en
Feedback
የፍቅር ታሪክ (seenaa jalaala)

የፍቅር ታሪክ (seenaa jalaala)

Open in Telegram

ማስተዋል(mastewal) Fikirr @AASH23

Show more
The country is not specifiedThe category is not specified
2 842
Subscribers
+224 hours
No data7 days
+230 days
Posts Archive
sticker.webp0.26 KB

✍✍✍ጠይሙ ባሌ✍✍✍ አዲስ የ ፍቅር ታሪክ ይጀመር እምትሉ.......

👍ፍቅር_ከ_ጅንጀና 👍 ማ ይንገርሽ ? ብዙ አስብና ማፍቀሬን ልነግርሽ መኖሬ ላንቺ ነው ወድሻለሁ ልልሽ ግና ገና ሳይሽ . . . ያ ሁሉ ስቃየን አይደለም ልናገር ላንቺ የሆንኩትን እንኳን ልመሰክር ጉልበቴም ይዝላል አካሌም ይደክማል ልሳኔም ይዘጋል ልቤም ያው ይፈራል ታዲያ የኔ ፍቅር . . . የልቤን ፍላጎት አፌ ካላወራው ፍቅርሽን መራቤን ልቤ ካላወጣው ገና ሳይሽ አንቺን ጉልበቴ ከዛለ አካል እስትንፋሴ ባንቺ ከተከለለ ማን ይንገርሽ እና? እንዴትስ ታቂያለሽ? እስከ ሞቴ ድረስ እኔ እንደምወድሽ፡፡ @libmalet @libmalet

✍✍ እስኪ ንገሪያቸው✍✍ ከኔ አንደበት ወጥቶ ስላንቺ ሲነገር የኔም ያንች ልኬት እኩል ስለ ፍቅር መሆኑ አናዷቸው የነሱ ለማድረግ ከእጄ ሊያወጡሽ እኔን በመገፍተር ያም የኔ ያም ለኔ ተሽቀዳደሙብሽ °°°_°°°° እናማ መቼም ላያርቁኝ ከስርሽ በመግፋት ከቶም ላያገኙሽ ተወጥረው ትዕቢት #ውዴ_ሆይ እስኪ ንገሪያቸው!? ባንችና በኔ ውስጥ በዝቶ የተቋተ ወደፊት የሚኖር ዘውትር እ'ዳጋተ #እስኪ_ንገሪያቸው በልብሽ በልቤ ሐሴት የሚሞላ ሁሌም የሚጠብቅ ዘውትር የማይላላ እንዳለ እውነት እስኪ ንገሪያቸው ምናልባት.........ምናልባት ቢረጋ ቀልባቸው @libmalet @libmalet

#ፍቅር በህይወት ስትኖር አንተን እድለኛ ሚያሰኝህ አብሮህ ያለው ሰው ነው፡፡ ሀብት እድለኝነት አይደለም ምክንያቱም ጠንክረ ከሰራህ ምትመኘውን ያህል ልታገኝ ትችላለህ፡፡ እውቀት እደለኛ አያስብልህም ማወቅ ምትፈልገውን ያህል ለማወቅ ከልብህ ከጣረክ ሁሉንም ታገኛለህ፡፡ ምትፈልገውን አይነት ሰው ግን በምትፈልገው አይነት ሁኔታ ማግኘት እድለኝነት ነው፡፡ የምትወደውን ሰው ማግኘት ፣ከምትወደው ሰው ጋ መኖር እጅጉን መታደል ነው! @libmalet @libmalet

❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️ 💋💋💋💋💋💋💋💋💋 🖐🖐🖐🖐🖐🖐🖐🖐🖐 እስቲ ፍቅር ይዞት እሚያውቅ?

🔊ካንተ አይጠበቅም! {Mulugeta Mengist Ayalew} ማን ነዉ ተብሎ የሚያውቅ? ካንተ አይጠበቅም ሲባል አንተን ለራስህ ታማኝ እንድትሆን በማሰብ አይደለም። ይህ ቢሆን ኖሮ መልካም ነበር. Integerity ጉዳይ ይሆን ነበር። ግን አይደለም። አንተ መሆን ያለብህን ነገር እነሱ ወስነዉ፣ ካንተ አይጠበቅም ይሉሃል! አንተም ለመሆን ትሟሟታለህ! የሰዉ ኑሮ ትኖራለህ! ሁለት ነጥብ አንድ፣ ካንተ አይጠበቅም ሲሉህ፣ አንተን ካንተ የበለጠ እናዉቃለን በሚል ነዉ። የሚገርመዉ ደግሞ አንተ ብለዉ የሚያስቡት፣ አንተ ሳይሆን ካንተ ዉጭ ያሉ ነገሮችን ነዉ።ሁለት፣ አላማዉ አንተን ማነፅ አይደለም። ስለ ራሳቸዉ መልካም እንዲሰማቸዉ ነዉ። እኛ እንዲህ ነን! የሱሪ ዋጋ እንኳን የምንወስነዉ በማነፃፀር ነዉ። ስለ ራሳችን እንኳን መልካም የሚሰማን ከሌላ ጋር በማወዳደር ነዉ። ስለዚህ ካንተ ይሄ አይጠበቅም የሚል አባባል ተናጋሪዉ ስለራሱ በጎ እንዲሰማዉ ነዉ። ለዛ እኮ ነዉ ቅፅል ስም (የመዉደድ ስም አይደለም) የምንወደው! ልዩነቱን ለማሳየት! ለቀፃዩ በሚጠቅመዉ መልኩ። ምፅዋት ፣ ማፅናናትም በዚህ ከተቃኙ፣ እኛ ግን ማነን⁉ @libmalet @libmalet

1፦ሰዎች ምክንያት እየፈለጉ ጥፋተኛ ካደረጉህ ሊርቁህ እንደፈለጉ እየነገሩህ ነውና ከአንደበትህ አልፎ ውስጥህን የሚያዳምጥ አምላክ መቼም የትም እንዴትም ካንተ ጋር ነው። 2፦በህይወት ውስጥ ፈተና ከበዛብህ አትዘን ታገስ...የጨረቃ ውበት የሚጨምረው ጨለማ በዙሪያዋ በጨመረ ቁጥር ነውና። 3፦ጨለማን ጨለማ አያጠፋውም ጨለማን ማጥፋት የሚችለው ብርሀን ብቻ ነው፣ጥላቻን ጥላቻ አያጠፋውም፣ጥላቻን ማጥፋት የሚችለው ፍቅር ብቻ ነው። @libmalet @libmalet

👍የታላላቅ ሰዎች ታላላቅ አባባሎች👈 1. ከሰዎች ጋር ሮጠህ ያልደረስክበት ነገር ካለ ወደ ተነሳህበት ተመልሰህ ከፈጣሪህ ጋር መሮጥ ጀምር፣ ያኔ ካሰብክበት ሳይሆን ካሰበልህ ቦታ ትደርሳለህ፡፡ 2. በአብዛኛው ጊዜ ሴቶች የፍቅርን ትርጉም የሚጠፋባቸው በውበታቸው ማምለክ ሲጀምሩ ሲሆን ወንዶች ደግሞ በገንዘባቸው ማምለክ ሲጀምሩ ነው፡፡ 3. መጀመሪያ ለራስህ ራስህ መሆን ስትጀምር ለማን ምን መሆን እንዳለብህ ትገነዘባለህ፡፡ 4. የሰው ልጅ የማሰብ ችሎታው ሲጨምር የጓደኞቹን ብዛት ይቀንሳል፡፡ 5. ዝቅተኛ እውቀት ባለህ ቁጥር የምትተኛው እንቅልፍ ከፍተኛ ይሆናል፡፡ 6. ጓደኛን አለማመን ከመካድ የከፋ ነው፡፡ 7. የራስህን ትኩስ እንጀራ ለመጋገር ስትል የሌላውን ቂጣ አትርገጥ፡፡ 8. አንዳንድ ሰዎች የሚወድቁት ሌሎችን በሁለት እግሮቻቸው ለመርገጥ ሲጣጣሩ ነው፡፡ 9. ሰው ከጊዜ እና ከማጣት ብዙ ይማራል፡፡ 10. አንዳንዴ ሽንፈትም ከድል የበለጠ ዋጋ አለው/ ከማሸነፍ ይልቅ በመሸነፍ ውስጥ ብዙ እውቀት አለ፡፡ 11. ሠው የበለጠ እያገኘ በሄደ ቁጥር የበለጠ ስግብግብ እየሆነ ይሄዳል፡፡ 12. ሠዎች ትርጉም ያለው ሥራ መስራት ካልቻሉ የመኖር ትርጉምም ይጠፋባቸዋል፡፡ 13. የሰው ልጅ ከደስታው ይልቅ የሀዘኑን ጊዜያት መቁጠር ይወዳል፡፡ 14. ባንኮች ዝናብ ሳይኖር ዣንጥላ ያበድሩህና መዝነብ ሲጀምር ግን ዣንጥላውን ይነጥቁሃል፡፡ 15. አዋቂ ሆኖ ለመታየት የምናደርገው ጥረትና ከንቱ ድካም አላዋቂ አድርጎ ያስቀረናል፡፡ @libmalet @libmalet

የፍቅር_ወሰን # ክፍል6 # የመጨረሻ_ክፍል ደውላ አገናኘችኝ ድመጿ ራሱ በጣም ናፍቆኝ ነበረ አንደዚህ እያልን ሳምንት አሳለፍን ከሳምንት በኋላ ግን የማልውቀው ስልክ ተደወለለኝ አንሰቼ ሄሎ ብዬ አስር ሰከንድ ሰላናግር ራሴን ስቼ ወድኩ ከቀናት በኋላ ራሴን ያገኘውት ሆስፒታል ውስጥ ነው ከጎኔ ሂሩት እና እናቷ ቁሟል ምን አለ በዛው ሙቼ በቀረሁ ብዬ ስቅ ስቅ ብዬ አለቀስኩ በስልክ የተነገረኝ እናቴ እንዳረፈች ነበረ በቃ ሁሉም ነገር አስጠላኝ እናቴን አንድም ቀን ደህና ፊት እንኳ ሳላሳያት ተለየችኝ ብዬ በቃ በጣም አዘንኩ ህይወቴ ቃና አልባ ሆነብኝ አንድ ቀን የልቤን ሳልነግራት ሁሌም እኔን ለመስማት ጆሮዋቿ ክፍት እንደ ሆኑ ነው ስንት ቀን ልታወራኝ ፈልጋ የልጇን ፍቅር እንዳጣች ገባኝ ምንድነው የኔ ጥቅም አልኩ ለእናቴ ያልሆንኩ ለማን ልሆን ነው ብዬ በጣም ነበር ያዘንኩኝ ሁለት ቀን በኋላ እንደ ምንም ከሆስፒታል ወጥቼ እናቴ ወደ አረፈችበት ቦታ ልንሄድ ብለን አንዴ ቤት ደርሰን እንምጣ አለች ሂሩት ሚገርመው ግን በዚህ ሁሉ ችግሬ ሂሩት ለደቂቃ አልተለየችኝም እሺ ብዬ አብረን ወደ ቤት እንደ ሄድነ ሳሚ ጥቁር በጥቁር ለብሶ ግቢ ውስጥ አቀርቅሮ ተቀምጧል በልቤ ምን አባቱ ሊያደርግ መጣ አልኩኝ ምንም አልተናገረንም ሂሩት እቤት ገብታ ለጉዞ የሚሆን ቦርሳ ይዛ ወጣች ስንወጣ ሳሚ ተከትሎን ወጣ ወዴት ነው ሚሄድ አልኳት ባክሽ ተይው ብላ መንገዳችንን ቀጠልን እሩቅ መስሎኝ ነበረ ግን እንጦጦ ኪዳነ ምህረት ነበረ በቃ ቤተክርስትያን አከባቢ ስደርስ መላ ሰውነቴ አልታዘዘኝ አለ እንደ ምንም ብለው ይዘውኝ ገቡ የእናቴ መቃብር የተባለውን እንዴት ልየው ከእንባ ብዛት አይኖቼ ደምዝዘዋል ድምፄ ተዘግቷል እማ አንዴ የልቤን ልንገርሽ ስሚኝ አልኳት መልስ የለም ምትሰማኝ ይመስል እማ አኮረፍሽኝ እንዴ አልኳት ሳሚ እና ሂሩት ከጀርባዬ ሲያለቅሱ ይሰማኛል ሰውነቴ ግን ደንዝዟል እማ አብረሽኝ እያለሽ እኮ ሁሉንም ነገር እንደ ዋዛ ነበረ ያየሁት እማ ስሚኝ አሁን እኔ ለማን ነው የምኖረው እቤትስ ማንን ላግኝ ብዬ ነው የምሄደው ብዬ በቃ ስቅስቅ ብዬ አለቀስኩ ከማልቀሴ የተነሳ ጉንጬ እንባዬ ሲያርፍበት ያቃጥለኛል ሳሚ አንዴ ሰለ እናት ያለኝ ትዝ አለኝ # የእናት_ሞት_እና_ድንጋ_ላይ_መቀመጥ_እያደረ # ይቆርቁራል በሰአቱ በጣም ነበር የሰኩበት ዛሬ ግን አንድ ደቂቃ እንኳ መቻል አቃተኝ በቃ እዛው መቃብሯ ላይ ራሴን ስቼ ወደኩ ስነቃ አንድ ፀበልተኛ ቤት ውስጥ ነኝ እንደ ምንም ብለው ከተኛውበት ደግፈው አነሱኝ ሂሩት ሁሉንም ነገረችኝ ቤዚ የሰጠችሽ ወረቀት ስላላወቅሽበት እንጂ አንቺ ያለሽበት ሁኔታ ነበረ ወረቁቱ ላይ ምንም አልተፃፈም ግን በመሀል ላይ ትንሽ በእስክብሪቶ ምልክት ነገር አለው ያ ማለት አንቺ ነሽ ምንም ያልተፃፈባት ወረቀት ደግሞ እናትሽ ናት እናትሽ ሁሌም አንቺን ወረቁት ላይ እንደ ሰፈረው ምልክት ነው የምታይሽ ሁሌም ለእሷ ህፃን ነሽ ትሳሳልሻለች አንቺ ደግሞ በተቃራኒው ትንቅያታለሽ ለሷ ያለሽ ቦታ በጣም የወረደ ነው ቤዚ አላረገዘችም ሳሚ ለሱ ያለሸውን ቦታ ለማወቅ ሲል ቤዚን እሱ ነው ያሰርረገዛት ብላ ትጠራጠር ይሆን ብሎ ነው እንደዚህ ያደረገ ሁሉም ነገሮች አንቺ ባልገባሽ መንገድ ነው የተደረጉ አለች ሁሉንም ስትነግረኝ አንዱን አለ መጠርጠሬ አናደደኝ ሂሩት ነገውን መመለስ አለብን ብላ ወደ ቤት ተመለስን ሰፈር ደረሰን ሳሚ ወደ ቤት ሊሄድ ሲል ሂሩት ቡና ጠተህ ሂድ ሳሚ አለችው እሺ ብሎ ገባ የሰፈር ሰው እንዴት አልሰማም የእናቴን መሞት ብዬ በጣም ገርሞኛል ግራ ገባኝ ቤት እንደ ገባን ሶፋው ላይ ቁጭ አደረጉኝ ሰውነቴ ዝሏል ሂሩት ሳሚን ሂድና መድሀኒት ይዘህላት ና ብላ ላከችው ሰራተኛችን ቡናውን እያቀራረበች ምናምን ራሴን በጣም ስላዞረኝ በእስካርፕ አሰርኩት ሂሩት አይታኝ በጣም አመመሽ እንዴ አለችኝ አዋ ብዬ እንባዬ ይፈስ ጀመረ ሲያመኝ እማ እንዴት እንደ ምትሆን ትዝ አለኝ ሂሩት መጣ እግሬ ስር ቁጭ አለች እንዳላለቅስ ለመነችኝ እንዴት አድርጌ ከአሁን በኋላ ያለው ዘመኔ በለቅሶ እንደ ምኖረው አውቃለሁ አልኳት እሺ ቆይ ይሄን ታክል ምትወጂያት ከሆነ ለምን እንደዛህ ትሆኚባት ነበረ አለችኝ መልስ የለኝም በእጅ ያለ ወርቅ ነው የሆነብኝ ሁሌም ሰው ከእጅ ከወጣ በኋላ ነው የሚፀፀተው በዚህ መሀል ሳሚ መጣ መድሀኒቱን አመጣህላት ብላ ተነሳች አዋ ብሎ ፊት ለፊቴ ቁጭ አለ አይኑን ሳየው ፈገግ አለ መድሀኒቱስ አልኩት ደምፄ በጣም ደክሟል ሶፋው ላይ አንገቴን ዘንበል አድርጌ ነበረ እሱስ አጠገብሽ አለኝ ዞር ስል ልቤ ለሁለት ስንጥቅ አለ እናቴ ፊቴ ቁማለች ግራ ገባኝ እንደዛ መቆም ያቃተኝ ልጅ ከተቀመጥኩበት ተስፈንጥሬ ተነሳሁ በቃ የሰው ልብ የሚቀልጥ ቢሆን ኑሮ እዛን ሰአት ልቤ ይቀልጥ ነበር ራሴ አዙሮ ሊጥለኝ አለ ወንበሩን አንደ ምንም ብዬ ያዝኩት ወንበሩ ላይ ያለውን ውሀ ፊቴ ላይ ረጨው በህልሜ አለመሆኑን አወኩ እናቴን ቀስ ብዬ ዳበስኳት በቃ እውነት መሆኑን ሳውቅ ጩኸቴን ለቀኩት ሁሉ በደስታ እንባ ታጠበ ድጋሚ ተወለድኩ እናቴን የምገልፅበት ቃል የለኝም ሁሉም ነገር ከአቅሜ በላይ ሆነብኝ ዝቅ ብዬ እግሮቿን ሳምኩ እማ ግን እውነት በሰመመን አለም ውስጥ አይደለሁም አይደል አልኳት አቀፈችኝ በጉያዋ ውስጥ አደረገችኝ ለዚህ ሁሉ ነገር ሂሩትን አመስግኛት አለችኝ ይሄን ሀሳብ ያመጣችው እሷ እንጂ እኔ አይደለሁም አለች ወደ ሂሩት ዞርኩ እያነባች ነበር አይኗን እንኳ ቀና ብዬ ማያት አቃተኝ ስላደረክሽልኝ ሁሉ አመሰግናለሁ አልኳት ተቃቅፈን አለቀስን #ፈጣሪ_ሲወደን_ደህና_ጓደ ኛ_ይሰጠናል # እናቴ_የፍቅር_ወሰን ናት ለእኔ ያላት ፍቅር ድንበር የለውም # ረጅም_እድሜ_እና_ጤና_ለእናቶቻችን_ይሁን # እናት_ሺ_አመት_ትኑር ሁሌም ለእናቶቻቹን በአፋቹ ሳይሆን በልባቹ ወደዱ አመሰግናለሁ ባለ ታሪኳ # ሜላት ነኝ ከመሀላቹ ነው ያለሁ አስተያየታችሁን እጠብቃለሁ አመሰግናለሁ @libmalet @libmalet

የፍቅር_ወሰን # ክፍል5 ወደነ ሂሩት ቤት ልሄድ ስወጣ መንገድ ላይ ሳሚ አገኘኝ አንዴ አንቺ ምን ሁነሽ ነው ምናምን አለኝ መልስ ሳልሰጠው ይቀባጥር ጀመረ እቺ ደደብ የሆነች ልጅ ነገረችሽ አደል አለ እንዳታምኛት እውነቱን እነግርሻለሁ አንዴ ስሚኝ አለ በጣም ደነገጥኩ የሆነ ነገር እንዳለ ገባኝ እኔ ቤዚ ጋር እዛን ቀን ምንም የተፈጠረ ነገር የለም በርግጥ ሁለታችንም ሰክረናል ግን እኔ እምልልሻለው ምንም የተፈጠረ ነገር የለም አለ በቃ እየ ተርበተበተ ያወራል መልስ ሳልሰጠው አልፌው ሄድኩ በጣም ተናድጃለው እንባ ተናነቀኝ እናቴ ያለችኝ ትዝ አለኝ ስለ ጓደኛሽ የቻልሽውን ያህል ማጣራት ሞክሪ ያለችኝ ነገር ገረመኝ እናቴ በሁለት ሳምንት ውስጥ በጣም ነው የናፈቀችኝ ሂሩት መንገድ ላይ መጣችብኝ እኔ እኮ ወደ አንቺ ነው ምመጣ ብላኝ ተያይዘን ወደ ቤት ሄድነ ሰፈር እንደ ደረስን ሳሚ ድንጋይ ላይ ቁጭ ብሎ ነበር ሂሩት ስታየው እንደ መደንገጥ አለ ሳሚ እንዴትነህ ብላ ሰላም አለችው ግራ ገባኝ ወደ ቤት እንደ ገባን የት ነው ምታውቂው አልኳት ባለፈው ወደ አንቺ ስመጣ ቤዚ ጓደኛዬ ነው ብላ አስተዋውቃኝ ነው ስትል ደነገጥኩ ሳሚን በቃል ከምገልፀው በላይ ነው የምወደው ታድያ ለምንድነው ለእኔ መታመን ያቃተው ብዬ ሳለስበው ከአፌ ወጣ ሰው የስራውንም አደል አለች ሂሩት ወደ ቤት የቡና ማፍያውን ይዛ እየገባች ደነገጥኩ ሰማችኝ እንዴ አልኩ በልቤ ተከትያት ገባሁ ምን ነበር ያልሽኝ አለኳት ፈገግ ብላ የልብሽ መንደር ውስጥ መጣው አደል አለች ሁለታችንም በጣም ተሳሳቅነ ሚገርነው ግን በቃ ስለ እኔ አንድ በአንድ ነገረችኝ በጣም ከመስመር እንደ ወጣሁ ብዙን ግዜ በስልክ ላገኝሽ ፈልጌ ነበረ ግን እንዳል ደውልልሽ አንድ ነገር ያግደኛል እውቆ የተኛ ቢቀሰቅሱት አይሰማም ሚባለው ነገር ሚጠቅምሽን እና ሚጎዳሽን በጣም ለይተሽ ታውቂያለሽ ምን ይሁን ብዬ ነው ምጨቀጭቅሽ አለች በጣም ደነገጥኩ ይሄ ነው ከምለው በላይ ልክ ልኬን ነገረችኝ እውነትም # ፈጣሪ_ሲወድህ_ጓደኛ_ይሰጥሀል የሚባለው ነገር እውነት ነውለእናቴ ከሄደች አንድ ግዜ ብቻ ነበር የደወልኩላት እሷ ደውላ አገናኘችኝ ድመጿ ራሱ በጣም ናፍቆኝ ነበረ አንደዚህ እያልን ሳምንት አሳለፍን ከሳምንት በኋላ ግን የማልውቀው ስልክ ተደወለለኝ አንሰቼ ሄሎ ብዬ አስር ሰከንድ ሰላናግር ራሴን ስቼ ወድኩ ከቀናት በኋላ ራሴን ያገኘውት ሆስፒታል ውስጥ ነው # ይቀጥላል.... @libmalet @libmalet

የፍቅር_ወሰን # ክፍል4 እንደገና እኔን እንደ ሰራተኛ ነው የሚያዩኝ በጣም እናደድ ነበረ ለካስ ሰው ፍቅር ሲገባው ቅናተኛ ይሆናል እኔም ነገሮችን ቆም ብዬ ሳየው በጣም አዘንኩ በዚህ መሀል ቤዚ ደውላ ሰፈር ነኝ አንዴ ነይ አለችኝ ትንሽ ድምጿ እንደ መረበሽ ብላለች ትንሽ ግር እንዳለኝ ወጣሁ ሳያት ተናዳለች ምን ሁነሽ ነው አልኳት ምንም አልሆንኩም አለች በጣም እንደ ተረበሸች ያስታውቃል የሆነ ወረቀት ሰጠች ምንድ ነው አልኳት ቤት ስትገቢ አንብቢው ብላ መልሴን ሳጠብቅ ሄደች በጣም ግራ ተጋባሁ ወረቀቱን እስካየው ድረስ ቸኮልኩ በርግጥ ሲበዛ ለምንም ነገር ቦታ የላትም ከሆነ ሆነ ካልሆነ ገደል ይግባ ምትል ልጅ ናት ጓደኞቼ በብዛት ለምን ነገር የማይጨነቁ ናቸው ለዛም ይሆናል እኔ ችላተኛ የሆንኩ ሁሉም ነገር እየ ሰለቸኝ ነው ከግዜ ግዜ እናቴም ህመሟ እየበረታባት መጣ እንደዛም ሁኖ ግን ፀባዬ በቃ ምንም አለቀኝ አለ ሁሌም የለመዱትን ባህሪ እርግፍ አድርጎ አንደ ቀላል ነገር መተው ይከብዳል ውስጤ ፍረሀት ፍረሀት ይለኛል እናቴ በዚህ መሀል ወደ ፀበል ልሄድ ነው ስላለችኝ ግራ ገብቶኛል ማታ ላይ ቤዚ የሰጠችኝን ወረቀት ሳየው በጣም ተናደድኩ ምንም ያልተፃፈበት ነገር የለም ምን ማለት እንደ ፈለገች ምንም አልገባኝም ከሁለት ቀን በኋላ እናቴ ወደ ፀበል ሄደች እኔም በህይወቴ ለመጀመርያ ግዜ ተሰማኝ በቃ እናቴ ምንም ይሁን ከእኔ ርቃ አታውቅም አሁን ግን በቃ ህይወቴ የለ እሷ ባዶ የሆነ ያህል ተሰማኝ እሷን የሰደብኩበትን ቀን ሳስብ ራሴን እረግማለሁ ስልኬን አጠፋፍቻለሁ ማንንም ማግኘት አልፈለኩም ሂሩት ቤት ድረስ እየመጣች ታጫውተኛለች በጣም የገረመኝ ግን በችግራቸው ግዜ የደረስኩላቸው ሰዋች አብሪያቸው ውዬ ያደርኩ ሰዋች ጭራሽ አላስታወሱኝም ፍቅረኛዬ ያልኩት ሳሚ እንኳ ረስቶኛል ሁለት ሳምንት በኋላ ወደነ ሂሩት ቤት ልሄድ ስወጣ መንገድ ላይ ሳሚ አገኘኝ አንዴ አንቺ ምን ሁነሽ ነው ምናምን አለኝ መልስ ሳልሰጠው ይቀባጥር ጀመረ እቺ ደደብ የሆነች ልጅ ነገረችሽ አደል አለ እንዳታምኛት እውነቱን እነግርሻለሁ አንዴ ስሚኝ አለ በጣም ደነገጥኩ የሆነ ነገር እንዳለ ገባኝ እኔ ቤዚ ጋር… # ይቀጥላል @libmalet @libmalet

የፍቅር_ወሰን # ክፍል3 የቷ ናት እናት ይባላል ለእናቷ ስትል የማታደርገው ነገር የላትም ሰፈራችን ነበሩ እሷ ወደ አረብ ከሄደች በኋላ ቤት ሰርታላት ሰፈር ቀይረዋል መምጣቷን ዛሬ ሰማሁ ግን ልሄድ ነው አልኳት ለባብሼ ወደ ውጭ እንደ ወጣሁ ሳሚንና ቤዚን ሳይ ደርቄ ቀረሁ ዝቅ ብሎ ሆዷን ይሰመዋል ግራ ገባኝ ይሄ ነገር እንዴት ነው አልኩኝ ማርገዟን የነገረኝ እሱ ነው ታድያ ምን ማለት ፈለጎ ነው ወይስ አባትዬው ማነው ብዬ ግራ እንደ ተጋባሁ የምሄድበትን ነግሬያቸው ሄድኩኝ ሂሩትን ሳያት በጣም ነበር ደስ ያለኝ ከምንም በላይ መካሪዬ ነበረች እናቷ ጋር ፊት ለፊት ይቀመጡና አይን ለአይን እየተያዩ ያወራሉ በቃ ይሄ ፍቅራቸው ያስቀናኛል ብዙ ካወራን በኋላ እኔም ወደ ሰፈር መጣሁ ስመለስ እናቴ የለችም ወጣለች ሰራተኛችንን ስጠይቃት ሰው ቤት መሰለኝ የሄደች አለችኝ ማታ ልይ ሁለት ሰአት አከባቢ መጣች ተናድጄ ሰለ ነበር በጣም ነበር የጨውኩባት እኔን ለምን ታመሺያለሽ ትይኛለሽ አንቺ በዚህ ሰአት ተመጪያለሽ ብዬ ጨውኩባት ምንም መልስ አልሰጠችኝም እኔም ወደ ክፍሌ ገባሁ መልስ ስላልሰጠችኝ ጥፋቷ ስለ ሆነ ነው ብዬ ነበረ ግን ተኝቼ ለረጅም ሰአት እንቅልፍ እንቢ አለኝ የተናገርኳት ነገር ይፀፅተኝ ጀመር እንዳይ ነጋ የለ ነግቶ ጥዋት ላይ ስታየኝ ማታ ትንሽ አበሳጨውሽ አይደል አለችኝ መአዛ እኮ ወልዳ እሷ ዘንድ ነበርኩኝ አለች በጣም ነበር የደነገጥኩኝ መአዛ ማለት የቅርብ ዘመዳችን ናት አርግዛ እንደ ነበር አውቃለሁ ሳላያት ስለቆየሁ ረስቻታለሁ ይባስ ፀፀተኝ ልወጣ እያለ የምሄድበት ቦታ ስላል ከሰፈር አትራቂ አለችኝ በህይወቴ እሺ የሚባል ነገር ከአፌ ወጦ አያውቅም ሆነም አልሆነም መልስ አልሰጥም በዚህ መሀል እናቴ ጋር ከበፊቱ ትንሽ ትንሽ እየተግባባን መጣን ጭራሽ ድሮ የለለኝ ባህሪ በውስጤ እየመጣብኝ ለእኔም ግራ እየገባኝ መጣ በቃ ቁጭ ብዬ እናቴን ባወራት ደስ ይለኛል ግን እንዴት አድርጌ ያለመደብኝን ከየት ላምጣ ብዙ ማማክራት ነገር ነበረ ግን እንዴት አድርጌ በቃ ሁሉ ነገር ሽንፈት ይመስለኛል ይባስ ደግሞ በሰራተኛችን እቀና ጀመርኩ እቤታችን ለመጣ እንግዳ እናቴን እና ሰራተኛችንን ላይ ልጅ እና እናት ነው ሚያደርጋቸው እንደገና እኔን እንደ ሰራተኛ ነው የሚያዩኝ በጣም እናደድ ነበረ ለካስ ሰው ፍቅር ሲገባው ቅናተኛ ይሆናል እኔም ነገሮችን ቆም ብዬ ሳየው በጣም አዘንኩ በዚህ መሀል ቤዚ ደውላ ሰፈር ነኝ አንዴ ነይ አለችኝ ትንሽ ድምጿ እንደ መረበሽ ብላለች # ይልቀጥላል …

የፍቅር_ወሰን # ክፍል2 ይቅርታ ልጄ እንድትናደጂብኝ አልፈልግም ግን ያው ስትል ግን በሎ ነገር የለም በቃ አልኳት አንገቷን አቀረቀረች አይኖቿ እንባ አዘሉ እንዳትጎጂብኝ ስለ ምፈልግ እኮ ነው ልጄ አለች እንዳቀረቀረች እረ አልኳት እንደ ማፌዝ ብዬ አዋ ልጄ ስለሱ በቻልሸው መጠን ለማቀወቅ ሞክሪ አለችኝ በጣም ተናደድኩባት በቃ ምን አይነት መንፈስ እንደ ያዘኝ አላውቅም እናቴ ይህን ታክል ፊት የነሰኋት ምን በድላኝ ነው እላለው አንዳንዴ በቃ ለራሴ የማለውቀው ነገር ሆኖብኛል አንድ ቀን ሰፈር አከባቢ ፍቅረኛዬ ጋር እያለሁ እናቴ ከገብያ እየመጣች ነበር በጣም ብዙ ዕቃ ይዛላች እኔ እና እሱ ተቀምጠን ነበረ አያትና ምን አለበት ከፍላ ለሰራተኛ ብታሸክም ምን አይነቷ ቋጣሪ ናት አለ እንርዳት እንዴ አለኝ በርግጥ እሱ እናቴ እንደ ሆነች አያውቅም ሳሚ ባክህ አርፈህ ተቀመጥ አልኩት እንዳታየኝ ብዬ ፊቴን አዙሬ ተቀመጥኩ እሷም ባላዬ አለፈችኝ ግን ውስጤ ትንሽ ቅር አለው እንዴት የፈለገ ቢመጣ ሰው በእናቱ ያፍራል እልኩኝ በዚህ መሀል ቁጭ ብለን እያለን ቤዚ ምንላት ጓደኛዬ መጣች ሲበዛ ቅንጦት ትወዳለች እናቷ ጋር በውሀ ቀጠነ ነው ሚጣሉ አንዴ ቤታቸው ሂጄ እሷ ጋር እናቷ ጋር ሲጨቃጨቁ ሳይ እናቷ በጣም ነበር ያሰጠላችኝ ጥፋቱ ግን የቤዚ ነበር ልብሷን ሳይቀር ምታጥብላት እናቷ ናት እንደዚህም ሁኖ ግን እናቷን ታማራለች ትልቅ ወንድሟ ደግሞ ይብሳል በቃ ላያቸው ሰው እናታቸው ናት ለማለት ይከብደዋል አይደለም ለእናት ይሄን ታክል ጥላቻ ይቅርና የማያውቁትን እንኳ እንደዚህ መጥላት አይቻልም ቤዚ ሰላም ብላን ቁጭ አለች ደብሯታል ሳሚ በመሀል አጠገቤ ተቀምጦ ሚሴጅ ላከለኝ ሳየው እሱ ነው የላከለኝ አርግዛለች እኮ አለኝ በጣም ነበር የደነገጥኩኝ ከዚህ በፊትም እንደዚሁ አርግዛ አቦርሽን አድርጋለች በጣም ተናደድኩ ድጋሚ እንደዚህ አይነት ጥፋት ውስጥ መግባቷ ምን ሁነሽ ነው አልኳት ምንም አለችኝ ነው ብዬ ተነስቼ ወደ ቤት ሄድኩ እናቴ ራሷን አሟት ተኝታለች ስታየኝ ሂሩት እኮ መጣለች ጠየቅሻት አለችኝ ሂሩት ማለት በጣም የምወዳት ጓደኛዬ ነበረች ከስድት አመት በፊት ነበር ለስራ ወደ አረበ ሀገር የሄደችው ሂሩት ለእኗቷ ያላት ፍቅር ላየ ሰው ግራ ነው ሚገባው ማነው እናት ሂሩት ናት ወይስ እናቷ ናት እናት ይባላል ለእናቷ ስትል የማታደርገው ነገር የላትም ሰፈራችን ነበሩ እሷ ወደ አረብ ከሄደች በኋላ ቤት ሰርታላት ሰፈር ቀይረዋል መምጣቷን ዛሬ ሰማሁ ግን ልሄድ ነው አልኳት ለባብሼ ወደ ውጭ እንደ ወጣሁ ሳሚንና ቤዚን ሳይ ደርቄ ቀረሁ… # ይቀጥላል … @libmalet @libmalet ❤️❤️invite❤️❤️

የፍቅር_ወሰን # ክፍል_1 ሰላም ለእናንተ ይሁን ጓደኞቼ ዛሬ በሌላ ታሪክ መጥቻለሁ # በጣም_ትማሩበታላቹ_እናት_ለልጇ_የምትከፍለው # መስዋት_ልጅ_የእናት_ፍቅር_ሲገባት_እናትን_ላለማጣት # የሚደርግ_እውነተኛ_እና_አሳዛኝ_ታሪክ_ነው ሜላት እባላለሁ ታሪኬ የሚጀምረው እናቴን እንደ ገረድ ማየት የጀመርኩበት ቀን ነው ሁላቹም ከእኔና ከጓደኞቼ ታሪክ እንደ ምትማሩ ተስፋ አደርጋለሁ ሁሉም ሰው ስለ እናቱ ቢጠየቅ እወዳታለሁ ነው ሚለው ግን በተግባር ግን ሚያሳይ ከአስር አንድ ቢገኝ ነው በህይወቴ አንድም ቀን ስለእናቴ ሆነ ለእናቴ ብዬም አስቤም አላውቅም በርግጥ አንዳንዴ እራሴን ጥፋተኛ አደርጋለሁ ግን ማን ያስተማረኝን እላለሁ ጓደኞቼ ከሆኑ ከእኔ የባሱ ናቸው እናቴ ለማንም የዋህ ናት በዚህ ባህሪዋ እኔ በጣም እናደዳለሁ ከዛን አልፎም እንጣላለን ጎረቤት ላይ ድንገት ከባሏ ጋር የተጣላች ሴት እናቴ ዘንድ ነው ምትመጣ እሷም እንደ ልጇ ታባብላታለች ሁሌም እናቴን ኋላ ቀር አድርጌ ነው ማስባት በጥቅሉ ሰለእናቴ ያለኝ አመለካከት የወረደ ነው አንድ ቀን ግን እንደ ተለመደው አምሽቼ ስገባ እናቴ በፈገግታ ተቀበለችኝና እስቲ ውሎ ዛሬ እንዴትነበር ንገሪኝ አለችኝ ፈገግ እያለች ጭራሽ ውሎዬንም እንድዘግብልሽ ፈለግሽ አልኳት ኮስተር ብዬ ምንችግር አለው እሺ እኔ ልንገርሽ አለች እማ ደክሞኛል ብዬ የሷን መልስ ሳልጠብቅ ወደ መኝታ ክፍሌ ገባሁ በርግጥ እናትን ፊት መንሳት ማለት በጣም ካባድ ነው እኔ በሰአቱ ቅንጣት ታክል አልተሰማኝም አሁንም በሌላ ቀን እፈለግሻለሁ አለችኝ እንደ ቆምኩ ምንድነው አልኳት ነይ ቁጭ ብዬ ብላ እሷ የተቀመጠችበትን ወንበር ሰጠችኝና ለራሷ ሌላ መቀመጫ አመጣች ትንሽ እንዳወራችኝ ስለ ጓደኛሽ ግን ምታውቂው ነገር አለ አለችኝ ምን ማለት ፈልገሽ ነው አልኳት እስቲ ስለሱ ባህሪ ንገሪኝ አለችኝ ጭራሽ በሱ መጣሽ ሰለሱ ምንም የሚያገባሽ ነገር የለም ሲቀጥል ደግሞ ማንም ስለ እሱ አይመለከተውም ከአሁን በኋላ ደግመሽ ባጠይቂኝ ደስ ይለኛል ምክንያቱም ጓደኛዬን እኔ እንጂ አንቺ ምታውቂው ጉዳይ የለም ብዬ ተናግሬ ሳልጨርስ ይቅርታ ልጄ እንድትናደጂብኝ አልፈልግም ግን ያው ስትል ግን በሎ ነገር የለም በቃ አልኳት አንገቷን አቀረቀረች አይኖቿ እንባ አዘሉ እንዳትጎጂብኝ ስለ ምፈልግ እኮ ነው ልጄ አለች እንዳቀረቀረች እረ አልኳት እንደ ማፌዝ ብዬ… ይቀጥላል......

ዴት ነሽልኝ በጣም..እኮ ነው የምውድሽ ከምን በላይ ደሞ አንቺው ታውቂዋለሽ አይደል.... ...ግራ ገባኝ እንዴት አቤል...መሞቱን ያውቅ ነበር....እኮ እንዴት እንባዬን መቆጣጠር አቃተኝ አሁን....ምንየሚሉት ነው.. ...ቀጠልኩ // ግን በጣም ደስ ብሎኛል አንቺ ጥሩ ሒውት አለሽ ሳሚን የመሰለ ባል አፍቃሪ ....ሄዋንዬ እንደዛ ስፎካከረው የነበረው እኮ እንደሚውድሽ ለማውቅ ነው.. ...hhhh ወይ እኔ ስራዬ እራሱ ያስቀናል ....ምን ሆነ መሰለሽ ላንቺ የላኩልሽን ሚሲጅ አንብቦ ለብቻዬ አናገረኝ ከማናገርም።ለመነኝ አቤል ታሸንፈኛለክ አውቃለው እውነት የምትውዳት ከሆነ እኔ ውዝድሮም ልሙላ እናተም የድሮ ፍቅራቹን አድሱት አልያም....እባክህን ተዋት .... ....እተዋታለው ግን አንተም አንድ ውለታ ዋላ ...ደስ ብሎት እሺ...ምን...... ተውልኝ ብለክ ጉልበቴ ላይ ውደቅ ጓደኝነታችን ላይ ምን ተፅኖ እንዳይኖር ....ተስማምተን ሁሉንም አደረገ እይው ፎቶ አለልሽ ከልብ ነው የሚውድሽ አትጠራጠሪ ....ሄዋንዬ ለምን ግን እንደተለየውሽ ታውቂያለሽ ያ የነገርኩሽ ውሸት እኮ ነው።.. ..ታስታውሻለሽ አብረን ያደርን ቀን አሁን ብሞትስ ስል ምን እንዳልሽኝ ለሁሉም ነገር ሁለታችንንም የመጀመሪያችን አይደል ሞትንም አንድላይ ነው እውነት ስልሽ አዎ አቤልዬ ፈፅሞ አላደርገውም omg ዝግንን እያለሽ አስበውሀል በስማም እያልሽ ስታውሪኝ ልቤ ፈራ ምን ብዬ ልንገርሽ ቢያንስ በአካል..እያለው ብለይሽ ከዳኝ ነው የምትይው አይከብድም .. የኔ ሳያንስ ለም ያንቺን ሒውት ላበላሽ እእእ ሄዋንዬ ሳሚዬ እኮ ጥሩ ልጅ ነው ሒውቴን ለትንሽ ውራት ታደገልኝ ምን ሳይሰስት ሁለቴ ድም..ሰጠኝ ...እንድመረቅ ካለው ጉጉት ነው ያደረገልኝ ለዛም...ሳሚ ስለኔ ስላንቺ የነበረንን ፍቅር ለም እንደከዳውሽ ሁሉንም ስነግረው ለኔ መኖር ጀመረ .... ........ .....ግን ቃል ይገባሽልኝን እንዳትረሺ ሴት ከውለድሽ ❤️ማራማዊት ሳሙኤል ❤️ .. ወንድ ከሆነ አባቱ ያውጣለት አይደል በፊት እቅዳችን ......ልጅሽን ሳላይ ይምሞትባት ቀን ቀረበች ...........ሄዋንዬ እኔ እኮ ከልጅነቴ ጀምሬ የካንሰር በሽተኛ ነበርኩ ...ለዛም ነው በአካል እያለው ልለይሽ የውሰንኩት እንደዛ አይንህን ስትይኝ እቤት ሁሉም በምትፅፊያቸው ድብዳቤ ....ተጎድተዋል እኔ ላንቺ ስለማልሆን ቻል አደረኩ። ....ብዙ ፈተንኩሽ ግን በሒውት እንደማትኖሪ ነው የሚያሳየኝ......ሄዋን እራስሽን እንዳትቀጪ...በፀፀት ....... ...... የሆነ ግጥም ገጥሚ ለሰጥሽ አልኩና ....አስጨንቅሻለው ብዬ ተውኩት ምን መሰለሽ። ..።። //.........ደህና ሁኚ....... የልቤ ቅኝቱ አንቺ ሆየም አይደል... ከባቲም አይገጥም ይለያል ካምባሰል.... የመናፈቅ ቅኝት የእፍቅሮ ማጣት ምት... በነጠላ አመት ውስጥ ማሳለፍ እልፍ አመት... ይከብዳል ሊገለፅ በባቲ አንቺ ሆየ... ደስታን ለረሳ ልብ ከሳቅ ለተለየ.... * * * * * ውዴ ሆይ ልንገርሽ ዛሬስ ተስኖኛል... በሽታዬ በዝቶ መረሳት ወርሶኛል... የሀዘኔ ጫፉ ከራስ ዳሽን ገዝፏል... የመከፋቴ ጥግ ቀይ ባህር ተሻግሯል... ብየ በመናፈቅ ጠኔ... እኔው በራሴ ውስጥ ገብቼ ምናኔ... በእምባ በታነፀ የሀዘን ተራራ... ሰው ከማይደርስበት ከህልም አለም ትመጫለሽስፍራ... ሀረግ የወረሳት ጎጆየን ዘግቼ... ባሮጌው ኮቴ ስር ሀብታም ልብ አንግቼ... ስንት ዘመን ኖርኩኝ መኖርን.... ዘንግቼ... * * * * * ዛሬ…ከጎጆየ በላይ እኔ ዘምሜያለሁ..... የኔ የነበረን ሁሉን አጥቻለሁ... በተከፋው ልቤ ደህና ሁኚ ብያለሁ... // ሄዋንዬ አደራ ሳሚ ከሒውትሽ በላይ ውደጂው......ያኔ እኔ እደሰታለው .....እራሴን ስቼ ውደኩ. ............... ...ከብዙ ሰዓታት በኃላ እንደመንቃት ስል አይኖቼን ስገልጥ ብርሀን ነገር ታየኝ ልነሳ ስል ውገቤ እዛው ተመለስኩ ሳሚ ዶክተር እያለ ይጣራ ጀመር እኔ ውደ ሆዴ ሳይ ሆዴ ውጥ ምንም የለም ልጄስ ብዬ ስጮህ ነስሶ እንኳን ደስ ያለሽ ውንድ ልጅ ከነቃጥሉ አለችን ስትሰጠኝ የደስታ እንባ.....አንዶ መታ ስሙን ንገሩን ...ሳሚ አይኔን አይቶ ❤️ አቤል ሳሙኤል❤️ በይው አለ ደነገጥኩ ከኔ በላይ ሳሚዬ አቤል ምን አይነት ለፍቅር ለኔ ሒውት እንደከፈለ .......ብቻ ብዙ ነገር ...... ........አቤልዬ በአካል ቡለየኝም....በቀን ብዙ ግዜ ስሙን እንጠራለን አቤልዬ ያንተን ማንነት በመጀመርያ ልጄ አየዋለው.... .... ....አቤል አሁን.በዳዴ መሄድ ጀምሮል ግን ......ሂውት ለካ።እንዲ ናት ለፍቅር ሲሉ....ፍቅርን አሳልፎ።ያሰጣል.....አቤም...በሂውት እስካለው የማንረሳው......... ...._______ተፈፀመ__________ #ፍቅር ማለት ለምንውደው ሰው ደስታን መፍጠር ነው ፍቅር እራሳችንን አሳልፈን የምንሰጠው የራሳችንን አለም ትተን ለምንውደው ለምናፈቅረው መኖር ...ያ ነው ፍቅር ... @libmalet @libmalet

ሁለት ልብ❤️❤️ የመጨረሻ ክፍል ዴት ነሽልኝ በጣም..እኮ ነው የምውድሽ ከምን በላይ ደሞ አንቺው ታውቂዋለሽ አይደል.... ...ግራ ገባኝ እንዴት አቤል...መሞቱን ያውቅ ነበር....እኮ እንዴት እንባዬን መቆጣጠር አቃተኝ አሁን....ምንየሚሉት ነው.. ...ቀጠልኩ // ግን በጣም ደስ ብሎኛል አንቺ ጥሩ ሒውት አለሽ ሳሚን የመሰለ ባል አፍቃሪ ....ሄዋንዬ እንደዛ ስፎካከረው የነበረው እኮ እንደሚውድሽ ለማውቅ ነው.. ...hhhh ወይ እኔ ስራዬ እራሱ ያስቀናል ....ምን ሆነ መሰለሽ ላንቺ የላኩልሽን ሚሲጅ አንብቦ .... ........ ይቅረብ.....

💋ታምሪያለሽ ልላት ነው💋 ሰራተኛ ብዬ አንዲት ሴት ቀጥሬ ማበዴ ነው ሰዎች በሷ ተማርሬ ድሮ አልሚ እያለች እንዲህ ሳልቸገር ዘይት የሚገዛው በየወሩ ነበር አሁን እቺ ጣሳ ከመጣች ጀምሮ ሁሌ ዘይት ሆኗል የሷ እንጉርጉሮ ጉዳዩ ምን ይሆን እያልኩ ሲጨኝቀኝ ሁሉን ግልፅ አርጎ ጎረቤት ነገረኝ ለካስ ባጫ የሚባል አንድ ሰው ወዳለች ባጫን ደስ እንዲለው ውብ ልሁን እያለች እጇን ስትቀባ አግሯን ስትቀባ ዘይቴን ጨረሰች “አላምርም ወይ ታሜ?” ብላኝ ነበር ያኔ አታሪም ማለቴ ከሆነ ጥፋቴ ዘይቴም ከሚልቅ ብርም ከማወጣ ታምሪያለሽ ልላት ነው የፈለገው ይምጣ፡: @libmalet @libmalet

I love you, that means I'm not just here for the pretty parts and happy days. I'm here for the rough times and bad days. I'm
I love you, that means I'm not just here for the pretty parts and happy days. I'm here for the rough times and bad days. I'm here no matter what. ❤️