cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

✞ኬብሮን

👉በዚህ ቻናል 📖የተመረጡ የመፅሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች ✍ተከታታይ ታሪኮች ✍ ወግ ✍ ብሂላተ አበው ✍የኢትዮጵያ ጥንታዊ ታሪክ ✍ከተለያዩ መፃህፍት እና ንግግሮች የተመረጡ ፅሁፎችን " ማንም አንዳች የሚያውቅ ቢመስለው ሊያውቅ እንደሚገባው ገና አላወቀም፤" (1ኛቆሮ 8:2) 💚💛❤️ማንኛውምንም ጠቃሚና አስተማሪ ፅሁፍ ካሎት @Teshubotላይ ይላኩልን*

Show more
The country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
Advertising posts
2 290
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

ከዚህ በፊት እንደ ነገርኋችሁ ልጆቻቸውን በምግባር በሃይማኖት እንዲያድጉ የማያደርጉ ወላጆች የልጆቻቸው ገዳዮች ናቸው፡፡ እስኪ ንገሩኝ! ለዔሊ ልጆች መሞት ተጠያቂው ማን ነው? እርሱ ራሱ አይደለምን? እርግጥ ነው የጠላት ጦር ልጆቹን ወግቶ ገድሏቸዋል፡፡ የአባታቸው የዔሊ ደንታቢስነት ግን ጦሩ ልጆቹን አነጣጥሮ እንዲወጋቸው አድርጎታል፡፡ ረድኤተ እግዚአብሔር ስለ ራቃቸው በፍልስጥኤማውያን ጦር ፊት እንዲቆሙ አደረጋቸው፡፡ በዚህም አባታቸው ራሱንም ልጆቹንም ገደለ፡፡ በአሁኑ ሰዓትም ይህንን ዕለት ዕለት በዓይናችን ፊት እያየነው ነው፡፡ የማይታዘዙትንና ሥርዐት የለሽ ልጆቻቸውን በአግባቡ መቅጣት የማይፈልጉ ወላጆች ስፍር ቊጥር የላቸውም! ልጆቻቸውን ጠንከር አድርገው መገሠጽን ይፈራሉ፡፡ የወላጆቹ እንደዚህ መኾንስ የሚያመጣው ውጤት ምንድን ነው? የልጆቹ ሥርዐት አልበኝነት ይጨምራል፡፡ አለመቀጣታቸው ወደ ዓመፃ ወንጀል ያመራቸዋል፡፡ ወደ ወኅኒ ይወሰዳሉ፡፡ ከዚህ እጅግ ከከፋም በሞት ይቀጣሉ፡፡ ወዮ! የራሳቸውንና የተፈቀደላቸውን የመቅጣት መብት ችላ በማለታቸው፥ ልጆቻቸውን ለከፋ ቅጣት አሳልፈው ይሰጣሉ፤ ሕዝባዊ ሕጉም ለራሱ የተፈቀደለትን ቅጣት ይቀጣቸዋል፡፡ እነርሱ (ወላጆቹ) እያዩአቸው በቀላል ቅጣት ሊያስተካክሏቸው ሲገባቸው፥ ይኸው ማንም አጠገባቸው በሌለበት አሰቃቂ ቅጣት ይፈጸምባቸዋል፡፡ © ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ ኦርቶዶክሳዊ ቤተሰብ፣ ገጽ 162
Show all...
Repost from ✞ኬብሮን
✞ኬብሮን: #ያቺ_ሰአት ።እጅግ ወኔ የተሞላው እና የሚነሽጥ ለሊት ነበር ንጉሱ ባስነገሩት አዋጅ መሠረት ማንም ከቀየው የቀረ ያለ አይመስልም የወራት የመንገዱ ጉዞ ሣይበግራቸው ሁሉም ቦታቦታውን ይዞል:ካህናቱ በተተከለው ድንኳን ውስጥ ጽላቱን ይዘው ማህሌቱን ተያይዘውታል በሌላ ወገንም ቅኔው እንደጉድ ይዘረፋል:: ህዝቡም ቢሆን "በእውነት ኢትዮጵያዊ መልኩን ወይስ ነብር ዥንጉርጉርነቱን ይለውጥ ዘንድ ይችላል" የሚለውን ቅዱስ ቃል በመቀበል ሀገራቸውን ሊበትን ሀይማኖትን ሊያጠፍ የመጣውን ጠላት ለመመከት በንቃት ቆመዋል:: አንዳንዱ እንደመነሸጥ ሲያደርገው ከወደ ጥግ ወደ መሀል እየመጣ "ጦርሜዳ ላይ ጀርባዬን ተመትቼ ካገኘህኝ አንስተህ እንዳትቀብረኝ አሞራ ይብላኝ ፈርቼ ስሸሽ ነው እና ለፈሪ ሚገባው ይሄ ነው,: ግንባሬን ተመትቼ ካገኘህኝ ግን በክብር ቅበረኝ " ይላል * ሰአቱ አልደርስያላቸውም ይቁጠነጠናሉ ግማሹ ጎራዴውን ይሞርዳል ግማሹ ጦሩን ይቀጠቅጣል ፈረሶቹም ቢሆን የበኩላቸውን ለመወጣት የቸኮሉ በሚመስል ሁኔታ ጭራቸውን እያወዛወዙ አለውልህ ይሉታል ጌታቸውን ባለፈረሱም ወገባቸውን መታመታ እያደረገ እንግዴ ፈረሴ አደራህን እንደ ይሁዳ በመጨረሻው ሰአት እንዳከዳኝ ባይሆን እንደ ሠማእቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ነጩፈረስ በርትተህ አበርታኝ ብሎ እንደወዳጁ ግንባሩን ሣም ያደርገዋል:: ፉከራው እና ሸለልቶው ደርቶል +መሣርያውን ታጠቅ ሁሉም ይሠናዳ(2) +ልክ ማስገባት ነው ይሄን ወራዳ አረጎራው አረጎራው ስትል አንዶ ባለገር አይዞሽ እያለች ገብታ በሚሸንጥ ቅላጼ + በለው በለው እና አሣጣው መድረሻ (2) +የሠውልክ አያቅም ባለጌ እና ውሻ ሀሀሀሀሀ !ዘራፍ አካኪ ዘራፍ !ዘራፍ አካኪ ዘራፍ !አባሮ ገዳይ አይዞህ !ቆንጥር ለቆንጥር ዘራፍ !በሀገር ለመጣ ዘራፍ የማይበገር በለው አስኪ አንተዬ አረ በለው እያለች አንዶም ትገባና +ያሣደግነው ጥጃ ለምለም ሣር አስግጠን(2) +ፈርገጥ ፈርገጥ አለ እኛኑ ሊረግጠን.........አረጎራው አረጎራው ሀገሬን ሀገሬን ሀገሬን እላለው ኢትየጵያን ለጠላት እንዴት እሰጣለው , አረስጡኝ እማ ዝናር ጥይቴን(2) ገፍቶ ለመጣ ሰው መመከቻዬን,,,አረጎራው አረጎራው አሁን ወሣኞ ሠአት ደርሳለች ሠማዩላይ ያለው ጭለማ ባታውን ለብርሀን ለመስጠጥ እየተንጎራደደ ነው አብዛኛው ጦረኛ ዳዊቱን ገልጦ የመጨረሻውን ፀሎት እያደረገ ነው ካህናቱም ወደ ቅዳሴ ለመግባት መዘጋጀት ጀምረዋል ያለውን ድባብ ግን ተውት ያቺ ነጫጭባ በእግሮ ፈርጥጣ ሮም ካልገባች ምን አለ በሉኝ በዚ መሀል ወደ አስር ሰአት ገደማ የጠለት ጦር መንቀሳቀሱን የሠሙት አጼውና ንግስቲቱ እንዲሁም መኳንቱ ሰራዊቱን ማንቀሳቀስ ጀመሩ እንግዴ የተናቀው አቢሲኒያው ህዝብ ማንነቱን ለማሳየት ከፈጣሪው ጋር መጋዝ ጀመር ,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,, እንበለው እና ጉልበት ጉልበቱን እያፎቀቀ ይውጣው ዳገቱን በሉ እንግዴ ብእሬን ከትቼ ከአባቶቼጋ በመንፈስ ወደ ፍልሚያው ልግባ። "አድዋ የሁላችንም ታሪክ" ተጻፈ የካቲት 2012 @kebbron @kebbron
Show all...
Repost from ✞ኬብሮን
ፆም ገባ ይሉኛል ቀኑን ሙሉ ብፆም እስኪደርቅ አንጀቴ ቅቤና ሥጋውን ባርቀው ከፊቴ ዘውትር ብሰግድ እስኪዝል ጉልበቴ ብቀድስ ባስቀድስ በመቅደሱ ግርማ ብዙም ባወድስ በሚጣፍጥ ዜማ ድርሳናት ብተርክ ሚስጥር አመስጥሬ ብናገር ባስተምር ግዕዝን ዘርዝሬ ጥልና ክርክር ካሉ በህይወቴf ሀሜትና አድመኝነት ካልጠፋ ከቤቴ እኔን ብሎ ጿሚ ከንቱ ነው ፀሎቴ ፈጣሪ ያዝንብኛል ፍቅር በማጣቴ ምንጭfb
Show all...
"ኦ ለዝንቱ መንክር ልዑል ላዕለ ኩሉ ሕሊናት ብእሲት ምድራዊት ወለደቶ ለእግዚአብሔር ቃል ዘኮነ ሰብአ፡፡ ድንግል ወለደቶ ለገባሪሃ ወለሊሁ ፈጠረ ወላዲቶ ወእምኔሃ ነስአ ሥጋነ ዘውእቱ ፈጣሪ" "ከሕሊናት ሁሉ ለራቀ ለዚህ ድንቅ ምስጢር አንክሮ ይገባል ምድራዊት ሴት ሰው የሆነ እግዚአብሔር ቃልን ወለደችው ድንግል ፈጣሪዋን ወለደችው እርሱም እናቱን ፈጠረ ከርሷም እርሱ የፈጠረውን ሥጋ ተዋሐደ" (ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ ኤፍሬም) እንኳን ለአምላካችን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ!
Show all...
" ሁልጊዜ በጌታ ደስ ይበላችሁ፤ ደግሜ እላለሁ፥ ደስ ይበላችሁ።" (ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች 4:4)
Show all...
✞ኬብሮን “ኦ ማርያም በእንተዝ ናፈቅረኪ ወናዓብየኪ - እስመ ወለድኪ ለነ መብልዓ ጽድቅ ዘበአማን | ወስትየ ሕይወት ዘበአማን +++ ማርያም ሆይ ስለዚህ እንወድሽለን ከፍ ከፍም እናደርግሻለን | እውነተኛ የጽድቅ መብልን እና እውነተኛ የሕይወት መጠጥን ወልደሽልናልና ሊቁ አባ ሕርያቆስ ( ቅዳሴ ማርያም ) @kebbron @kebbron
Show all...
✞ኬብሮን ወንድሜ ሆይ በዝናብ ጊዜ ከሚሞላው ሐይቅ ተማር።ዝናቡ በጣለና ውኃው ሐይቁን በሚሞላበት ጊዜ መጀመሪያ ላይ ውኃው ይደፈርሳል።ነገር ግን የዝናቡ ጊዜ ሲያልፍ በቆይታ ሐይቁ መጠኑ ከመጨመሩ በላይ እንደ መስታወት ጥርት ብሎ በውስጡ የሚመላለሱት ዐሣትን ያሳየናል።ስለዚህ ተወዳጆች ሆይ በመከራ ምክንያት ልባችሁ አይዛል።ጸጋ ሊሰጣችሁ ሲል መከራ ይመጣባኝኋልና መከራ ካለፈ በኋላ በጸጋው ይሞላችኋል፤ጽድቃችሁም በሰው ሁሉ ፊት የተገለጠ ይሆናል.... @kebbron @kebbron ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ
Show all...
ኬብሮን ንስሐ ፦ ነስሐ ተፀፀተ ካለው የተገኘ ሲሆን ፤ ንስሐ ማለት በሠሩት ኃጢአት መፀፀት ፣ ማዘን ፣ ወደ እግዚአብሔር ለመመለስ መወሰን ማለት ነው። ንስሐ ከዘለዓለማዊ ፍርድ የሚያድን ፤ ዘማዊውን እንደ ድንግል ፤ ሌባውን መጽዋች የሚያደርግ በፊት ከተሠራው ኃጢአት ንጹህ አድርጎ ፤ ከእግዚአብሔር ጋር አንድ የሚያደርግ ምሥጢር ነው ። ከንስሐ በፊትመፀፀት አንድ ክርስቲያን በድፍረትም ይሁን በስህተት “የሠራው በደል” መጻሕፍት በማንበብ ፣ ከመምህራን ተምሮ ፣ የስብከት ካሴት አዳምጦ ፤ ህሊናው ወቅሶት ፣ ወይም በሌላ በአንድ ምክንያት ስህተት መሆኑን ከተረዳ በኋላ ተፀፅቶ ከእግዚ አብሔር ለመታረቅ (በደሉን ለማስተስረይ) የሚያደርገው ጉዞ ንስሐ ይባላል ። በሠራው በደል ሳይፀፀት ፤ ለጊዜው ህሊናውን ስለረበሸው ብቻ ንስሐ የሚገባ ሰው ፤ ከስሐውን በኋላ ወደ ቀደመ ሕይወቱ ሊመለስ ይችላል ። ምክንያቱም ፡ ንስሐ የገባው ፡ በሠራው በደል ከልቡ ተፀፅቶ ሳይሆን ፤ በስሜት ተነሳስቶ ነውና ፤ ❖ኃጢአትን መጥላት በበደላችን ከተፀፅትን በኋላ የሰራነውን በደል መጥላትና ወደፊትም መሥራት እንደሌለብን ራሳችንን ማሳመንና ከኃጢዓት መንገድ መራቅ ማለት ነው ። ❖ከንስሐ በኋላ ስላለው ሕይወት መወሰን አንድ ምዕመን ንስሐ ከመግባቱ በፊት ለወደፊቱ የሚኖረውን ሕይወት አስቀ ድሞ መመርመርና መወሰን ይገባዋል የእግዚአብሔን ቃል ስንሰማ ለጊዜው ልባችን ሊነካ ፣ ምን እናድርግ ልንል እንችላለን ። የሐ ሥ 2 ፥ 37 ። ነገር ግን ከተወሰነ ጊዜ በኋላ ዓለሙን ወደመምሰል እንደማንመለስ አስቀድመን ራሳችንን መመርመር አለብን ። ብዙዎቹ በስሜት ወደ ክርስትና ከገቡ በኋላ ፤ በጊዜያዊ ነገር ተታለው በድንገት ከሃይማኖት መንገድ ወጥተዋልና ። @kebbron @kebbron
Show all...
✞ኬብሮን ✍ብሂላተ አበው 🙏እግዚአብሔር ሆይ አፈርና ትቢያ ሆኜ ሳለ ጻድቅ አድርገው ከሚቆጥሩኝ ሰዎች አድነኝ ›› አባ እንጦንስ 🙏ፍጡራንን መርምሮ ማወቅ ካልተቻለን ሁሉን የፈጠረ እርሱን መርምሮ ማወቅ እንደምን ይቻለናል›› ቅዱስ አትናቴዎስ 🙏ወርቅ በእሳት እንደሚፈተን ሁሉ የክርስቶስን ጸጋና ክብር ሳይፈተኑ ማግኘት አይቻልም የዚህ ዓለም ፈተናና እሳት ቶሎ ያልፋል ይጠፋል ኃጢአተኞች የሚገቡበት የገሃነም እሳት ግን ለዘላለም እንዲሁ ይኖራል፡፡›› ቅዱስ ሚናስ 🙏በማንም ላይ ክፋትን አትሥሩ አትፍረዱ ይህንን ከጠበቃችሁ ርስቱን ትወርሳላችሁና›› ታላቁ አባ መቃርስ 🙏ብዙ ጊዜ ብዙ እናገራለሁ በመናገሬም አዝናለሁ በዝምታዬ ግን ያዘንኩበት ጊዜ የለም›› ቅዱስ አርሳንዮስ 🙏ቤተክርስቲያን መጠሪያችን ነች ፤ ቤተ ክርስቲያን የኖኅ መርከብ ነች ፤ በውስጧ እንጠለላለን ከውጪው ግን ማዕበልና ቀላያት ተከፍተዋል›› ቅዱስ እንድርያስ ??🙏ሥጋዊ ፍላጎቶችን ማሸነፍ ለአክሊለ ሕይወት የሚያበቃ ሰማዕትነት ነው›› ብፁዕ አቡነ ጎርጎሪዮስ ካልዕ ?? 🙏ልባችንን ጠፊና በስባሽ ከሆነው ከምድራዊው ምኞት አርቀን ከበደል በንስሐ ንጹሕ ካደረግነው በጸጋ መንፈስ ቅዱስ የተሞላን እንሆናለን ›› አባ አብርሃም መፍቀሬ ነዳያን 🙏የቤተክርስቲያን ሕይወት በመስቀል ላይ ስለሆነ ፈተና ይበዛበታል ስለዚህ ከግል ሕይወታችሁ ይልቅ የቤተ ክርስቲያናችሁን አቋም አጠንክሩ›› ብፁዑ አቡነ ጎርጎሪዮ ካልዕ 🙏ከመኝታህ በፊት የምታደርገውን ጸሎት ትተህ እንድትተኛ መንፈስህ ሲገፋፋህ እሺ ብለህ አትቀበለው እንዲያውም መዝሙረ ዳዊትን ጨምርና ሌሊትን በሙሉ ስትጸልይ እደር›› ቅዱስ ይስሐቅ ሶሪያዊ 🙏እራ?ራስህን በሐሰት አትውቀስ፤ ራስን መክሰስ ትህትና አይደልም ታላቁ ትህትና ሰዎች ሲወቅሱህ መታገስ ነው›› ቅዱስ ስራፕዋን 🙏አንደበቱን ከቧልት ፣ ከሐሜት፣ ያየውንም ምሥጢር ከመናገር የሚከለከል ሰው ልቦናውን ከሃልዮ ኃጢአት ያርቀዋል፡፡›› አርጋዊ መንፈሳዊ ?‹🙏ጸጋ ሲሰጥህ በተሰጠህ ጸጋ አመስግን ያልተሰጠህን እሻለሁ በማለት የተሰጠህን እንዳታጣ›› ማር ይስሐቅ @kebbron .
Show all...
✞ኬብሮን ✍ በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ የመስቀሉ ኃይል እንደ ምን ይደንቅ? በሰው ልጆች ዘንድ በመስቀሉ ኃይል የኾነው የተደረገው ለውጥ እንደ ምን ይረቅ? ከድቅድቅ ጨለማ ወደሚደነቅ ብርሃን አውጥቶናልና፤ ከሞት ወደ ዘለዓለም ሕይወት መልሶናልና፤ ከዘለዓለም ጥፋት ወደ ዘለዓለም ልማት አሸጋግሮናልና፡፡ በመስቀሉ ያልተደረገልን በጎ ነገርስ ምን አለ? ምክንያቱም በመስቀሉ ርትዕት ሃይማኖትን ዐወቅን፤ የእግዚአብሔር የጸጋውን ብዛት ተረዳን፡፡ በመስቀሉ ስለ እግዚአብሔር እውነት የኾነውን ዐወቅን፡፡ በመስቀሉ፥ ርቀን የነበርን እኛ ሕዋሳተ ክርስቶስ እስከ መኾን ደርሰን የቀረብን ኾንን፡፡ በመስቀሉ ከመንፈስ ቅዱስ ጸጋ ተካፋይ የመኾን መብት (ሥልጣን) አገኘን፡፡ በመስቀሉ የፍቅርን ኃያልነት ዐወቅን፡፡ በመስቀሉ ለሌሎች መሞትን ተማርን፡፡ በመስቀሉ ንቀት፣ ውርደት፣ መከራ ማለት ምን ማለት እንደ ኾነ ዐወቅን፡፡ ጊዜያዊ ያይደለ የዘለዓለም በረከት ምንጭ መኾኑን ተረዳን፤ የማይታየውን እንደሚታይ አድርገን ተቀበልን፡፡ በመስቀሉ የተሰቀለው ይሰበካል፤ በእግዚአብሔር ማመንን እውነትም ለዓለም ኹሉ ይነገራል፡፡ በመስቀሉ የተሰቀለው ክርስቶስ ይሰበካል፤ በትንሣኤ ማመንንና በላይ በሰማያት ያለችውንም ሕይወት መንግሥተ ሰማያትም በእውነት ያለ ሐሰት ያለ ጥርጥር ይሰበካል፡፡ ከመስቀሉ በላይ የከበረ፣ ለነፍስም ድኅነትን የሚሰጣት ምን አለ? መስቀል አጋንንት ድል የተነሡበት ነው፡፡ መስቀል የኃጢአት ድል መንሻ የጦር ዕቃ ነው፡፡ መስቀል ጌታችን እባቡን የመታበት ሰይፍ ነው፡፡ መስቀል የአብ ፈቃድ፣ የወልድ ክብር፣ የመንፈስ ቅዱስ ደስታ፣ የመላእክት ጌጥ፣ የቤተ ክርስቲያን አጥር፣ የቅዱስ ጳውሎስ ውዳሴ፣ የቅዱሳን ጋሻ፣ የዓለምም ብርሃን ነው፡፡ © አምስቱ የንስሐ መንገዶች @kebbron @kebbron
Show all...