en
Feedback
ማዳኑን አውሩ | ᴘʀᴏᴄʟᴀɪᴍ ʜɪꜱ ꜱᴀʟᴠᴀᴛɪᴏɴ

ማዳኑን አውሩ | ᴘʀᴏᴄʟᴀɪᴍ ʜɪꜱ ꜱᴀʟᴠᴀᴛɪᴏɴ

Open in Telegram

Thank you for your interest to join Our Telegram channel. ▫️The primary function of this channel is : ☞To proclaim our savior JESUS CHRIST through a lifestyle of praise and worship. መዝሙረ ዳዊት 96 2፤ እግዚአብሔርን አመስግኑ ስሙንም ባርኩ፥ ዕለት ዕለትም ማዳኑን አውሩ።

Show more
1 241
Subscribers
No data24 hours
+57 days
+1030 days
Posts Archive
ወደ ቲቶ 2:1 #አንተ_ግን_ሕይወት_ለሚገኝበት ትምህርት የሚገባውን ተናገር። But speak thou the things which become sound doctrine: ከኅዳር 26-29 /2017 ዓ.ም
+3
ወደ ቲቶ 2:1 #አንተ_ግን_ሕይወት_ለሚገኝበት ትምህርት የሚገባውን ተናገር። But speak thou the things which become sound doctrine: ከኅዳር 26-29 /2017 ዓ.ም በሆሳዕና እናት ቃለ ህይወት ቤ/ክ እግዚአብሔር የተባረከን ጊዜ ሰጥቶናል። #ክብር_ለኢየሱስ_ይሁን። @hymnsofmes

2ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 3:14 #አንተ_ግን_በተማርህበትና_በተረዳህበት_ነገር_ጸንተህ_ኑር፥ ከማን እንደ ተማርኸው ታውቃለህና፤ #ከኅዳር_26-29 /2017 ዓ.ም በሆሳዕና እናት ቃለ ህይወት ቤ/ክ እግዚአ
+9
2ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 3:14 #አንተ_ግን_በተማርህበትና_በተረዳህበት_ነገር_ጸንተህ_ኑር፥ ከማን እንደ ተማርኸው ታውቃለህና፤ #ከኅዳር_26-29 /2017 ዓ.ም በሆሳዕና እናት ቃለ ህይወት ቤ/ክ እግዚአብሔር የተባረከን ጊዜ ሰጥቶናል። #ክብር_ለኢየሱስ_ይሁን። @hymnsofmes

Pr_Tamirat_Hile_Ahunim_alehu_bemerkebu_ፓ_ር_ታምራት_ኃይሌ_አሁንም_አለሁ.m4a12.20 MB

#ዛሬ_የአምልኮና የቃል ጊዜ 🗓 እሮብ ህዳር 11/2017 ⏰ ከምሽቱ 12:00 ሰአት ጀምሮ ⛪️ ዩጎ ሲቲ ቤተክርስቲያን
#ዛሬ_የአምልኮና የቃል ጊዜ 🗓 እሮብ ህዳር 11/2017 ⏰ ከምሽቱ 12:00 ሰአት ጀምሮ ⛪️ ዩጎ ሲቲ ቤተክርስቲያን

⭐️በ ማቴ 17 : 1-8 ኢየሱስ 3 የፀሎት ጓደኞች ነበሩት ። እነርሱም ዮሐንስ ፣ ዼጥሮስ እና ያዕቆብ ነበሩ። ⭐️በትንቢተ ዳንኤል 2:17-19 ስናይ ደግሞ ዳንኤል 3 የፀሎት ጓደኞች (ሲድራቅ ፣
⭐️በ ማቴ 17 : 1-8 ኢየሱስ 3 የፀሎት ጓደኞች ነበሩት ። እነርሱም ዮሐንስ ፣ ዼጥሮስ እና ያዕቆብ ነበሩ። ⭐️በትንቢተ ዳንኤል 2:17-19 ስናይ ደግሞ ዳንኤል 3 የፀሎት ጓደኞች (ሲድራቅ ፣ ሚሳቅና አብድናጎ ) እንደ ነበሩት እናያለን። ⭐️የፀሎት ጓደኝነት ታላቅ ውጤት አለው። ሲፀልዩ የተቋጠረ እንቆቅልሽ ተፈቷል (ዳን 2:19 )። ከዚህ የምንማረው ዳንኤል የፀሎት ጓደኝነትን የያዘው በቅድስና ጉዳይ ከእርሱ ጋር አንድ አቋም ከነበራቸው ጓደኞቹ ጋር ነበር (ዳን 1:8)። #የፀሎት_ጓደኝነት - ተመሳሳይ ሸክም ያላቸው ሰዎች። - ተመሳሳይ አቋም ያላቸው ሰዎች። - የመንፈስ እና የልብ አንድነት ያላቸው ሰዎች። - ተመሳሳይ የፀሎት ትጋት ያላቸው ሰዎችን ያካትታል። ⭐️የፀሎት ጓደኞች ፀሎታቸው በጣም ውጤታማ ከመሆኑም በላይ ፈጣን የሆነ የፀሎት ምላሽ ያስገኛሉ። በፀሎታቸው ሰዓት የእግዚአብሔር መንፈስ በነፃነትና በሙላት ይሰራል። 🔔የፀሎት ጓደኛ አለህ / ሽ? @hymnsofmes @hymnsofmes

ወደ ፊልጵስዩስ 1 6፤ በእናንተ መልካምን ሥራ የጀመረው እስከ ኢየሱስ ክርስቶስ ቀን ድረስ እንዲፈጽመው ይህን ተረድቼአለሁና፤ 🌟 Bishoftu Mehal Ketema Full Gosple Church ,
+9
ወደ ፊልጵስዩስ 1 6፤ በእናንተ መልካምን ሥራ የጀመረው እስከ ኢየሱስ ክርስቶስ ቀን ድረስ እንዲፈጽመው ይህን ተረድቼአለሁና፤ 🌟 Bishoftu Mehal Ketema Full Gosple Church , Ethiopia Sunday Service Recap 🌟 November 10, 2024 #ማዳኑንአውሩ @hymnsofmes

የዕለቱ ቃል ⭐️ጳውሎስ በተከታታይ በተያያዙ አጫጭር ትእዛዛት በክርስቶስ ያለንን ሕይወት መግለጹን ቀጥሏል። በዚህ ቁጥር ውስጥ ያሉት ሦስቱ ትእዛዛት ለእያንዳንዱ ክርስቲያን መንፈሳዊ ደህንነት ቁልፍ
የዕለቱ ቃል ⭐️ጳውሎስ በተከታታይ በተያያዙ አጫጭር ትእዛዛት በክርስቶስ ያለንን ሕይወት መግለጹን ቀጥሏል። በዚህ ቁጥር ውስጥ ያሉት ሦስቱ ትእዛዛት ለእያንዳንዱ ክርስቲያን መንፈሳዊ ደህንነት ቁልፍ ነገሮች ናቸው። #በተስፋ_ደስ_መሰኝት። #በመከራ_ታጋሽ_መሆን። #በፀሎት_መፅናት። ⭐️ ተስፋ ወደፊት የሚያዝ ቢሆንም ዛሬን ያስይዛል። ይህም ማለት፣ ተስፋ ነገን እያስናፈቀ ለዛሬ የሚሆን ስንቅና አቅም ነው። ስለዚህም፣ "በተስፋ ደስተኞች ሁኑ" (ሮሜ 12፥12) ተብሎ ተጽፏል። ደስታው ደግሞ ነገን ብሩህ የሚያደርግ ብቻ ሳይሆን ዛሬንም የሚያፈካ ነው፤ ደስ የሚላቸው ብርሃን የበዛላቸው፣ ጉልበት የሚጨምሩም ናቸው። ተያይዞም፣ "በመከራ ታገሡ፤ በጸሎት ጽኑ" ተብሏል። ⭐️መከራ ምሬትን በመውለድ ፈንታ ትዕግሥትን ሊያበዛ ይገባል። በአስቸጋሪ ሁኔታዎች መካከል (መከራ) ደግሞ በጸሎት መጽናት የማይተካ መፍትሄ ነው። የመከራ ብዛት በጽኑ ጸሎት ይሳሳል፤ ይታለፋልም። ጊዜው ደስታ ባያመነጭም እንኳን፣ በእግዚአብሔር የተያዘ ተስፋ ዛሬን በደስታ ይሞላል። ⭐️ሕይወት ደስ የማይል ሊሆን ይችላል ፣ እና ሁሉም ጊዜዎች ደስተኛ ጊዜዎች አይደሉም። ሆኖም ጳውሎስ በምድር ላይ ያለው የህይወት ትግል ከሚመጣው ክብር ጋር ሲወዳደር ዋጋ እንደሌለው ጠቁሟል (ሮሜ 8፡18)። ፀሎት🙏🏾 አባቴ ሆይ ስለጨመርክልኝ ቀን አመሰግንሀለው ፥ ወደ ጥሪዬ ግብ ስጓዝ በተስፋ እንድደሰት፣ በመከራ እንድጸና እና በጸሎት እንድጸና እርዳኝ። በኢየሱስ ስም እጸልያለሁ ፤ አሜን 🙏🏾 ⭐️ በመልዕክቱ ከተጠቀማችሁ ለ 1 ሰው #share አድርጉት። @hymnsofmes @hymnsofmes

⭐️ ሐዋሪያው ጳውሎስ በኋላ ከሚጠቀምባቸው ቁጣ እና ማስጠንቀቂያ የተሞላባቸው የእርምት ቃላት አኴያ ስንመለከት ይህ መክፈቻ ይበልጥ አስደናቂ ነው። ⭐️በመካከላቸው ለሰማቸው የተሳሳቱ ባህሪዎች እና አ
⭐️ ሐዋሪያው ጳውሎስ በኋላ ከሚጠቀምባቸው ቁጣ እና ማስጠንቀቂያ የተሞላባቸው የእርምት ቃላት አኴያ ስንመለከት ይህ መክፈቻ ይበልጥ አስደናቂ ነው። ⭐️በመካከላቸው ለሰማቸው የተሳሳቱ ባህሪዎች እና አመለካከቶች ምላሽ ለመስጠት የፃፈው ደብዳቤም ነው። ⭐️ጸጋን በክርስቶስ የሆኑ ሁሉ ይቀበላሉ፤ ያለ ልዩነት ይሰጣልና። ጳውሎስ የቆሮንቶስ አማኞችን የሚነቅፍባቸው ብዙ ነገር ቢኖርም፣ በጌታ ለሆኑትና ላገኙት ሁሉ ግን እውቅና ይሰጣል፤ "በክርስቶስ ኢየሱስ ስለ ተሰጣችሁ ጸጋ ዘወትር ስለ እናንተ እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ" (1፥4)። ⭐️ ይህ ጸጋ ማንነት ላይ የሚመሠረት ስላልሆነ የሰዎችን መንፈሳዊነት አይለካም። ተቀባዮቹ ሲጠቀሙበት ግን ጸጋው መንፈሳዊ እንዲሆኑ ያስችላቸዋል። ⭐️ የጸጋ መብዛት ደግሞ ተቀባዮቹ እንዲታረሙ፣ እንዲያድጉና እንዲጸኑ ስለሚያደርግ እግዚአብሔርን ያስከብራል። ይህ ጸጋም በክርስቶስ የተሰጠ ብቻ ሳይሆን፣ በክርስቶስም የሚጠበቅ ነው። 🙏🏾ፀሎት! እግዚአብሔር ሆይ ስለማይቋረጠው የ ጸጋ ስጦታህ ዘወትር ላመሰግንህ እወዳለው! ይህንን የጸጋ ስጦታ የሰጠህኝ ፥ የጌታዬን የኢየሱስ ክርስቶስን መገለጥ እየጠበኩኝ ፥ ደግሞ እስከ መጨረሻ ጸንቼ፥ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ቀን ያለ ነቀፋ እንድሆን ነውና ዕለት ዕለት አንተን እንድመስልህ በመንፈስህ ሙላኝ። በኢየሱስ ስም አሜን!! ——————————————————— #ማዳኑንአውሩ @hymnsofmes

“በዙፋንም የተቀመጠው፦ እነሆ፥ ሁሉን አዲስ አደርጋለሁ አለ። ” — ራእይ 21፥5 — 🌟 Yougo City Church Addis Ababa, Ethiopia Sunday Service Recap 🌟 November 3, 2024 #ማዳኑንአውሩ @hymnsofmes

የዕለቱ ቃል ኢሳይያስ 26፡3 ትንቢተ ኢሳይያስ 26 3፤ በአንተ ታምናለችና በአንተ ለምትደገፍ ነፍስ ፈጽመህ በሰላም ትጠብቃታለህ። ⭐️ ይህ ክፍል የህይወት አውሎ ነፋሶች በዙሪያችን በሚሽከረከሩበት
የዕለቱ ቃል ኢሳይያስ 26፡3 ትንቢተ ኢሳይያስ 26 3፤ በአንተ ታምናለችና በአንተ ለምትደገፍ ነፍስ ፈጽመህ በሰላም ትጠብቃታለህ። ⭐️ ይህ ክፍል የህይወት አውሎ ነፋሶች በዙሪያችን በሚሽከረከሩበት ጊዜ እንኳን እኛን የሚያረጋጋንን ፍጹም ሰላም እንድንገኝ አቅጣጫዎችን ይሰጠናል። ይህን ሰላም ለማግኘት ሚስጥሩ እምነታችንን በእግዚአብሔር ላይ ማድረግ ነው። ⭐️መታመናችንን በእርሱ ላይ ስናደርግ እና በሕይወታችን ውስጥ በሁሉም ነገር ስንታመን እግዚአብሔር ፍጹም ሰላማችንን ይጠብቅልናል። ⭐️እግዚአብሔር ለሚታመኑበት ሁሉ አውነተኛ ተገንና ጋሻ ነው። ነቢዩ ኢሳይያስ በእግዚአብሔር የሚታመኑ በእርሱ የተደገፉ ስለሆኑ፣ በሰላም እንደሚጠበቁ ይናገራል፤ "በአንተ ላይ ታምናለችና፣ በአንተ የምትደገፈውን ነፍስ ፈጽመህ በሰላም ትጠብቃታለህ።" (26፥3)። ⭐️የነፍስ እረኛ የሆነው አምላክ ነፍስን (የውስጥ አካልን) እንዴት በሰላም መጠበቅ እንዳለበት ያውቃል። የእርሱ ሰላም በምድር አይሰነቀም (አይበጅም)፤ ሰላሙ የተሠራው በምድር ካሉ ሁኔታዎችና መሠረታውያን አይደለም። እግዚአብሔር በርግጥ ያረጋጋል፤ በኅልውናውም ይሞላል። ከርሱ የሚወጣው ሰላምም ከሚጠበቁት በላይ ሌሎች የሚታይ ነው። ፀሎት 🙏🏾 ጌታዬ ሆይ ከተፈጥሮ በላይ የሆነ ሰላም ስለሰጠህኝ አመሰግንሀለው ፤ ዘወትር አንተን የሚታመን እና ፊትህን የሚናፍቅ ልብ ስጠኝ። አሜን! @hymnsofmes @hymnsofmes

Day 3 - Closing program #gcme #indigitous #hack #Degital_mission_mobilization #gcme #indigitous #hack @hymnsofmes
+1
Day 3 - Closing program #gcme #indigitous #hack #Degital_mission_mobilization #gcme #indigitous #hack @hymnsofmes

The annual #hackAddis has started
+8
The annual #hackAddis has started

▫️◽️◻️◽️▫️▫️◽️◻️◽️▫️▫️◽️ ◽️እግዚአብሔርን እንድንፈልግ በግልፅ በቃሉ ታዝዘናል። በዚህ ጉዳይ ላይ ቃሉ "ፈልጉ" ሲለን የጠፋውን ነገር መፈለግ ማለት አይደለም ። አስቀድመን ወደዚህ ግን
▫️◽️◻️◽️▫️▫️◽️◻️◽️▫️▫️◽️ ◽️እግዚአብሔርን እንድንፈልግ በግልፅ በቃሉ ታዝዘናል። በዚህ ጉዳይ ላይ ቃሉ "ፈልጉ" ሲለን የጠፋውን ነገር መፈለግ ማለት አይደለም ። አስቀድመን ወደዚህ ግንኙነት ተጋብዘናል ፤ እግዚአብሔር የት እንዳለ እናውቃለን። አምላክ የሆነ ቦታ እንደጠፋ አድርገን መፈለግ የለብንም። #መፈለግ (Seek) ማለት ኤክስፖዚተር መዝገበ ቃላት እንደሚለው "በመታመን እና በመተማመን ወደ እርሱ መዞር" / "to turn to Him in trust and confidence “ ማለት ነው። ◽️ በዚህ ቃል መሰረት ሁለቱም "መፈለግ" እና "መኖር" የግድ አስፈላጊ መሆናቸውን እናስተውላለን ፤ ትጉ፣ ትጉ እና በትጋት እንድንከታተል “ለመፈለግ” ትእዛዝ ነው። ◽️ እኛ ሰዎች የእግዚአብሔርን አብሮነት እንፈልጋለን፤ ለዚያ ዝግጅት ያለን ግን ጥቂቶች ነን ። እግዚአብሔር ለእስራኤል የንስሓ ጥሪ ሲያደርግ እንዲህ ብሏል፤ "በሕይወት ትኖሩ ዘንድ፣ መልካሙን እንጂ ክፉውን አትፈልጉ፤ ከዚያ በኋላ እንደ ተናገራችሁት፣ የሰራዊት አምላክ እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር ይሆናል" (አሞ 5፥14)። ◽️መልካሙን መፈለግ ዝግጅት ነው፤ ይህ ዝግጅትም ክፉውን መጥላትን፣ ሀጢያትን መራቅ ፣ ዐመፃንም መጠየፍን ያቅፋል። ◽️ እግዚአብሔር ለባሕርይው ከማይመች ነገር ጋራ አይተባበርም፤ ክፋትን ስለሚጠየፍም ራሱን ይሰውራል። ምሕረቱንና ርኀራኄውን ታምነውና ቀናውን ለማድረግ ወድደው ለሚፈልጉትም ይገኝላቸዋል። እርሱ በሚገኝበት ጊዜ፣ ስፍራና ሁኔታም በጎነቱና ባርኮቱ ያጅቡታል። ፀሎት 🙏🏾 ▫️ጌታን በእውነተኛ የልብ ዝግጅት እንድንፈልገው በፀጋው ይርዳን! አሜን!! @hymnsofmes

ሰላም የተወደዳችሁ ኮንፍረንሳችን ከረቡዕ ጀምሮ እንደቀጠለ ነው። ጌታ እጅግ የተወደደ ጊዜ ሰጥቶናል። ዛሬም ከ11:00 ጀምሮ #ከዘማሪ_መሳይ እና #ወንድም_ዮሴፍ_በቀለ በቃል እና በጸሎት ያገለግሉናል
ሰላም የተወደዳችሁ ኮንፍረንሳችን ከረቡዕ ጀምሮ እንደቀጠለ ነው። ጌታ እጅግ የተወደደ ጊዜ ሰጥቶናል። ዛሬም ከ11:00 ጀምሮ #ከዘማሪ_መሳይ እና #ወንድም_ዮሴፍ_በቀለ በቃል እና በጸሎት ያገለግሉናል። ሁላችሁም ተጋብዛችኋል። ተባረኩ

🎵 I'm listening to Egziabher Ayitlenem by Mesay Birhanu on Hasset! Check it out: https://hasset.org