en
Feedback
ማዳኑን አውሩ | ᴘʀᴏᴄʟᴀɪᴍ ʜɪꜱ ꜱᴀʟᴠᴀᴛɪᴏɴ

ማዳኑን አውሩ | ᴘʀᴏᴄʟᴀɪᴍ ʜɪꜱ ꜱᴀʟᴠᴀᴛɪᴏɴ

Open in Telegram

Thank you for your interest to join Our Telegram channel. ▫️The primary function of this channel is : ☞To proclaim our savior JESUS CHRIST through a lifestyle of praise and worship. መዝሙረ ዳዊት 96 2፤ እግዚአብሔርን አመስግኑ ስሙንም ባርኩ፥ ዕለት ዕለትም ማዳኑን አውሩ።

Show more
1 241
Subscribers
No data24 hours
+57 days
+1030 days
Posts Archive
"ቃሉን ለማየትና ለመስማት፣ እነማን የእግዚአብሔር ምክር ባለበት ቆመዋል? ቃሉን ያደመጠ፣ የሰማስ ማን ነው?" (ኤር 23፥18 አመት)
"ቃሉን ለማየትና ለመስማት፣ እነማን የእግዚአብሔር ምክር ባለበት ቆመዋል? ቃሉን ያደመጠ፣ የሰማስ ማን ነው?" (ኤር 23፥18 አመት)

1ኛ ቆሮንቶስ 2፡11 -ይህ የእግዚአብሔር ቃል፤ እግዚአብሄርን የሚገልጥልንን የእግዚአብሔር መንፈስ ኃይል ያሳየናል። ——————————————————— ● ሐሳብ የራስ ነው። ማንም የሚያስበውን ሐሳብ ሌ
1ኛ ቆሮንቶስ 2፡11 -ይህ የእግዚአብሔር ቃል፤ እግዚአብሄርን የሚገልጥልንን የእግዚአብሔር መንፈስ ኃይል ያሳየናል። ——————————————————— ሐሳብ የራስ ነው። ማንም የሚያስበውን ሐሳብ ሌላው ሊያውቀው አይችልም። ሰይጣን እንኳን የሚያድግ ሐሳብ ሊያቀብል ይችላል እንጂ የሰውን ሐሳብ አይመራም። ብቸኛው የሐሳብ ሁሉ መርማሪና አዋቂ እግዚአብሔር ነው። የሰው ሐሳብ በመንፈሱ ብቻ እንደሚታወቅ፣ የእግዚአብሔርም ሐሳብ እንዲሁ በመንፈሱ ብቻ ነው የሚታወቀው፤ "በውስጡ ካለው ከራሱ መንፈስ በስተቀር ከሰው መካከል የአንድን ሰው ሐሳብ የሚያውቅ ማን አለ? እንደዚሁም ከእግዚአብሔር መንፈስ በስተቀር፣ የእግዚአብሔርን ሐሳብ የሚያውቅ ማንም የለም" (1ቆሮ 2፥11)። እንግዲህ፣ እግዚአብሔር መንፈሱን ሲሰጠን ሐሳቡንም ነው አብሮ ያጋራን። ለሕይወትም ሆነ ለእውነተኛ መንፈሳዊነት ሐሳቡን አካፍሎናል። መንፈሱን ለኀይል ከምንፈልገው ባሻገርም፣ ለሐሳቡ—ፈቃድ—ልንፈልገው ይገባል።

𝗜 𝗮𝗺 𝘃𝗲𝗿𝘆 𝗲𝘅𝗰𝗶𝘁𝗲𝗱 𝗮𝗯𝗼𝘂𝘁 𝘁𝗵𝗲 𝗼𝗽𝗽𝗼𝗿𝘁𝘂𝗻𝗶𝘁𝘆 𝗚𝗼𝗱 𝗵𝗮𝘀 𝗴𝗶𝘃𝗲𝗻 𝗺𝗲, 𝗕𝗲𝗮𝘂𝘁𝗶𝗳𝘂𝗹 𝘁
+4
𝗜 𝗮𝗺 𝘃𝗲𝗿𝘆 𝗲𝘅𝗰𝗶𝘁𝗲𝗱 𝗮𝗯𝗼𝘂𝘁 𝘁𝗵𝗲 𝗼𝗽𝗽𝗼𝗿𝘁𝘂𝗻𝗶𝘁𝘆 𝗚𝗼𝗱 𝗵𝗮𝘀 𝗴𝗶𝘃𝗲𝗻 𝗺𝗲, 𝗕𝗲𝗮𝘂𝘁𝗶𝗳𝘂𝗹 𝘁𝗶𝗺𝗲 𝘄𝗶𝘁𝗵 𝗯𝗲𝗮𝘂𝘁𝗶𝗳𝘂𝗹 𝗽𝗲𝗼𝗽𝗹𝗲 𝗳𝗿𝗼𝗺 𝗦𝗵𝗮𝗸𝗶𝘀𝗼. “𝗧𝗿𝘂𝗲 𝘄𝗼𝗿𝘀𝗵𝗶𝗽 𝗶𝘀 𝗮 𝘃𝗮𝗹𝘂𝗶𝗻𝗴 𝗼𝗿 𝗮 𝘁𝗿𝗲𝗮𝘀𝘂𝗿𝗶𝗻𝗴 𝗼𝗳 𝗚𝗼𝗱 𝗮𝗯𝗼𝘃𝗲 𝗮𝗹𝗹 𝘁𝗵𝗶𝗻𝗴𝘀.” 📷𝗥𝗲𝗰𝗮𝗽: 𝗦𝗵𝗮𝗸𝗶𝘀𝗼 𝗙𝘂𝗹𝗹 𝗚𝗼𝘀𝗽𝗹𝗲 𝗰𝗵𝘂𝗿𝗰𝗵 #𝗪𝗼𝗿𝘀𝗵𝗶𝗽_𝘀𝗲𝗺𝗶𝗻𝗮𝗿 𝗙𝗲𝗯 𝟳- 𝟭𝟮

Track-2-Kante-Wichi-ካንተ-ዉጪ-Addishiwot-Feleke-Vol-1.m4a4.57 MB

#ለአንድ_ነገር_ብቻ_መኖር #የአንድ_ነገር_ሰው_ሆኖ_መጨረስ 🌟ፍላጎት መጠንም ሆነ ማለቂያ የለውም፤ ካልገደቡት ይዞ ይሄዳል እንደ ውሃ ይወስዳል። መጠኑን ላወቁበትና ዐይነቱን ለለዩት ደግሞ ክቡር መ
#ለአንድ_ነገር_ብቻ_መኖር #የአንድ_ነገር_ሰው_ሆኖ_መጨረስ 🌟ፍላጎት መጠንም ሆነ ማለቂያ የለውም፤ ካልገደቡት ይዞ ይሄዳል እንደ ውሃ ይወስዳል። መጠኑን ላወቁበትና ዐይነቱን ለለዩት ደግሞ ክቡር መድረሻ አለው። 🌟 ዳዊት በሕይወት ዘመኑ ሁሉ በእግዚአብሔር #ፊት እንዲኖር ጸለየ ። ዳዊት በየቀኑ ከጌታ ጋር የጠበቀ ኅብረት መፍጠር ለድርድር የሚያቀርበው አይደለም። ዳዊት #በመዝሙር 26 : 8 ላይ “ አቤቱ ፣ አንተ የምትኖርበትን ቤት፣ የክብርህም ማደሪያን እወዳለሁ” ሲል ጸለየ። " 🌟የዳዊት ዋነኛ ቅድሚያ የሚሰጠው ከጌታ ጋር ያለው ግንኙነት ነው። ምንም እንኳን ከጠላቶቹ መሸሸጊያ ለማግኘት በምድረ በዳ ቢሆንም ልቡ ግን በማደሪያው ድንኳን ውስጥ የእግዚአብሔርን ውበት ይፈልጋል። 🌟 እንዲህ ብሎ ተቀኘ፤ "እግዚአብሔርን አንዲት ነገር እለምነዋለሁ፤ እርሷንም እሻለሁ፤ ይኸውም በሕይወቴ ዘመን ሁሉ፣ በእግዚአብሔር ቤት እኖር ዘንድ፣ የእግዚአብሔርን ክብር ውበት አይ ዘንድ፣ በመቅደሱም ሆኜ አሰላስል ዘንድ ነው" (27፥4)። 🌟አንድ መሻት፣ ክቡር መሻት፣ የሁልጊዜ መሻት! ከፍላጎት ሁሉ በላይ የሆነው ፍላጎት፣ ከመሻትም ሁሉ በላይ የሆነው መሻት ይሄ ነው እግዚአብሔርን፣ ክብሩንና ማንነቱን መጠጋት፣ ማየትና በዚያው መቆየት። ታላቅ መሻት ታላቁን ትኩረትና ጕልበት ይወስዳል። ለዚህ መሻት የሚውል ትኩረትና አቅም ደግሞ ትርፍ እንጂ ብክነት የለውም። 🙏🏼እግዚአብሔር ያለማቋረጥ እርሱን በመፈለግ እና በትኩረት ተመልክተነው ፤ ለቅድስናው ውበት መገዛት እንድንችል ይርዳን። Join @hymnsofmes

የመሳይ ብርሀኑ አዲስ ነጠላ መዝሙር "እግዚአብሔር አይጥለንም" ከሀሴት የመዝሙር መተግበሪያ ላይ ማግኘት ይችላሉ:: You can get Mesay Birhanu Single song "Egziyabher Ay
የመሳይ ብርሀኑ አዲስ ነጠላ መዝሙር "እግዚአብሔር አይጥለንም" ከሀሴት የመዝሙር መተግበሪያ ላይ ማግኘት ይችላሉ:: You can get Mesay Birhanu Single song "Egziyabher Ayitlenm" on Hasset. 🎵🎶 Listen to Mesay Birhanu Egziabher Ayitlenm on Hasset! Check it out: 👉https://share.hasset.org/song/S0eT14UueokKfkgzmpBC 👉Facebook: https://www.facebook.com/HassetApp 👉Instagram: https://www.instagram.com/hassetapp 👉Telegram https://t.me/HassetMezmurApp

🌟 የምኩራብ አለቃው ኢያኢሮስ፣ "በሞት አፋፍ ላይ" ያለችው ልጁ ላይ እጁን እንዲጭን ጌታን ከለመነ በኋላ ጕዞ ላይ ነበሩ። በመካከል ግን 12 ዓመት ደም ይፈሳት የነበረች ሴት በግርግሩ መካከል እን
🌟 የምኩራብ አለቃው ኢያኢሮስ፣ "በሞት አፋፍ ላይ" ያለችው ልጁ ላይ እጁን እንዲጭን ጌታን ከለመነ በኋላ ጕዞ ላይ ነበሩ። በመካከል ግን 12 ዓመት ደም ይፈሳት የነበረች ሴት በግርግሩ መካከል እንደምንም ብላ የኢየሱስ ክርስቶስን "የልብሱን ጫፍ ነካች"። 🌟 “ #የነካኝ_ማነው “ ይህ ጥያቄ የመንካት አለማወቅን ለማሳየት ሳይሆን ሴቲቱን ለመሳብ እና እምነቷን በይፋ እውቅና ለመስጠት ሲሆን ይህም በተጨናነቀ ሁኔታ ውስጥ የእምነቷን ኃይል በማጉላት ብዙዎች በአካል ሲነኩት ነገር ግን እርሷ ብቻ ፈውስ አግኝታለች።  🌟 ይህንን ያደረገችውም እምነት ስለ ነበራት ነው። ከሕዝቡ ብዛት የተነሣ ከነበረው መጨናነቅና መነካካት በላይ ይሄኛው መንካት የተለየ ሆነ፤ "ኢየሱስም፣ 'የነካኝ ማነው?' አለ" (ሉቃ 8፥45)። 🌟#ብዙ_መጋፋት_ቢኖርም ፣ #ጌታን_የሚነካኩ_ቢበዙም፣ ይሄ መንካት ግን የተለየ ነበር፣ ኅይል ከጌታ እንዲወጣ አድርጓልና። ጌታ በእምነት—በጸሎት፣ በዝማሬ፣ በተማጽኖ፣ በአምልኮ፣ ቃሉን በማሰላሰል—የሚነኩትን ያውቃል፤ እነርሱም መነካካታቸውን 'በሰውነታቸው' (በማንነታቸው) ይረዳሉ ። #እንደ_ቃሉ_የእውነት_መነካት_ይሁንልን። #አሜን @hymnsofmes

G-B-Song-of-the-Week-ስጸልይ-ነፍሴ-ይነቃቃል.m4a4.66 MB

#Mission_Opportunities #Business_As_Mission #UPGs_pray #Worship #Experience_sharing #Connecting - jan 12, 2025 (እሁድ ጥር 4) @ E
#Mission_Opportunities #Business_As_Mission #UPGs_pray #Worship #Experience_sharing #Connecting - jan 12, 2025 (እሁድ ጥር 4) @ Eastridge Church bole medanialem, next to mamas kitchen. - Sunday afternoon 10:00 (local time). come with your friends. #Ethiopia_Mission_Friends

ወደ ቲቶ 2:1 #አንተ_ግን_ሕይወት_ለሚገኝበት ትምህርት የሚገባውን ተናገር። ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ ከታህሳስ 29-30 /2017 ዓ.ም በቡታጅራ ሙሉ ወንጌል ቤ/ክ የአምልኮ ጊዜ እንዲሁም ከከተማው አብ
+4
ወደ ቲቶ 2:1 #አንተ_ግን_ሕይወት_ለሚገኝበት ትምህርት የሚገባውን ተናገር። ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ ከታህሳስ 29-30 /2017 ዓ.ም በቡታጅራ ሙሉ ወንጌል ቤ/ክ የአምልኮ ጊዜ እንዲሁም ከከተማው አብያተ ክርስቲያናት የኳየር መሪዎች ጋር እግዚአብሔር የተባረከን ጊዜ ሰጥቶናል። #ክብር_ሁሉ_ለኢየሱስ_ይሁን። @hymnsofmes

✨ መልአኩ ለዮሴፍ የገለጠው መገለጥ የተለየ ነው፡ ኢየሱስ ህዝቡን፣ አይሁዶችን በጥቅል መልኩ ነጻ እንደሚያወጣ አይደለም። መልአኩ ኢየሱስ የእስራኤልን ግዞት በሮም ያቆማል አላለም። ትንቢቱ ክርስቶስ
✨ መልአኩ ለዮሴፍ የገለጠው መገለጥ የተለየ ነው፡ ኢየሱስ ህዝቡን፣ አይሁዶችን በጥቅል መልኩ ነጻ እንደሚያወጣ አይደለም። መልአኩ ኢየሱስ የእስራኤልን ግዞት በሮም ያቆማል አላለም። ትንቢቱ ክርስቶስ ሕዝቡን ከኃጢአታቸው እንደሚያድናቸው ነው። ✨ዮሴፍ ፈቃዱ፣ ማንነቱና ምንነቱ የሌለበትን ልጅ ማርያም እንደምትወልድ ተነገረው፤ "ወንድ ልጅ ትወልዳለች፤ ስሙንም ኢየሱስ ብለህ ትጠራዋለህ፤ ሕዝቡን ከኀጢአታቸው ያድናቸዋልና" (ማቴ 1፥21)። እግዚአብሔር ያንን ቤተሰብ ሳያስፈቅድ፣ ሐሳቡንና ✨የከበረውን ዕቅዱን አስቀመጠባቸው። በጊዜው የታመኑና የተዘጋጁ ስለ ነበሩ የርሱ ዕቃ ሆኑ። ሕፃኑ ኢየሱስ በዚያ ቤት ቢወለድም፣ ልጅ ሳይሆን ወላጅ ነው የሚሆናቸው። መወለዱም የሰው ልጆችን ሁሉ ከኀጢአት ለማንፃት ነው። ——————————————————— In this Christmas, may people come to Christ in mass. #every_day_Christmas

የዕለቱ ሐሳብ ዮሴፍ ፈቃዱ፣ ማንነቱና ምንነቱ የሌለበትን ልጅ ማርያም እንደምትወልድ ተነገረው፤ "ወንድ ልጅ ትወልዳለች፤ ስሙንም ኢየሱስ ብለህ ትጠራዋለህ፤ ሕዝቡን ከኀጢአታቸው ያድናቸዋልና" (ማቴ 1
የዕለቱ ሐሳብ ዮሴፍ ፈቃዱ፣ ማንነቱና ምንነቱ የሌለበትን ልጅ ማርያም እንደምትወልድ ተነገረው፤ "ወንድ ልጅ ትወልዳለች፤ ስሙንም ኢየሱስ ብለህ ትጠራዋለህ፤ ሕዝቡን ከኀጢአታቸው ያድናቸዋልና" (ማቴ 1፥21)። እግዚአብሔር ያንን ቤተሰብ ሳያስፈቅድ፣ ሐሳቡንና የከበረውን ዕቅዱን አስቀመጠባቸው። በጊዜው የታመኑና የተዘጋጁ ስለ ነበሩ የርሱ ዕቃ ሆኑ። ሕፃኑ ኢየሱስ በዚያ ቤት ቢወለድም፣ ልጅ ሳይሆን ወላጅ ነው የሚሆናቸው። መወለዱም የሰው ልጆችን ሁሉ ከኀጢአት ለማንፃት ነው። ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ In this Christmas, May people come to Christ in mass. #every day Christmas @hymnsofmes

"...እግዚአብሔር የፈቃዱን ዕውቀት በመንፈሳዊ ጥበብና መረዳት ሁሉ ይሞላችሁ ዘንድ ስለ እናንተ መጸለይና መለመን አላቋረጥንም፤" (ቈላ 1፥9 አመት) ✨ ጳውሎስ እሱና ጢሞቴዎስ ያለማቋረጥ ሲጸልዩ እ
"...እግዚአብሔር የፈቃዱን ዕውቀት በመንፈሳዊ ጥበብና መረዳት ሁሉ ይሞላችሁ ዘንድ ስለ እናንተ መጸለይና መለመን አላቋረጥንም፤" (ቈላ 1፥9 አመት) ✨ ጳውሎስ እሱና ጢሞቴዎስ ያለማቋረጥ ሲጸልዩ እንደነበሩ ተናግሯል፣ ምናልባትም ስለ ቆላስይስ ቤተ ክርስቲያን ካወቁበት ጊዜ ጀምሮ ሊሆን ይችላል። በ 1ኛ ተሰሎንቄ 5:16-18 ፣ ጳውሎስ ስለ ጸሎት ያለማቋረጥ ተናግሯል እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ለሁሉም ክርስቲያኖች። እዚህ ክፍል ላይ ጳውሎስ የቆላስይስ አማኞችን ወክሎ የአገልግሎቱ የፀሎት ሸክም አካል አድርጎ አቅርቧል። ✨ የእግዚአብሔር ፈቃድ እንዲፈጸም የሚጸለየውን ያህል እንዲታወቅም መጸለይ ያስፈልጋል። 'በዚህ ጉዳይ ላይ የጌታ ፈቃድ ምንድነው?' ተብሎ ይጠየቃል። የፈቃዱን ዕውቀት ለማወቅ ደግሞም ይጸለያል። ይህም ሰማያዊ ጥበብና ግልጽ መረዳትን የሚፈልግ ነው፤ ጳውሎስ እንዲህ ብሎ እንደ ጻፈ፤ "እግዚአብሔር የፈቃዱን ዕውቀት በመንፈሳዊ ጥበብና መረዳት ሁሉ ይሞላችሁ ዘንድ ስለ እናንተ መጸለይና መለመን አላቋረጥንም" (ቈላ 1፥9)። ✨ ፈቃዱን ለማወቅና ለመረዳት፣ ሌሎችም እንዲሁ የፈቃዱን ዕውቀት እንዲያስተውሉ መጸለይ፣ ፈቃዱን ለመለየትና ለመፈጸም ዐይነተኛ መፍትሄ ነው። ብርሃን ያላገኘ ዐይን ማየት እንደማይችል ሁሉ፣ "መንፈሳዊ ጥበብና መረዳት" ያላገኘ ልብና አእምሮ ፈቃዱን መለየት ይቸገራል። #በመጨረሻም ✨ ኢየሱስን በሁሉም ነገር ለማየት እንድንችል ዘንድ በአካሉ በክርስቶስ ውስጥ በተለያየ መስክ ለሚተጉ እና እያገለገሉ ስላሉ ወንድሞቻችን እና እህቶቻችን ይህ ጥበብ እና ዕውቀት እንዲበዛላቸው ያለማቋረጥ እንድንጸልይ ይፈልጋል። ይህንን እንድንፈፅም ጌታ በሀይሉ ይርዳን። @hymnsofmes #2025

የዘመናችን የቅድስና ተግዳሮት እንዲሁ በድንገት ከሰማይ የዘነበ ወይም ከጥልቁ የፈለቀ አይደለም። መነሻ አለው። መነሻውም የትምህርት መዛባት ነው። ባለፉት ሦስት አሥርት ዓመታት በቤተክርስቲያን ውስጥና በዙሪያዋ የተንሸራሸሩት ስሁት ትምህርቶች ቀስ በቀስ ሾልከው እየገቡና እየተደላደሉ ትውልዱን ለርኩሰትና ለአፍቅሮተ ነዋይ አሳልፈው ሰጥተውታል። በትምህርት የመጣ በሽታ የሚፈወሰው በትምህርት ነው። ይህ የቅድስና ኃይል በሚል ርዕስ በቃሉ አገልጋይ በወንጌላዊ ያሬድ ጥላሁን የተሰጠ ተከታታይ ትምህርት ለበርካታ ጥያቄዎቻችን መልስ የሚሰጥና የቅድስናን ኃይል የሚያስታጥቅ ነው። እንዲከታተሉት ተጋብዘዋል። ©️yaredtilahun https://youtu.be/YXOJM6Y4I9Y

Ketena Hulet Full Gospel Church Location የቀጠና ሁለት ሙሉ ወንጌል ቤተክርስቲያን መንገድ / አቅጣጫ

"በጠባቡ በር ግቡ፤ ወደ ጥፋት የሚወስደው መንገድ ትልቅ፣ በሩም ሰፊ ነውና፤ ብዙዎችም በዚያ ይገባሉ።" (ማቴ 7፥13 አመት) የዕለቱ ሐሳብ ክርስቲያኖች መንገድ ቀያሽ አይደሉም፤ የሚገቡበት በርም ሆ
"በጠባቡ በር ግቡ፤ ወደ ጥፋት የሚወስደው መንገድ ትልቅ፣ በሩም ሰፊ ነውና፤ ብዙዎችም በዚያ ይገባሉ።" (ማቴ 7፥13 አመት) የዕለቱ ሐሳብ ክርስቲያኖች መንገድ ቀያሽ አይደሉም፤ የሚገቡበት በርም ሆነ የሚሄዱበት መንገድ ተቀይሶላቸዋል። እግዚአብሔር አስቀድሞ በኢሳይያስ አፍ እንደ ተናገረ—"የእግዚአብሔርን መንገድ በምድረ በዳ አዘጋጁ"—መንገዱ ተስተካክሎ እውነትና መንገድ የሆነው ጌታ መጣ፤ እርሱም የበሩንና የመንገዱን መጠን ገለጠ፤ "በጠባቡ በር ግቡ፤ ወደ ጥፋት የሚወስደው መንገድ ትልቅ፣ በሩም ሰፊ ነውና፤ ብዙዎችም በዚያ ይገባሉ" (ማቴ 7፥13)። በሩ ጠባብ ስለሆነ ግፊያ የለበትም፣ ለሁሉ ይበቃልና። መንገዱም እንደ በሩ ሰፊ አይደለም። እግዚአብሔር አንድ ስለሆነ፣ ወደርሱ የሚያደርሰው መንገድ አንድ ነው። በየዘመኑ የተነሡ የሃይማኖት መሥራቾች መንገዶችን ቀይሰዋል። እነዚያ መንገዶች ግን ደባሎች እንጂ ዋናዎች አይደሉም። በሩንም ሆነ መንገዱን ለብዙዎቸ ብለን አናሰፈም። በሩ ወደ ጎን ቢጠብም፣ ወደ ሰማይ እጅግ ከፍ ያለ ስለሆነ ለብዙ "ብዙዎች" ይበቃል። በዚያም የሚገቡና የሚሄዱ ትኩረታቸው አንድ ነው። @hymnsofmes

#የዕለቱ_ቃል “ በጌታ በኢየሱስ በኩል ድልን ያገኘና ድሉ የገባው አማኝ ጸንቶ ለመቆም አይቸገርም። “ ጳውሎስ ያስገነዘበው ይህንኑ ነው፤ "ስለዚህ የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ፤ ጸንታችሁ ቁሙ፤ በምንም
#የዕለቱ_ቃል “ በጌታ በኢየሱስ በኩል ድልን ያገኘና ድሉ የገባው አማኝ ጸንቶ ለመቆም አይቸገርም። “ ጳውሎስ ያስገነዘበው ይህንኑ ነው፤ "ስለዚህ የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ፤ ጸንታችሁ ቁሙ፤ በምንም ነገር አትናወጡ። ለጌታ ሥራ ዘወትር የምትተጉ ሁኑ፤ ምክንያቱም ለጌታ የምትደክሙት በከንቱ እንዳልሆነ ታውቃላችሁ" (1ቆሮ 15፥58)። 🔅በምንም ነገር አለመናወጥ እንዴት ይቻላል? ተብሎ ሊጠየቅ ይችላል። የክርስቶስ ትንሣኤ ያስገኘልን ውጤት ግን ለማረፍም ሆነ ለመበርታት፣ ለመሥራትም ሆነ ለመድከም አቅም ይሆናል። የማይናወጥ ሕዝብ ያረፈ ብቻ ሳይሆን የሚተጋም ነው። ድል ነሺው ጌታ ድሉ ውስን ወይም የአንድ ጊዜ አይደለም፤ የዘላለም እንጂ! ስለዚህም በርሱ የሚታመኑ በሁኔታዎች አካሄድ ወይም መወሳሰብ ወይም መባባስ አይናወጡም። ይልቁንም፣ እየታመኑ ይቀጥላሉ፤ እየቀጠሉም ይተጋሉ። 🔅 ጳውሎስ በክርስቶስ ውስጥ እንዳሉ እርግጠኛ ነው። አንድ ቀን ከአብ ጋር ዘላለማዊነትን ወደ ሚኖሩበት ወደ አዲስ የተከበሩ አካላት እንደሚለወጡም ያስረግጥላቸዋል። የቆሮንቶስ ሰዎች በክርስቶስ ስላላቸው እና ምንም እንኳን ድክመታቸው ቢኖርም ጳውሎስ #በእግዚአብሔር_ጸጋ በመተማመን እንዲፀኑ በመናገር ይጠቀልላል። መልካም ቀን 🕊️ @hymnsofmes