ማዳኑን አውሩ | ᴘʀᴏᴄʟᴀɪᴍ ʜɪꜱ ꜱᴀʟᴠᴀᴛɪᴏɴ
Open in Telegram
Thank you for your interest to join Our Telegram channel. ▫️The primary function of this channel is : ☞To proclaim our savior JESUS CHRIST through a lifestyle of praise and worship. መዝሙረ ዳዊት 96 2፤ እግዚአብሔርን አመስግኑ ስሙንም ባርኩ፥ ዕለት ዕለትም ማዳኑን አውሩ።
Show more1 241
Subscribers
No data24 hours
+57 days
+1030 days
Posts Archive
Here’s my official YouTube channel.. You can subscribe and share the Grace of God!!!👇🏻👇🏻
Hello Dear families 😍 We’ve been working on something that I can’t wait to share. Stay tuned ❤️#newmusic #Metegiyachin
Psalm 46:1 - "God is our refuge and strength, an ever-present help in trouble."🙌🏽
☞ የዕለቱ መልዕክት
ያልታወቀ ስም ቢሰሙት አይከብድም። ስሙ እየታወቀ ሲሄድ ግን አክብሮቱም እንዲሁ ለስሙ የሚመጥን ይሆናል። የእግዚአብሔር ስም የማይወዳደር፣ ሁሉን ግን የሚበልጥ ስም ነው። ስሙ ገናና ነው፤ ብቸኛ ነው፤ ብርቱም ነው። ስሙም የሚጠሩት ብቻ ሳይሆን የሚያውቁት፣ የሚያውቁትም ብቻ ሳይሆን የሚታመኑበትም ጭምር ነው። የእርሱን ስም ለሚያውቁም ታላቅ መታመን አላቸው፤ "ስምህን የሚያውቁ ይታመኑብሃል፤ እግዚአብሔር ሆይ፤ የሚሹህን አትተዋቸውምና" (መዝ 9፥10)።
☞ ዳዊት እግዚአብሔር ከሕዝቡ ጋር ያለው ሁሉም ነገር በተስተካከለ ሁኔታ ሲሄድ ብቻ እንዳልሆነ ተናግሯል። ፈተናዎች ሲያሸንፏቸውም እሱ አለ።
☞ ስሙ እንደ ሳበን፣ ስሙ ያስቀረናል፤ ስሙ መታመኛችን እንደ ሆነ፣ ስሙ ልምላሜ ይሆነናል። ስንጠራበት ያስከበርነው ስም ፣ ስንጠራው ያስከብረናል።
ጌታ ኢየሱስ አብዝቶ ይባካችሁ ❤️❤️
@hymnsofmes
ብጹዕ ሆኖ
በመንፈሱ ድኻ ... የመንግሥተ ሰማያት የእርሱ የሆነ፣ የሚገባ፣ ሌሎችን የሚያስገባ ድኻ
የሚያዝን... የሚጽናናና ሌሎችን አልቃሾች የሚያጽናና።
የዋሕ... በመስቀሉ ሞት ምድርን የሚወርስ፣ ቀሊል ቀንበሩን ሌሎች ላይ አድርጎ ራሳቸውን ወደመካድ የሚመራ ልዝብ፣ ልስልስ መሪ፣ ዓለምን የሚያንበረክክ ጽኑ ፍቅር።
ጽድቅን የሚራብ፣ የሚጠማ... የሞቱን ጽዋ ጨልጦ የራሱን ብቻ ሳይሆን የሌሎችን የጽድቅ ረሃብ የሚያረካ።
ምህረትን የሚያደርግ፣ ለጠላቶቹ የሚሞት ... በእግዚአብሔር አብ የትንሳዔን ምህረት የሚያገኝ፣ የትንሳዔን ምህረት የሚያስገኝ።
ሰላምን የሚያወርድ፣ ጨቋኞቹ እየሰቀሉት የሚመሰክሩለት ... "እውነትም ይኽ ሰው የእግዚአብሔር ልጅ ነበር!" (ማቴ. 27፥54)
ስለጽድቅ ብሎ የተሰደደ ባለመንግሥት።
@hymnsofmes
_________________________
እኔ ደካማው ላይ በረከትህ ይውረድብኝ ጌታዬ! 🤲
©️sara a.
ብጹዕ ሆኖ
በመንፈሱ ድኻ ... የመንግሥተ ሰማያት የእርሱ የሆነ፣ የሚገባ፣ ሌሎችን የሚያስገባ ድኻ
የሚያዝን... የሚጽናናና ሌሎችን አልቃሾች የሚያጽናና።
የዋሕ... በመስቀሉ ሞት ምድርን የሚወርስ፣ ቀሊል ቀንበሩን ሌሎች ላይ አድርጎ ራሳቸውን ወደመካድ የሚመራ ልዝብ፣ ልስልስ መሪ፣ ዓለምን የሚያንበረክክ ጽኑ ፍቅር።
ጽድቅን የሚራብ፣ የሚጠማ... የሞቱን ጽዋ ጨልጦ የራሱን ብቻ ሳይሆን የሌሎችን የጽድቅ ረሃብ የሚያረካ።
ምህረትን የሚያደርግ፣ ለጠላቶቹ የሚሞት ... በእግዚአብሔር አብ የትንሳዔን ምህረት የሚያገኝ፣ የትንሳዔን ምህረት የሚያስገኝ።
ሰላምን የሚያወርድ፣ ጨቋኞቹ እየሰቀሉት የሚመሰክሩለት ... "እውነትም ይኽ ሰው የእግዚአብሔር ልጅ ነበር!" (ማቴ. 27፥54)
ስለጽድቅ ብሎ የተሰደደ ባለመንግሥት።
_________________________
Repost from AASTU-ECSF
#የፋሲካ_አዳር_እና_የመዝሙር_ድግስ
🥁🥁🎤ደረሰ ደረሰ 🥁🥁🎤
የዮሐንስ ወንጌል 15 ፤ነፍሱን ስለ ወዳጆቹ ከመስጠት ይልቅ ከዚህ የሚበልጥ ፍቅር ለማንም የለውም።ONLY ONE DAY LEFT...!!!!!!!!! 🗓 ሚያዚያ 18 📍በአቃቂ ቆርቆሮ ሙሉ ወንጌል ቤተክርስቲያን #እንለያለን #እንመለሳለን #እንጠብቃለን #FAITHFUL_SERVANTS_OF_THE_KINGDOM #የፋሲካ_አዳር_እና_የመዝሙር_ድግስ #True_Love #Concert WITH GUEST SINGER MESAY BIRHANU AASTU ECSF Worship and Media Team presents
#የእግዚአብሔር _ቃል
"በምክርህ መራኸኝ፤ ኋላም ወደ ክብር ታስገባኛለህ።"
(መዝ 73፥24 አመት) ከቻልን ሙሉ ምዕራፉ ይነበብ)
☞ አሳፍ ለጌታ መገኘት ብቻ ሳይሆን ለመንግስተ ሰማያት ስላለው መመሪያ እና ማረጋገጫም አመስጋኝ ነበር። ከገጠመው #የእምነት_ቀውስ ወዲያውኑ እንዲያገግም የረዳው ያ መመሪያ ነው። በመዝሙር 73፡2–3 እንዲህ ብሎ ነበር ❝ እኔ ግን እግሮቼ ሊሰናከሉ፥ አረማመዴም ሊወድቅ ትንሽ ቀረ። የኃጢአተኞችን ሰላም አይቼ፡ በዓመፀኞች ቀንቼ ነበርና ። ❞ ይላል !
☞ እግዚአብሔር #ከኀይሉ በፊት #ምክሩንና_ሐሳቡን ያስቀድማል። የግንኙነት አምላክ ስለሆነውም በምክሩ የሚመራ አምላክ ነው። በምሪቱ ውስጥም አቅርቦቱና ከለላነቱ አጃቢ ናቸው።
☞ እግዚአብሔር ሲመራ የሚመራው ወደ ራሱ ወደ መታወቁ ስለሆነ መድረሻው ወይም ግቡ የሚሰላው በምናከማቸው በስኬት ቅደም ተከተል አንድ፣ ሁለት፣ ሦስት ተብሎ አይደለም፤ #በሕልውናውና #በክብሩ በመገኘት እንጂ።
☞ እንደ ሰው የምናስቀምጣቸው ግቦች አሉ፤ እነዚህ ጥሩ ናቸው፤ የሕይወት ምዕራፎች እንጂ ዋነኛ ፍጻሜዎች ግን አይደሉም፤ ሲደረስባቸው ሌላ ድጋፍ፣ ሌላ አቅርቦት፣ ሌላም ምሪት ይፈልጋሉና። ከጌታ ጋር የምናደርገውና በምክሩ የምናሳምረው ጕዞ መዳረሻ ግን ክብሩ ነው፤ እግዚአብሔር እየመራቸው ከክብሩ የሚጎድሉ የሉም።
⚠️ ወዳጆቼ የጌታን ፈቃድ እና ምክሩን በየዕለቱ እንድናውቅ ሰውነታችንን ሕያው ቅዱስና ደስ የሚያሰኝ መሥዋዕት አድርገን ለጌታ እያቀረብን ፤ በአእምሮ መታደስ እየተለወጥን ፤ ዓለምን ለመምሰል እምቢ እያልን #ወጥነት እና #ፅናት ያለውን #ትጋት እና #ባህሪ እያሳየን ጌታ ባስቀመጠን ስፍራ በታማኝነት እንድናገለግለው ደግሞ እንድንኖር ይርዳን። አሜን !
Join @hymnsofmes
#የዕለቱ_ቃል
“ነፍሴ በዛለች ጊዜ፣ እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተን ዐሰብሁ፤ ጸሎቴም ወደ አንተ፣ ወደ ቅዱስ መቅደስህ ዐረገች።"
(ዮና 2፥7 አመት)
የዕለቱ ሐሳብ
☞ የእግዚአብሔር ምሕረት ነፍስን ያተርፋል።
☞ እግዚአብሔር ከ120 ሺ በላይ ነዋሪ የነበራትን ነነዌን ለማትረፍ ፈልጎ የንስሐ ስብከት እንዲሰብክ ነቢዩ ዮናስን ላከው።
☞ እርሱ ግን በድርጊቱ እምቢታውን ገለጠ፤ ወደ ተርሴስ ኮበለለ። ሁሉን የሚገዛ አምላክም በትልቅ ዓሣ ወደ ተልዕኮው አቅጣጫ መለሰው።
☞ በዚያም መካከል እንዲህ ብሎ ጸለየ፤ “ነፍሴ በዛለች ጊዜ፣ እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተን ዐሰብሁ፤ ጸሎቴም ወደ አንተ፣ ወደ ቅዱስ መቅደስህ ዐረገች" (2፥7)።
☞ ስለ ነነዌ ነፍስ ግድ ያላለው ነቢይ፣ በዓሣው ሆድ ሳለ ነፍሱ ዛለች፤ ምሕረቱ ለሁሉ የሚበቃውንም አምላክ ዐሰበ።
☞ አይገርምም ዩናስ ከመሬት ያቃተው ጸሎት ከባሕሩ ጥልቅ ወደ ሰማይ ዐረገ። በርግጥም፣ የዛለች ነፍስ በጸሎት ከዝለቷ ነፃ ትወጣላች፤ ጸሎቷም ሰማይ ድረስ 'መሄድ' ይችላል።
☞ እዚህ ላይ ሌላው መገንዘብ ያለብን ዩናስ እግዚአብሔር ያደረገለትን፣ ለሌሎች ያደረገውን፣ ምን ማድረግ እንደሚችል ና ለማድረግ ቃል የገባለትን አስታወሰ። ይህም ነፍሱ እንዳይዝል አድርጎታል።
☞ እናስተውል፣ መከራችን አምላክን እንድናስብና በዚህም ወደ እሱ እንድንጸልይ ያደርገናል። ነፍሳችን ስትደክም እግዚአብሔርን ማስታወስ አለብን ፤ እርሱንም ስናስታውስ ዘውትር ጸሎትን ወደእርሱ ማቅረብ አለብን።
☞ እግዚአብሔር ነፍሳችንን ከዝለት ይጠብቃት!
አሜን!!
@hymnsofmes
የዕለቱ ቃል
☞ ይህ ሙሉ ምዕራፍ በተስፋ የተሞላ ነው…እና ወደዚህ ምዕራፍ መጨረሻ ስትደርሱ… ሞት በድል እንደሚዋጥ የድል አዋጅ ብቻ ታያላችሁ… ሞት ከእንግዲህ መውጊያ የለውም ፣ የሞት መውጊያ ፣ የኃጢአት ኃይል ሕግ ነው… ግን እግዚአብሔርን ይመስገን ፣ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል #ድልን ሰጥቶናል ደግሞ በየዕለቱም ይሰጠናል።
☞ "በጌታ በኢየሱስ በኩል #ድልን" ያገኘና ድሉ የገባው ማኅበረሰብ ጸንቶ ለመቆም አይቸገርም። ጳውሎስ ያስገነዘበው ይህንኑ ነው፤ "ስለዚህ የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ፤ ጸንታችሁ ቁሙ፤ በምንም ነገር አትናወጡ። #ለጌታ_ሥራ_ዘወትር_የምትተ_ሁኑ፤ ምክንያቱም ለጌታ የምትደክሙት #በከንቱ_እንዳልሆነ ታውቃላችሁ" (1ቆሮ 15፥58)።
☞ በምንም ነገር አለመናወጥ እንዴት ይቻላል? ተብሎ ሊጠየቅ ይችላል።
☞ የክርስቶስ ትንሣኤ ያስገኘልን ውጤት ግን ለማረፍም ሆነ ለመበርታት፣ ለመሥራትም ሆነ ለመድከም አቅም ይሆናል።
☞ #የማይናወጥ ሕዝብ #ያረፈ_ብቻ_ሳይሆን #የሚተጋም_ነው።
☞ ድል ነሺው ጌታ ድሉ ውስን ወይም የአንድ ጊዜ አይደለም፤ የዘላለም እንጂ! ስለዚህም በርሱ የሚታመኑ በሁኔታዎች አካሄድ ወይም መወሳሰብ ወይም መባባስ አይናወጡም። ይልቁንም፣ እየታመኑ ይቀጥላሉ፤ እየቀጠሉም ይተጋሉ።
🙏ወዳጆቼ እግዚአብሔር ለመንግሥቱ ስራ በትጋት እንድንቀጥል እና ዘውትር በፀጋው እና በሀይሉ እንድንፀና ይርዳን !!!
አሜን !!
@hymnsofmes
