cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

የክርስቲያን ወጣቶች ህብረት

በዚህ ህብረት ውስጥ #1 መንፈሳዊ የሆኑ መጣጥፎችን በመለጠፍ እንማማር እንጂ ለሌላ መጥፎ ዓላማ ማዋል የተከለከለ ነው። #2 መንፈሳዊ መዝሙሮችን ፣ ስብከቶችን ፣ እይታዎችን በመለጠፍ...አብረን ወደ ክርስቶስ ሙላት እንደግ ዘንድ ግብዣችን ነው።

Show more
Advertising posts
314
Subscribers
No data24 hours
+57 days
+2130 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

እሰራለሁ አሁን ስራዬን አለቅም ዘመኔ ላይ ቆሜ ዘመን አልጠብቅም
Show all...
👍 2
ኢየሱስ ክርስቶስ በታላቅ ገድሉ የተዘከረበት ድንቅ መዝሙር ተጋበዙልኝ።
Show all...
በደም ተለውሼ ሲያየኝ ፊቱን ዞሮ ያላለፈኝ ጠርቶ በሕይወት ኑር ያለኝ ምሕረቱን ያበዛልኝ እንደ እኔ ማን አለና ነው? ከማመስገን የምዘገየው
Show all...
👍 2 2🥰 1
Photo unavailableShow in Telegram
በዚህ ሳምንት ተስፋችሁ ይለምልም :ጉልበታችሁ ይታደስ: ወዳችሁ እንደማታውቁ ውደዱ :ተበድላችሁ እንደማታውቁ ይቅር በሉ: ሰርታችሁ በማታውቁበት በትጋት ተገለጡ ታሪክ የምትሰሙበት ብቻ ሳይሆን ታሪክ የምትሰሩበት ሳምንት ይሁን! አዳዲስ የስራ :የአገልግሎት:የድል በሮች ይከፈቱላችሁ ::ሰው አልችልም ያላችሁን እግዚአብሔር ችሎ ያሳያችሁ ::🙌🙌 አሜን እወዳችሗለው! @feven_gashewu
Show all...
👏 1
ጩኸት ጩኸት ፉጨት ፉጨት ወደላይ ወደላይ መዝለል የሚችል ብቻ (ማሟሟቂያ ፣ ማዳመቂያ ፣ መልዕክት አልባነትን መሸፈኛ) ✍️ እንደ ገጣሚም እንደ ዘማሪም የብዙ ዝማሬዎቻችን መልዕክት አልባነትና አቅም አልባነት ያሳስበኛል!! 📌 እንኳን ተዘመሩ ከምላቸው ይልቅ ምነው ባልተዘመሩ(መዝሙር ከተባሉ) የምላቸው ይበዛሉ!! ✍️ መዝሙር ስሜት ኮርኳሪ....ብሶት አካኪ....መበሻሸቂያ አይደለም!! 👉 ጥለኸኝ አትሂድ....አንዴ አስበኝ....እባክህ ጎብኜኝ.....ስትመጣ እንዳታጣኝ....ዝም አትበለኝ ወዘተራረፈ 📌 መዝሙር እግዚአብሔር ለሰው ያለውን ፍቅር መግለጫ እንጂ ሰው ለእግዚአብሔር ያለውን ፍቅር መግለጫ አይደለም!! ሆንክልኝ እንጂ ሆንኩልህ የምንልበት አይደለም!!....አደረክልኝ እንጂ አደረኩልህ የምንልበት አይደለም!!....ያልሆንክልኝ የለም የምንልበት እንጂ ያልሆንኩልህ የለም የምንልበት አይደለም!! 📌 የተሰራው የመስቀል ሥራ ላይ ሳይቆሙ መዝለል ትርፉ ላብ ነው!! ✍ መዝሙር ስለሰይጣን የሚዘመርም አይደለም!!.....መዝሙር ስለ አሸነፈው እንጂ ስለ ተሸነፈው አይዘመርም!! 📌 መዝሙር የሚገባው አለ እርሱም የታረደው በግ ኢየሱስ!! ✍ በርካታ መዝሙሮቻችንን ብናይ ስለ ሰይጣን የተዘመሩ ናቸው.....ጠላት....ጠላቴ....ደጋሚው....ሟርተኛው.....ከሳሼ....ድያብሎስ....ሰይጣን....ፈርዖን.....ጎልያድ.....ሀማ....ሰንባላጥ.....ጦቢያ የሚሉ ቃላት ይበዛባቸዋል......ነገር ግን ልብ ልንልና ልናስተውል የሚገባን ነገር መዝሙር ክርስቶስ ተኮር እንጂ ሰይጣን ተኮር አይደለም.....ማምለኪያ እንጂ መበሻሸቂያ አይደለም......ወዳጃችንን ማመስገኛ እንጂ ጠላታችንን ማስፈራሪያ አይደለም.......ወዳጆቼ ጊዜያችንን ለክርስቶስ ማትረፍ እንጂ ለሰይጣን ማባከን የለብንም......ሰይጣንን እናንተ በክርስቶስ ከመሆናችሁ በላይ የሚያበሳጨው ነገር የለምና ሰይጣንን ለማበሳጨት ብላችሁ አትዘምሩ......ከኢየሱስ ውጭ የሆነ የመዝሙር ግጥም አይኑራችሁ!!......ሰይጣን ከእግራችሁ በታች የወደቀ ፣ የተሸነፈ ፣ አቅም አልባ እንጂ እኩያችሁም የበላያችሁም አይደለምና በላይ ያለውን ክርስቶስን እያያችሁ ሽቅብ ዘምሩ እንጂ ከእግራችሁ ሥር የወደቀውን እያያችሁ ቁልቁል አትዘምሩ!! 📌 ሰው ኢየሱስን አይቶ እንዴት ስለ ሌላ ይዘምራል? ✍ እግዚአብሔር ሰይጣን ጉዳዩ አይደለምና ሰይጣን የቤተክርስቲያን አጀንዳዋ አይደለም.....ቤተክርስቲያን ከባሏ ውጭ ርዕስ የላትም!! 📌 ጠላቴ ጠላቴ ከሚል ግጥም ወጥተን ወዳጄ ወዳጄ ወደሚል ማደግ አለብን!! ✍ ፈርዖንም ጎልያድም በሌሉበት እኛም ሙሴ እና ዳዊት ባልሆንበት እዘርረዋለው ግንባሩን እለዋለሁ እያልን ጉም መዝገኑ ይብቃንና ድል ለነሳው ድሉንም ለሰጠን ለኢየሱስ ብቻ ፣ ስለ ኢየሱስ ብቻ እንዘምር!! በክርስቶስ ያላለቀና ያልተፈጸመ የለም!! የተጣለ እንጂ ገና የምንጥለው ጠላት የለም!! 📌 መዝሙሬ አንተው ነህ ብለን ዘምረን ስናበቃ ስለ ጠላት መዘመር እርስ በእርሱ ይታኮሳል!! ✍ ሰይጣን ሰይጣን ማለቱ ይብቃንና ያለቀውን የክርስቶስ ኢየሱስን የመስቀል ሥራ እንዘምር.....የጸጋውን ብርታት እንዘምር.....የደሙን ኃይል እንዘምር.....የዳንበትን መዳን እንዘምር.....ያገኘነውን እረፍት እንዘምር......የውዳችንን ውበት እንዘምር.....እኛን የወደደበትን የዘላለም ፍቅር እንዘምር......በክርስቶስ ኢየሱስ ያለውን ቸርነቱን እንዘምር.....እንዲያው የተሰጠንን የዘላለም ሕይወት እንዘምር.....የተረጋጋንበትን ሰላም እንዘምር......በእርሱ መጽደቃችንን እንዘምር......ስለእኛ ቀድሞ ሰማይ የገባውን ሊቀካህናታችንን እንዘምር.....ሥራውን ሁሉ ፈጽሞ በአብ ቀኝ የተቀመጠውን ክርስቶስን እንዘምር....እኛም በእርሱ ውስጥ መሆናችንን እንዘምር.....የክርስቶስን ማንነት እና በክርስቶስ ያገኘነውን ማንነት እንዘምር.........በቃ ኢየሱስን ብቻ እንዘምር.....ይሄ ሲሆን እውነትም ለመዘመር ዘላለም አይበቃንም!! https://t.me/Henokashebir
Show all...
ዘማሪ እንዳለ ወ/ጊዮርጊስ #ብቻዬን_አይደለሁም❤ የብቸኝነት ስሜት ተሰምቷችሁ ልባችሁ የወረደባችሁ ሰዎች ይህንን መዝሙር ተጋበዙልን🙏
Show all...
ግታው ሰበቤን ያለዘበኝን አክብጄ እንዳልይዝ ያጠመደኝን ግታው ምክኒያቴን የታገለኝን ለሁለት ጌቶች ያሰለፈኝን
Show all...
👍 3
#ድነት_እና_የዳነ_ሰው_ሃጥአት ™
``°```
’
˙¯˙‛``````°``````™ ፪ አንድ ሰው በክርስቶስ በሚያምንበት ጊዜ ወድያውኑ የድነቱ አንድ ክፍል የሆነውን የሃጥአት ይቅርታ ያገኛል፤ ለድነት የሚያበቁ ብዙ ነገሮችም በእግዚአብሔር ይሠሩለታል። በጸጋ አጠቃላይ ሥራ ከሚገኝ ድነትና በክርስቶስ አዳኝነት ከማመን ውጪ ግን ይቅርታ አይገኝም። ፪, ክርስቲያን በሚሠራው ኃጥአት ላይ የሚመጣውን መለኮታዊ ቅጣት በተመለከተ፤ የሚታየው ኃጥአቱ ብቻ ነው። በዚህ መሠረት የክርስቲያኑ ኃጥአት ይቅር የሚባለው #ለድነት በማመን ሳይሆን፥ ለሠራው ኃጥአቱ ንሰሃ በመግባት ነው (1ዮሐ 1:9) ... ኃጥአት በአማኝ ላይ የሚያስከትለው ከሌሎች ነገሮች በተጨማሪ ከአብና ከወልድ ጋር ያለውን አንድነት (ህብረት) ማጣት፥ በራሱ ውስጥ ያለውን መንፈስ ቅዱስ ማሳዘን ነው። ያም ሆኖ ኃጥአት የሰራ ክርስቲያን ኃጥአቱን ስናዘዝ፥ አንድነቱ፣ ደስታው፣ በረከቱና ኃይሉ ይመለስለታል። ኃጥአት በአማኝ ላይ የሚያስከትለው ነገር በረከትን ማጣት ቢሆንም በንስሃ ይታደሳል። አማኝ የሚሠራው ሃጥአት በእግዚአብሔር ፊት የከፋ ውጤት አለው። የፈሰሰው የክርስቶስ ደም እና እርሱ በሰማያት የሚያከናውነው ጥብቅና (ሮሜ 8:34፤ ዕብራ 9:24፤ 1ኛ ዮሐ 2:1) ዋስትና አለው። ሃጥአት የሚያደርግ ክርስቲያን በአብ ዘንድ ጠበቃ ስላለው፥ ሃጥአት ቢያደርግ እንኳን ከሃጥአቱ የተነሣ ድነቱን አያጣም። ሆኖም ይህ እውነት #ክርስቲያን_ሃጥአት_እንዲሰራ_ነፃነት_የሚሰጠው_አይደለም። መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ''ኃጥኣትን አታድርጉ'' የሚለው ይህ እውነት (1ኛ ዮሐ 2:1) በግልፅ ተጽፏል። አዳኛችን ስለእኛ በሰማይ ጠበቃ መሆኑን መረዳቱ፥ ለማንኛውም ኃጥኣት በቀላሉ እንዳንጋለጥ ሊያደርገን ይገባል እንጃ ኃጥአትን ለመስራት አያበረታታንም!! @Dr. Lewis Sperry Chafer ''Major Bible Themes'' 1995 - 2003
Show all...
👏 1
በስሙ ላይ ክብር አለ
Show all...
👍 1 1🥰 1