የፍቅር ታሪክ (seenaa jalaala)
Open in Telegram
2 842
Subscribers
+224 hours
No data7 days
+230 days
Posts Archive
ጠቃሚ ምክር ለእርስዎ!
ይሄን ፅሁፍ ማንበብ 100 መፅሐፍት እንደማንበብ ነው!
★★★
በወጣትነት ሁሉም ነገር ትክክል ነው ከሚል መመሪያ
ውጣ ፤ ሁሉንም ካላየሁ አላምንም አትበል ። ሰምቶ ማመን ፣
ከተጎዱት መማር አስተዋይነት መሆኑን አትርሳ ። የሰማንያ
ዓመት ዕውቀትን ለመገብየት ግድ ሰማንያ ዓመት መኖር
የለብህም ። ሰማንያ ዓመት ከኖሩት በትሕትና መጠየቅ
ይገባሃል ።
:
ምክርን ብትሰማ በነጻ ትማራለህ ። ምክርን አልሰማ
ብትል ግን በዋጋ እንደምትማር እወቀው ። በዋጋ መማር ግን
አድካሚ ደግሞም የሚያስመርር ነው ። ብልህ ከሆንህ በሰው
ከደረሰው ትማራለህ ፣ ሞኝ ከሆንህ ግን በራስህ ሲደርስ
ትማራለህ ።
:
የታየህን አሳይ ፣ ያልታየህን አጥራው ። በደንብ
ያልተረዳኸውን አታስተምረው። ያልቀመስከውን ለሰው
አትጋብዝ ። የሰማኸውን ሁሉ አትመን ። ያየኸውን ሁሉ ስጡኝ
፣ የተናገርከውን ሁሉ ፈፅሙ አትበል ። የሰጠኽውን እርሳ
እንጂ አታውራ። ፍፃሜውን ሳታይ ምስጋና አታብዛ ። ቀኑ
ሳይመሽ ቀኑ ጥሩ ነው አትበል ።
:
ዓይንህ የፊቱን ቢያይ ልብህ የኋላውን ያስብ ። ነገ ላይ
እንድትደርስ የትናንቱን አትርሳ ። የምትሄድበት እናዳይጠፋህ
የመጣህበትን አትዘንጋ ።
:
የአባቶችህን መልካም ሥራ አብነት አድርግ ። ካሳለፉት
ሕይወት ተማር እንጂ አወዳሽና ወቃሽ አትሁን ። ሌሎች
መሆን ያለባቸውን ስታውቅ አንተ መሆን ያለብህ
እንዳይጠፋህ ተጠንቀቅ ። ደግሞም አንተም በታሪክ ፊት
መሆንህን እወቀው ።
:
ክፋት አይሙቅህ ፣ መልካም ነገርም ብርድ ብርድ
አይበልህ ። ለክፋት አቅም ካለህ ለበጎ ነገርም አቅም አለህና
ተግባርህ የምርጫ ውጤት ነውና አስብበት ።
:
ገንዘብ የሚመልሰው የገንዘብን ጥያቄ ብቻ ነውና ሁሉንም
ነገር ገንዘብ ያስገኝልኛል ብለህ አታስብ ። ላለው አትሩጥ ፣
ምጽዋትህና ተግባርህ በአቅምህ መጠን ይሁን እንጂ
ከአቅምህ አትነስ ። ድሃም ሆነህ ተበድረህ ስጦታ አትስጥ ።
በጣም ካልቸገረህ ለቅንጦት አትበደር ። ያንተን ድርሻ
ከጨረስህ ያልተጨረሰ የሌሎችን ድርሻ ፈፅምላቸው ።
:
ለሀብታም አትሳቅ ፣ የደሀ ጉልበት አይለፍብህ ፣ ያለ ሰው
ሰው አልሆንክምና ሰው አትጥላ ፣ የወጣህበትን መሰላል
አትገፍትር ፣ ለመውረድም ያስፈልግሃልና ፣ ያየኽውን ሴት
ሁሉ የመውደድ ጠባይህ ካለቀቀህ ትዳር አትያዝ ፣
ካልጋበዙህ በቀር አማካሪ አትሁን ፣ ባልጠሩህ ሥፍራ አቤት
አትበል ፣ ካልሾሙህ መሪ አትሁን ፣ ጉድለት በሌለበት ቦታ
ጊዜህን አታባክን ፣ የሰው ፊት ጥገኛ ሁነህ ሲስቁልህ
የምትስቅ ሲቆጡህ የምታለቅስ አትሁን ፣ ነገርህን በልክ ፣
ቃልህን በጣዕም ፣ ድምፅህን በዝግታ ፈፅመው ።
:
እውር እንዳይሉህ ያልታየኽን አያለሁ አትበል ። ጨካኝ
እንዳይሉህ ያልተሰማህን ጩኸት እሰማለሁ አትበል ። ንፉግ
እንዳይሉህ ያለ አቅምህ እረዳለሁ አትበል ። ነገር
አይገባውም እንዳይሉህ ያልገባህን እንደገባህ አድርገህ
አትለፍ ። አንድ በጎ ዕውቀት ሳትጨብጥ የዋልክበትን ቀን
እንደ ኖርክበት አትቁጠረው ፣ ስለዚህ መፅሐፍትን አንብብ ፣
አዋቂዎችን ጠይቅ ፣ ሁሉን ሳትንቅ ስማ ።
:
ሥልጣን ሲሰጥህ መሪ እንጂ አለቃ አትሁን ፤ ከፊት
እየቀደምህ አስከትል እንጂ ከኋላ ሆነህ አትቅደም ።
:
በዓላማ ኑር ፤ እንቅፋቶች የሚያጸኑህ እንጂ ተግባርህን
የሚያስተውህ አይሁኑ ። ሕይወት ትምህርት ቤት መሆኑና
ባለማወቅ ብዙ ትህምርቶች እንዳያመልጡህ ተጠንቀቅ ።
:
የመከራ ቀን ወዳጆችህን አትርሳ ፤ የዛሬ ሰው ብቻ አትሁን
፤ የትላንቱንም አስብ ፤ አንገት የተፈጠረው ዞሮ ለማየት ነውና
።
:
ዓለም ዋዣቂ ናት ። ከፍና ዝቅ ስትል አትደናገጥ ፤ ፀሐይ
ዝናብን ተከትላ ትፈነጥቃለች ። ከመከፋትም በኋላ ትልቅ
መፅናናት ይሆናል ። ከሌሊት በኋላም ሌሊት አይመጣም ።
ከሀዘን በኋላ ደስታ ይሆናልና በርታ!
:
መነቀፍን አትፍራ ፤ ነቀፋህን ግን አጥራው ፤ ስለ ሀሰት
ሳይሆን ስለ እውነት ተገፋ ፤ ሌሎችን ውደድ ፍቅር ስጦታ
እንጂ ብድር አይደለምና አልወደዱኝም ብለህ በአበዳሪዎች
አንቀጽ አትካሰስ ፤ የገባህን አድርግ የዚህ ዓለም ሰው
ሲወድህም ሲጠላህም ባለማወቅ ነው ። ብዙዎች
ስለወደዱህ ይወድሃል ፤ ብዙዎች ስለጠሉህ ይጠላሃል ።
:
ሁልጊዜ የበላዮችህን አትመልከት ፤ የበታቾችህንም
ተመልከት ። ለድምፅ አልባዎች ጩህላቸው ፣ ለተጠቁት
ተሟገትላቸው ። እውነት እውነት በማለትህ የምታጣው
ሀሰተኛ ወዳጅህን ብቻ ነው ። እውነት እውነት በማለትህ
የምታተርፈው ግን እውነተኛ ወዳጅን ነው ።
:
ደጋፊዎች ተከታዮች አይደሉም ። ሰዎች ስለደገፉህም
የያዝኩት እውነት ነው ብለህ መንቻካ አትሁን ፤ ምናልባት ዛሬ
የሚጮሁልህ ዛሬን ሊረሱብህ ሊሆን ይችላልና ።
ሲያለቅሱልህም ቃልህ ማርኳቸው ሳይሆን የሞተ ዘመዳቸው
ትዝ ብሏቸው ሊሆን ይችላልና አለቀሱ ብለህ ንግግርህን
ድንበር አታሳጣው ። እውነትንም በደጋፊ ብዛት እንዳትመዝናት
ተጠንቀቅ ።
:
ለእውነታ እንጂ ለይሉኝታ አትኑር ፤ ያን ስልህ የምትኖርበት
ሕዝብና ባሕል ከእውነት ጋር እስካልተጋጨ መጋፋት
የለብህም። ሠዎች የሚቀበሉህ ባሕላቸውን ስታውቅና
ስታከብርላቸው ነው ።
:
ልጅነት የለሰለሰ መሬት ፣ ወጣትነት የአዝመራ ዘመን ፣
ሽምግልና ደግሞ የአጨዳ ዘመን መሆኑን አስተውል ።
በሽምግልናህ የምታጭደው የወጣትነትህን አዝመራ ነውና
ዛሬ ለምትዘራው ተጠንቀቅ ።
:
የሰዎችን ያለማወቅ አግዝ ፤ ዕውቀትህ ባላወቁት ላይ
እንድትኮራና እንድትፈርድ አያድርግህ የአዋቂ ኩሩ ቁጥሩ
ካላዋቂዎች ነውና ማወቅ ባለዕዳነት እንዳይሆን አላዋቂዎችን
እርዳቸው !!
፡
ሁሉን ወሬ ላውራ አትበል ፣ የደበቁህን ምስጢር
አታውጣጣ ፣ የሰማኽውን ወሬና የተገለጠልህን ምስጢር
ምን መፍትሔ ሰጠኸውና ? ያየህውን ሥራ ሁሉ እሰራለሁ
የሰማኸውን ትምህርት ሁሉ እማራለሁ አትበል ። ይህ
የተሰወረው የቅንዓት ጠባይ ነውና ሁሉን ልያዝ ማለትም ዝንጉ
አድረጎ እንዳያስቀርህ ሁሉም ውስጥ ልኑር አትበል ።
፡
ቆንጆዎች ቁንጅናቸው ሁሉን የሚተካ እየመሰላቸው
ከዕውቀትና ከትሕትና ይርቃሉ ። ሁሉንም ሰው በመልካቸው
የሚማርኩት ስለሚመስላቸው ኩሩና ተንኮለኞች ይሆናሉ ።
አንተ ግን ቆንጆ ወዳጅን እንጂ ቆንጆ ቁመናን አትሻ ፤ ቆንጆ
ትዳርን እንጂ ቆንጆ ሴትን አትመኝ ፤ የላይ ነገር ከንቱና ኀላፊ
ነውና በሚፈርስ አካል ፣ ኑሮ በሚለውጠው መልክ አትደለል።
፡
እወድሃለሁ ብለህ የምትናገረውን ቃል ውለታ አታድርገው
፣ መውደድህን የምትናገረው እንወድሃለን እንዲሉህ አይሁን ፣
ሠላም ያለው አፍቃሪ የራሱን ፍቅር ያለ ምክንያት መፈፀም
የሚችል ብቻ እንደሆነ እወቅ ። መወደድህን ለመስማት
አትጠብቅ ።
፡
የሰዎችን ያለማወቅ አግዝ ፤ ዕውቀትህ ባላወቁት ላይ
እንድትኮራና እንድትፈርድ አያድርግህ የአዋቂ ኩሩ ቁጥሩ
ካላዋቂዎች ነውና ማወቅ ባለዕዳነት እንዳይሆን አላዋቂዎችን
እርዳቸው ።
፡
ዛሬ የመዝራት ዘመንህ ነገ መከርህ ነውና በእምነት
እውነትን ዝራ ፤ በምታውቀው ቦታ ላይ አገልጋይ
በማታውቀው መልካም ተግባር ላይ ደጀን ሁን ፤ በቦታህ
መምህር ያለቦታህ ተማሪ ሁን ፤ ክብሩ እንዳይቀንስብህ ከዕቃ
ትምክህት ፣ ከዕውቀት ሙግት ራቅ ።
፡
ሁሉን ወሬ ላውራ አትበል ፣ የደበቁህን ምስጢር
አታውጣጣ ፣ የሰማኽውን ወሬና የተገለጠልህን ምስጢር
ምን መፍትሔ ሰጠኸውና ? ያየህውን ሥራ ሁሉ እሰራለሁ
የሰማኸውን ትምህርት ሁሉ እማራለሁ አትበል ። ይህ
የተሰወረው የቅንዓት ጠባይ ነውና ። ሁሉን ልያዝ ማለትም
ዝንጉ አድረጎ እንዳያስቀርህ ሁሉም ውስጥ ልኑር አትበል ።
፡
ቂም አፍን የሚያመር ፣ ልብን የሚያነቅዝ ፣ ተግባርን
የሚያልፈሰፍስ ነውና
"ዘመድ ኣዝማዶቼ እርገሙኝ እርገሙኝ
ያች የምትወዳት ልጅ ይዛህ ትሂድ በሉኝ" (ኣዝማሪ)
.
ልክ የዛሬ ወር ገደማ ነው ያየኋት። እዚህ ኣዝማሪ ቤት
እዚህቺው ወንበር ላይ ቁጭ ብዬ። ከወዲያ ካለው ወንበር ላይ
የኣንድ ፈረንጅ ጎን ውስጥ ተሸጉጣ … ከጣራ በላይ ስትስቅ ኣይኔ
ገባች። ጮሃ የምትስቅን ሴት ነፍሴ ብትጠየፍም በኣንዳች
ምትሃታዊ ምክንያት ልጅቷን መጥላት ኣልሆነላትም። ገና
እንዳየኋት ኣወቅኳት... ገና እንዳየችኝ ኣወቀችኝ። ስትከንፍ
መጥታ ኣቀፈችኝ፣ ሳመችኝ። እኔም ኣልቦዘንኩም። ፈረንጁ
...በኣንዳች የመገረም ኣለም ውስጥ ሠጥሞ የጎንዮሽ ያየናል።
በጨዋ ደንብ እጄን ኣውለበለብኩለት። ኣፀፋውን ከሚንፎለፎል
ፈገግታ ጋር መለሰልኝ። እጥር ምጥን ካለች ሰላምታ በውሃላ
ስልኳን ሰጥታኝ ወደ ሰውዬዋ ተመለሰች።
.
"ፍቅር ኣሞራ ነው ደርሶ እንደነፋስ
ስንቱን ጋራ ጥሶ የሚገሰግስ"
(ኣዝማሪ)
.
ከ7A ክፍል በውሃላ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው የተያየነው። በብዙ
ተለውጣለች። ድሮ ወንድ ማናገር ያሽኮረምማት የነበረች ጉብል
ዛሬ የኣገሪቱ የባህል፣ የውበት እና ወሲብ ኣምባሳደር ሆና
ህዝብና መንግስት የጣለባትን ግዴታ በትጋት ትወጣለች።
(ኣልተገረምኩም)
ፈረንጁ እስክስታ እንደመውረድ፣ እንደመውረግረግ እያለ
ትከሻውን ይሰብቃል። ወገቡን በእጆቹ ይጨምቃል። ኣንገቱን
ይነቀንቃል። የሆነ… የፍስሃን ጸጋ የደፋበት ሰውዬ ነው። እርሱ
ለተዝናናው ቀሪውን ያስቃል። እርሷ ግን ኣይኖቿን እኔው ላይ
ታንከራትታቸዋለች። ቀና ባልኩ ቁጥር እይዛታለው።
ትደነባበራለች … ለምን ይሆን? የታዘብኳት መስሏት ኣፍራ ይሆን
እንዲህ መሳቀቋ ?
(ቀረብ ብዬ "ኣረ ኣንቺ ይመችሽ ነፍሴ።" ልበላት?) ሰባተኛ
ክፍል ያስጀመርከኝ የማታውቀው ፍቅር ኣለ። … ኣስጨርሰኝ
ልትለኝ ይሆን? ("ግዴለም ፍቅሩ ይደርሳል። ስራ ክቡር ነው!
ሸቀል ሸቀል ኣድርጊና ተመለሺ" ብዬ ሞራል ልሁናት ?) እያልኩ
ስሳከር … ተያይዘው እብስ ኣሉ። .
በበነጋው ሀሳቤን ሁሉ እሷ ሞላችው። ከሰባተኛ ክፍል እስከ
"ጣይቱ" የባህል ምሽት ቤት ድረስ እየተመላለስኩ ኣሰብኳት።
ናፈቀችኝ። ኣሰኘችኝ። ፈለኳት። … ደጋግሜ ኣሰላሰልኳት።
ከመቀመጫዋ ተስፈንጥራ መጥታ ያቀፈችኝ ኣስተቃቀፍ …
እንዳሻው መንፈሴ ላይ ጋለበ።
"ኣመመኝልሽ ... ደከመኝልሽ
ትናንትና ማታ የወጋኝ ጡትሽ"
(ኣዝማሪ)
.
በሳምንቱ በሰጠችኝ ስልክ ቁጥር ደወልኩ። ኣነሳችው።
ከሰላምታዎች በኋላ … ዘላለሜን የማልረሳቸው ጉዶች ነግራኝ
ተሰነባበትን። ልክ በሳምንቱ ከሰውዬው ጋር ወደ ካናዳ በረረች።
.
እና ዛሬ … የጨበጥኩትን ብርሌ ሙሉ ጠጅ እያጎደልኩ … ያን
ግዜ ተቀምጣበት ወደነበረው መቀመጫ እማትራለው። እዛ ቦታ
ጋር ቀልቤን የወሰደው መልኳ የለም። የሚያቅጠብጥ ሳቋ
የለም። ዙሪያዋን እንደ ጆፌ ኣሞራ እያንዣበበ ትከሻውን
የሚሰብቀው ባሏ የለም። የሚልመዘመዝ የኣንገት ነቀላው
የለም። ተመልካቹን ሁሉ የሚያስቀው እፍግምግሙ የለም።
"ኣላነሳው የለኝ ኣልቀለውጠው
ዛሬስ ከነባሏ ልትናፍቀኝ ነው"
(ኣዝማሪ)
* * * /// * * *
@libmalet
@libmalet
"ያለምክንያት ከሄድክ በምክንያት አትምጣ"
********************************
በህይወት ሰልፍ ውስጥ ሳለህ ልብ ልትላቸው የሚገቡ
እነኚህን 10 ነጥቦች በአጽንኦት አንብባቸው
➊."ያለፈ ነገር እንደማይቀየር አትርሳ!" ላወቀበት ሰው ግን
ያለፈው ለወደፊቱ የራሱ የሆነ ትምህርት አለው፤ ካለፈው
ነገርህ
ተማር እንጅ በፍፁም አታማርር፤
ማማረር ነገህን በጎ አያደርገውም።
➋.የሰዎች ሃሳብ የአንተን ማንነት አይገልፅም! ማንነትህ አንተ
ውስጥ ነው ያለው፤ መልካም አድርግ ሌላውን እርሳው
የሁሉም
ሰው የህይወት መንገድ (ጉዞ) ይለያያል፤ ለሁሉም ጊዜ
አለውና
ጊዜው በደረሰ ሰው ሁኔታ አትቅና።
➌.መኪና ገዛ ብለህ "እኔስ" አትበል! ጊዜህ ሲደርስ
መኪናዎች
ወይም ‘አውሮፕላን’ ትገዛለህ ፣ ያውም ለመኖር አስፈላጊ
ከሆነ
፣ ደግሞስ እንዴት እንደገዛው የት ታውቃለህ? እርሱን
ተወውና
በራስህ ላይ አተኩር ፣ ያለህ ነገር በቂ ነው።
➍."ለሰዎች ለደስታቸው እንጂ ለሀዘናቸው መንስዔ አትሁን!"
►በሰዎች ደስታ→ደስ ይበልህ!
►ለሰዎች→ክፉ አትመኝ፣
►በሃዘናቸውም→አብረህ እዘን፣
►ሰዎች ሲያዝኑ→አትደሰት፣
►ሰው ከሆንክ→የሰው ነገር ይሰማህ፣ ይህ ማለት ግን
ተንኮል
እየሰሩ ከሚደሰቱ ሰዎች ጋር ተደሰት ማለት አይደለም።
ሰው እያስከፋ ብሎም እየገደለ የሚደሰት አለ ፣ አንተ
ከተጎዳው
ሰው ጋ ሁን፣ አስተውል።
➎."በጊዜ ስራ እንጂ ጊዜ ባንተ ላይ አይስራ!" ጊዜ
የማይፈውሰውና የማይቀይረው ነገር የለም። አንተንም
ጊዜው
ይቀይርህ ዘንድ ፍቀድለት፤
በተሰጠህ ጊዜ ለመልካም ነገር ሱሰኛ ሁን።
➏. "መክሊትህን ፈልግ!"
ውስጥህ የሚችለውና የሚያምንበት ተሰጥኦ ምን አለህ?
ምን
አይነት ስራ መስራት ትችላለህ? አስተውል ጓደኛህን
አትመልከት
፣ ትለያያላችሁና። አለማችን በትምህርት ብቻ ወይም
በጥበባት
ብቻ ወይም በተወሰኑ ዘርፎች አይደለም እየኖረች ያለችው።
በጣም ብዙ ነገሮች ናቸው እየደገፏት ያቆሟት። አንተም
ጥቂትም ብትሆን ያለህን ችሎታ ፈልገውና አውጣው። ቁፋሮ
ነው ወይስ ቾክ ይዞ ማስተማር ነው ወይስ መምከር መገሰፅ
ነው? ቆንጆ ሽሮ ወጥ እየሰሩ መሸጥ ነው? ድንጋይ ቅርፅ
(ኮብልስቶን) እየሰሩ መኖር ነው? ምንድነው? እባክህ
ፈልገው
አጎልብተው ጀምረው፣ "ምን ይሻለኛል?" እያልክ ጊዜህ
እንዳያልቅ። በእርግጥ ጊዜህ ሳይሆን አንተ ነህ የምታልቀው።
➐. "መልካም ነገር ሁሉ ከፈጣሪ መጥፎ ነገር ሁሉ ደግሞ
ከሰይጣን እንዳልሆነ አስተውል!" ፈጣሪ መጥፎን ወደ
መልካም
የመቀየር ብቃት አለው። ሰይጣንም ያጠፋህ ዘንድ መልካም
የሚመስል ነገር ሊያዘጋጅልህ ይችላል። መልካም ማሰብና
መልካም መሆን መልካም ነገር እንዲገጥምህ ማመቻቸት
ነው፤
መጥፎነት ከአንተ ይራቅ፤ ለአንተም ሆነ ለሰዎች ጉዳት እንጅ
ጥቅም የለውም።
➑. "ሰው የዘራውን ያጭዳል" የሚለውን አባባል አስታውስ፤
የሰራኸውና የምትሰራው ነገር የሆነ ጊዜ ላይ ዞሮ ያገኝሃል፤
መጥፎ ከሰራህ እንደስራህ፤ መልካም ከሰራህም እንደዚያው
ይገጥምሃል። ክፉ ነገር እየዘራህ መልካም ነገር አትጠብቅ፤
ራስህን አትሸውድ። ጤፍ ዘርተህ ባቄላ አትጠብቅ፤ ጤፍ
የዘራ
ገበሬ ጤፍ እንደሚያጭድ ሁሉ አንተም የዘራኸውን በእጥፍ
ታጭዳለህ።
➒. "ለራስህ ስትል መልካም ሁን፣ በጎውንም አስብ!" ለራስ
ማሰብ ማስተዋል እንጅ ራስ ወዳድነት አይደለም። ራሱን
የማይወድ ሰው ሌላውን አይወድም።
➓. "በማንም ላይ አትፍረድ!"
ፍርድ የፈጣሪ ነው። ፍጥረት ሁሉ እንከን አለበት። የተሻለ
ሀሳብ
አለኝ ብለህ ካሰብክና ከቻልክ ምከር ካልሆነ ዝም በል።
*ለውጥ ከራስ ይጀመራል! እናም አሁኑኑ መለወጥ ጀምር።
@libmalet
@libmalet
It's all about felling in love with yourself and sharing that love with someone who appreciates you, rather then looking for love to compensate for a self love deficit.✨
You are only telegram girl I write, and I think about you all day. I feel so stupid and crazy thinking about you, because you are just telegram girl. Still I think about you so much. So I decided OK, maybe I want you as more than telegram girl.
'Maybe I want her to be mine"
Maybe I want to take you out for dinner, hug you touch you, hold you. Be with you. I like you. It is not so crazy.
Can I come?
«ልብ ብለው ያንብቡ»
ውበትሽን አይቶ የተመኘሽ እና ከውበትሽ ጀርባ ያለውን
ማንነትሽን አውቆ ያፈቀረሽ ሰው የተለያዩ ናቸው።
ለምን ነገርከኝ እንዳትይ?
እኛ ወንዶች የፈለግነውን እስክናገኝ ሴትን ንግስት ማድረግ እናውቅበታለን።
ያፈቀረ ግን ተብታባ ነው፤ ውበትሽን ለመግለፅ እንኴን አንደበት የለውም፤
ነገር ግን በውስጣዊ ማንነትሽ እሱነቱን አጥቶ ሌት ተቀን አንቺን በምናቡ
ሲያወጣና ሲያወርድ፣ የአንቺን ህይወት ለማድመቅ የራሱን ሲያፈዝ፣ ከሰው
በላይ የነበረው መቀመቅ ሲወርድ........ያኔ ላንቺ ያንስብሻል።
እናም ፍቅርሽን ገላሽን ለተመኘው ትሰጪና ደግመሽ ብትፈጠሪ እንኴን
የማታገኝውን ንፁህ አፍቃሪሽን ልብ አንኮታኩተሽ ትሰብሪዋለሽ። እሱም
ለዘለዓም ልቡ ታሞበት እንደማቀቀ ፍቅሩን ተቀምቶ አዝኖ አፈር ይሆናል።
አንቺ ሳታውቂ ራስሽን የሰጠሽው ግን አውቆ ይተውሻል። በቃላት ድርደራ
በስጦታ ጋጋታ ንግስት ያስመሰለሽ.......ያሻውን ፈጽሞ ሲያበቃ ከጥፍሩ
ቆሻሻ እንኴን አይቆጥርሽም። ለዚ ነው የተመኘሽ እና ያፈቀረሽ የተለያዩ
ናቸው ያልኩሽ።
ምርጫው ግን ያንቺ ነው።
@libmalet
@libmalet
ሳጣሽ ኣቅም ኣጣሁ!
____
.
የሽንፈትን ዳገት በፍቅርሽ ኣልፌ
የሃፍረትን ካባ በሳቅሽ ገፍፌ
በስምሽ ፎክሬ ግዳይ እንዳልወጣሁ
ሳጣሽ ኣቅም ኣጣሁ::
.
ከቃልሽ ቃል ሆኜ ኣደብ እንዳልገዛሁ
ትንፋሽሽ ገላዬን ዳብሶ እንዳላወዛው
ብትለይኝ ግዜ ...
ከንፋስ ቀልዬ መፈንገል ኣበዛው::
.
ይህውልሽ ውዴ ስሚኝ የኔ እመቤት
እንደ ሶምሶን ዞማ እንደ ጳውሎስ እምነት
ፍቅርሽ ብቻ ነበር የታጠቅኩት ጉልበት::
.
ብትለይኝ ግዜ ...
ቃልሽን ኣምኜ
ስንደው የኖርኩት የሃዘን ተራራ
ጦር የሰበቅኩት የችግር ወጋግራ
ዳግም ጉልበት ገዛ ዳግም ነፍስ ዘራ!
.
በስምሽ ፎክሬ ለድል እንዳልወጣሁ
ሽንፈቴ ኣሸንፎኝ በናፍቆት ተቀጣሁ
ሳጣሽ ኣቅም ኣጣሁ!
@libmalet
@libmalet
እንደምነሽ?
========
እንደምነው ዓይንሽ ጥቁር እና ነጩ
እንደጊዜው መንግስት ሕዝብ አበጣባጩ.
እንደምነው ጡትሽ እንደጦር የቆመው
እንደጊዜው ምርጫ የተጭበረበረው.
እንደምነው ጭንሽ የሚወዛወዘው
እንደ ህዝብ ንብረት የሚበዘበዘው።
እባክሽ ንገሪኝ ወገብሽ እንዴት ነው?
እንደ ጋዜጠኛ ሲታሰር የኖረው። .
እኔ እንዳለሁ አለሁ እቴ ምን ጎሎብኝ
የማይመጣ ባቡር ቆሜ እየጠበኩኝ
ኔትወርክ ለሌለው ስልክ ካርድ እየገበርኩኝ
ለማይመጣ ውሃ ቧንቧ እየተከልኩኝ
ለማይበራ መብራት ደሞዝ እየላኩኝ
ለሎተሪው ቤቴ እያጠራቀምኩኝ አለሁ እንደተውሽኝ ። .
እየውልሽ እቴ የዘንድሮ ኑሮ ሆነልሽ አስፈሪ
ድንገት ተገጣጥመው ግንቦት ስላሴና የሆነ አሸባሪ
"መብራት የለም" ያለው እየተፈረጀ
"ውሃ የለም" ያለው እየተፈረጀ
"ኔቶርክ የለም" ያለው እየተፈጀ
ዘብጥያ ተጥሎ ስንት ወጣት አረጀ.
አሁን እሱን ትተሽ እንቺ እንደምን አለሽ? .
እንደምነው ፀጉርሽ ንፋስ የበተነው
እንደ ግል ፓርቲዎች የተዝረከረከው
^
ንገሪኝ እንዴት ነው?
ይመቻችሁ
@libmalet
@libmalet
የካምፓስ ሕይወት
..
በመጀመሪያ ዩንቨርስቲ ገባን፡፡ ያስገረመንን ትልቅ በር
እያለፍን፡፡
ገና በመጀመሪያዎቹ ቀናት ምድብ ድልድል ወጣልን፡፡ ልዩ
የቅበላ ፕሮግራም ከአማራ ክልል ለመጣችሁ፣ ለኦሮሚያ
ተወላጆች፣ ለተጋሩ፣ በጌታ ለሆናችሁ፣ ለኦርቶዶክሳዊያን፣
ለሙስሊም ወንድሞቻችን ወ.ዘ.ተ አይነት ማስታወቂያዎች
ግድግዳዎቻችንን እያጨናነቁት፡፡ “እየመደቡን ይሁን
እየሰደቡን ማርያም ትወቅ፡፡” ነቄ ያልነው ሰኞ የአማራ
ክልል የስነፅሁፍ ፕሮግራም፣ ማክሰኞ የተጋሩ የጥበብ
ምሽት፣ እሮብ የኦሮሚያ የባህል ምሽት፣ ሃሙስ
ግቢጉባዔ፣ አርብ ፌሎውሺፕ.....እያልን ሰባቱንም ቀናት
መታደም ጀመርን፡፡ ምንያቱም ፍሬሽ ነበርን፡፡በዚያውም
ዶርም ሲደለደል የአገር ልጅ የሚለው ሃሳብ የጎጥ ልጅ
የሚለውን እንደሚወክል ተማርን፡፡
በገባንበት ሰሞን ለመጀመሪያ ጊዜ ካፌ ገባን፡፡ ሽታው
እያጥወለወለን መሰለፍ ጀመርን፡፡ “አመቱን ሙሉ ይሄንን
እንዴት ነው የምንለምደው” ስንል ተገረምን፡፡ በዚያው
ሰሞን ላውንጅ የሚባል ማስታገሻ እንዳለ አወቅን፡፡
እዚያም ሄደን ተሰለፍን፡፡ የያዝነው ገንዘብ እና ዳቦ ቆሎ
ስላለቀ ባንክቤትም ሄደን ተሰለፍን፡፡
ታናሼ ህይወት በካምፓስ እንዲህ ይጀምራል፡፡
ብዙ ሳትቆይ ክላስ ትጀምራለህ፡፡ ገና በመጀመሪያው ቀን
አስደንጋጭ እንግሊዘኛ ጆሮህ ላይ እንደ መብረቅ
ይወርድብሃል፡፡ “ከእነዚህ ጋ ተምሬ አንድስ ሴሚስተር
እዘልቃለሁ?” ትላለህ፡፡ አትፍራ ፡፡ በሴሚስተሩ መጨረሻ
አንተ አስኮራጅ እነሱ ኮራጅ በአመቱ መጨረሻ ደግሞ አንተ
ሰቃይ እነሱ ወራጅ ትሆናላችሁ፡፡
ከጎንህ የብርጋዴር ጀነራል እከሌ ልጅ ይቀመጣል፡፡ ከሱ
ፊት የፓስተር እከሌ ልጅ አለች፡፡ ከኋላህ ሰለሳ ግመልና
መቶሃምሳ ፍየል ያለው የአርብቶ አደር ልጅ አለ፡፡ ከሱ ጎን
“የጤፍ ተክል አይቼ አላውቅም” ያለችዋ ልጅ፥ “የዶሮ
ብልት ስንት እንደሆነ አላውቅም” ካለችዋ ሞልቃቃ ጋ
ተቀምጣ ታያለህ፡፡ እነዚህ ሁለቱ ክፍል በጊዜ ገብተው
አያውቁም፡፡ ከነሱ ጎን ከሁሉም ቆንጆ ነኝ ብላ
የምታስበዋ፣ አንገቷን እንኳን ስታዞር ሜካፕዋ እንዳይበላሽ
የምትጠነቀቅ የምትመስለው ቄንጠኛ ልጅ ትቀመጣለች
..እኛ ግን አንወዳትም፡፡ ጥግ ላይ ከሁሉም ቆንጆ ናት
ብለን የምናስባትና የምንወዳት አይናፋር ትቀመጣለች፡፡
ከሁላችንም ፊት ክረምት ክረምት በሰራው ቀን ስራ ራሱን
የሚያስተዳድረው ሰቃይ ይቀመጣል፡፡ ከጎኑ እንትን ሆቴል
በስሙ የተሰየመለት ልጅ አለ፡፡ ይህ ሁሉ የሚገባህ ግን
ስትቆይ ነው፡፡ ስትቆይ በኢትዮ-ኤርትራ ጊዜ የዘመተ
ልታከብረው የሚገባህ ሰው አብሮህ እንደሚማር
ታውቃለህ፡፡ ስትቆይ በጣም ዝምተኛው ልጅ ጎበዝ ሰአሊ
እንደሆነ ይገባሃል፡፡ ብረት የሚገፋው ጉልቤው ልጅ
ከሁሉም ፀባየኛ እና ምስኪን ይሆንብሃል፡፡ ከሁሉም
ሴቶች አስቀያሚ ናት ያልካት የሚያምር ድምፅ ያላት
ዘማሪ ትሆናለች፡፡ ከዛ ደግሞ እንደኔ አይነት አንድ ሁለት
“ጥበብ ጠራችኝ ወ አጠናገረችኝ ፍሪኮች” እንኖራለን፡፡
ጎበዝ ዘፋኝ፣ ጎበዝ አትሌት፣ ጎበዝ እግርኳስ ተጫዋች ና
ጎበዝ ምንም ሁሉንም አይነት ተማሪዎች ታያለህ፡፡ ስምንት
ሴቶች ሲጀምሩ በቡድን ይንቀሳቀሱና ሲጨርሱ ስምንት
ባላንጣዎች ይሆናሉ፡፡ ሲጀምሩ ስምንት ብቸኛ የነበሩ
ወንዶች ሲጨርሱ አንድ ቡድን ይፈጥራሉ፡፡
ክፍል እንደ ማቅለጫ ድስት (Melting Pot)ነው፡፡
ሁላችሁም አንድ ላይ ተቀምጣችሁ ትማራላችሁ፡፡ ፈተና
ይደርሳል፡፡ ቴንሽን ያከሳሃል፡፡ ያንጨባርርሃል፡፡ እስኪነጋ
ታጠናለህ፡፡ በሶ ስትበጠብጥ ታድራለህ፡፡ ታስጠናለህ
ታጠናለህ፡፡ ትኮርጃለህ ታስኮርጃለህ፡፡ ውጤት ሲመጣ
የተገላቢጦሽ ይሆናል፡፡ ከለፈለፉት ጥቂቶች ይሰቅላሉ፡፡
ዝም ካሉትም ጥቂቶች ይሰቅላሉ፡፡ ነጋ ጠባ ካጠኑትም
ጥቂቶች ይሰቅላሉ፡፡ ትንሽ ትንሽ ያጠናህ አንተም ትሰቅልና
ትገረማለህ፡፡ በተገለጠለት እንጂ በገለጠ አይደለም
ትላለህ፡፡ እንኳን ሊያስኮርጁህ አሳይመንት እንኳን
የሚደብቁህም አሉ፡፡ የቡድን ስራ ብቻህን ሰርተህ
ትቀፍላለህ፡፡ ወራጅ እየተጫረ፣ ሰቃይ እየሰቀለ አብዛኛው
በመሃል ቤት ሆኖ ጊዜው እንደዚህ ይነጉዳል፡፡ በዚህ
መልኩ ስማቸውን የማይፅፉ አብረውህ ይመረቃሉ፡፡
የሶስት አመት ትምህርት ሰባት አመት የሚፈጅባቸውም
ይመረቃሉ፡፡
ሴሚስተሮች ያልፋሉ፡፡ ፍሬሽነት ቀርቶ ሲኒየር ትሆናለህ፡፡
ስትቆይ ከብዙ ሰዎች ጋር ትግባባለህ፡፡ ባህሪ
ትወራረሳለህ፡፡ ፀጉርህን ታንጨባርራለህ፡፡ የማታውቀውን
ብሄር ቋንቋ ትማራለህ፡፡ የፅዳት ሰራተኛ እናቶች የግቢ
እናት ይሆኑሃል፡፡ ካፌ ሳይገቡ የመኖር ሚስጥር
ይገለጥልሃል፡፡ ትቀፍላለህ፡፡ ካልሆነልህ ትሰቅላለህ፡፡
ሰልፍ የማጭበርበር ክህሎትን ታዳብራለህ፡፡ ከብረት
ገፊዎች ጋ ዶርም ከደረሰህ ብረት ገፊ ትሆናለህ፡፡ “በጌታ
ነኝ” ትል የነበረች አይናፋር የበግተራ ቦዘኔዎች የጋራ
ንብረት ትሆናለች፡፡ ምናልባት ሰክራ ወድቃ ተሸክመህ
አስገብተሃት ይሆናል፡፡ አስካለች ...ፌቨን ነኝ ትላለች፡፡
ያምራል የሚባለው ልጅ እንኳን የሚያምር ስሙን
ይቀይራል፡፡ እልል ያልክ ወመኔ ሆነህ ገብተህ ጌታ
ይጠራህና “አመለጥኩ” የሚለውን መዝሙር በነጋ
በጠባው እየከፈትክ ሰፈር ትረብሻለህ፡፡ ነጠላ ይዘህ
የገባህ ዲያቆን አርብ እሮብ መግደፍ ትጀምራለህ፡፡
ከአጫሾች ጋር ውለህ ማጨስ ትማራለህ፡፡ መቃም
ትማራለህ፡፡
ሲጠጡ እያነጉ ባጥር ዘሎ መግባት ትማራለህ፡፡ ቢጤህን
ሴት ወንድ ዶርም ማስገባት ትማራለህ፡፡ ጭፈራ
ትማራለህ፡፡ ቁማር ትለምዳለህ፡፡ ጭማድ ትለምዳለህ፡፡
ደህና ሰው ያልከው ይበላሻል፡፡ ተበላሸ ያልከው ደህና ሰው
ይወጣዋል፡፡ የኮፒ ታጣለህ፥ የውስኪ ታገኛለህ፡፡
ሃንድአውት ትሰርቃለህ ወይ ትዋሳለህ፡፡ አጤሬራ ኮፒ
ታደርጋለህ፡፡ “እግዜር የለም፥ አንተም የለህም” የሚሉህ
ጀማሪ ፈላስፋዎች ታገኛለህ፡፡ በተቃራኒው በንባብና
በአስተውሎት የበሰሉ ልጆች ታገኛለህ፡፡ ማታ ማታ ወክ
እያደረክ ወይም ቡና እየጠጣህ የከረሩ እሳቤዎችን
ትለዋወጣለህ፡፡ እመነኝ.... እናንተ በተመስጦ
ያወራችሁትን ወሬ በስንተኛው ቀን የሆነው ኮርስ ላይ
በሆነው ፈረንጅ ስም የሆነ አይነት ቲዎሪ ተብሎ
ሲመጣልህ እንዳትገረም፡፡ በጊዜ ቀደሙህ እንጂ
አልበለጡህም፡፡ በገንዘብ የበለጡህን፥ በግሬድ
ትበልጣለህ፡፡ በግሬድ የበለጡህን በጠቅላላ እውቀት
ትበልጣለህ፡፡
ከክላሳችሁ ብዙዎች ተግባብተው ታያለህ፡፡ ስታየው
ያስጠላህ የነበረው ልጅ ምርጥ ጓደኛህ ይሆናል፡፡ ረጅሙ
ጺማሙ ሙስሊም አክራሪዋን ነጠላ ለባሽ ኦርቶዶክስ
ይጠብሳል፡፡ በግቢው የሚያስቀኑ ጥንዶች ይወጣቸዋል፡፡
አንተም ከማን አንሼ ብለህ በግተራ ቆመህ ትለክፋለህ፡፡
ፉንቃ ይገባልሃል፡፡ ትጀናጀናለህ፡፡ በለስ ይቀናህና
ትጠብሳለህ፡፡ ኪሲንግፑል ስትሳሳም ታመሻለህ፡፡
ቤተመፅሃፍት አብረህ ታድራለህ፡፡ ኳስ ሜዳ ሄደህ
በኩለሌሊት ትዳራለህ፡፡ ትፋታለህ ሌላ ትጠብሳለህ፡፡
እውነቱ ምንድነው ከግቢ ፍቅር በጣም ጥቂቱ ብቻ ዘላቂ
ይሆናል፡፡ አንዳንዶቹ ከመጡበት ቦታ ትዳራቸውን
አስቀምጠውት እንደመጡ ሳትዘነጋ፡፡ ጊዜው እየሄደ አመት
ትጨምራለህ፡፡ አመት ሲጨምር የሴቶች ተፈላጊነት
ይቀንሳል፥ አዳዲስ ሴቶች ስለሚመጡ፡፡ አመት ሲጨምር
የወንዶች ተፈላጊነት ይጨምራል፥ በልምድ፣ በብልሃትና
በድፍረት ከፍሬሹ ወንድ ስለሚሻሉ፡፡ አመት ሲጨምር
ገበያውን እና ችግራቸውን ያወቁ ሲኒየር ሴቶች ሹገር
ይጠብሳሉ፡፡ ካጣበስካቸው ደግሞ አንተም ከጥቅሙ
ትካፈላለህ፡፡ ቢያንስ ማታ ማታ የማዘር ቤት ፍርፍር
ትበላለህ፡፡...ልክ እንደኔ 😂😂😂😜😜
@libmalet
@libmalet
* እኔኮ ስወድሽ *
፡
እኔኮ ስወድሽ ቃላት ይደክማሉ፣
ፊደላት ሰልለው ድጋፍን ይሻሉ፣
፡
ምን ቃል አለኝና ፍቅሬን ነግርሻለሁ፣
በልቤ ወድጄሽ ለፍቅርሽ ሞቻለሁ፣
፣
አንቺን መተው ለኔ ይገርምሻል ውዴ፣
ከሞት ከቶ አያንስም እወቂው እንግዴ፣
፡
አረ እንደውም መሞት ሳይሻል አይቀርም፣
የማፍቀር ሰቀቀን ጠባሳው አይሽርም፣
የናፍቆትን እከክ ጥፍር አያከውም፣
የመውደድን መሞት አይኖች አያዩትም፣
፡
እናምልሽ ውዴ እራቀኝ ስትዪኝ፣
በቁም ሳለሁ በድን እንደሆንኩ እወቂኝ፣
፡
በፍቅርሽ ሰንሰለት እግረ ሙቅ ታስሬ፣
አቅም የተቀማሁ የማልቆም ዳክሬ፣
የመከነ ልፋት ሰርክ ምድርን ዞሬ፣
የድጋይ ላይ ተክል የማይበዛ ዘሬ፣
እንዲ ነኝ አለሜ ካጣሁሽ አፍቅሬ፣
፡
ዓሳ ከውሃ ወጥቶ ይኖር ዘንድ እንዳይችል፣
ንስር ምድር ወርዶ እንደማይሄድ ቁልቁል፣
እየተገረፈ እንደማይድን ቁስል፣
ለመርዶ ነጋሪ እንዳይባል እልል፣
እኔም አንቺን ካጣሁ ፍቅሬ ይከብደኛል፣
፡
እኔኮ ስወድሽ ከገደቡ አልፌ፣
ጧት ማታ ሳልምሽ መውደድሽን ታቅፌ፣
ሌላ ምንስ አለኝ ፍቅርሽ ነዋ ትርፌ፣
ልተውሽ አልችልም ልቤ ላይ ሸክፌ፣
፡
ውሰጂው ያለኝን ልሁን ነጭ ደሃ፣
ወይኑንም ተጎንጪ ለኔ ደሞ ውሃ፣
፡
ከጮማው ቁረጪ አማርጪ ያሻሽን፣
እኔ ውዬ ልደር እየራበኝ ጦሜን፣
፡
ላንቺ ነው
@libmalet
@libmalet
Easter greetings! May this be the best Easter ever for you & your loved ones! Let joy & peace from God ascend in your home. These are may heart felt wishes for you & your family this season, Happy Easter🎉❤️✝
"የሕይወትህ መርሆዎች በእነዚህ ላይ የተመሰረቱ ይሁኑ!"
.
1. የፈለከውን ነገር ሁልጊዜ ላታገኝ ትችላለህ፡፡
ያገኘኸውን
ነገር መውደድን ግን ተለማመድ፡፡ መሻትህ ሁሉ ላይኖርህ
ይችላል ያለህን መንከባከብ ግን አትርሳ፡፡
.
2. ኑሮዬ ይበቃኛል ማለትን ተለማመድ፤ ኑሮዬ ይበቃኛል
ማለት ስለ ግብህ ማሰብ አቆምክ ማለት አይደለም፡፡
በዚህ ውሳኔ ማረፍ ቅሬታን ያርቅልሃል እምነት ማጣትን
ያስወግድልሃል ተስፋ መቁረጥንና የተዛባ
አመለካከትህንም ያስተካክልልሃል፡፡
.
3. አሳብህም ልብህም ሰፊ ይሁን፤ አመለካከቶችህ ሁሉ
ሁሉንም ነገር በቀናነት በመልካም ጎኑ በመመልከትና
በማሰብ ላይ የተመሰረቱ ይሁኑ፡፡
.
4. ሥራህንና ቃልህን ለማዛመድ ትጋ፡፡ ልብህና እጅህ
እርስ በእርሳቸው እንዳይጣረሱ ጥረት አድርግ፡፡
.
5. ወሳኙ ነገር የምትኖርበት ቦታ ሳይሆን አኗኗርህ ነው፡፡
ከምታምንበት ነገርም በላይ ዋጋ ሊሰጠው የሚገባው
ባመንክበት ነገር እንዴት ትኖራለህ የሚለው ነው፡፡
.
6. ሁላችንም በሕይወት ያለነው ደስተኞች እንድንሆን
ነው፡፡ ለዚህም የእግዚአብሔርን ድምጽ አድምጥ፤ ለኑሮህ
ብልጥግና ፍቃዱን ተከተል፤ ስኬታማ ለመሆንም በእውነት
ላይ ቁም፡፡
.
7. እኛ ቀብረን የምናዝነውን ሀዘን ቆመው፣ እኛ ርቦን
የምንሰቃየውን ስቃይ ጠግበው፣ እኛ አጥተን የምናነባውን
እንባ አግኝተው የሚያነቡት ብዙ ናቸው፡፡ ልዩነቱ እኛ ሁሉን
ለእርሱ ክብር ማድረጋችን ነውና ሁኔታዎችህን ሁሉ
ለእርሱ ክብር ማድረግን መልመድ ይገባሃል፡፡
.
8. ማንም ሰው ከጠባቡ ግለኝነት ሕይወት ወደ ሰፊው
ጠቅላላው የሰው ልጅ ምልከታ ከፍ እስኪል ድረስ መኖርን
ተማረ አይባልም፡፡ ማለዳ ማለዳ አዲስ ትርጉም ባለው
መንገድ ለመኖር ራሳችንንን ብቻ መመልከታችን ወደ ፊት
ከመመልከት ጋር ሊዋሐድ ይገባዋል፡፡
.
9 . ያለህን ስትሰጥ ጥቂት ሰጥተሃል፤ ራስህን ስትሰጥ
ግን
ያኔ በእውነት ሰጥተሃል እንደሚባለው የእኛን ብቻ ሳይሆን
እኛንም ለሌሎች ማካፈል አለብን፡፡ ለምሳሌ፦ ማየት
ለተሳነው ሰው መመልከት ቢችል ኖሮ ሊያከናውን
የሚችለውን እኛ ብናከናውንለት፣ መራመድ ለማይችል
ቢራመድ ኖሮ ሊሠራው የሚችለውን እኛ በመራመድ
ብንሠራለት፣ መናገር ለማይችለው መናገር ቢችል ኖሮ
የሚያስረዳውን አፍ ሆነን ብንናገርለት ይህ ራስን ማካፈል
ነው፡፡
.
10. በፍቅር መግዛት በጥላቻ ከመግዛት፣ ብቸኝነትን
ከመንከባከብ ሕይወትን ማጋራት አብዝቶ የተሻለ ነው፡፡
በትህትና ልንሠራው የምንችለውን መልካም ነገር በሸካራ
ቃላቶች ልናውከው፣ በግለኝነት ልናፍነው አይገባም፡፡
@libmalet
@libmalet
"you felt familiar the moment I met you. When you spoke or laughed or danced I become over whelmed by the powerful sensation we had been here before. when we kissed I felt the energy of thousands lives on our lips, as through our souls had known one another all along."💞🌷
. . . ድሮ_ቀረ_ፍቅር . . .
ፈራን ፍቅር ፈራን
በውሸት ተደብቀን በሀሜት እየተመራን
እስኪ ተናገሪ
ማንንም ሳትፈሪ
ፍቅር ማለት ምንድነው እንዴት ተረጎምሽው?
"አሁን ፍቅር የታል? ድሮ ቀረ " ያልሽው
ጊዜው ነው ወይስ ፍቅር ?
እንዲ ተቀይሮ
ፍቅር የለም ያስባለሽ ውስጥሽኝ አሳርሮ
አንተም ተናገር እስኪ ልጠይቅህ ወንድሜ
ፍቅር ድሮ ቀረ ስትል ገና በዚ እድሜ
እስኪ ልስማህ ተናገር
ድሮ ፍቅር ምን ነበር?
እንዴት ነው የተረዳከው?
ፍቅር ድሮ ቀረ ብለህ ያማረርከው?
ወዴት ቀርቶ ነው ፍቅር?
ምክንያትህን በሙሉ እንስማ ተናገር
ሰአቱም 24 ወራቱም 13
ጊዜው ምን ተቀየረ?
የቀነሰ የለም ወይም የጨመረ
ታዲያ የትናንት ፍቅር ዛሬ ወዴት ቀረ?
ድሮ ድሮ እየተባለ ታሪክ ሆኖ ሲቀር
በስሜት ጥላ ስር
በውሸት ተደብቆ
ድሮና ዘንድሮ እጅጉን ተራርቆ
የሄደው ሳይመለስ የሚመጣውም ሳይደርስ
ከደጅ እየደረሱ ከመንገድ ሲቀሩ
ምን አጉድለን ይሆን?እስኪ ተናገሩ!
የማን ስተት ነው? ምን አይነት ሚስጥር?
ለምን ጊዜን አልተሻገረም ድሮ የነበረው ፍቅር?
@libmalet
@libmalet
♡ #አንቺ_ማለት_ለኔ. . . . . .
ጊዜ ሲጠምብኝ፣ አንገቴን ስደፋ፣
ቀን ሲጨልምብኝ፣ ፅልመቱ ሲከፋ።
ሰው ተራምዶኝ ሲሄድ፣ አለሁ የሚል ሳጣ፣
ኑሮ ዳገት ሲሆን፣ በችግር ስቀጣ።
ጉድፌን ያጠፋሽ፣ የስኬቴ ዋጋ፣
የቀን ሲሳየ ነሽ፣ የችግሬ አለንጋ።
አንቺ ማለት ለኔ. . . . . . . . . .
ደግነትሽ ቢታይ፣ በፍቅር መነፅር፣
መውደድሽ ቢለካ፣ ውለታሽ ቢሰፈር፣
እልፍ አላፍ ቃላቶች፣ ብፅፍ ብደረድር።
ካንደበቴ አውጥቼ፣ በቃል የማልገልፅሽ፣
የሴትነት ወዙ፣ ሚስጥሩ ያልጠፋሽ።
የቤቴን ወናነት፣ የደጄን ጭርታ፣
ደስታ የመገብሽው፣ በሀዘኔ ፈንታ፣
አንቺ ማለት ለኔ፣
የክፉ ቀን ደራሽ፣ ታማኝ ግራ ጎኔ፣
ፅድቅን ያለበሰሽ ያልነካሽ ኩነኔ . . . .።
@libmalet
@libmalet
በአንድ ክሊኒክ ውስጥ ዶክተሩ ለምሳ ይወጣና ለዘበኛው ያስጠብቀዋል!
ዶክተሩ: ታካሚ ከመጣ ትንሽ ጠብቁ ዶክተሩ ይመጣል በላቸው (ዶክተሩ እንደ ቀልድ)
የምትቸለውንም አስተናግድ! ይለዋል፡፡
ዘበኛው: እሺ !
ከ 1 ሰአት በኃላ.........
ዶክተሩ: ሰው መጥቶ ነበር ?
ዘበኛው: አዎ አንዱ ራስ ምታት አሞኝ ነው
ሲል (parastamol) ሰጠሁት!
ዶክተሩ: ጎበዝ ሌላስ ?
ዘበኛው: አንዷ መጥታ እየሮጠች አልጋው ላይ
ተኛች!
ዶክተሩ: ከዛስ (በድንጋጤ እያየው......)
ዘበኛው: ከዛ...... ሙሉ ልብሷን አውልቃ ለ15
አመት አንድም ቀን ወንድ አይቼ አላውቅም
አለችኝ!
ዶክተሩ: ከዛስ (አሁንም በድንጋጤ እያየው..)
ዘበኛው: ያው ለ15 አመት አንድም ቀን ወንድ
አይታ ስለማታውቅ......
- — — — — — — — — —
አይኗ ላይ የአይን ጠብታ አደረኩላት!
- — — — — — — — — — — -
ወንዶች በዘበኛው ቦታ ብትሆኑ ምን
ታደርጋላችሁ ?
@libmalet
@libmalet
አንድ የህግ ባለሙያ በባቡር እየተጓዘ ሳለ አንድ
በጣም ቆንጆ የሆነች ልጅ መጥታ ፊት ለፊቱ ከሚገኘው
ወንበር ላይ ተቀመጠች።
:
በዚህም የህግ ባለሙያው ደስ አለው።ቀና ብሎ ሲመለከታት
አይን ለአይን ተያዩ ከዛም ፈገግ አለች።
:
አሁን ደግሞ በይበልጥ ደስ አለው። ትንሽ ቆይታ አጠገቡ ሄዳ ተቀመጠች።በዚህን ጊዜ እጅግ በጣም ደስ አለው።
:
ትንሽ ቆየችና ወደ ጆሮው ጠጋ ብላ በሹክሹክታ
"ያለህን ገንዘብ; የATM ካርድህን ከነፓስ ዎርዱ እና የሞባይል ቀፎህን አሁኑኑ ካልሰጠኸኝ ስትጎነትለኝ እንደ ነበረና ፆታዊ ትንኮሳ እንደደረሰብኝ እዚህ ባቡር ውስጥ ላሉት ሁሉ በመንገር እጮኃለሁ።" አለችው።
:
የህግ ባለሙያው በቸልተኝነት ቀና ብሎ ተመለከታትና ከቦርሳው ውስጥ ወረቀትና እስክሪብቶ አውጥቶ እንዲህ ብሎ ፃፈላት
"ይቅርታ መናገርና መስማት የተሳነኝ ነኝ።
እባክሽን ማለት የፈለግሽውን ሁሉ እዚህ ወረቀት ላይ ፃፊልኝ።
:
"ልጅቷም ቀደም ብላ ስትነግረው የነበረውን ሁሉ ጽፋ ሰጠችው።
የህግ ባለሙያው ወረቀቱን ተቀብሏት በጥሩ ሁኔታ አጥፎ ኪሱ ከከተተው በኋላ ከተቀመጠበት ተነስቶ ጎርነን ባለ ድምጽ ምን ቢላት ጥሩ ነው
"አሁን እንደፈለግሽ መጮህ ትቺያለሽ።"
:
የታሪኩ ምግባር: ሰነድን በአግባቡ መያዝ ምን ግዜም
አስፈላጊ ነው።
@libmalet
@libmalet
