TSEGA
Mongent..hono aydlm fkrun kemshe..nw neyi silng..ytktlkut Nebsem temarka nw♥
Show moreThe country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
517Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
- Subscribers
- Post coverage
- ER - engagement ratio
Data loading in progress...
Subscriber growth rate
Data loading in progress...
📌📌📌📌📌📌📌📌📌📌📌📌📌📌📌
🔆 ክርስቶስን ማወቅ !!
✅ ክፍል አራት 4
(2) 📋 "የሰው ልጅ"
🤴 ኢየሱስ ክርስቶስ በተደጋጋሚ "የሰው ልጅ" የሚለውን ማዕረግ ሲጠቀም እናያለን👇
✍ማር 14
📌60 ሊቀ ካህናቱም በመካከላቸው ተነሥቶ፦ አንዳች አትመልስምን? እነዚህስ በአንተ ላይ የሚመሰክሩብህ ምንድር ነው? ብሎ ኢየሱስን ጠየቀው።
📌61 እርሱ ግን ዝም አለ አንዳችም አልመለሰም። ደግሞ ሊቀ ካህናቱ ጠየቀውና፦👉 የቡሩክ ልጅ ክርስቶስ አንተ ነህን? 👈 አለው።
📌 62 ኢየሱስም፦ 👉 እኔ ነኝ፤ 👉 የሰው ልጅም 👈በኃይል ቀኝ ሲቀመጥ በሰማይም ደመና ሲመጣ ታያላችሁ አለ።
📌 63 ሊቀ ካህናቱም ልብሱን ቀደደና፦ ከእንግዲህ ወዲህ ምስክሮችን ምን ያስፈልገናል?
📌64 ስድቡን ሰማችሁ፤ ምን ይመስላችኋል? አለ። እነርሱም ሁሉ፦ ሞት ይገባዋል ብለው ፈረዱበት።
📌 "የሰው ልጅ" የሚለውን ሲያሜ ሚስጥር የምናገኘው በትንቢት ዳንኤል 7:13-14 ላይ ነው፦
📍ዳን 7
📌13 በሌሊት ራእይ አየሁ፤ እነሆም፥ 👉 የሰው ልጅ 👈 የሚመስል ከሰማይ ደመናት ጋር መጣ በዘመናት ወደ ሸመገለውም ደረሰ፤ ወደ ፊቱም አቀረቡት።
📌 14 ወገኖችና አሕዛብ በልዩ ልዩ ቋንቋም የሚናገሩ ሁሉ ይገዙለት ዘንድ ግዛትና ክብር መንግሥትም ተሰጠው፤ ግዛቱም የማያልፍ የዘላለም ግዛት ነው፥ መንግሥቱም የማይጠፋ ነው።
📌 በዚህ ጥቅስ መሠረት ይህ "የሰው ልጅ" የተባለው አካል 👇👇👇
✅ ሕዝቦችን ሁሉ የሚገዛ
✅ የማያልፍ
✅ የዘለዓለም ግዛት ያለውና የማይጠፋ መንግስት ያለው ነው።
📌 ኢየሱስ የሰው ልጅ የሚለውን ማዕረግ መጠቀሙ 👉 ሥጋ ለብሶ 👈 የመጣ 👉 አምላክ 👈መሆኑን ለማሳየት እንደነበረ ከዚህ ትንቢት እንረዳለን።
......ይቀጥላል
✍ ሳሚ ወንዴ
7100
ዲዮጋን ከዕለታት አንድ ቀን መብራት አብርቶ ከገበያው መካከል ገብቶ ውድያና ወዲህ ሲመላለስ አንድ ግብሩን የሚያውቅ ሰው ቀርቦ "ዲዮጋን! ዛሬስ በቀትር ጊዜ መብራት ይዘህ በገበያ መካከል ትዞር ጀመር? ለምንድነው?" ቢለው።
"ሰው ጠፍቶብኝ እፈልጋለሁ" አለው ዲዮጋን። "ይህ የምታየው ሁሉ ሰው አይደለምን?" ቢለው፣ "አይ! እኔ ይህ እዚህ የሚታየው ሕዝብ ሁሉ ሰው አልለውም" ዲዮጋን መለሰ። "እንዴት?" ቢለው፣ "ይህ የምታየው ሕዝብ ሁሉ ከእውነት የራቀ ሐሰትን ያጸደቀ የራሱን ጥቅም ያወቀ ለግል ምኞቱ የሚገዛ የሰው አካል የለበሰ ውስጡ ከእንስሳዎች ያነሰ ስለሆነ ሰው አልለውም" አለው።
"ታዲያ፣ አንተ የምትፈልገው ሰው እንዴት ያለ ነው?" ቢለው። ዲዮጋንም አለ "የግል ጥቅሙን የማይሻ ሰውን እንደራሱ የሚያይ ሐሰትን የጠላ ለእውነት ያደላ ሲሆን ነው::"
22000
"ቅርቤ"
ይስሃቅ ሰዲቅ
Ymiaschnkngn hulu bant lay tiye
Shekime teragfual sigat aygbangm
libe befith eref blual
Ke aymroye blay ejig tilk nh
zelkh tayngalh kant aleswrm
westen mermrh huluyen tawkalh
🙏🙏🙏🙏
21000
💪💪💪💪
“በተስፋ ደስ ይበላችሁ፤ በመከራ ታገሡ፤ በጸሎት ጽኑ፤”
ሮሜ 12፥12
በተስፋ ፅኑ !
🤷♂ ሰውን ሚያኖረው ሚበላው እንጀራ ሰይሆን ተስፋ ነው።
☄እምነት እንኳን ተስፋ ላይ ነው የተሰራው፦ያ ማለት ተስፋ ካሌለ እምነት የለም ማለት ነው።
👇እንዲ እንደሚለው የእግዚአብሔር ቃል ማለት ነው
☄“እምነትም ተስፋ ስለምናደርገው ነገር የሚያስረግጥ፥ የማናየውንም ነገር የሚያስረዳ ነው።”
ዕብራውያን 11፥1
🙋♂ተስፋ ሰውን በሕይወት እንዲኖረ ያደርገዋል።
👉ብዙ ጊዜ ሴጣን ነገን ነው መምታት ሚፈልገው፤ ምክንያቱም ነገ ተስፋ ነውና።
😃ነገው የተመታ ሰው ቀድሞ ዛሬ ነው ሚሞተዉ ፤ ምክንያቱም ነገ ተስፋ ነውና።
🤷♂ታውቃላቹሁ አሁን እንኳን ምንኖረው በተስፋ ነው።
🤷♂ምንአምነው ክርስቶስ እንኳን ገና ወርስን የልጨረስነው ተስፋችን ነው። ገና ወደ ፈት ምንወርሰዉ የተባረከ ተስፋችን ነው።
🤷♂መጽሐፍ እንዲ እንደሚለው👇👇👇
“ለእነርሱም እግዚአብሔር በአሕዛብ ዘንድ ያለው የዚህ ምሥጢር ክብር ባለ ጠግነት ምን እንደ ሆነ ሊያስታውቅ ወደደ፥ ምሥጢሩም የክብር ተስፋ ያለው ክርስቶስ በእናንተ ዘንድ መሆኑ ነው።”
ቆላስይስ 1፥27
🤷♂ የቱ ነው ተስፋ ያልሆነዉ ነገራችን?
👇 ዳዊት እንዲ እንዳምለው
☄ ሥጋዬም ደግሞ በተስፋ ታድራለች
መዝሙር 16፥9
🙏 ሕይወታችን እንኳን ተስፋ ነው።
😭 ሚበላ ጠፍቶ ነገ እንዳምንበላ ግን ስንአወቅ😁☺️እንዳምንጽነናው ማለት ነው።
በተስፋ ፅኑ !
“በተስፋ ደስ ይበላችሁ፤ በመከራ ታገሡ፤ በጸሎት ጽኑ፤”
ሮሜ 12፥12
😁😁ስለዚህ በተስፋ ደስ ይበላችሁ።😁
✍ሳሚ ወንዴ🙋♂
25400