺን ብር ሰጥተን ልናግዛቸዉ ይገባል።" አለ። በርግጥ ሚኪ ልክ ነዉ። ሀጂ ብዙ ብር ነበር ያወጡት። ወዲያዉ ከሪሜ "በነገራችን ላይ ፋይናል እሮብ ይጀመራል። ማስታወቂያ ተለጥፏል።" አለን። "ዛሬ ቀኑ ምንድነዉ?" አልኩ ወደ ከሪሜ እየዞርኩ። ከሪሜ "ዛሬ ሰኞ ነዉ ፈተናዉ ከነገ ወዲያ ነዉ።" አለ። ሚኪ "ባክህ አሽቅ የለዉም እኛ እንደሆነ አናጠናም ያዉ ከሪሜ ቸክይና ከቀለሞቹ ጋር እያዋዛን እንሰራዋለን።" አለ። . ትንሽ እንደቆየን አምሪያ እና ወ/ሮ ለይላ መጡ። አምሪያ በእጇ ዘንቢል ይዛለች። አጠገባችን ሲደርሱ ወ/ሮ ለይላ ፈገግ ብለዉ "ሀቢቤ ሽኩሪያዬ የት ናት?" አሉኝ። ፈገግ ብዬ ወደ ዉስጥ ይዣቸዉ ገባሁ። አምሪያ ዘንቢሉን ለሚኪ ሰጠችዉ። ወ/ሮ ለይላ ቁጭ ብለዉ ትንሽ ካወሩን በኋላ ከመቀመጫቸዉ እየተነሱ "ምሳችሁን አምጥቼላችኋለሁ። አደራ በደንብ ብሉ። ወደ ማታ ብቅ እላለሁ።" አሉን። ወዲያዉ አምሪያን እያየሁ "አምሪ ግን ወደ ማታ መምጣት ትችይ ነበር ትምህርት ለምን ቀረሽ?" አልኳት። አምሪ ሳቀችና በከንፈሯ ጥርሷን ያጠረዉን ሽቦ ለመከለል እየሞከረች "ሀቢቤ ባለፈዉ አርብ እኮ ኢንትራንስ ወሰድን ረሳኸዉ እንዴ አስራሁለት ነኝ እኮ ጨርሰናል።" አለችኝ። ዉይ ሶደሬ ፈተና ጨርሳ ዘና ልትል እንደተገናኘን ትዝ አለኝና "እንዴ ለካ ..." ብዬ ልቀጥል ስል አምሪያ አቋርጣኝ "ለካ አስራሁለተኛ ክፍል ነኝ።" አለች። እኔ ሶደሬ ተገናኝተን ነበር ልል ነበር። እንዴት እንዳወቀች እኔንጃ! ደሞ ለማንም እንዳልናገር አስጠንቅቃኝ ነበር። ወዲያዉ አምሪ እና ወ/ሮ ለይላ ተነስተዉ ወጡ። እነሱ እንደሄዱ ሚኪ ምግቡን አዘገጃጀና ለአራት አጣደፍነዉ። . ወደ አመሻሹ አስራ አንድ ሰዓት ሲሆን ፌቪ ደወለችልኝ። ስልኩን አንስቼ ሆስፒታሉ የት እንደሆነ ነገርኳት። ስትደርስ ምልክት አደረገችልኝና ወጥቼ አገኘኋት። ከትምህርት ቤት በቀጥታ ነበር የመጣችዉ ዩኒፎርሟን እንደለበሰች ናት። ገና አጠገቧ ስደርስ "የኔ ጌታ!" ብላ ተጠመጠመችብኝ። የሸሚዜን ኮሌታ ይዛ "ሀቢቤ አሁን ማማ እንዴት ናቸዉ?" አለችኝ። "ደህና ናት ማታ ኦፕራሲዮን ተደርጋ ነበር። አሁን እንደ መንቃት ብላለች።" አልኳት። ፈገግ ለማለት ሞከረችና ከቦርሳዋ ዉስጥ አንድ እሽግ ብር እያወጣች "ይኸዉ ሀቢቤ ለአንዳንድ ነገር ይሆናቸዋል። ብራዘር ለአንዳንድ ነገር የላከልኝ ነዉ እትጨነቅ።" አለችኝ። ፈገግ ብዬ ስለ ሀጂ ራህመቶ ተረኩላት። ገንዘቡ ለጊዜዉ ስለማያስፈልገኝ እንደማልቀበላት ነገርኳት። ሲያስፈልገኝ ልቀበላት ቃል አስገብታኝ ተለያየን። ሌላ ጊዜ ቢሆን እንዴት ሰፍ ብዬ ብሩን እንደምቀበላት አስቤ ገረመኝ። ሀዘን ትንሽ ስርዓት ያስይዛል። . ማታዉን ሀጂ ራህመቶ መጡ። ትናንት ማታ ስላልተኙ ዛሬ ቤት ሄደዉ እንዲተኙ አስገደድናቸዉ። አብነት እና እኔ አደርን። ሚኪ እና ከሪሜ ወደ ቤት ሄዱ። ትናንት ያሻትን በማድረግ ስትደሰት የነበረችዉ ነብሳችን በሀዘን ተሸምቅቃ አደብ ገዝታለች።... #ይቀጥላል... ❥..................🍃⚘🍃...................❥ 🌳ከወደዱት ሼር ያድርጉ🌳 ,,,,,🌹❣🌹❣🌹❣🌹,,,,, ••●◉Join us share◉●•• @achachr

መልካም ጓደኛ ምረጥ‼ ================ ✍ መልካም ጓደኛ ከያዝክ፤ ስትሳሳት ያርምሀል። መልካም ወደ መሥራት ይመራሀል። ጧት ማታ ዚክር ሲያደርግ፤ አንተም አብረህ ታደርጋለህ። ለጀማዓ ሰላት ወደ መስጅድ ሲሄድ ስታይ አብረህ ትሄዳለህ። ቁርኣን ሲቀራ ትቀራለህ። * በተቃራኒው መጥፎ ጓደኛ ከያዝክ ግን፤ ወደ ጀማዓ ሰላት ልትሄድ ስትል "እባክህን ከቤትህ ውስጥ ስገድና ወደ መዝናኛ እንሂድ፣ ኳስ እንዳያልፈን እንመልከት፣ ሙዚቃ እናዳምጥ፣ ፊልም ወይም ድራማ እንመልከት… ወዘተ" ይልሀል። እርሱን ወደ አንተ ጥንካሬ ማምጣትህ ይቀርና ቀስ በቀስ አንተን ወደርሱ ዝቅጠት ይወስድሀል። «ሰው በጓደኛው ይለካል!» ይባል የለ! ልክ እንደዚሁ ትዳር መመስረት የሚፈልጉ ጥንዶችም፤ አንዳቸው የሌላቸውን የእምነት ጥንካሬ መስፈርት ሊያደርጉ ይገባል። ምናልባትም አላህ እድሜ ከለገሳቸው፤ ብዙዎን የህይዎት ጊዚያቸውን በጋራ ስለሚያሳልፉ የአንዳቸው መልካምነት ለሌላቸው ወሳኝ ነው። || t.me/MuradTadesse

"በዚች ምድር ላይ እንደ ረሱል ﷺ ያፈቀረ እንደሳቸውም የተፈቀረ የለም። ወደፊትም አይኖርም!👌 ሰሉ አለ ነቢ አላሁመ ሰሊ🌹 ወሰሊም አላ ነቢይና ሙሀመድﷺ መልካም ጁምዓ🌹🌹🌹 @achachr
"በዚች ምድር ላይ እንደ ረሱል ﷺ ያፈቀረ እንደሳቸውም የተፈቀረ የለም። ወደፊትም አይኖርም!👌 ሰሉ አለ ነቢ አላሁመ ሰሊ🌹 ወሰሊም አላ ነቢይና ሙሀመድﷺ መልካም ጁምዓ🌹🌹🌹 @achachr