471
Subscribers
No data24 hours
+47 days
+1230 days
Posts Archive
ውድ የአማራ ባንክ አ.ማ (በምስረታ ላይ) ባለአክሲዮን:
ባንካችን ከፌደራል ሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ኤጀንሲ ጋር በመተባበር እያከናወነ ያለውን ውክልና የማሰጠት ሂደት በመጪው ቅዳሜና እሁድ ማለትም ህዳር 12, እና 13, 2013 ዓ.ም በአካል በመገኘት እና አክሲዮን የገዛችሁበትን ሰነድ እና መታወቂያ ኦርጅናልና ኮፒ በመያዝ ቀኑን ሙሉ ውክልና ማከናወን እንደምትችሉ ለማሳወቅ እንወዳለን::
ዕጅግ ጠቃሚ መረጃ! አንብቡት እና አጋሩት።
የአማራ ባንክ ምስረታ ሂደት በተመለከተ እጅግ በርካታ ጥያቄዎች እየቀረቡ ይገኛሉ።
የሁላችሁንም ጥያቄዎች መልስ እንደሚከተለው እናቀርበዋለን።
1) ማንኛውም አክሲዮን የገዛ ሰው የአማራ ባንክ መስራች ነው።
ይህ ማለት ባንኩን ሊመሩት የሚችሉ ባለሙያዎች የመምረጥ፥ የመመረጥ፥ የባንኩን ተግባራት የማፅደቅና ውልና ማስረጃ የሚቀርቡ ሰነዶች ላይ በመፈረም በባንኩ ምስረታ ላይ ንቁ ተሳትፎ ማድረግ የሚችልበት ወቅት አሁን ብቻ ነው።
2) አክሲዮን የገዛ ማንኛውም ሰው አማራ ምስረታ ሂደት ሲያስተባብሩ ከቆዩ 34 ግለሰቦች እኩል የመመረጥ፥ የመወከል፥ ውክልና የመቀበል፥ የመምረጥ እና በአጠቃላይ በምስረታው ሂደት ንቁ ተሳትፎ የማድረግ መብት አለው።
3) ለምን ውክልና እንሰጣለን?
በተለያዩ ምክንያቶች የምስረታ ሂደቱ መዘግየቱ የባለአክሲዮኖችን ቁጥር ከ 150,000 አደረሰው። ይህ ቁጥር ጠቅላላ ጉባኤውን በተሳካ ሁኔታ ለማካሄድ አስቸጋሪ ይሆናል። ስለሆነም ባላክሲዮኖች ሰብሰብ ብለው በቡድን አንድ ሰው ቢወክሉ በህዝብ ብዛት ሊኖር የሚችሉትን ችግሮች ያቃልላል ከሚል እሳቤ የተወሰደ መፍትሄ ነው።
ማሳሰቢያ፦
ሀ) 150,000+ አክሲዮን የገዛ ሰው ሁሉ መሥራች ነው።
ለ) በአማራ ባንክ ፕሮጀክት ሲሰሩ የቆፈዩት 34 ግለሰቦች በተለምዶ አደራጅ ይባላሉ እንጅ ስልጣናቸው ማስተባበር ብቻ ነው። አክሲዮን ገዝተው ከሆነ ወይም ውክልና ከተሠጣቸው ግን አደራጅም መሆን ይችላሉ።
4) ማንን እንወክላለን?
ከአማራ ባንክ አክሲዮን የገዛ ማንኛውም ግለሠብ፥ ከባንኩ አስተባባሪዎች ውጭ የሆኑ ግለሰቦችን፥ አክሲዮን የገዙ ባለድርሻዎችን ወይም ከአስተባባሪዎች አንዱን መወከል ይችላሉ።
የባንኩን አስተባባሪዎች (“አደራጆች”) ብቻ እንድትወክሉ የሚያስገድድ ህግ ግን የለም ።
አክሲዮን የገዛ ግለሠብ በቀጥታ /በተወካዩ አማካኝነት በምስረታ ጉባኤው በመገኘት የባንኩን የወደፊት እጣ ፈንታ የመወሰን መብታችሁ እና መልካም አጋጣሚ ያለው አሁን ብቻ ነው ።
ስዚህ ውክልና በግልም ሆነ በቡድን መስጠት እንደሚቻል ሁሉ ውክልና ሳይሰጡ አክሲዮን የገዛ ሰው በቀጥታ ምስረታው ላይ በመገኘት የመምረጥና የመመረጥ መብቱ የተጠበቀ ነው።
በአካል መገኘት ያልቻሉ ባላክሲዮኖች ካሉበት ቦታ ሆነው ባቅራቢያቸው ከሚገኘው ውልና ማስረጃ ፅ/ቤት ውክልና መስጠት ይችላሉ ።
5) በምስረታ ስብሰባ ላይ በቀጥታ ወይም በተወካይ አማካኝነት አለመገኘት መብት ቢሆንም፥ በጠቅላላ ጉባኤው ተገኝቶ አለመምረጥ የመስራችነትን ድምፅ አለመጠቀም ነው። ስብሰባ በተገኙ አባላት ውሳኔ ተገዢ ለመሆን መፍቀድም ነው።
ባንኩን ተገቢ ያልሆነ ሰው እንዲመራው ክፍተት መፍጠርም ነው።
50%+ ካፒታል አክሲዮን የገዙት ባባለአክሲዮኖች በመሰብሰብ ባንኩን ለማቋቋም ኮረም መሙላት አለበት።
6) አክሲዮን የገዛችሁበት ፎርም እና የከፈላችሁበት የባንክ ደረሰኝ የጠፋባችሁ ባለአክሲዮኖች መረጃችሁን ከኘሮጀክት ቢሮ የባለአክሲዮኖች መረጃ ቋት ላይ እንዲጣራላችሁ ማመልከት ትችላላችሁ።
7) ፎርምና ደረሠኝ ስለጠፋባችሁ፥ውክልና ከመሥጠት፤ በአካል ቀርቦ ከመምረጥና ከመመረጥ፥ በምስረታ ላይ ከመሳተፍ አያግዳችሁም።
8) ውክልና የሚሰጠው በየአካባቢው ባሉ የውልና ማስረጃ ቢሮዎች በአካል በመቅረብ ወይም በፍትህ ተቋማት እንጅ አክሲዮን በገዛችሁበት ባንክ አይደለም።
9) በአዲስ አበባና አካባቢው ፤ በድሬዳዋ ፤ በአማራ ክልል የዞን ከተሞች ውክልና የሚሰጠው በፌደራል የሰነዶች ማረጋገጫ እና ምዝገባ ኤጀንሲ ነው ። የውክልና ፎርሞች፥ መታወቂያ ፤ የአክሲዮን ግዢ ፎርም ፤ ገንዘብ የተከፈለበት ደረሰኝ.. ባንኩ ከፌደራል ሰነዶች ማረጋገጫ እና ምዝገባ ኤጀንሲ ስለሚያገኝ እናንተ መላክ አይጠበቅባችሁም
10) ነገር ግን በአማራ ክልል ወረዳዎች ፤ ከአማራ ክልል ውጭ ባሉ ክልሎች ውክልና የሚሰጠው በየክልል ጠቅላይ አቃቢ ህግ ቢሮ ስር ባሉ የሰነዶች ፤ የሲቪል ማህበራት ድርጅቶች እና ጠበቆች ዳይሬክተሬት ባሉ ቢሮዎች ናቸው ። የውክልና ፎርሞችን እና የግል መታወቂያ.. ዶክመንቶች በአማራ ባንክ የፖስታ ሳጥን ቁጥር 149 አዲስ አበባ ብላችሁ መላክ አለባችሁ ።
11) ስለውክልናው ተጨማሪ መረጃ ከአማራ ባንክ ፕሮጀክት ፅ/ቤት፥ በቲቪ ፤ በሬዲዮ እና በየአካባቢው ያሉ የፍትህ ተቋማት ማግኘት ይቻላል።
12) ማንኛውም አክሲዮን የገዛ ግለሠብ፥ ድርጅቶች ወይም ወኪሎቻቸው በባንኩ ጠቅላላ ጉባኤ በመገኘት የባንኩን የወደፊት ስራ አስፈፃሚ ይሆናሉ የሚላቸውን አመራሮች የመምረጥ እና የመመረጥ ሙሉ መብት አለው።
13) የተወካይ ተወካይ ይቻላል ። የሚቻለው ግን የመጀመሪያው ተወካይ ሌላ ሰው የመወከል ስልጣን ካለው ብቻ ነው ።
14) የውክልና ፎርሙን ከውልና ማስረጃ ማግኘት ይቻላል።
15. አንድ ተወካይ የውክልና ፎርሙ እስከቻለ ድረስ 10ም 15ም... ባለአክሲዮኖችን ሊወክል ይችላል ።
16. ውክልና online መስጠት አይቻልም።
አሜሪካን ሃገር ለሚኖሩ ዲያስፖራና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ግን በኢምሲ በኩል online መወከል ይቻላል።
17) የአክሲዮን ሽያጭ የሚያበቃው ህዳር 21፤ 2013 ዓ.ም ነው ።
18) ባንኩ ከተመሰረተ ጀምሮ ባሉት 6 ወራት ወቅት ቀሪ የአክሲዮን ክፍያን መክፈል ይቻላል ።
19) አክሲዮን ወደ ሌላ ሰው ማዛወር የሚቻለው ባንኩ ከተመሰረተ በኋላ ነው ። አሁን ባንኩ ገና በምስረታ ሂደት ላይ ስለሆነ አክሲዮን ከአንድ ነው ወደ ሌላ ማዛወር አይቻልም ።
20) ጠቅላላ ጉባኤው የሚካሄደው አዲስ አበባ ነው።
21) የአክሲዮን ሰርተፊኬት የሚሰጠው ባንኩ ከተመሰረተ በኋላ ነው ።
22) አንድ ባለአክሲዮን በገዛው የአክሲዮን ልክ ድምፅ በመሥጠት መምረጥና መመረጥ መብት አለው።
ለምሳሌ፦የ10,000 ብር የገዛ ሰው 10 ድምፅ አለው።
የ100,000 ብር የገዛ ባላክሲዮን ሲመርጥ 100 ድምፅ ይቆጠርለታል።
Any Question and Suggestion
@Amharabanksbotየአማራ ባንክ ምስረታ ላይ የነቃ ተሳትፎ የምናደርግበት ዕድልና ወቅት አሁን ነው!
በዚህ የምስረታ ወቅት መሳተፍ የባንኩን የወደፊት ህልውና መወሰን ይቻላል።
እንደሚታወቀው ሰሞኑን ባንኩ በውክልና እንዲመሠረት እንቅስቃሴ ተጀምሯል።
ይህ ማለት ባንኩን ለመመስረት፥ የባንኩን የወደፊት አመራር አካላት ለመምረጥ፥ ለመመረጥ፥ በሰነድ ለመፈረም... ጠቅላላ ጉባኤ ለማካሄድ ከ 150,000 ባለአክሲዮኖች በላይ ለማስተናገድ አመች ስለማይሆን አስርም ይሁን አስራ አምስት ባለአክሲዮኖች በቡድን አንድ ለሚያውቁት ግለሰብ በመወከል፥ በጉባኤ ላይ የሚገኘውን የባለአክሲዮኖች ቁጥር ለመቀነስና ምስረታውን ማቀላጠፍ ስለሚፈለግ ነው።
ማሳሰቢያ
በሚዲያ ላይ ባደራጅነት ከተዘረዘሩት ግለሰቦች ውጭ ሌላ ሰው መወከል ይቻላል።
እራሳችሁም(አክሲዮን የገዛ ሰው)በቀጥታ መሳተፍ ትችላላችሁ።
ባለአክሲዮኖች የአማራ ባንክን ወደፊት በስራ አስፈፃሚነት እና በየደረጃው ያሉ የባንኩን አመራር አካላት ለመምረጥ፥ ለመመረጥ፥የባንኩን የወደፊት አቅጣጫና ተግባራት ለመወሰንና በሰነዶች ለመፈረም በዚህ ወቅት ንቁ ተሳትፎ ማድረግ ተገቢ ነው።
የአመራር አካላት የሚመረጡት በባለአክሲዎኖች አብላጫ ድምፅ ነው።
ለምሳሌ የ 10ዐ,ዐዐዐ ሽ ብር አክሲዮን የገዛ ግለሰብ 100 ድምፅ ይኖረዋል ማለት ነው። ድምፁን ጉባኤ ላይ ለሚጠቆሙት ዕጩ ተመራጮች መስጠት ነው። ውሳኔዎች በድምፅ ብልጫ ይፀድቃሉ።
ከአደራጆች ውጭ ያለ ሰው ቢወከል ልምድ ያላቸውን ሰዎችን ለማካተት መልካም አጋጣሚ አሁን ነው።
የምትወክሉ ከሆነ ግን የሚወከለው ሰው በባንክ ሙያ ልምድ ያለው፥ የፕሮጀክት ስራ፥ የክሲዮን ምስረታ፥ ወዘተ ልምድ ያለውና ከፖለቲከኛ እና ጎጠኝነት ስሜት የፀዳ ምስጉን ግለሠብ ቢሆን ለባንኩ ጠቃሚ ይሆናል።
የባንኩን እጣ ፋንታ ለመወሰን፥ ለመምረጥ፥ ለመመረጥ፥ ብቃት ያላቸው ባለሙያዎች እንዲመሩት ለማድረግ... በገዛችሁት አክሲዎን ልክ ድምፅ በመስጠት ወሳኙ ዕድል አሁን ነው።አማራ ባንክ ለምስረታ ቅድመ ዝግጅት እያደረገ ይገኛል።
የአማራ ባንክ ምስረታ በስኬት እንዲጠናቀቅ የባለአክሲዮኖችም ሆነ የሁላችንም ንቁ እና መልካም ተሳትፎ ወሳኝነት አለው።
አማራ ባንክ የምስረታ ጉባኤውን ለማካሄድ አክሲዮን በገዙ መሥራቾች፥ በሙያ ዘርፉ ልምድና የትምህርት ዝግጅት ባላቸው ግለሰቦች እና በ 34 አደራጆች አማካኝነት እንዲካሄድ ተፈቅዷል።
አክሲዮን የገዙ ግለሰቦች በቀጥታ በአካል በመገኘት ወደፊት የአማራ ባንክን ሊመሩ የሚችሉ ስራ አስፈፃሚዎችን እና የባንኩን ተግባራት ለመወሰን ድምፅ መሥጠት ይችላሉ።
ሆኖም ከ150,000 በላይ የመሥራች ባለአክሲዮኖች ጉባኤ ለማካሄድና ውልና ማስረጃ ቀርቦ በሰነድ ለመፈረም ከሰው ብዛት አኳያ የሚኖረውን ጫና ለመቀነስ ሲባል ምስረታው በቡድንና በተናጠል የሚሰጥ ውክልና አማካኝነት እንዲካሄድ እንቅስቃሴዎች ተጀምረዋል።
ውክልና ለምን ይሰጣል?(የተወካይ ተግባራት)
1) ውክልና የምትሰጡት ባለሙያ/ግለሠብ እንደራሳችሁ ሆኖ በውሳኔዎች ላይ ድምፅ እንዲሰጥ፥ እንዲመርጥ/እንዲያስመርጥ ነው።
ይህ ማለት ወደፊት አማራ ባንክን በዋና ስራ አስፈፃሚነት፥ እና በአስተዳአዳሪነት ሊመሩ የሚችሉ በዘርፉ ልምድና የትምህርት ዝግጅት ያላቸውን ባለሙያዎች በነፃነትና በፍትሃዊነት ለመምረጥ፥ የባንኩን ተግባራትና የወደፊት አቅጣጫ ለመወሰን… ጉባኤ ሲካሄድ ድምፅ እንዲሰጥላችሁ እና
2) ተወካዩ ውልና ማስረጃ በአካል ቀርቦ የመመስረቻ እና የመተዳደሪያ ሰነዶች ላይ እንዲፈርምላችሁ ውክልና ትሰጡታላችሁ።
ውክልና ለማን ይሰጣል?
1) ማንኛውም የመምረጥና የመመረጥ መብት ያለው ህጋዊ ግለሰብ መወከል ይቻላል።
እንደ አማራ ኢኮኖሚክ ቲንክ ታንክ አስተያየት ደግሞ ተወካዮች አክሲዮን የገዙ ከሆነ የመመረጥም ዕድል ስለሚኖራቸው፦ በባንክ የሙያ ዘርፍ፥ በአክሲዮን ምስረታ፥ ተቋማትን በማደራጀት ልምድ እና የትምህርት ዝግጅት ያላቸው፥ አማራ ባንክ ምስረታ በተቀላጠፈ ሁኔታ፥ በብሄራዊ ባንክ መሥፈርት መሠረት በአጭር ጊዜ ውስጥ ብቃት ባላቸው ባለሙያዎች እንዲመሠረት ቅን ፍላጎት ያለው ግለሠብ፥ የፖለቲካ ድርጅት ስር/አባል ሆነው ተፅኖ የማይፈጥሩ፥ በህብረሰሰቡ ዘንድም ምስጉን ቢሆኑ…በምስረታ ሂደቱ ላይ ንቁ ተሳታፊ በመሆን አስተዋፅኦ የማድረግ ዕድል ይኖራዋል የሚል ዕምነት አለን።
2) አደራጆች፦ በአማራ ባንክ ምስረታ ሂደት ሲሳተፉ ከቆዩ 34 ግለሠቦች የምትፈልጉትን አንድ ግለሰብ መወከል ሌላው አማራጭ ነው።
የባለአክስዮኖች/የወካዬች መብት
ሀ) አክሲዮን የገዛ ግለሠብ በቀጥታ ስብሰባ በመሳተፍ የባንኩን አመራር ለመምረጥ፥ ድምፅ መሥጠት፥በአካል ተገኝቶ በሰነድ የመፈረም ሙሉ መብት አለው።
ለ) ከአደራጆች ውጭ ያለ እንደእራሴ ሆኖ ይሰራልኛል ብለው ያሰቡትን ሌላ ማንኛውም ግለሰብ የመወከል መብት አላቸው ፤
ሐ) በተጠናል ወይም የቡድን ውክልና መስጠት ይቻላል ።
አንድ ባለአክሲዮን አንድ አደራጅ የመወከል መብት አለው፤
ወይም በጋራ(ለምሳሌ 10 ባለአክሲዮኖች) ስማቸውን ለዚህ አገልግሎት በተዘጋጀው አንድ የውክልና ፎርም ላይ በማስፈር የሚያምኑበትን አንድ ባለሙያ/ግለሰብ/ወይም አደራጅ መወከል ይችላሉ።
ማሳሰቢያ፦
አንድ ባንክ በባለሙያዎች ሲደራጅ እና ሲመራ፦
i) ጊዜን ገንዘብ እና የሠው ሃይል ወጭ በመቀነስ በብቃት ይመሠረታል፤
ii) ከዚህ ቀደም እንደታየው ሁሉ በልምድና ብቃት ማነስ ምክንያት አላስፈላጊ መጓተትና ዝርክርክ ሂደቶችን ያስቀራል፤
iii) በሙያ ብቃት፥ በቴክኖሎጂ፥በአገልግሎት...ገብያ ላይ ተወዳዳሪ እንዲሆን መሠረት ይጥላል፤
iv) ከፖለቲከኞች እና ጎጠኞች ተፅኖ ነፃ ሆኖ በቅጥር፥ በግዥ አፈፃፀም ሂደቶች፥ በብድር አሰጣጣ፥ እና በሁሉም ውሳኔዎች አድሎአዊ አሰራር የሌለበት፥ በሙያ፥ በችሎታ እና በብሄራዊ ባንክ/በአለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ህግ መሥፈርት የሚገዛ ስኬታማ ተቋም ለመሆን ያስችለዋል።
ስለሆነም አንድ ባላክሲዮን/ወካይ ወይም ተወካይ በጠቅላላ ጉባኤ ላይ ተገኝቶ ወደፊት የአማራ ባንክን ሊመሩ የሚችሉትን ባለሙያዎች ለመምረጥ ድምፅ ሲሰጡ የብሄራዊ ባንክ መሥፈርቶችን ግምት ውስጥ ያስገባ መሆን እንዳለበት መገንዘብ ያስፈልጋል። ይህ እንዲሆን ደግሞ የምንወክለውን ግለሰብ በጥንቃቄ መምረጥ እንዳለብን መረዳት አለብን።
ውክልና የሚሰጥባቸው ቦታዎች፦
1) በአዲስ አበባ እና አካባቢዋ እና ድሬዳዋ፦
ቀን፦ከህዳር 1-15 ፥ 2013 ዓም
ቦታ፦ በየአካባቢያችሁ በተለይ በየክፍለ ከተማው ባሉ የፌደራሉ ውልና ማስረጃ ፅ/ቤት ለአማራ ባንክ ብቻ የተዘጋጀ መሥኮት በመቅረብ መፈረም፥
2) በአማራ ክልል የዞን ከተሞች፦
ቀን፦ከህዳር 16-30 ፤ 2013 ዓም
ቦታ፦ ወደፊት በሚመቻቹ የፌደራሉ ውልና ማስረጃ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ሲሆን ትክክለኛ ቦታዎች በቅርቡ ይገለፃል።
3) በአማራ ክልል የወረዳ ከተሞች እና በሌሎች ክልሎች ፦
ቀን፦ከህዳር 1-30 ፤ 2013 ዓም
ቦታ፦ በየአካባቢያችሁ የሚገኙ የወረዳ የውልና ማስረጃ አገልግሎት የሚሰጡ የፍትህ ተቋማት ውክልና በአካል ቀርቦ መሥጠት፥ የውክልናውን ወረቀት በሚከተለው አድራሻ መላክ አለበት፤
ለአማራ ባንክ አማ
የፖስታ ሳጥን ቁጥር 149
የአዲስ አበባ
4) በውጭ አገር የምትኖሩ ዳያስፖራ ኢትዮጵያዊያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን
ከላይ በተጠቀሱት የጊዜ ገደብ ውስጥ ሆኖ በምትኖሩበት አገር ኤምባሲ በመቅረብ መወከል ይቻላል ።
ውክልናውን ለመስጠት የሚያስፈልግ ዶክመንት፦
ሀ) የታደሰ የቀበሌ መታወቂያ፤ ወይም መንጃ ፈቃድ ወይም ፓስፖርት
ለ) አክሲዮን ስትገዙ የሞላችሁት የአማራ ባንክ ፎርም እና ገንዘቡን ገቢ ያደረጋችሁበት የባንክ ደረሰኝ ።
ሐ) ለህፃናት አክሲዮን ከገዛችሁ የልደት ሰርተፊኬታቸው ።
አማራ ባንክ አትርፈው የሚበለፅጉበት!!!!
Share በማድረግ ላልሰሙት እናሰማ!!!አማራ ባንክ አክሲዮን ማህበር የመሥራች ጉባኤውን በውክልና ለማካሄድ መወሰኑን አደራጅ ኮሚቴው ገለፀ❗
ባንኩ ምስርታ ጉባኤውን በውክልና ማካሔድ የወሰነበት ዋና ምክንያት የአባላቱ ቁጥር በጣም ከፍተኛ በመሆኑ እና ወቅቱም በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ጉባዔ ለማካሄድ አስቸጋሪ በመሆኑ ነው ብሏል።
የውክልና አሰጣጡ ከህዳር 1 እስከ ህዳር 30/2013 ዓ.ም ይጠናቀቃል፤ የምስረታ የጉባኤው ቀንም ወደፊት ይገለጻል ተብሏል። የባንኩ አደራጅ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ መላኩ ፈንታ እንዳሉት በምስርታ ላይ ያለው የአማራ ባንክ አክሲዮን ማህበር የአክሲዮን ሽያጭ ከጀመረበት ከነሃሴ 11/2011 ዓ.ም እስከ ጥቅምት 2013 ዓ.ም ድረስ የተፈረመው ወይም ቃል የተገባው የአክሲዮን ሽያጭ 6 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር ደርሷል፤ የተከፈለው ደግሞ 4 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር በላይ መድርሱን አስታውቀዋል።
የባንኩ ምሥረታ በተለያዩ ምክንያቶች ቢዘገይም ሁሉንም አሳታፊ በሆነ መንገድ አክሲዮን መሸጥ በመቻሉ የባንኩን የካፒታል አቅም አሳድጓል ያሉት አቶ መላኩ በሽያጩ መሳተፍ ላልቻሉ የህብረተሰብ ክፍሎችም እድል ተፈጥሯል ብለዋል። የአክሲዮን ሽያጭ የመዝጊያ የመጨረሻ ቀኑ ህዳር 21/2013 ዓ.ም መሆኑን ጠቁመው ባለው ቀናት አክሲዮን መግዛት የሚፈልግ ሰውም እንዲሳተፍ ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡
በግዥውም የውጭ ዜጋ ሆነው የትውልደ ኢትዮጵያውያን መረጃ የያዙ ሰዎች በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ በአቢሲኒያ ባንክ፣ በአዋሽ ባንክ እና ዳሽን ባንክ አክሲዮን መግዛት እንደሚችሉ ተገልጿል፡፡ በዜግነት ኢትዮጵያዊ የሆኑ ደግሞ በአባይ ባንክ ፣ በአቢሲንያ ባንክ፣ አክሲዮን ማህበር፣ በአንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ፣ በዳሽን ባንክ ፣ አዋሽ ኢንተርናሽናል፣በኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ፣ በህብረት ባንክ፣ በንብ ኢንተርናሽናል በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እንዲሁም በቡና ኢንተርናሽናል መግዛት ይችላሉ ተብሏል።
የአክሲዮን ገዥዎች ቁጥርም ከ155 ሽህ በላይ መድረሱ ተመልክቷል።
አማራ ባንክ
አማራ ባንክ፤አትርፈው የሚበለፅጉበት!
Facebook account share, like and follow
https://www.facebook.com/አማራ-ባንክ-አማAmahara-bank-sc-124827542252667/
በምስረታ ላይ ያለው አማራ ባንክ አ.ማ. የመስራቾች ጠቅላላ ጉባኤ ዝግጅት ወቅታዊ መረጃ❗️
✔️- አክስዮን የገዙ ባለአክስዮኖች ቁጥር 150‚000 (አንድ መቶ ሃምሳ ሽህ) ሰዎች፤
✔️- እስካሁን የተፈረመ ካፒታል (Subscribed Capital) ብር 6,300,000,000.00 (ስድስት ቢሊየን ሶስት መቶ ሚሊየን ብር)፤
✔- በጥሬ ገንዘብ የተከፈለ ካፒታል (paid up) ብር 4,700,000,000.00 (አራት ቢሊየን ሰባት መቶ ሚሊየን ብር)፤
ባንኩ መስራች ጉባኤውን በኮቪድ19 ወረርሽኝ ስጋት በታወጀው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እና የባንኩ ባለአክስዮኖች ቁጥር ከአንድ መቶ ሃምሳ ሽህ በላይ በመሆናቸው ምክንያት ጉባኤውን በመደበኛ ሁኔታ ለማከናወን ሳይችል ቆይቷል፡፡
ባንኩ ካለው የባለአክስዮኖች ቁጥር አንጻር እና ከወቅቱ የኮሮና ወረርሽኝ አኳያ መስራች ጉባኤውን በመደበኛ ሁኔታ ለማድረግ ስላልተቻለ፣ መስራች ጉባኤውን በውክልና አሰራር ለማከናወን የባንኩ አደራጆች ጉዳዩ ከሚያገባቸው የመንግስት መስሪያ ቤቶች እና የሥራ ሃላፊዎች ጋር ስኬታማ ውይይት ያደረጉ ሲሆን፣ አሰራሩን ስራ ላይ ለማዋል የሚያስችል ሰፊ ዝግጅት ሲያደርጉ ቆይተዋል፡፡
የባንኩ አደራጆች ዝግጅታቸውን ማጠቃለላቸው የተሰማ ሲሆን፣ ስለ መስራች ጉባኤው ዝግጅት እና የውክልና አሰራሩ ስራ ላይ ስለሚውልበት ሁኔታ በቅርቡ መግለጫ እንደሚሰጡ ይጠበቃል።
አደራጆቹ ዛሬ በዕለተ ሰንበት እሁድ ቀን በኢንተር ኮንቲኔንታል ሆቴል ስብሰባ ይደረጋል።
👉 ውድ ቤተሰቦች አስተያየታችሁን እና በቀጣይ ምን መደረግ የምትሉትን ሀሳብ አስቀምጡ? http://t.me/Amharabanksbot
አማራ ባንክ የተፈረመ ካፒታሉ 6,213,836,423 ብር ነው ። ይህ ዶላሩን ሳይጨምር ነው ።
Facebook account share, like and follow
https://www.facebook.com/አማራ-ባንክ-አማAmahara-bank-sc-124827542252667/
በአማራ ባንክ ምንም ጥርጥር አይግባችሁ፤ የተገነባው በጠንካራ አለት ላይ ነው። ንቁና ትገህ የአማራ ልጆች በደንብ እያስኬዱት ነው። ለምን በቅርብ አልጀመረም ለምትሉ
የአማራ ባንክ አክሲዮን የገዙ ሰዎች ብዛት ከ150,000 በላይ መሆናቸው አጃኢብ ቢያስብልም ዋናውን የቦርድ አባላት ለመምረጥ ቢያንስ 60-70% የሚሆን አባል መገኘት ስላለበት ነው። ይህን ለማድረግ የመሰብሰቢያ ቦታ ስታዲየም ካልሆነ በቀር ወይም ጃን ሜዳ መሆን ስላለበት፤ በእነዚህ ቦታ እንኳ ስብሰባውን ለማስኬድ ቢታሰብ የኮቪድ ኮማንድ ፓስት አዋጅ ስለማይፈቅድ እገዳው እስኪነሳ እየተጠበቀ እንጂ ከሌላ አንግል እንዳልሆነ ልብ በሉ።
አማራ ባንክ የእኛ የሁላችን ባንክ ነው!!!
አማራ ባንክ ዘመን ተሻጋሪ የህዝብ አለኝታ ባንክ ነውና በድጋሜ እላለሁ ስጋት አይግባችሁ!!!
የተከበራችሁ የአማራ ባንክ ቤተሰቦች እባካችሁ ከአጭበርባሪዎች ተጠንቀቁ!!
"ሸር በማድረግ እስከ ግንቦት 20 ይሄን ፅሁፍ ለ50 ሰው ሼር ያደረጉ 100 ሰዎችን ለያንዳዳቸው የ10,000ብር ስጦታ ያዘጋጅን መሆኑን ስንገልፅ በታላቅ ደስታ ነው::" የሚል አጭበርባሪዎች አሉ እባካችሁ ተጠንቀቁ!!
አማራ ባንክ አ.ማ
http://amharabank.com.et
❸ አንድ ትውልደ ኢትዮጵያዊ በዘመድ ስም አክሲዮኑን ለመግዛት እና በኋላ ወደራሱ እንዲዞርለት ቢፈልግ ምን ያደርጋል?
▾
የብሔራዊ ባንክ መመሪያ ቁጥር 73/2020 በሚያዘው መሠረት አንድ ሰው የገዛውን አክሲዮን ስለማዘዋወር ሲያወሳ :-
➻ አንድ ኢትዮጵያዊ የገዛውን አክሲዮን ለትውልደ ኢትዮጵያዊ በውርስ አሊያም በሽያጭ ሊያዘዋውር ይችላል። በስጦታ ማዘዋወር ግን አይችልም።
☝ ሆኖም አንድ የውጭ ዜግነት ያለው ትውልደ ኢትዮጵያዊ ከአንድ ኢትዮጵያዊ አክሲዮን ሲገዛ የአክሲዮን መጠኑን ዋጋ በውጭ ምንዛሬ የወቅቱ ተመን አስልቶ መክፈል ይኖርበታል። ትውልደ ኢትዮጵያዊ የአክሲዮን ግዢን በብር መግዛት አይችልምና።
አንድ ትውልደ ኢትዮጵያዊ በዘመድ ስም አክሲዮኑን ለመግዛት እና በኋላ ወደራሱ እንዲዞርለት ቢፈልግ ምን ያደርጋል? ወደሚለው ጥያቄ ስንመጣ : በህግ ባለቤት ሆኖ አክሲዮን የተገዛለት ሰው አክሲዮኑን ወደ ትውልደ ኢትዮጵያዊ በሽያጭ አሊያም በውርስ ለማስተላለፍ ፈቃደኛ እስከሆነ ድረስ አክሲዮኑን በሽያጭ አሊያም ውርስ ሊያስተላልፍ ይችላል።
ወቅቱ የምንዛሬ ተመን ባንኩ ዘንድ በመቅረብ አክሲዮኑ በሽያጭ ሲዘዋወር ገዢው ትውልደ ኢትዮጵያዊ በውጭ ምንዛሬ ከፍሎ አክሲዮን ባለቤት ሲሆን ለሻጩ በብር ገንዘቡ ይከፈላል።
❷ የውጭ ዜግነት ያላቸው ትውልደ ኢትዮጵያውያን በአገር ቤት ወኪል ሳይኖራቸው መግዛት ይችላሉ ወይ?
▾
በብሔራዊ ባንክ መመሪያ መሠረት የአክሲዮን ግዢው የሚፈፀመው በኢትዮጵያ መልክአም ምድር ውስጥ ብቻ ነው። ስለሆነም በውጭ አገር የሚኖር ትውልደ ኢትዮጵያዊ ገንዘቡን በተመረጡት ባንኮች የSwift code እና ለአክሲዮን ግዢው በተከፈቱ የሂሳብ ቁጥሮች በማስገባት : ኢትዮጵያ ውስጥ አክሲዮኑን ፈርሞ የሚገዛላቸው ወኪል ያስፈልጋቸዋል።
ወኪል የማያስፈልጋቸው : -
ሀ) ገንዘቡን በswift code እና የባንክ ሂሳቦች አስገብተው አስገቢው ትውልደ ኢትዮጵያዊ አገር ውስጥ ከመጣ ወይም በአካል ለመፈረም ከቻለ ነው። (ይሔም በቀጣይ የባለአክሲዮኖች ስብሰባ ለመሳተፍና ድምፅ ለመስጠት የማይገኙ ከሆነ ወኪል ያስፈልጋቸዋል። አለበለዚያ የጠቅላላ ጉባኤ ውሳኔዎች በሌሉበት ይወሰናሉ: ይፀድቃሉ።)
ለ) ኑሯቸውን በአገር ቤት ያደረጉና የDiaspora account ያላቸው ትውልደ ኢትዮጵያውያን የሚገዙበትን ገንዘብ መጠን ከDiaspora account ወደ escrowed account በማዘዋወር ራሳቸው በአካል ግዢውን ከፈፀሙ ወኪል አያስፈልጋቸውም።
የውክልና አሠራርን በተመለከተ :-
ሀ) ውክልናው ካሉበት አገር ኤምባሲ ተሞልቶ ወኪል የሆነው ሰው አዲስአበባ ከሚገኘው ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በአካል ቀርበው ውክልናውን ማረጋገጥ ይኖርባቸዋል።
ለ) የሚወክሉትን ሰው በውስን ጉዳዮችም መወከል ይችላሉ። " በስሜ የተለያዩ አክሲዮኖችን እንዲገዛ ÷ ሰነዶች ላይ እንዲፈርም ÷ በአክሲዮን ጉባኤዎች እንዲሳተፍና ድምፅ እንዲሠጥ" ወዘተ በሚል መወከል ይቻላል።
ሐ) የተወከለው ሰው ወደባንኮች ሄዶ አክሲዮኑን ለመግዛት ወካይ ትውልደ ኢትዮጵያዊ በswift code ገንዘብ ገቢ ያደረጉበትን ደረሰኝ : የውክልና ፎርም እና ቢጫ ካርድ ቅጂ ማቅረብ ይኖርባቸዋል። (እነዚህን ፎቶ ግራፍ አንሰተው ወይም በemail ለወኪል መላክ ይችላሉ።)
--
ለአክሲዮን ገዢ የዲያስፖራ አባላት ሶስት ጥያቄዎች ተጨማሪ ማብራሪያ
(ዝርዝር ጉዳዮችን ከላይ ከተያያዙት የአማራ ባንክ መግለጫ እና የባንክ Instruction ሰነዶች ይመልከቱ)
👇
❶ የውጭ ዜግነት ያላቸው ትውልደ ኢትዮጵያውያን አክሲዮን ለመግዛት ገንዘብ የሚከፍሉት እንዴት ነው?
▾
በኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ መመሪያ ቁጥር 73/2020 መሰረት ትውልደ ኢትዮጵያውያን የውጭ ሀገር ዜጎች የአክስዮን ግዥውን የምትፈጽሙት፦
1ኛ. በአሜሪካን ዶላር፣ በእንግሊዝ ፓውንድ፣ በዩሮ እና የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ተቀባይነት አላቸው ብሎ በሚያሳውቃቸው የሌሎች ሀገራት ገንዘብ ነው፤
2ኛ. ክፍያውን መፈጸም የምትችሉት፦
- ከምትኖሩበት ሀገር በባንክ በኩል በሚላክ የውጭ ምንዛሬ፤
- ወይም ኢትዮጵያ ውስጥ ካላቹህ የዲያስፖራ አካውንት /from non-residence foreign account/ በማዘዋወር፤
ማለትም ሀገር ውስጥ ካላቹህ የዲያስፖራ አካውንት /Non-resident Foreign Account/ ወደ አማራ ባንክ የውጭ ምንዛሬ አካውንት /Foreign Currency Escrow Account/ የአክስዮን ግዥውን ክፍያ እና የአገልግሎት ክፍያውን የውጭ ምንዛሬ በማስተላለፍ፣ ክፍያውን መፈጸም ትችላላቹህ።
- ወይም ኢትዮጵያ ውስጥ በውጭ ምንዛሬ የትርፍ ክፍፍል ማግኝት ከምትችሉበት ኢንቨስትመንት ከምታገኙት ትርፍ ላይ /Dividend generated from investment activities deemed eligible for repatriation/ እና በባንክ በኩል ከሚተላለፍ ክፍያ ላይ ብቻ ነው፤
➻ በብር መግዛት አይችሉም
➻ አገር ቤት በአካል ቢገኙም በውጭ ምንዛሬ በጥሬ ገንዘብ መግዛት አይችሉም። Electronic transfer የግድ ነው።
3ኛ. የባንክ ደረሰኝ /credit advice/ ማቅረብ ግዴታ ነው፤ ደረሰኙ የአክስዮን ገዥውን ማንነት፣ የገንዘቡን መጠን እና የክፍያውን ምክንያት መግለጽ አለበት።
--
