cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

Unique generation

ያደረኩት የለም ስለመዳኔ የከፈልኩት የለም ስለመዳኔ እንዲው በነፃ የዳንኩት እንዲው በፀጋ እንዲው በፀጋ!!!!!!!!! @Frajc

Show more
Advertising posts
676
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

ህይወት እንደ ፐላኔት Rev. Dr. Tony Campolo የተባለ የባፕቲስት ቤተክርስቲያን ፓስተር "ለምን ሜርኩሪ የተባለችው ፕላኔት ሞቃታማ ስትሆን ፕላቶ ደግሞ በጣም ቀዝቃዛዋ ፕላኔት ሆነች?" ሲል ይጠይቃል፡፡ ለዚህም ዋና ምክንያት ከጸሐይ ያላቸው ርቀትና ቅርበት ነው፡፡ ይህም የሚያሳየው ጸሐይን በራቅን ቁጥር መቀዝቀዝ፤ በቀረብናት መጠን መሞቅን (ትኩስ መሆንን) ነው፡፡ የእኔ፤ የአንተና፤ የአንቺ (የእኛ) ክርስትና ግለት እንደ ፕላኔቶቹ ቢለካ፤ የየትኛዋ ፕላኔት የሙቀት ጠባይ ይታይብናል?  ሁልጊዜ ሞቃት የሆነ ክርስትና -እንደ ሜርኩሪ?፤ወይስ ሁልጊዜ ቀዝቃዛ የሆነ ክርስትና -  እንደ ፕላቶ? ወይስ በወቅት የተከፋፈለ ተለዋዋጭ ክርስትና (ክረምት ፤በጋ ፤ጸደይና፤ በልግ) እንደ መሬት? እግዚአብሔር ሜርኩሪ ክርስቲያኖችን ይፈልጋል፡፡💎 የክርስትናችንን ግለት ጠብቆ የሚያቆየው ከልጁ ከክርስቶስ ጋር ያለንን ቅርበት ወይም ግንኙነት ጠብቆ መቆየት ነው፡፡ (close and stay hot all the time by being stay close to the S-o-n.) “በእኔ ኑሩ፤ እኔም በእናንተ እኖራለሁ”ዮሐ.15፡4፤ ራዕ.3፡16 @UniquegenerationJc
Show all...
ፕሮቴስታንት ፣ ኦርቶዶክስ፣ ካቶሊክክ፣  መሆን አያኩራራም፣ አያመፃድቅም፣ አያዘልልም፣ አያስደስትም፣ መኩራራት እና መደሰት እንዲሁም መመጻደቅ ካለብን ክርስቶስ ክርስቲያን ስላደረገን እንዲሁም የዘለዓለም ህይወት ባለቤት ስላደረገን ብቻ መሆን አለበት!!! √💎💎💎ሰው የመሰረተው ድርጅት ለዘላለም አይኖርም!!! √ 🕊🕊🕊ክርስቶስ የመሰረተው ቤተ ክርስቲያንን ነው እሷም በደም ስለተመሰረተች ለዘላለም ትኖራለች ከሙሽራዋ ጋር!!!! 🕊 Join us @uniquegenerationJc @uniquegenerationJc #Frajc
Show all...
አቤት የአለም ሀሳብ አቤት የአለም ነገር አረ እንዴት ይገርማል አረ እንዴት ይደንቃል ሰውን ሰው የሚሉበት የአለም መመዘኛው ሆኖ አገኘሁት ሀብት ብልጥግናው ቃሉ ግን የሚለው በአለም ካለው በፍጹም መልኩ የተለየ ነው የእግዚአብሔርን ፍቃድ ያረገ በእምነቱ ታምኖ ፀንቶ የኖረ ከአለም ግርግር ራሱን የለየ ኢየሱስ ኢየሱስ ህይወቱ የሚለው በህልውና ውስጥ የሚኖረው ሁሌ የሚናፍቅ ክብርህን ሊያየው ሰው አድርገኝ አድርገኝ ያንን ሰው በሀሳብህ ያለው በፍቃድህ ያለው በልብህ ያለውን ገና ከማህፀን ስለኔ ያሰብከው ስለኔ ያለምከውን በዕቅድህ ለዘመኔ ስኖር አደራ ሰጥተህኛል በምድር ለሀሳብህ የሮጥኩኝ መስሎኝ ምደክመው ብቻዬን እንዳይሆን አቤቱ ይህን ለምንሃለሁ ስንፍና ቤቴ እንዳያገኘው ያንተ ሰው አድርገኝና ሩጫህን ፈፅም በእኔማ እኔማ መኖሬስ ካልቀረ እኔማ በዚህ ምድር ላይ ሀሳብህ ይፈፀም አባ በኔ ላይ እኔማ የምድሩን ትቼ እኔማ ታይቶ ሚያልፈውን     ለሀሳብህ ኖሬ ለአንተ ሰው ልሁን ዳዊትም በዘመኑ ማብቂያ የልቡን አጀንዳ ሲያወራ ልጄ ሰለሞን ሆይ ሰው ሁን አትርሳው የአባትህን ምክር ዘመኔ የኔ እንደው አብቅቷል መንፈሱ ባንተ ይቀጥላል የልቡ ማረፊያው ሆነ ሩጫውን ጨርስ ፈፅመህ እኔማ ይሄን ተምሪያለሁ እኔማ ከእምነት አባቶቼ ማለፍን እሻለሁ እንደ ሀሳብህ ሆኜ እኔማ በቀረው ዘመኔ እኔማ ሆኜ እንደ ልብህ ፀሎቴ ነው ይሄ ሰው ሆኜ ማለፍ Join us @UniquegenerationJc @UniquegenerationJc @UniquegenerationJc @UniquegenerationJc #FiraJc
Show all...
Father's Love Letter An intimate message from God to u.... Father's Love Letter My Child, You may not know me, but I know everything about you.   Psalm 139:1 I know when you sit down and when you rise up.   Psalm 139:2 I am familiar with all your ways.  Psalm 139:3 Even the very hairs on your head are numbered.   Matthew 10:29-31 For you were made in my image.  Genesis 1:27 In me you live and move and have your being.   Acts 17:28  For you are my offspring.    Acts 17:28  I knew you even before you were conceived.   Jeremiah 1:4-5  I chose you when I planned creation.  Ephesians 1:11-12  You were not a mistake, for all your days are written in my book.   Psalm 139:15-16 I determined the exact time of your birth and where you would live.   Acts 17:26  You are fearfully and wonderfully made.   Psalm 139:14  I knit you together in your mother's womb.   Psalm 139:13  And brought you forth on the day you were born.   Psalm 71:6 I have been misrepresented by those who don't know me.   John 8:41-44 I am not distant and angry, but am the complete expression of love.  1 John 4:16  And it is my desire to lavish my love on you.   1 John 3:1  Simply because you are my child and I am your Father.   1 John 3:1 I offer you more than your earthly father ever could.   Matthew 7:11  For I am the perfect father.  Matthew 5:48  Every good gift that you receive comes from my hand.   James 1:17 For I am your provider and I meet all your needs.   Matthew 6:31-33  My plan for your future has always been filled with hope.  Jeremiah 29:11  Because I love you with an everlasting love.   Jeremiah 31:3    My thoughts toward you are countless as the sand on the seashore.  Psalm 139:17-18 And I rejoice over you with singing.   Zephaniah 3:17  I will never stop doing good to you.   Jeremiah 32:40  For you are my treasured possession.  Exodus 19:5  I desire to establish you with all my heart and all my soul.  Jeremiah 32:41  And I want to show you great and marvelous things.   Jeremiah 33:3  If you seek me with all your heart, you will find me.   Deuteronomy 4:29  Delight in me and I will give you the desires of your heart.   Psalm 37:4  For it is I who gave you those desires.   Philippians 2:13  I am able to do more for you than you could possibly imagine.  Ephesians 3:20  For I am your greatest encourager.   2 Thessalonians 2:16-17 I am also the Father who comforts you in all your troubles.   2 Corinthians 1:3-4  When you are brokenhearted, I am close to you.   Psalm 34:18  As a shepherd carries a lamb, I have carried you close to my heart.   Isaiah 40:11  One day I will wipe away every tear from your eyes.   Revelation 21:3-4  And I'll take away all the pain you have suffered on this earth.  Revelation 21:3-4  I am your Father, and I love you even as I love my son, Jesus.   John 17:23  For in Jesus, my love for you is revealed.    John 17:26 He is the exact representation of my being.   Hebrews 1:3  He came to demonstrate that I am for you, not against you.    Romans 8:31  And to tell you that I am not counting your sins.    2 Corinthians 5:18-19 Jesus died so that you and I could be reconciled.    2 Corinthians 5:18-19  His death was the ultimate expression of my love for you.   1 John 4:10 I gave up everything I loved that I might gain your love.    Romans 8:31-32  If you receive the gift of my son Jesus, you receive me.    1 John 2:23 And nothing will ever separate you from my love again.   Romans 8:38-39 Come home and I'll throw the biggest party heaven has ever seen.   Luke 15:7  I have always been Father, and will always be Father.    Ephesians 3:14-15  My question is…Will you be my child?     John 1:12-13  ተባረኩበት 🙏🙏🙏 @UniquegenerationJc
Show all...
ፋሲካዬ ነውር እና ሀጢአት፡ ከቶ የሌለበት እስራኤል እንዲሰዋ፡ ስለሰራው ሀጢአት የታዘዘው፡ የተባዕት በግ አይነት ስለሰው መተላለፍ ፡ሚሰዋ ሚታረድ ቢፈለግ ቢታጣ ፡በሰማይ በምድር ክርስቶስ ተገኘ ፡ነውር የሌለበት በግ ክርስቶስ ተገኘ ፡ፍቃደኛ የሆነ በባህሪው ፡አምላክ ሆኖ ሳለ የባሪያን መልክ፡ ይዞ ሊያድነኝ ወደ ምድር የመጣ ፡እራሱን አዋርዶ ወደ ምድር የመጣ፡ እራሱን ባዶ አርጎ ያቀረበኝ ፡በደሙ ፃዲቅ አርጎ ነውር እና ነቀፋ ፡የሌለኝ አድርጎ ወደ እግዚአብሔርም ፡ በቅድስና እንድቀርብ ለያህዌ ቅዱስ ፡ መሰዋዕትን እንዳቀርብ ቅዱሱንም ስም ፡ ደፍሬ እንድጠራ ፋሲካዬ ፡ ክርስቶስ ታርዶልኛል የረዳኝ ያገዘኝ፡ በመስቀል ላይ የሞተልኝ ከነአመፃዬ፡ በፍቅር የተቀበለኝ ለሀጢአቴ ብሎ ፡በሞት የተቀጣልኝ ደዌን ፡ማያውቀው ሰውነት ደዌን ያወቀው፡ ስለኔ ሀጢአት ስለኔ ሀጢአት ፡እንደሌሎች በጎች ሳይሆን መቶ ፡አንድ ጊዜ ሚታረድ ሳይሆን ፡እንደሌሎች በጎች ደም ለአንድ ጊዜ፡ ብቻ የሚጠቅም አንዴ ለማንፃት፡ ብቻ የሚጠቅም የክርስቶስ ደም፡ ሳይሆን አንድ ጊዜ ለዘላለም ፡ሚያነፃ ሚጠቅም የደሙ ድምፅ ፡ይቅር በላቸው የሚል ደሙ የሻረ ፡መርገምን ከአለም ከምህረት ፡እስከ ምህረት ፅድቁን አልብሶ ፡መንፈሱን ያስታጠቀኝ ሞት ፡ሲያይ ፋሲካዬን መርገም ፡ሲያይ ፋሲካዬን ከኔ አልፎ ሚሄድ ፡ከቶ ማይደርስብኝ ፋሲካዬ ፡ክርስቶስ ታርዶልኛል እርሱ ታርዶ ፡በህይወት ያኖረኝ ሞቱ ደፍሬ፡ በእግዚአብሔር ፊት ፃዲቅ ሆኜ፡ እንድቆም ያረገኝ ፋሲካዬ ክርቶስ ፡አንዴ ታርዶልኛል ሀጢአቴን ፡በፅድቅ ቀይሮልኛል ሞቴን ፡በህይወት ለውጦልኛል በሰዎች ተርታ ፡እንድቆም አርጎኛል ✍FiraJ @FiraJc
Show all...
✍ ይሄ ነው ገዳይ * ሰቀልነው ሲ ፣ የሰቀላቸ ቀበርነው ሲ ፣ የቀበራቸው ሰይጣንን ገፎ ፣ እርቃን ያ'ረገ ያለቀሱትን ፣ ከልብ ያሳቀ የእባቡን ራስ ፣ የቀጠቀጠ ለሙታን ሁሉ ፣ ህይወት የሰጠ ሽታው የፍቅር♥♥♥ ድምፁ የፍቅር♥♥♥ መጠሪያው ፍቅር♥♥♥ ምግባሩ ፍቅር♥♥♥ የጠጡት ጊዜ ፣ ሰው የሚያሰክር ይሄ ነው ፍቅር♥ የዕድሜው ዘመን ፣ የማይቆጠር ፊቱ ሰዎች ላይ ፣ የማይቋጠር በሞቱ ሞትን ፣ ወግቶ የገደለ ከዲያብሎስ አፍ ፣ እኔን ያስጣለ ለሟች ለመሞት ፣ ለነፍሱ ያልሳሳ ባሪያ ለማድረግ ፣ ጆሮ 'ማይበሳ ሰይጣን ሲያዘጋጅ ፣ የመስቀልን ሞት እንደሚነሳ ፣ ተናግሮ 'ሚሞት ያለምን ብልጠት ፣ በሞኝነቱ ሞኝነት 'ሚያደርግ ፣ ድል በመንሳቱ ሲክዱት ጊዜ ፣ በቀል 'ማያስብ ሄዶ እንደገና ፣ የሚሰበስብ "ባለፈው እኮ" ፣ ብሎ 'ማይጠቅስ በቸርነቱ ፣ ሰው የሚመልስ ይሄ ነው ጀግና♥ አንድን መስዋዕት ፣ ለዘላለሙ መንፈስ በሆነ ፣ በህያው ደሙ ዳግመኛ ላይሞት ፣ አንዴ ያቀረበ የበዳዮችን ፣ በደል ያጠበ ሀጥያተኛውን ፣ ፅድቅ ያደረገ ከአሮን ክህነት ፣ እጅግ የላቀ ከሙሴ ፊደል ፣ በሚሻል መንፈስ ሞትን በመሻር ፣ ህይወት የሚያፈስ ከመላ'ክት ይልቅ ፣ እጅግ የሚበልጥ ሁሉ ከ'ግሩ ስር ፣ የተገዛለት ህያው መስዋዕት ፣ ላባቱ ያስገባ ስለኛ ቀድሞ ፣ ሰማይ የገባ አሁን በአብ ቀኝ ፣ የተቀመጠ እኔንም ከሱ ፣ ጋር ያስቀመጠ ይሄንን ታላቅ ፣ ሊቀ ካህን ነው አፌን ሞልቼ ፣ አለኝ የምለው ገ'ሎ ያስወገደ ፣ የሞቴን ጉዳይ ይሄ ነው ጀግና ፣ ይሄ ነው ገዳይ♥ ይሄ ነው ፍቅር♥♥♥ #ሄኖክ_አሸብር https://t.me/joinchat/RrbSCabYHAXQ6nx7
Show all...
#የየትኛው ጀማ አባል ናቹ??(ጓደኞችህ እነማን ናቸው???) የምን ጀማ?😳 ልትሉኝ ትችችላቹ እስቲ ትንሽ ስለጀማ ልበላቹ ........ሁለት አይነት ጀማዎች አሉ አንድ ሰው ከሁለት አንዱ ውስጥ የጀማው አባል መሆኑ ግድ ነው ግን ሁለቱም ውስጥ አባል መሆን አይቻልም ለምን?😳 በሉኛ😜 ሁለቱም ጀማዎች #ፍፁም ተቃራኒ ኧረ ከነ ማይገናኙ ናቸው ስላቹ(ይሄኔ እኮ በቃ እነማን ናቸው እያላቹ ሆዳቹ እየጮኸ ነዋ😜😁 #ታዲያ እነዚያ ጀማዎች እነማን ናቸው??🤔🤔🤔 👉#የጀማውን ስም አስቀድሜ ልንገራቹ.....#የመንፈስ ጀማ እና #የአለም(የስጋ) ጀማ ይባላሉ ለምሳሌ አንድ ሰው የአለም ጀማ ውስጥ Join ካሉ በኃላ ሁሉ ነገሩ በጀማው ውስጥ እንዳሉት አባላቶች ነው ሚሆኑት እና እላቹዋለው ሁለቱ ጀማዎች ያፈሯቸው የራሳቸው የሚሏቸውም አላቸው 🤔እነማን ናቸው አትሉኝም ታዲያ ...ለምሳሌ የመንፈስ ጀማ ውስጥ በዋነኛነት #ፍቅር የሚባል አለ በቃ ተውኝ ሚገርም ባህሪ ነው ያለው ብታዩ እኮ አይቀና ፣አይመቀኝ ፣አይሳደብ፣ ሽንገላንማ ከነ አያውቅም፣ወላ ስለነምቀኛ ምናምን ብትጠይቁት እነማን ናቸው ነው ሚላቹ ክፋት ሚባል ነገርንማ ጭራሽ አያቅም፣ደግ ነው፣ቂም አይዝም በቃ ተውኝ ሚገርም ልጅ እኮ ነው ይሄን ባህሪውን ከአባቱ ነው የተማረው ኧረ አባቱና ፍቅርን ራሱ አትለዩዋቸውም እኮ እናም በቃ ሌሎችም አሉ እምነት ቅድስና ቸርነት ሚባሉ ሚገራርም ባህሪ ያላቸው አሉ የአለም ጀማ ደግሞ ክፋት፣ ስካር፣ አስመሳይ ፣ምቀኛ ገንዘብ መውደድ ሚባሉ አሉ ገንዘብ መውደድንማ ተውኝ የክፋት መሠረትና ስር ነው እኮ ከገንዘብ መውደድ ጋር ሆናቹ ከትዕቢት ከሚባለው ጋር አለመሆን አትችሉም 🤔ኧረ መሪዎቹ እነማን ናቸው ታዲያ????🥺🥺 👉👉#የመንፈስ ጀማው መሪ "'"#ኢየሱስ"""ይባላል ሚገርም leader ነው እኮ ቅድም እንዳልኳቹ በቃ #ፍቅርና #ኢየሱስ አንድ ናቸው ፍቅር ማለት ኢየሱስ ነው 👉👉የስጋው ጀማ leader ደግሞ 🤭 "ሰይጣን" ነው ሚገርማቹ ገንዘብ መውደድ ከመሪው ጋር እኩል ልሁን ልሁን ይላል ኧረ ከመንፈስ ጀማው leader ጋርም ሊወዳደር ይፈልጋል እኮ ➡️እና እስቲ ልጠይቃቹ አንተ/አንቺ የየትኛው #ጀማ አባል ናቹ??? አላውቅም የሚል ደግሞ ባህሪውን አይቶ የማን ጀማ አባል አይቶ ራሱን ይወቅ ##ራሱንም ##ይፈትሽ ##ራሱንም ##ይመርምር #⃣በመጀመሪያ ግን የትኛው ጀማ ውስጥ ነው join ማለት ምትፈልገው/ጊው????? ###ምረጡ ⏩⏩⏩ገላ5 :17-23⏪⏪⏪ ተባረኩልኝ ተመናቹ ይለምልም በኢየሱስ ደም ተሸፈኑ ከፍቅር በቀር በሰው ላይ ምንም እዳ አይኑርባቹ ጌታ በመንፈሱ ያረስርሳቹ ➡️ብቻ ምን አለፋቹ ክብር አለ እሳት አለ #ሀሌሉያ ከእህታቹ #ጵንኤልkulman @uniquegenerationjc @uniquegenerationjc
Show all...
ዮሐንስ 14 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ²³ ኢየሱስም መለሰ አለውም፦ የሚወደኝ ቢኖር ቃሌን ይጠብቃል፤ አባቴም ይወደዋል ወደ እርሱም እንመጣለን በእርሱም ዘንድ መኖሪያ እናደርጋለን። ²⁴ የማይወደኝ ቃሌን አይጠብቅም፤ የምትሰሙትም ቃል የላከኝ የአብ ነው እንጂ የእኔ አይደለም። ²⁵ ከእናንተ ዘንድ ስኖር ይህን ነግሬአችኋለሁ፤ ²⁶ አብ በስሜ የሚልከው ግን መንፈስ ቅዱስ የሆነው አጽናኝ እርሱ ሁሉን ያስተምራችኋል እኔም የነገርኋችሁን ሁሉ ያሳስባችኋል። ²⁷ ሰላምን እተውላችኋለሁ፥ ሰላሜን እሰጣችኋለሁ፤ እኔ የምሰጣችሁ ዓለም እንደሚሰጥ አይደለም። ልባችሁ አይታወክ አይፍራም። ²⁸ እኔ እሄዳለሁ ወደ እናንተም እመጣለሁ እንዳልኋችሁ ሰማችሁ። የምትወዱኝስ ብትሆኑ ከእኔ አብ ይበልጣልና ወደ አብ በመሄዴ ደስ ባላችሁ ነበር። ²⁹ ከሆነም በኋላ ታምኑ ዘንድ አሁን አስቀድሞ ሳይሆን ነግሬአችኋለሁ። ³⁰ ከእንግዲህ ወዲህ ከእናንተ ጋር ብዙ አልናገርም፥ የዚህ ዓለም ገዥ ይመጣልና፤ በእኔ ላይም አንዳች የለውም፤ ³¹ ነገር ግን አብን እንድወድ ዓለም ሊያውቅ፥ አብም እንዳዘዘኝ፥ እንዲሁ አደርጋለሁ። ተነሡ፤ ከዚህ እንሂድ።
Show all...
ዮሐንስ 17 (John) 1-2፤ ኢየሱስም ይህን ተናግሮ ወደ ሰማይ ዓይኖቹን አነሣና እንዲህ አለ፦ አባት ሆይ፥ ሰዓቱ ደርሶአል፤ ልጅህ ያከብርህ ዘንድ፥ በሥጋም ሁሉ ላይ ሥልጣን እንደ ሰጠኸው፥ ለሰጠኸው ሁሉ የዘላለምን ሕይወት ይሰጣቸው ዘንድ ልጅህን አክብረው። 3፤ እውነተኛ አምላክ ብቻ የሆንህ አንተን የላክኸውንም ኢየሱስ ክርስቶስን ያውቁ ዘንድ ይህች የዘላለም ሕይወት ናት። 4፤ እኔ ላደርገው የሰጠኸኝን ሥራ ፈጽሜ በምድር አከበርሁህ፤ 5፤ አሁንም፥ አባት ሆይ፥ ዓለም ሳይፈጠር በአንተ ዘንድ በነበረኝ ክብር አንተ በራስህ ዘንድ አክብረኝ። 6፤ ከዓለም ለሰጠኸኝ ሰዎች ስምህን ገለጥሁላቸው። የአንተ ነበሩ ለእኔም ሰጠሃቸው፤
Show all...
#ጥበብ_የአምላክ_ስጦታ_ነው ( ምሳሌ 2:1-9) ሰለሞን በምሳሌ መፅሀፍ ምዕራፍ 1 ላይ አመፀኞችን ፣ ሞኞችን እና ትዕቢተኞችን ያስጠነቅቅ ነበር ፤ ምክንያቱም ሰለሞን ጥበበኛ ሰው እንደሚያደምጥ አምኗልና (ምሳሌ 1:5) ። 👉 እግዚአብሔርም እነዚህ አመፀኞች እና የጠፋት ልጆቹ በሙሉ ወደ እሱ እንዲመለሱ ይጠብቃል ፤ "ለአንዳንዶች የሚዘገይ እንደሚመስላቸው ጌታ ስለ ተስፋ ቃሉ አይዘገይም፥ ነገር ግን ሁሉ ወደ ንስሐ እንዲደርሱ እንጂ ማንም እንዳይጠፋ ወዶ ስለ እናንተ ይታገሣል።" (2 ጴጥ 3: 9) 👉በመንፈስ ቅዱስ እርዳታ የተጣለው እና ትዕቢተኛው ወደ እርሱ ይቀርባል ፣ አመፀኛውም በንስሀ ወደ እርሱ ይመለሳል #ሉቃ_15 ላይ የጠፋውም ልጅ እንዳደረገው። 👉 የመፅሀፈ ምሳሌ ምእራፍ 2 የመጀመሪያዎቹ 9 ቁጥሮችም ያንኑ ገፅታ የያዙ ናቸው። #እግዚአብሔርን_መፈለግ ፣ #እውነቱን_መቀበል እና #አሰራሩን_ማወቅ። (ምሳሌ 2 ) ------------ 1፤ ልጄ ሆይ፥ ቃሌን ብትቀበል፥ ትእዛዜንም በአንተ ዘንድ ሸሽገህ ብትይዛት፥ 2፤ ጆሮህ ጥበብን እንዲያደምጥ ታደርጋለህ፥ ልብህንም ወደ ማስተዋል ታዘነብላለህ። 3፤ ረቂቅ እውቀትን ብትጠራት፥ ለማስተዋልም ድምፅህን ብታነሣ፥ 4፤ እርስዋንም እንደ ብር ብትፈላልጋት፥ እርስዋንም እንደ ተቀበረ ገንዘብ ብትሻት፤ 5፤ የዚያን ጊዜ እግዚአብሔርን መፍራት ታውቃለህ፥ የአምላክንም እውቀት ታገኛለህ። 👉 ሰለሞን በዚህ ምእራፍ ትኩረቱን ተምረው መለወጥ ፣ ታዘው ማገልገልን የሚፈልግ ልብ ወዳላቸው ሰዎች አዙሯል። ከብዙ አመታት በፊትም #እዮብ አንድ ጥያቄን ጠይቆ ነበር "፤ እንግዲያሳ ጥበብ ከወዴት ትመጣለች?የማስተዋልስ ስፍራ ወዴት ነው? " (ኢዮብ 28: 20) በዚህ ክፍል ላይ ለዚህ ጥያቄ ከመፅሀፍ ቅዱስ ውስጥ መልስን እናገኝለን። 1. የእግዚአብሔር ቃል የመጀመሪያው ሊደረግ የሚገባው ነገር ቢኖር የእግዚአብሔርን ቃል መቀበል ነው። ብዙ የመፅሀፍ ቅዱስ ክፍሎች ይህ ምን ማለት እንደሆነ አስረድተውናል። ለምሳሌ #ኢየሱስ ዘር ሊዘራ ስለወጣው ሰው በተናገረበት ክፍል ውስጥ ይህንኑ አውርቷል ፦ "፤በመልካም መሬት ላይም የወደቀ እነርሱ በመልካምና በበጎ ልብ ቃሉን ሰምተው የሚጠብቁት በመጽናትም ፍሬ የሚያፈሩ ናቸው። " (ሉቃ 8: 15)። #ማርያም የማርታ እና አላዛርም እህት ይህንኑ ቃል ተቀብላ ተግብራዋለች ፦ "፤ ለእርስዋም ማርያም የምትባል እኅት ነበረቻት፥ እርስዋም ደግሞ ቃሉን ልትሰማ በኢየሱስ እግር አጠገብ ተቀምጣ ነበረች። " (ሉቃ 10: 39) 👉 ሀዋርያው ጳውሎስ የእግዚአብሄርን ቃል ለብዙ ሰዎች፣ ቡድኖች እና ቤተክርስያኖች ተናግሯል። ከእነዚህም መሀል #የቤርያ ሰዎች ስማቸው በጥሩ ተነስቷል ፦ "፤ እነዚህም በተሰሎንቄ ከሚኖሩት ይልቅ ልበ ሰፊዎች ነበሩና። ነገሩ እንደዚሁ ይሆንን? ብለው ዕለት ዕለት መጻሕፍትን እየመረመሩ ቃሉን በሙሉ ፈቃድ ተቀበሉ። " (ሀዋ 17: 11) ስለዚህ እዚህ ክፍል ላይ እንደምንመለከተው #ጥበብን ከእግዚአብሔር ቃል ማግኘት እንችላለን ፤ በመጀመሪያ ግን ቃሉን መቀበል ያስፈልጋል። #ይቀጥላል... @UniquegenerationJc👈👈 @UniquegenerationJv👈👈 👆👆👆👆👆👆
Show all...