cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ትንሳዔ ዘኢትዮጵያ ✝✝✝

📢 ስለ ቅድስት ቤተክርስቲያን እና ገዳማት ስርዓት ፣አሁናዊ ዜና እና ስለ ቅድስት ቤተክርስቲያን ፡ ቅዱሳን መካናት እና ገዳማት ታሪክ 📢 የቅዱሳን ገድላት 📢 ቅዱሳን አበው ሊቃውንት 📢 ህዝበ ክርስቲያንን ማንቃት 📢 ቅድመ ኢትዮጵያ ትንሳዔ እና የኢሉሚናቲ ኅቡእ ማኅበር ኢትዮጵያ ላይ የተሸረቡትን ሴራዎችን ማጋለጥ ለውይይት @Tinsae_ze_ethiopiaofficialgrp

Show more
Advertising posts
3 963
Subscribers
-824 hours
-657 days
-28530 days
Posting time distributions

Data loading in progress...

Find out who reads your channel

This graph will show you who besides your subscribers reads your channel and learn about other sources of traffic.
Views Sources
Publication analysis
PostsViews
Shares
Views dynamics
01
በመንግስት አፋኞት ከተወሰደ በኃላ እስከ አሁን ያለበት ሁኔታ በቤተሰብም ሆነ በህግ ባለሙያ አልተጎበኘም ሁላችንም የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ልጆች ድምፅ ልንሆነው ያስፈልጋል
450Loading...
02
በቅድስት ቤትክርስቲያን ሥርዓተ አስተምህሮ ውስጥ በጊዜ ቅዳሴ ከወንጌል በኋላ ዲያቆኑ “ፃኡ ንዑሰ ክርስቲያን “ በማለት ያዛል። ይኸውም ፍሬ ቅዳሴ ህብስት እና ወይኑ ወደ ከበረ ስጋ ወደሙ ሚለወጥበት ጊዜ ስልሆን ይህም ለንዑሰ ክርስቲያን ማለትም በማህተመ መንፈስ ቅዱስ ላልታተሙ ላልተጠመቁ ክርስትና ላልተነሱ የተፈገደ የተገባ ስልይድለ ነው። በዚህ ላይ አስተያየት ስጡበት …
2361Loading...
03
ከእለታት አንድ ቀን አንድ አባት ወደ አባታችን አባ መቃርዮስ በኣት ሄደና "አባቴ ሆይ ድኅነትን አገኝ ዘንድ ምን ላድርግ?" ሲል ጥያቄ አቀረበላቸው። አባታችንም እንዲህ በማለት አሉት። "ወደ መቃብር ሂድና ሙታንን ሰድበሃቸው ና" አሉት። ይህ አባትም የተባለውን አድርጎ ተመለሰ። አባታችንም "ምን አሉህ?" ሲሉ ጠየቁት። ሰውየዉም "ምንም አልመለሱልኝም" ሲል መለሰ። አባ መቃርዮስም "አሁን ደግሞ ሂድና ሙታንን አመስግናቸው" አሉት። ሄዶም አመሰገናቸው። "አሁንስ ምን አሉህ" ሲል በድጋሚ ጠየቁት። ሰውዬም "ምንም አልመለሱልኝም" ሲል መለሰ። አባታችን አባ መቃርዮስም: "ስትሰድባቸው ፤ስታመሰግናቸው እና  ስታወድሳቸው ምንም አልመለሱም፤ አንተም ለነፍስህ ድህነትን ከፈለግህ እንደሞተ ሰው ሆነህ ኑር። ሰዎች ክፉ ቢያደርጉብህም፣ ቢያመሰግኑህም ምንም አይሰማህ" አሉት። @Tinsae_ze_ethiopia
1030Loading...
04
እንኳን ለዳግም ትንሣኤ አደረሳችሁ በዋናው ትንሣኤ ሳምንት የምትመጣዋ ዕለተ እሑድ ‹ዳግም ትንሣኤ› ተብላ ትዘከራለች፡፡ ጌታችን በትንሣኤው ዕለት ማታ በዝግ በር ገብቶ፣ በቅዱሳን ሐዋርያት መካከል ተገኝቶ ‹‹ሰላም ለዅላችሁ ይኹን!›› በማለት ትንሣኤውን ሲገልጽላቸው ሐዋርያው ቶማስ አልተገኘም ነበር፡፡ በኋላ ከሔደበት ሲመጣ ጌታችን እንደ ተነሣ እና እንደ ተገለጸላቸው ሐዋርያት በደስታ ሲነግሩት ‹‹ እናንተ ‹አየን› ብላችሁ ስትመሰክሩ፤ ስታስተምሩ፤ እኔ ግን ‹ሰምቼአለሁ› ብዬ ልመሰክር፤ ላስተምር? አይኾንም፡፡ እኔም ካላየሁ አላምንም›› አለ፡፡ ስለዚህም የሰውን ዅሉ፤ ይልቁንም የመረጣቸው የወዳጆቹን የልብ ዐሳብ የሚያውቀው፣ ቸርነቱ ወሰን የሌለው የባሕርይ አምላክ መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ ልክ እንደ መጀመሪያው ትንሣኤ ዕለት አበው ሐዋርያት በተዘጋ ቤት በአንድነት ተሰባስበው እንዳሉ በሩን ሳይከፍት ገብቶ ‹‹ሰላም ለዅላችሁ ይኹን!›› በማለት በመካከላቸው ቆመ፡፡ ቶማስንም ‹‹ያመንህ እንጂ ተጠራጣሪ አትኹን፤ እነሆ የተቸነከሩ እጆቼንና እግሮቼን፣ የተወጋ ጐኔንም ናና እይ፤›› ብሎ አሳየው፡፡ እርሱም ምልክቱን በማየቱ፣ በመዳሰሱ ትንሣኤውንና አምላክነቱን እንደ ፍላጎቱ በመረዳቱ ‹‹ጌታዬ፣ አምላኬ ብሎ መስክሮ›› የክርስቶስን ትንሣኤ አመነ፡፡ የሳምንቷ ዕለተ ሰንበት፣ የትንሣኤው ምሥጢር ለሁለተኛ ጊዜ ለሐዋርያት የተገለጠበት ዕለት በመኾኑ የትንሣኤው ሳምንት እሑድ ‹ዳግም ትንሣኤ› ተብሎ ይጠራል፤ ይከበራል (ዮሐ. ፳፥፳፬-፴)፡፡ ብርሃነ ትንሣኤውን የገለጸልን አምላካችን ለብርሃነ ዕርገቱም በሰላም ያድርሰን! ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡
1120Loading...
05
✏የድንግል ማርያም ልደት (መወለድ) "The Nativity of the blessed Virgin Mary” 👉የፈጣሪያችን እናት ቅድስት ድንግል ማርያም የተወለደችበትን ግንቦት አንድን ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ልደታ_ለማርያም በማለት ከጥንት ጀምሮ በታላቅ መንፈሳዊ ሐሤት በቅዳሴ፣ በማሕሌት የምታከብርላት ሲኾን፤ በተለያዩ ክፍላተ ዓለማት ያሉ ክርስቲያኖችም ይኽነን በዓል “The Nativity of the blessed Virgin Mary” (የተባረከችው የድንግል ማርያም ልደት (መወለድ) በማለት ያስባሉ። 👉ስለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የልደቷ ቀን ሊቁ ዮሐንስ ዘደማስቆ እንዲህ ብሏል፦ "'The day of the Nativity of the Mother of God is a day of Universal joy, because through the Mother of God, the entire Human race was renewed. " 🙏ትርጉም (የአምላክ እናት የልደቷ ቀን ለዓለም ሁሉ የደስታ ቀን ነው፥ ምክኒያቱም በአምላክ እናት የሰው ሁሉ ዘር ባሕርይ ታድሷልና) ይህ ከመጽሐፍ ቅዱስ ጋር ሲገናዘብ ሊቀ መልአክ ቅ/ገብርኤል ካህኑ ዘካርያስን ልጅ እንደሚወልድ ባበሠረው ጊዜ “•••ደስታ ተድላም ይሆንልሃል፥ በመወለዱም ብዙዎች ደስ ይላቸዋል።”ሉቃስ 1፥14 በማለት ነግሮታል። የጌታ መልእክተኛ የሆነ መጥምቁ ቅዱስ ዮሐንስ በመወለድ ብዙዎች ደስ ይለቸዋል ከተባለ የአምላክ እናት ወላዲተ አምላክ ድንግል ማርያም በመወለዷ ምን ያህል ሰውን ሊያስደስት እንደሚችል ማወቅ ይቻላል። 👉አባ ሕርያቆስም የእመቤታችን መጸነስና መወለድ ሲገልጽ:- “ድንግል ሆይ በኃጢአት ፍትወት የተፀነስሽ አይደለሽም በሕግ በሆነ ሩካቤ ከሐና ከኢያቄም ተወለድሽ እንጂ!” ቅዳሴ ማርያም 🙏(ቅዱስ ኤፍሬም ) 👉ፍህም የተሸከመች የወርቅ ማዕጠንት ድንግል ሆይ ቡሩክ ከቤተ መቅደስ ይዞሽ የወጣ እሳትነት ያለውን ፍህም የተሸከምሽ የወርቅ ማዕጠንት አንቺ ነሽ ። ፍህም የተባለውም ኃጢአትን የሚያስተሠርይና በደልን የሚደመስስ ነው፤ ይኸውም ካንቺ ሰው የሆነና ራሱን የተወደደ መስዋዕት አድርጎ ያሳረገ የእግዚአብሔር ቃል ነው 🙏የእመቤታችን በረከት በሁላችን ላይ ይደርብን ‼ ©️Ethio beteseb media @Tinsae_ze_ethiopia
1500Loading...
06
ልደታ ለማርያም በግንቦት አንድ ቀን አምላክን የወለደች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ተወለደች። እርሷም ለሰው ሁሉ ወገን ድኅነት የሆነባት ናት፡፡ ከወንዶች ወገን የከበረ አባቷም ስሙ ኢያቄም ከሴቶች ወገን የከበረች ሚስቱ ሐና ይባላሉ፡፡ ሁለቱም ልጅ በማጣት ሲያዝኑ ኖሩ። በዚያ ወራት የመካኖች መብዓ ካህናቱ አይቀበሉም ነበርና፡፡ እነርሱም ከሰው የሚደርስባቸውን ሽሙጥና ኅዘናቸውን ያርቅላቸው ዘንድ በቀንና በሌሊት ወደ እግዚአብሔር ፈጽሞ ይማልዱ ነበር፡፡ ሰውን የሚወድ እግዚአብሔርም ከዘራቸው ለዓለሙ ሁሉ መድኃኒት ይሆን ዘንድ መልካም የሆነ ሐሳባቸውን ተመለከተ፡፡ ክቡር ኢያቄምም አርባ ቀን እስኪፈጸም በተራራ ውስጥ ቁሞ ሲጸልይ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ ተገለጸለትና ለዓለሙ ሁሉ ድኅነት የሚደረግባት ዘር እንደሚሰጠው አበሠረው፡፡ በፍጹም ልብ አምኖ ከተራራው ወረደ፤ ለተመሰገነች ሚስቱ ለሐናም ከእግዚአብሔር መልአክ የሰማውን ያንን ራእይ ነገራት። ቃሉ እውነት እንደሆነ እርሷም አመነች። ልዑል እግዚአብሔርንም አመሰገነች። የተመሰገነች ቅድስት ሐናም ከእርሷ የሚወለደውን በዘመኑ ሁሉ ለቤተ እግዚአብሔር አገልጋይ ታደርገው ዘንድ ለእግዚአብሔር ስለትን ተሳለች፡፡ ከዚህም በኋላ ይህችን የከበረች ሕፃን ፀንሳ ወለደች። ስሟንም ‹ማርያም› ብላ ሰየመቻት። ትርጓሜውም ‹እመቤት› ነው። ‹ደግሞም ሀብታና ስጦታ› ማለት ነው፡፡ በእውነት የዓለሙ ሁሉ እመቤት ሁላችን በእርሷ ሰማያዊ ሀብት ልጅነትን ያገኘንባት ናትና። የሥጋና የነፍስ መድኃኒት የሆነች እርሷን እናቱን ለሰጠን ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፤ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በረከቷም ከሁላችን የክርስቲያን ወገኖች ለዘለዓለሙ ይኑር፤ አሜን፡፡ ከመጽሐፈ ስንክሳር ዘወርኃ ግንቦት @Tinsae_ze_ethiopia
1521Loading...
07
"ከውሸት ፣ ከክፋት ፣ ከመወነጃጀል ነጽተን ትንሣኤውን በእውነትና በፍቅር እናክብር " ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ሚያዝያ 29 ቀን 2016 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ) የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የኒውዮርክና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ በዓለ ትንሣኤን አስመልክተው የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላልፈዋል። ትንሣኤ ማለት ሕዝበ ክርስቲያኑ በጠቅላላ አምኖ የሕይወትን ትንሣኤ ስናከብር ነው በማለት የገለጹ ሲሆን አያይዘውም በዓለማችን ላይ የ ትንሣኤ ሕይወትን የሚለማመድ እና በሞት ጥላ ስር የሚኖሩ አሉ በመሆኑም በሞት ጥላ ለሚኖሩት ትንሣኤ የሚባል ነገር የለም ነገር ግን በሕይወት ትንሣኤ ስንኖር ዛሬ ብቻ ሳይሆን ሁሌም ትንሣኤ ነው በማለት ምክራቸውን ለግሰውናል። ምድራችን ሁል ጊዜ በበሽታ ላይ ነው ያለችዉ በሕመም ላይ ነው ያለችው ስለዚህ ትንሣኤ ዛሬ ነው ካልን ከውሸት ፣ ከክፋት ፣ ከመወነጃጀል ነጽተን ትንሣኤውን በእውነትና በፍቅር እናክብር በዓሉም የሰላም ፣ የፍቅር ፣ የመተሳሰብ እና የአንድነት ይሁንልን በማለት መልእክታቸውን አስተላልፈዋል። ©️ተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል @Tinsae_ze_ethiopia
1620Loading...
08
"ከውሸት ፣ ከክፋት ፣ ከመወነጃጀል ነጽተን ትንሣኤውን በእውነትና በፍቅር እናክብር " ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ሚያዝያ 29 ቀን 2016 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ) የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የኒውዮርክና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ በዓለ ትንሣኤን አስመልክተው የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላልፈዋል። ትንሣኤ ማለት ሕዝበ ክርስቲያኑ በጠቅላላ አምኖ የሕይወትን ትንሣኤ ስናከብር ነው በማለት የገለጹ ሲሆን አያይዘውም በዓለማችን ላይ የ ትንሣኤ ሕይወትን የሚለማመድ እና በሞት ጥላ ስር የሚኖሩ አሉ በመሆኑም በሞት ጥላ ለሚኖሩት ትንሣኤ የሚባል ነገር የለም ነገር ግን በሕይወት ትንሣኤ ስንኖር ዛሬ ብቻ ሳይሆን ሁሌም ትንሣኤ ነው በማለት ምክራቸውን ለግሰውናል። ምድራችን ሁል ጊዜ በበሽታ ላይ ነው ያለችዉ በሕመም ላይ ነው ያለችው ስለዚህ ትንሣኤ ዛሬ ነው ካልን ከውሸት ፣ ከክፋት ፣ ከመወነጃጀል ነጽተን ትንሣኤውን በእውነትና በፍቅር እናክብር በዓሉም የሰላም ፣ የፍቅር ፣ የመተሳሰብ እና የአንድነት ይሁንልን በማለት መልእክታቸውን አስተላልፈዋል። ©️ተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል @Tinsae_ze_ethiopia
10Loading...
09
በትንሣኤ እና በጠቅላላው በሐምሳው ቀናት ክርስቲያናዊ ሰላምታችን በረዥሙ እንዲሁም በአጭሩ (ሐሳብ መስጠት ይቻላል!!!) +++ Orthodox Greetings at Easter & the 50 days: ++++ ሀ/ በረዥሙ ካህን: ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን Priest:- Christ is risen from the dead ሕዝብ፦ በዓቢይ ኃይል ወሥልጣን People:- With great strength and authority ካህን: ዓሠሮ ለሰይጣን Priest:- He chained Satan ሕዝብ፦ አግዓዞ ለአዳም People:- He freed Adam ካህን:- ሰላም Priest:- Peace ሕዝብ፦ እምይእዜሰ People:- Henceforth ካህን:- ኮነ Priest:- Became … ሕዝብ፦ ፍሥሐ ወሰላም People:- Joy and peace ++++++ ለ/ በአጭሩ፤ + Short greeting form (as in the Other Orthodox Churches) in our day to day encounters could be:- ** ሰላምታ አቅራቢ:- "ክርስቶስ ተንሥአ [እሙታን]" = (ክርስቶስ ተነሥቷል) ++ Greeter:- Christ is risen [from the dead.] ** ሰላምታ ተቀባይ:- "በአማን ተንሥአ እሙታን!!" = (በእውነት ተነሥቷል) ++ Person receiving the greeting:- "Truly He is risen [from the dead.]" + በሌሎች ክርስቲያኖች ዘንድ ያለው ሰላምታ!!!! ** “Christ is Risen!”, ** “Truly, He is Risen”. (This is used in almost all Christian nations, each translating it to its own language.) A/ Greek: ** “Χριστός ἀνέστη! Ἀληθῶς ανέστη! ** (Khristós Anésti! Alithós Anésti!)”, B/ Latin: ** “Christus resurrexit! Resurrexit vere!”, C/ Aramaic Syriac: “ܡܫܝܚܐ ܩܡ! ܫܪܝܪܐܝܬ ܩܡ!‎ (Mshiḥa qām! sharīrāīth qām! ; Mshiḥo Qom! Shariroith Qom!)”, D/ Hebrew: “המשיח קם! באמת קם!‎ (Hameshiach qam! Be’emet qam!)”, E/ Arabic: “المسيح قام! حقا قام!‎ (al-Masīḥ qām! Ḥaqqan qām!); المسيح قام! بالحقيقة قام!‎ (al-Masīḥ qām! Belḥāqiqāti qām!)”. F/ Coptic, the Paschal greeting is: ** Neo-Bohairic as “Pikhristos Aftonf! Khen oumethmi aftonf!” and in Old Bohairic as “pikhristos afdonf! khen oumetmei afdonf!”. ++++ ©️ TMC @Tinsae_ze_ethiopia
3093Loading...
10
ኢሀሎ ዝየ ተንሥአ በከመ ይቤ፤ ነዓ ርእያ ኀበ ተቀብረ። ወንጌል ዘማቴዎስ 28፥6 #ትንሣኤ የዕለቱን ወንጌል እናንብብ! ሚያዝያ 27 ቀን 2016 ዓ.ም በበዓለ ትንሣኤ የሚነበብ የማቴዎስ ወንጌል ም 28 ፥ 1 - 19 የማርቆስ ወንጌል ም 16 ፥ 1 - 20 የሉቃስ ወንጌል ም 24 ፥ 1 - 12 የዮሐንስ ወንጌል ም 20 ፥ 1 - 18 መልካም በዓለ ትንሣኤ ! ©️TMC
4581Loading...
11
ወዳጄ ማኅበረ ቅዱሳን አስተሳሰብ ኾኗል ብለንህም አይደል። ከአባላቱ አንዳንዶችን ልታስር ትችል ይኾናል። ትደክማለህ እንጅ አሳብ አይታሰርም። ሕንፃውን ልታፈርስበት ትችላለህ፤ አሳብ ግን አይፈርስም። ለክርስቲያኖች ፈተና ኦክስጅናቸው ነው። እሳት ላይ ኦክስጅን ከጨመርህበት ደግሞ እሳቱ ይብስበታል እንጅ ታጠፋው ዘንድ አይቻልህም። ከእግዚአብሔር ጋር ስትጣሉ እንዳትገኙ እንዲል ሊቁ ገማልያል። ©️Abayneh kassie @Tinsae_ze_ethiopia
5201Loading...
12
፯. ሙታን ተነሡ (ማቴ. ፳፯፥፶፩-፶፬)፡፡ ጌታችን በመስቀል ላይ ሳለ የሚከተሉትን ሰባት ዐበይት ቃላት አሰምቶ ተናግሯል፤ ፩. ‹‹ኤሎሄ ኤሎሄ ላማ ሰበቅታኒ (አምላኪየ አምላኪየ ለምን ተውኸኝ?)››፤ ፪. ‹‹እውነት እውነት እልሃለሁ፤ ዛሬ ከእኔ ጋር በገነት ትኖራለህ››፤ ፫. ‹‹አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁትምና ይቅር በላቸው››፤ ፬. እመቤታችንን ‹‹ሴትዮ ሆይ፣ እነሆ ልጅሽ››፤ ደቀ መዝሙሩንም ‹‹እናትህ እነኋት›› በማለት የቃል ኪዳን እናትነትና ልጅነት ማከናወኑ፤ ፭. ‹‹አባት ሆይ በአንተ እጅ ነፍሴን አደራ እሰጣለሁ›› ፮. ‹‹ተጠማሁ››፤ ፯. ‹‹ዅሉ ተፈጸመ›› (ማቴ. ፳፯፥፵፭-፵፮፤ ሉቃ. ፳፫፥፵፫-፵፮፤ ዮሐ. ፲፱፥፲-፴)፡፡ ከስድስት ሰዓት እስከ ዘጠኝ ሰዓት ጨለማ ኾኖ ከቈየ በኋላ ከዘጠኝ እስከ ማታ እንደ ተለመደው ብርሃን ኾኖአል፡፡ ‹‹ወፍና ሠርክ ይበርህ ብርሃነ ፀሐይ›› እንዲል (ዘካ. ፲፬፥፯)፡፡ በዚህ ዕለት ሰባት መስተፃርራን (ጠበኞች) ታረቁ፤ ተስማሙ፡፡ እነዚህም፡- ሰውና እግዚአብሔር፣ ሰውና መላእክት፣ ሕዝብና አሕዛብ፣ ነፍስና ሥጋ ናቸው (ኤፌ. ፪፥፲፤ ቈላ. ፩፥፳)፡፡ ጌታችን ጠዋት በሦስት ሰዓት ተገረፈ፤ በስድስት ሰዓት ተሰቀለ (ማቴ. ፳፯፥፩-፴፯፤ ሉቃ. ፳፫፥፩-፵፬፤ ዮሐ. ፲፱፥፩)፡፡ በዘጠኝ ሰዓት ጌታችን በውኃው ተጠምቀን፣ ደሙን ተቀብለን የእግዚአብሔር ልጆች እንኾን ዘንድ ከቀኝ ጎድኑ ጥሩ ውኃ፣ ትኩስ ደም አፈሰሰልን (ዮሐ. ፲፱፥፴፬)፡፡ በዐሥራ አንድ ሰዓት ዮሴፍና ኒቆዲሞስ ከመስቀል አውርደው ሽቶ እየረበረቡ በድርብ በፍታ ገንዘው ቀበሩት (ሉቃ. ፳፫፥፶-፶፬፤ ዮሐ. ፲፱፥፴፰-፵፪)፡፡ ቅድስት ነፍሱ ወደ ሲኦል ወርዳ ነፍሳትን ነጻ አወጣች (፩ኛ ጴጥ. ፫፥፲፱)፡፡ በዚህ ጊዜ በርሃነ መለኮቱ በሲኦል ተገለጠ፡፡ ስለዚህም ‹‹ንሴብሖ ለእግዚአብሔር›› እየተባለ ይዘመራል፡፡ ከሆሣዕና አንሥቶ ተከልክሎ የነበረው ኑዛዜ ይናዘዛል፤ ጸሎተ ፍትሐት ይደረጋል፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡ ©️ Deacon Yaregal Abegaz @Tinsae_ze_ethiopia
3480Loading...
13
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያንን ክብር የሚነካ ቃላት ተናገሮ ማረሚያ ቤት በእስር ላይ የነበረው ልጅ ያሬድ ከ 8 ወራት ቆይታ በኋላ በዛሬው ዕለት ተፈቷል። @Tinsae_ze_ethiopia
2810Loading...
14
✏መረጃ ✍️ ከቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት ጸሐፊነት በቅርቡ በቋሚ ቅዱስ ሲኖዶስ ፈቃድ የደቡብ አፍሪካ አህጉረ ስብከት ዋና ስራ አስኪያጅ ተደርገው የተዘዋወሩት ወንድማችን ሊቀ ማእምራን ብርሃኑ ተ/ያሬድ በዛሬው እለት በፌዴራል ፖሊስ ለጥያቄ ይፈለጋሉ በሚል ከቤታቸው ተወስደዋል! የመምህሩን አገልግሎት ለማደናቀፍ ሰሞኑን ብዙ ድርጊቶች ሲፈጽሙባቸው የነበረ ሲሆን ከዚህ ጀርባ እነማን እንዳሉ ደግሞ ግልጽ ነው። © Jerry Enyew's
2840Loading...
15
ሊቀ ትጉኀን ቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ ሥዩም እና መ/ር ዋሲሁን በላይ ከእስር ተፈቱ ! ሚያዝያ 25 ቀን 2016 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ) የማኅበረ ቅዱሳን ሰብሳቢ ሊቀ ትጉኀን ቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ ሥዩም እና የማኅበሩ ዋና ጸሐፊ መ/ር ዋሲሁን በላይ በዛሬው ዕለት ሚያዚያ 25 ቀን 2016 ዓ.ም ከእሥር ተፈተው ወደ ቤታቸው መመለሳቸውን የማኅበረ ቅዱሳን ብሮድካስት አገልግሎት ዘግቧል። በትናንትናው ዕለት ሚያዚያ 24 ቀን 2016 ዓ.ም በመንግሥት የጸጥታ አካላት ከመኖሪያ ቤታቸው ተወስደው ሜክሲኮ በሚገኘው የፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ እንደሚገኙ መገለጹ ይታወሳል። ይህ በእንዲህ እንዳለ የደቡብና ምዕራብ አፍሪካ አህጉረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ማእምራን ብርሃኑ ተክለ ያሬድ ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ሰዓት ድረስ ከእስር አለመለቀቃቸውን ከቤተሰቦቻቸው ለማጣራት ችለናል። ©️ ተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል @Tinsae_ze_Ethiopia
2430Loading...
16
Media files
2440Loading...
17
የ"ገብረ ሰላመ" በዓል ቅዱስ ፓትርያርኩ በተገኙበት በደማቅ ሃይማኖታዊ ሥነ-ሥርዓት ተከበረ ! ሚያዝያ 26 ቀን 2016 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ) በየዓመቱ በበዓለ ትንሣኤ ዋዜማ "በቀዳም ሥዑር" ዕለት የሚከበረው የገብረ ሰላመ በዓል ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአከኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በተገኙበት ዛሬ ሚያዝያ 26 ቀን 2016 ዓ.ም በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በደማቅ ሃይማኖታዊ ሥርዓት ተከብሯል። በዓሉ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የማዳን ሥራውን መፈጸሙ የሚዘከርበት ፣ በመስቀል ላይም በፈጸመው የማዳን ሥራ ለዓለም ድኅነትን መስጠቱ የሚታወጅበት ታላቅ ሃይማኖታዊ በዓል ነው። በኖኅ ዘመን መጥቶ የነበረው ጥፋት ማብቃቱ ርግቧ ይዛ በመጣችው የወይራ ቅጠል እንደታወቀ ሁሉ በአዳም በደል ምክንያት በሰው ልጆች የውድቀት ዘመን ማብቃቱ የሚታወጅበት ቄጤማም በቅዱስ ፓትርያርኩ ለበዓሉ ታዳሚዎች ሁሉ ከመልካም ምኞት ጋር ታድሏል። በቅዱስ ያሬድ ለዕለቱ የተዘጋጀው "ገብረ ሰላመ በመስቀሉ ትንሣኤሁ አግሃደ..." የሚለው ቃለ እግዚአብሔርም ለዕለቱ በተመደቡት በመርካቶ ደብረ አሚን ዳግሚት ደብረ ሊባኖስ ገዳም ሊቃውንት ደርሷል። በዓሉ ላይም ቅዱስነታቸውን ጨምሮ ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ፣ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት እና የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሥራ ኃላፊዎች ፣ የአዲስ አበባ ገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች ፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ፣ ካህናትና በርካታ ምእመናን ተገኝተዋል። ©️TMC
2110Loading...
18
Media files
2320Loading...
19
የዕለቱን ወንጌል እናንብብ! ሚያዝያ 24 ቀን 2016 ዓ.ም ቀን 6:00 የሚነበብ የማርቆስ ወንጌል ም 14 ቁ 12 - 16 ሰሙነ ሕማማት ©️TMC
2700Loading...
20
፬. ዕለተ ሐሙስ ሀ. ጸሎተ ሐሙስ- በዕለተ ሐሙስ ጌታችን መደኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እርሱ የዓለም መድኃኒት የሰው ልጆችንም ልመና የሚቀበል አምላክ ሆኖ ሳለ በዚች ቀን በአትክልቱ ቦታ ገብቶ አይሁድ መጥተው እስከሚይዙት ድረስ ሥጋን የተዋሐደ ፍጹም አምላክ፤ፍጹም ሰው መሆኑን ለማጠየቅ ለአርአያነት ይጸልይ ስለነበረ ይህች ዕለት ጸሎተ ሐሙስ ተብላ ትጠራለች: (ማቴ. 12-02-92) ለ. የምሥጢር ቀን:: መድኃኒታችን ክርስቶስ በዚች ዕለት ሐሙስ ለዓርብ ምሽት በሁለተኛው ሰዓተ ሌሊት ኅብስቱን ባርኮ ለዐሥራ ሦስት ከፈተተ በኋላ ለደቀ መዛሙርቱ ሰጥቶአቸዋል:: ‹‹እንጀራን አንሥቶ ባረከ፤ ቈርሶም ለደቀ መዛሙርቱ ሰጠና- እንካችሁ ብሉ፤ ይህ ሥጋዬ ነው አለ። ጽዋንም አንሥቶ አመስግኖ ሰጣቸው፤ እንዲህም አለ፦ ሁላችሁ ከእርሱ ጠጡ፤ ስለ ብዙዎች ለኃጢአት ይቅርታ የሚፈሰሰው የሐዲስ ኪዳን ደሜ ነው,, ተብሎ እንደተጻፈ። ሐ. የሐዲስ ኪዳን ሐሙስ:- ይህቺ ዕለት መድኃኒት ክርስቶስ ራሱን የተወደደ መሥዋዕት አድርጐ የገለጠባት በእንሰሳት ደም ይቀርብ የነበረው መሥዋዕተ ኦሪትም አብቅቶ አማናዊው የሐዲስ ኪዳን መሥዋዕት ለድኅነተ ዓለም የተበሠረባትና የተጀመረባት ዕለት በመሆንዋ የሐዲስ ኪዳን ሐሙስ እየተባለች ትጠራለች። መ. የሕፅበተ እግር ቀን:- ጌታ በፍጹም ትህትና የደቀ መዛሙርቱን እግር ያጠበበት ከሐዋርየት ጋር ግብር የገባበትና የክርስትና ህይወት ማሕተም የሆነውን ምስጢረ ቀርባን ያከናወነበት ዕለት ነው ©️TMC @Tinsae_ze_Ethiopia
5051Loading...
21
Media files
4871Loading...
22
📷 የሰሙነ ሕማማት የመጀመሪያ ቀን በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም
4721Loading...
23
ሰሙነ ሕማማት ከጠዋቱ 9:00 የሚነበብ የማቴዎስ ወንጌል 21 23፤ ወደ መቅደስም ገብቶ ሲያስተምር የካህናት አለቆችና የሕዝብ ሽማግሎች ወደ እርሱ ቀረቡና፦ በምን ሥልጣን እነዚህን ታደርጋለህ? ይህንስ ሥልጣን ማን ሰጠህ? አሉት። 24፤ ኢየሱስም መልሶ፦ እኔ ደግሞ አንዲት ነገር እጠይቃችኋለሁ፤ እናንተም ያችን ብትነግሩኝ እኔ ደግሞ እነዚህን በምን ሥልጣን እንዳደርግ እነግራችኋለሁ፤ 25፤ የዮሐንስ ጥምቀት ከወዴት ነበረች? ከሰማይን ወይስ ከሰው? አላቸው። እነርሱም እርስ በርሳቸው ሲነጋገሩ፦ ከሰማይ ብንል፦ እንኪያስ ስለ ምን አላመናችሁበትም? ይለናል፤ 26፤ ከሰው ግን ብንል፥ ዮሐንስን ሁሉም እንደ ነቢይ ያዩታልና ሕዝቡን እንፈራለን፡ አሉ። 27፤ ለኢየሱስም መልሰው፦ አናውቅም፡ አሉት። እርሱም ደግሞ፦ እኔም በምን ሥልጣን እነዚህን እንዳደርግ አልነግራችሁም፡ አላቸው።
4652Loading...
24
ከጠዋቱ 3:00 የሚነበብ የማቴዎስ ወንጌል ም 21 ቁ 18 - 22 ሰሙነ ሕማማት
2380Loading...
Photo unavailableShow in Telegram
በመንግስት አፋኞት ከተወሰደ በኃላ እስከ አሁን ያለበት ሁኔታ በቤተሰብም ሆነ በህግ ባለሙያ አልተጎበኘም ሁላችንም የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ልጆች ድምፅ ልንሆነው ያስፈልጋል
Show all...
በቅድስት ቤትክርስቲያን ሥርዓተ አስተምህሮ ውስጥ በጊዜ ቅዳሴ ከወንጌል በኋላ ዲያቆኑ “ፃኡ ንዑሰ ክርስቲያን “ በማለት ያዛል። ይኸውም ፍሬ ቅዳሴ ህብስት እና ወይኑ ወደ ከበረ ስጋ ወደሙ ሚለወጥበት ጊዜ ስልሆን ይህም ለንዑሰ ክርስቲያን ማለትም በማህተመ መንፈስ ቅዱስ ላልታተሙ ላልተጠመቁ ክርስትና ላልተነሱ የተፈገደ የተገባ ስልይድለ ነው። በዚህ ላይ አስተያየት ስጡበት …
Show all...
ከእለታት አንድ ቀን አንድ አባት ወደ አባታችን አባ መቃርዮስ በኣት ሄደና "አባቴ ሆይ ድኅነትን አገኝ ዘንድ ምን ላድርግ?" ሲል ጥያቄ አቀረበላቸው። አባታችንም እንዲህ በማለት አሉት። "ወደ መቃብር ሂድና ሙታንን ሰድበሃቸው ና" አሉት። ይህ አባትም የተባለውን አድርጎ ተመለሰ። አባታችንም "ምን አሉህ?" ሲሉ ጠየቁት። ሰውየዉም "ምንም አልመለሱልኝም" ሲል መለሰ። አባ መቃርዮስም "አሁን ደግሞ ሂድና ሙታንን አመስግናቸው" አሉት። ሄዶም አመሰገናቸው። "አሁንስ ምን አሉህ" ሲል በድጋሚ ጠየቁት። ሰውዬም "ምንም አልመለሱልኝም" ሲል መለሰ። አባታችን አባ መቃርዮስም: "ስትሰድባቸው ፤ስታመሰግናቸው እና  ስታወድሳቸው ምንም አልመለሱም፤ አንተም ለነፍስህ ድህነትን ከፈለግህ እንደሞተ ሰው ሆነህ ኑር። ሰዎች ክፉ ቢያደርጉብህም፣ ቢያመሰግኑህም ምንም አይሰማህ" አሉት። @Tinsae_ze_ethiopia
Show all...
እንኳን ለዳግም ትንሣኤ አደረሳችሁ በዋናው ትንሣኤ ሳምንት የምትመጣዋ ዕለተ እሑድ ‹ዳግም ትንሣኤ› ተብላ ትዘከራለች፡፡ ጌታችን በትንሣኤው ዕለት ማታ በዝግ በር ገብቶ፣ በቅዱሳን ሐዋርያት መካከል ተገኝቶ ‹‹ሰላም ለዅላችሁ ይኹን!›› በማለት ትንሣኤውን ሲገልጽላቸው ሐዋርያው ቶማስ አልተገኘም ነበር፡፡ በኋላ ከሔደበት ሲመጣ ጌታችን እንደ ተነሣ እና እንደ ተገለጸላቸው ሐዋርያት በደስታ ሲነግሩት ‹‹ እናንተ ‹አየን› ብላችሁ ስትመሰክሩ፤ ስታስተምሩ፤ እኔ ግን ‹ሰምቼአለሁ› ብዬ ልመሰክር፤ ላስተምር? አይኾንም፡፡ እኔም ካላየሁ አላምንም›› አለ፡፡ ስለዚህም የሰውን ዅሉ፤ ይልቁንም የመረጣቸው የወዳጆቹን የልብ ዐሳብ የሚያውቀው፣ ቸርነቱ ወሰን የሌለው የባሕርይ አምላክ መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ ልክ እንደ መጀመሪያው ትንሣኤ ዕለት አበው ሐዋርያት በተዘጋ ቤት በአንድነት ተሰባስበው እንዳሉ በሩን ሳይከፍት ገብቶ ‹‹ሰላም ለዅላችሁ ይኹን!›› በማለት በመካከላቸው ቆመ፡፡ ቶማስንም ‹‹ያመንህ እንጂ ተጠራጣሪ አትኹን፤ እነሆ የተቸነከሩ እጆቼንና እግሮቼን፣ የተወጋ ጐኔንም ናና እይ፤›› ብሎ አሳየው፡፡ እርሱም ምልክቱን በማየቱ፣ በመዳሰሱ ትንሣኤውንና አምላክነቱን እንደ ፍላጎቱ በመረዳቱ ‹‹ጌታዬ፣ አምላኬ ብሎ መስክሮ›› የክርስቶስን ትንሣኤ አመነ፡፡ የሳምንቷ ዕለተ ሰንበት፣ የትንሣኤው ምሥጢር ለሁለተኛ ጊዜ ለሐዋርያት የተገለጠበት ዕለት በመኾኑ የትንሣኤው ሳምንት እሑድ ‹ዳግም ትንሣኤ› ተብሎ ይጠራል፤ ይከበራል (ዮሐ. ፳፥፳፬-፴)፡፡ ብርሃነ ትንሣኤውን የገለጸልን አምላካችን ለብርሃነ ዕርገቱም በሰላም ያድርሰን! ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡
Show all...
✏የድንግል ማርያም ልደት (መወለድ) "The Nativity of the blessed Virgin Mary” 👉የፈጣሪያችን እናት ቅድስት ድንግል ማርያም የተወለደችበትን ግንቦት አንድን ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ልደታ_ለማርያም በማለት ከጥንት ጀምሮ በታላቅ መንፈሳዊ ሐሤት በቅዳሴ፣ በማሕሌት የምታከብርላት ሲኾን፤ በተለያዩ ክፍላተ ዓለማት ያሉ ክርስቲያኖችም ይኽነን በዓል “The Nativity of the blessed Virgin Mary” (የተባረከችው የድንግል ማርያም ልደት (መወለድ) በማለት ያስባሉ። 👉ስለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የልደቷ ቀን ሊቁ ዮሐንስ ዘደማስቆ እንዲህ ብሏል፦ "'The day of the Nativity of the Mother of God is a day of Universal joy, because through the Mother of God, the entire Human race was renewed. " 🙏ትርጉም (የአምላክ እናት የልደቷ ቀን ለዓለም ሁሉ የደስታ ቀን ነው፥ ምክኒያቱም በአምላክ እናት የሰው ሁሉ ዘር ባሕርይ ታድሷልና) ይህ ከመጽሐፍ ቅዱስ ጋር ሲገናዘብ ሊቀ መልአክ ቅ/ገብርኤል ካህኑ ዘካርያስን ልጅ እንደሚወልድ ባበሠረው ጊዜ “•••ደስታ ተድላም ይሆንልሃል፥ በመወለዱም ብዙዎች ደስ ይላቸዋል።”ሉቃስ 1፥14 በማለት ነግሮታል። የጌታ መልእክተኛ የሆነ መጥምቁ ቅዱስ ዮሐንስ በመወለድ ብዙዎች ደስ ይለቸዋል ከተባለ የአምላክ እናት ወላዲተ አምላክ ድንግል ማርያም በመወለዷ ምን ያህል ሰውን ሊያስደስት እንደሚችል ማወቅ ይቻላል። 👉አባ ሕርያቆስም የእመቤታችን መጸነስና መወለድ ሲገልጽ:- “ድንግል ሆይ በኃጢአት ፍትወት የተፀነስሽ አይደለሽም በሕግ በሆነ ሩካቤ ከሐና ከኢያቄም ተወለድሽ እንጂ!” ቅዳሴ ማርያም 🙏(ቅዱስ ኤፍሬም ) 👉ፍህም የተሸከመች የወርቅ ማዕጠንት ድንግል ሆይ ቡሩክ ከቤተ መቅደስ ይዞሽ የወጣ እሳትነት ያለውን ፍህም የተሸከምሽ የወርቅ ማዕጠንት አንቺ ነሽ ። ፍህም የተባለውም ኃጢአትን የሚያስተሠርይና በደልን የሚደመስስ ነው፤ ይኸውም ካንቺ ሰው የሆነና ራሱን የተወደደ መስዋዕት አድርጎ ያሳረገ የእግዚአብሔር ቃል ነው 🙏የእመቤታችን በረከት በሁላችን ላይ ይደርብን ‼ ©️Ethio beteseb media @Tinsae_ze_ethiopia
Show all...
👍 2
ልደታ ለማርያም በግንቦት አንድ ቀን አምላክን የወለደች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ተወለደች። እርሷም ለሰው ሁሉ ወገን ድኅነት የሆነባት ናት፡፡ ከወንዶች ወገን የከበረ አባቷም ስሙ ኢያቄም ከሴቶች ወገን የከበረች ሚስቱ ሐና ይባላሉ፡፡ ሁለቱም ልጅ በማጣት ሲያዝኑ ኖሩ። በዚያ ወራት የመካኖች መብዓ ካህናቱ አይቀበሉም ነበርና፡፡ እነርሱም ከሰው የሚደርስባቸውን ሽሙጥና ኅዘናቸውን ያርቅላቸው ዘንድ በቀንና በሌሊት ወደ እግዚአብሔር ፈጽሞ ይማልዱ ነበር፡፡ ሰውን የሚወድ እግዚአብሔርም ከዘራቸው ለዓለሙ ሁሉ መድኃኒት ይሆን ዘንድ መልካም የሆነ ሐሳባቸውን ተመለከተ፡፡ ክቡር ኢያቄምም አርባ ቀን እስኪፈጸም በተራራ ውስጥ ቁሞ ሲጸልይ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ ተገለጸለትና ለዓለሙ ሁሉ ድኅነት የሚደረግባት ዘር እንደሚሰጠው አበሠረው፡፡ በፍጹም ልብ አምኖ ከተራራው ወረደ፤ ለተመሰገነች ሚስቱ ለሐናም ከእግዚአብሔር መልአክ የሰማውን ያንን ራእይ ነገራት። ቃሉ እውነት እንደሆነ እርሷም አመነች። ልዑል እግዚአብሔርንም አመሰገነች። የተመሰገነች ቅድስት ሐናም ከእርሷ የሚወለደውን በዘመኑ ሁሉ ለቤተ እግዚአብሔር አገልጋይ ታደርገው ዘንድ ለእግዚአብሔር ስለትን ተሳለች፡፡ ከዚህም በኋላ ይህችን የከበረች ሕፃን ፀንሳ ወለደች። ስሟንም ‹ማርያም› ብላ ሰየመቻት። ትርጓሜውም ‹እመቤት› ነው። ‹ደግሞም ሀብታና ስጦታ› ማለት ነው፡፡ በእውነት የዓለሙ ሁሉ እመቤት ሁላችን በእርሷ ሰማያዊ ሀብት ልጅነትን ያገኘንባት ናትና። የሥጋና የነፍስ መድኃኒት የሆነች እርሷን እናቱን ለሰጠን ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፤ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በረከቷም ከሁላችን የክርስቲያን ወገኖች ለዘለዓለሙ ይኑር፤ አሜን፡፡ ከመጽሐፈ ስንክሳር ዘወርኃ ግንቦት @Tinsae_ze_ethiopia
Show all...
👍 3
Photo unavailableShow in Telegram
"ከውሸት ፣ ከክፋት ፣ ከመወነጃጀል ነጽተን ትንሣኤውን በእውነትና በፍቅር እናክብር " ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ሚያዝያ 29 ቀን 2016 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ) የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የኒውዮርክና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ በዓለ ትንሣኤን አስመልክተው የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላልፈዋል። ትንሣኤ ማለት ሕዝበ ክርስቲያኑ በጠቅላላ አምኖ የሕይወትን ትንሣኤ ስናከብር ነው በማለት የገለጹ ሲሆን አያይዘውም በዓለማችን ላይ የ ትንሣኤ ሕይወትን የሚለማመድ እና በሞት ጥላ ስር የሚኖሩ አሉ በመሆኑም በሞት ጥላ ለሚኖሩት ትንሣኤ የሚባል ነገር የለም ነገር ግን በሕይወት ትንሣኤ ስንኖር ዛሬ ብቻ ሳይሆን ሁሌም ትንሣኤ ነው በማለት ምክራቸውን ለግሰውናል። ምድራችን ሁል ጊዜ በበሽታ ላይ ነው ያለችዉ በሕመም ላይ ነው ያለችው ስለዚህ ትንሣኤ ዛሬ ነው ካልን ከውሸት ፣ ከክፋት ፣ ከመወነጃጀል ነጽተን ትንሣኤውን በእውነትና በፍቅር እናክብር በዓሉም የሰላም ፣ የፍቅር ፣ የመተሳሰብ እና የአንድነት ይሁንልን በማለት መልእክታቸውን አስተላልፈዋል። ©️ተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል @Tinsae_ze_ethiopia
Show all...
👍 2
"ከውሸት ፣ ከክፋት ፣ ከመወነጃጀል ነጽተን ትንሣኤውን በእውነትና በፍቅር እናክብር " ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ሚያዝያ 29 ቀን 2016 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ) የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የኒውዮርክና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ በዓለ ትንሣኤን አስመልክተው የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላልፈዋል። ትንሣኤ ማለት ሕዝበ ክርስቲያኑ በጠቅላላ አምኖ የሕይወትን ትንሣኤ ስናከብር ነው በማለት የገለጹ ሲሆን አያይዘውም በዓለማችን ላይ የ ትንሣኤ ሕይወትን የሚለማመድ እና በሞት ጥላ ስር የሚኖሩ አሉ በመሆኑም በሞት ጥላ ለሚኖሩት ትንሣኤ የሚባል ነገር የለም ነገር ግን በሕይወት ትንሣኤ ስንኖር ዛሬ ብቻ ሳይሆን ሁሌም ትንሣኤ ነው በማለት ምክራቸውን ለግሰውናል። ምድራችን ሁል ጊዜ በበሽታ ላይ ነው ያለችዉ በሕመም ላይ ነው ያለችው ስለዚህ ትንሣኤ ዛሬ ነው ካልን ከውሸት ፣ ከክፋት ፣ ከመወነጃጀል ነጽተን ትንሣኤውን በእውነትና በፍቅር እናክብር በዓሉም የሰላም ፣ የፍቅር ፣ የመተሳሰብ እና የአንድነት ይሁንልን በማለት መልእክታቸውን አስተላልፈዋል። ©️ተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል @Tinsae_ze_ethiopia
Show all...
በትንሣኤ እና በጠቅላላው በሐምሳው ቀናት ክርስቲያናዊ ሰላምታችን በረዥሙ እንዲሁም በአጭሩ (ሐሳብ መስጠት ይቻላል!!!) +++ Orthodox Greetings at Easter & the 50 days: ++++ ሀ/ በረዥሙ ካህን: ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን Priest:- Christ is risen from the dead ሕዝብ፦ በዓቢይ ኃይል ወሥልጣን People:- With great strength and authority ካህን: ዓሠሮ ለሰይጣን Priest:- He chained Satan ሕዝብ፦ አግዓዞ ለአዳም People:- He freed Adam ካህን:- ሰላም Priest:- Peace ሕዝብ፦ እምይእዜሰ People:- Henceforth ካህን:- ኮነ Priest:- Became … ሕዝብ፦ ፍሥሐ ወሰላም People:- Joy and peace ++++++ ለ/ በአጭሩ፤ + Short greeting form (as in the Other Orthodox Churches) in our day to day encounters could be:- ** ሰላምታ አቅራቢ:- "ክርስቶስ ተንሥአ [እሙታን]" = (ክርስቶስ ተነሥቷል) ++ Greeter:- Christ is risen [from the dead.] ** ሰላምታ ተቀባይ:- "በአማን ተንሥአ እሙታን!!" = (በእውነት ተነሥቷል) ++ Person receiving the greeting:- "Truly He is risen [from the dead.]" + በሌሎች ክርስቲያኖች ዘንድ ያለው ሰላምታ!!!! ** “Christ is Risen!”, ** “Truly, He is Risen”. (This is used in almost all Christian nations, each translating it to its own language.) A/ Greek: ** “Χριστός ἀνέστη! Ἀληθῶς ανέστη! ** (Khristós Anésti! Alithós Anésti!)”, B/ Latin: ** “Christus resurrexit! Resurrexit vere!”, C/ Aramaic Syriac: “ܡܫܝܚܐ ܩܡ! ܫܪܝܪܐܝܬ ܩܡ!‎ (Mshiḥa qām! sharīrāīth qām! ; Mshiḥo Qom! Shariroith Qom!)”, D/ Hebrew: “המשיח קם! באמת קם!‎ (Hameshiach qam! Be’emet qam!)”, E/ Arabic: “المسيح قام! حقا قام!‎ (al-Masīḥ qām! Ḥaqqan qām!); المسيح قام! بالحقيقة قام!‎ (al-Masīḥ qām! Belḥāqiqāti qām!)”. F/ Coptic, the Paschal greeting is: ** Neo-Bohairic as “Pikhristos Aftonf! Khen oumethmi aftonf!” and in Old Bohairic as “pikhristos afdonf! khen oumetmei afdonf!”. ++++ ©️ TMC @Tinsae_ze_ethiopia
Show all...
ኢሀሎ ዝየ ተንሥአ በከመ ይቤ፤ ነዓ ርእያ ኀበ ተቀብረ። ወንጌል ዘማቴዎስ 28፥6 #ትንሣኤ የዕለቱን ወንጌል እናንብብ! ሚያዝያ 27 ቀን 2016 ዓ.ም በበዓለ ትንሣኤ የሚነበብ የማቴዎስ ወንጌል ም 28 ፥ 1 - 19 የማርቆስ ወንጌል ም 16 ፥ 1 - 20 የሉቃስ ወንጌል ም 24 ፥ 1 - 12 የዮሐንስ ወንጌል ም 20 ፥ 1 - 18 መልካም በዓለ ትንሣኤ ! ©️TMC
Show all...
1