en
Feedback
Bahir Dar | ባህር ዳር

Bahir Dar | ባህር ዳር

Open in Telegram
471
Subscribers
No data24 hours
+47 days
+1230 days
Posts Archive
አማራ ባንክ(አባ) በይፋ ተመሠረተ።
አማራ ባንክ(አባ) በይፋ ተመሠረተ።

ውድ የአማራ ባንክ ባለአክሲዮኖች ባንካችን ነገ የካቲት 21: 2013 ዓ:ም በጎልፍ ክለብ የመስራቾች ጉባኤ ያደርጋል:: ለዚህ ታሪካዊ ቀን በመድረሳችን እንኳን ደስ አላችሁ::

አማራ ባንክ/አባ/ ለነገው ዝግጅት
+4
አማራ ባንክ/አባ/ ለነገው ዝግጅት

መልካም ዜና! አማራ ባንክ የፈራሚዎችን ጠቅላላ ጉባኤ እንዲያደርግ በብሔራዊ ባንክ ተፈቅዷል።
መልካም ዜና! አማራ ባንክ የፈራሚዎችን ጠቅላላ ጉባኤ እንዲያደርግ በብሔራዊ ባንክ ተፈቅዷል።

ውድ የአማራ ባንክ አ.ማ (በምስረታ ላይ) ባለአክሲዮኖች የውክልና መስጫ ጊዜው መጨረሻው ቀን ታህሳስ 15 2013 ዓ:ም ጥቂት ቀናት ብቻ ቀርተውታል:: እባክዎን በቀሩት ቀናት ውክልናዎን ይስጡ::

የባንክ አክሲዮን ምስረታ ሂደት ቅደም ተከተል ከ170,000 በላይ ባለ አክሲዮኖች የተሳተፉበት አማራ ባንክ አማ የአክሲዮን ሽያጭ ከ9 ቢሊዩን ብር ካፒታል በላይ በመሠብሰብ በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል። የሽያጭ ክንውኑ እንዲሳካ የሁሉም ባለ ድርሻ አካላት ርብርብ ከፍተኛ አስተዋኦ ነው። ባንኩ ቅርንጫፍ ከፍቶ አገልግሎት እስኪጀምር ድረስ ለሚኖሩት ቀሪ ስራዎች የባለሙያ ቀጥተኛ ተሳትፎ አስገዳጅ ጉዳይ መሆኑን ተገንዝበን ፕሮጀክቱን በሁለት ዕግሩ እንዲቆም በቀጣይ ስራዎች በንቃት መሳተፍ አለብን ። ለግንዛቤ ይሆን ዘንድ፥ የተከናወኑ እና ቀሪ የባንኩ ምስረታ የስራ ሂደቶች በዳሰሳው የሚከተሉት ናቸው። 1) የባንክ አክሲዮን ለማቋቋም የተስማሙ አስተባባሪዎች ተሰብስበው ረቂቅ መተዳደሪያ ደንብ ሰነድ ማርቀቅ፤ (በ2011 ዓ.ም የተሰራ) 2) የአክሲዮን ድርጅቱን የንግድ ስም ማውጣት፤( በ2011 ዓ.ም የተሠራ) 3) የንግድ ስም በንግድ እና ኢንደስትሪ ማስመዝገብ( የካቲት 09 ቀን 2011 ተከናወነ) 4) የመጀመሪያ የአስተባባሪዎች ጉባኤ ማካሄድ( ግንቦት 2011 ዓ.ም የተከናወነ) 5) አማራ ባንክ አክሲዮን ካፒታል መሠብሰብ ይችል ዘንድ አላማውን አቅርቦ ባንክ ሂሳብ ቁጥር እንዲከፍት በብሄራዊ ባንክ ማስፈቀድ ( ነሃሴ 2011 ተከናወነ) 6) የአክሲዮን ሽያጭ ባንክ አካውንት መክፈትና የሽያጭ በማስታወቂያ በመንገር ባንክ ለመመስረት የሚያስችል ካፒታል መሠብሰብ (ከመስከረም 2012 ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ ተከናወነ) ቀጣይ (ቀሪ)ክንውኖች፦ 7) አማራ ባንክን ለመመስረት የመሥራቾች ጠቅላላ ጉባኤ በማካሄድ ባንኩን ሊመሩ የሚችሉ ከ9-13 የሚደርሱ እጩ የቦርድ አባላትን በመጠቆም መምረጥ/ማስመረጥ እና በባንኩ የወደፊት ተግባራት ላይ ተወያይቶ በሰነድ በመፈረም ውልና ማስረጃ ማፅደቅ። 8) በጠቅላላ ጉባኤ የተመረጡት የቦርድ አባላት ፥ ዋና ስራስኪያጅ ወዘተ ለብሄራዊ ባንክ በመላክ ሹመታቸው እንዲፀድቅ መከታተል፤ ሹመታቸው የፀደቀው የባንኩ አዲስ አመራር አካላት በጋዜጣ ከወጣ በኋላ ስራቸውን በይፋ ይጀምራሉ፤ ቀጥሎ… 9) ለባንኩን ቅርንጫፍ ህንፃ መምረጥ፥ ሊዝ መዋዋል፥ የውስጥ ዲዛይን ስራ መጨረስ እና ቅርንጫፍ መክፈት፥ የሰው ሃይል ቅጥር፥ የውጭ ኮረስፖንደንት ባንክ ጋር ግንኙነት መፍጠር፥ የመተግበሪያ ሶፍትዌሮችን መትከል፥ ቅፆችን እና የመስሪያ ቁሳቁሶችን ጨረታ የማውጣት ስራ እና በግዥ ማሟላት…፤ሁሉንም ጎን ለጎን ማካሄድ ይቻላል፤ 10) አማራ ባንክ በአምሳያው ይፋዊ አገልግሎት መስጠት እንዲጀምር የመነሻ መስፈርት አሟልቶ ከብሄራዊ ባንክ የስራ ፈቃድ(operation license) ተቀብሎ አገልግሎት መጀመር የመጨረሻው ጉዞ ይሆናል። መልካም ቀን!

ማንኛውም መረጃ ለመጠየቅ የባንኩን የጥሪ ማዕከል ቁጥር 7285 ይጠቀሙ!! ⒸⒶⓁⓁ ❼❷❽❺

#ባህርዳር የአማራ ባንክ ውክልና የሚሰጥበት ቦታ ! ውክልና በመስጠት የባንኩን ምስረታ እውን ያድርጉ!
#ባህርዳር የአማራ ባንክ ውክልና የሚሰጥበት ቦታ ! ውክልና በመስጠት የባንኩን ምስረታ እውን ያድርጉ!

በአዲስአበባ ለምትገኙ የአማራ ባንክ ባለአክሲዮኖች፦ በሚከተሉት የፌደራል ሰነዶች ማረጋገጫ ኤጀንሲ ቅርንጫፎች ማለትም ላንቻ፤ መሳለሚያ፤ መገናኛ፤ 6ኪሎ፤ ጉለሌ፤ አየር ጤና፤ ቃሊቲ፤ ካሳንቺስ፤ ንፋስ ስልክ ላፍቶ፤ ልደታ፤ ሲምሲ፤ ቦሌ፤ ጎጃም በረንዳ እና ጆሞ በመሄድ ውክልና መስጠት ይኖርብናል። እናንተን ለማስተናገድ ከታች በምስሉ እንደሚታየው የተዘጋጀ መስኮት አለ:: ከእናንተ የሚጠበቀው የታደሰ መታወቂያ የባንክ አክሲዮን ከገዙበት ደረሰኝ ጋር ይዞ መገኘት ብቻ ነው።

ውክልና ስለመስጠት! በምስረታ ላይ ያለው አማራ ባንክ አ.ማ መስራች ጉባኤውን በውክልና ለማከናወን ባለአክስዮኖች በሰነዶች ምዝገባ እና ማረጋገጫ ኤጀንሲ እየቀረቡ ለአደራጆች ውክልና እየሰጡ ይገኛሉ፡፡ ባንኩ ባወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት፦ 1/ በአዲስ አበባ፣ በአዲስ አበባ እና አካባቢዋ እንዲሁም በድሬዳዋ የሚገኙ የባንኩ ባለአክስዮኖች ከህዳር 1 እስከ 15/2013 ዓ.ም በአዲስ አበበ እና በድሬዳዋ በሚገኙ የሰነዶች ምዝገባ እና ማረጋገጫ ኤጀንሲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች እየቀረቡ ውክልና እንዲሰጡ ጥሪ አስተላልፏል። 2/ በአማራ ክልል በሚገኙ ዋና ዋና ከተሞች የሚገኙ ባለአክስዮኖች ከህዳር 16 – 30/2013 ዓ.ም በክልሉ ዋና ዋና ከተሞች በሚገኙ የውክልና መስጫ ጣቢዎች ቀርበው ውክልና እንዲሰጡ ጥሪ አቅርበዋል፤ 3/ በሌሎች የኢትዮጵያ አካባቢዎች እና ከኢትዮጵያ ውጭ የሚገኙ ባለአከስዮኖች ደግሞ ከህዳር 1 – 30/2013 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ ስልጣን ባለው አካል ፊት በመቅረብ ውክልና እንዲሰጡ እና ከውክልና ማስረጃው ጋር አክስዮን የገዙበትን ፎርም፣ የባንክ ስሊፕ እና የመታወቂያ ፎቶ ኮፒ አያይዘው ባንኩ ባዘጋጀው የፖስታ ሳጥን ቁጥር እንዲልኩ ባንኩ ጥሪ እያስተላለፈ ይገኛል፡፡ የአስክዮን ሽያጩ ህዳር 21/2013 ዓ.ም ይዘጋል።

ማንኛውም መረጃ ለመጠየቅ የባንኩን የጥሪ ማዕከል ቁጥር 7285 ይጠቀሙ!! ⒸⒶⓁⓁ ❼❷❽❺