en
Feedback
የፍቅር ታሪክ (seenaa jalaala)

የፍቅር ታሪክ (seenaa jalaala)

Open in Telegram

ማስተዋል(mastewal) Fikirr @AASH23

Show more
The country is not specifiedThe category is not specified
2 842
Subscribers
+224 hours
No data7 days
+230 days
Posts Archive
*በጭስ ተደብቄ* የኔታ ፍቄ(ግጥም እና ፍቅር) ፡ በጭስ ተደብቄ ራሴን ሳቃጥል፣ ለብቻዬን ሆኜ ርቄ ከሰው መሀል፣ ፡ ያለፈን ትዝታ ከውስጤ ላወጣ፣ በጭስ ተደበኩኝ ደስታዬ ላይመጣ፣ ፡ እለኩሰዋለሁ ደግሜ ደግሜ፣ የሲጋራው ጫፍ በከንፈሬ ስሜ፣ በጭሱ ግርዶሽ ውስጥ እልፍ ተጋድሜ፣ ባይመጤ ትዝታ ክፉኛ ሰጥሜ፣ ባልታየ በሽታ ለማልድን ታምሜ፣ ፡ ታሪኬን በሙሉ የምረሳው መስሎኝ፣ የከንፈሬን ወዳጅ ለኩሳታለሁኝ፣ ፡ ከጢሱ መሀከል አንቺን ስፈልግሽ፣ ስምሽ ካፌ ውሎ ደግሜ ብጠራሽ፣ የለሽም እናቴ ኸረ ወዴት ገባሽ፣ ፡ አይኔ እኮ ተያዘ ሳል ተፈታተነኝ፣ እንደ ልጅነቴ እስቲ አይዞህ በዪኝ፣ እንደ ደጉ ጊዜ ትኩሱን አቅምሺኝ፣ ፡ ሀዘኔ ቢከፋ ውስጤን ቢያነድለው፣ በጭስ ተደብቄ ራሴን ቀብራለው፣ በሱስ ተነክሬ ከትላንት ሸሻለው፣ ፡ የእናቴ ምትክ ያልኳትንም ፍቅሬን፣ ቀልቧን ሌላ ገዛው ቀረሁ ለብቻዬን፣ ፈጣሪም አበዛው ከመረው ስቃዬን፣ ፡ ለማንም ሳልነግር በጭስ ተደብቄ፣ ህመሜ ሳይታይ ብቻዬን ማቅቄ፣ ፡ መኖር አያሰኘኝ፣ ነገም አይናፍቀኝ፣ የከንፈሬን ወዳጅ ብቻ ስማለሁኝ፣ ፡ እንደ ልጅነቴ ልክ እንደናቴ ጡት፣ ከከንፈሬ ውላ ታድራች ከኔ ጣት፣ ፡ ችዬ ላልሄድ ነገር ከትዝታ ርቄ፣ ኖራለሁ ዘመኔን በጭስ ተደብቄ፡፡ @libmalet @libmalet

ስናፍቅሽ ጊዜ ።።።።።።።።።። የናፍቆቴን መጠን ስፅፍልሽ ጊዜ ፎቶሽን እያየሁ ያገኘውሽ ያህል ዝም ብዬ ስቃለሁ። እንኳን ፎቶሽ ኖረኝ በቅርቤ አድርጎ ካንች ሚያተያየኝ። ፡ ፡ እያየውሽ ሳለ.. አጠገቤ ሆነሽ ታወሬኝ መሰለኝ ካለሽበት ቦታ መንገድ አሳብሬ በምናብ መጣሁኝ። ፡ ፡ እንዴት ነህ አንችዬ !? በቀን ቀኑን ሙሉ ባሳቤ የነገስሽ ባሳቤ የሞላሽ ታውቂው ነበር አይደል? ሳላገኝሽ ውዬ እንኳን ዝም ብለሽ እያየውሽ ሳለ መሄድሽን ሳስብ ት..ና. ፍ ..ቂ..ኛ..ለ..ሽ . . ንፍቅ። . . አንችዬ!? እንደው ከሰው መሀል ዓይኔ ከፈለገሽ ሌላ ምንም አይደል በዚህ በኔ ዓለም ስስት የሌለበት 'አንች መውደድ አለሽ'.. ፡ ታድለሽ! ፡ ፡ የኔ ሰው ጥላዬ አይግረምሽ እና ... ...አይግረምሽ እና አይኔ እንደቦዘዘ ስናፍቅሽ ጊዜ ቀን ዓመት ከሆነ ባለመምጣትሽ ውስጥ መጠበቅ የመታው አብሮነት ተነነ በኮንትራት ዓለም ከዚች እፍኝ ዕድሜ መኖርም ባከነ። ፡ ፡ በቃ ... ከመኖር አትጉደል ነብሴ አንችን ተጠምታ ዘመኗ አይጨልም ውበቷ አይደብዝዝ ነግቶ አይምሽባት ያንች መሆን ሽታ ፡ ፡ አንች የኔ ትላንት አንች የኔ ዛሬ አንች የኔ ነገ በናፈቅኩሽ ሰዓት ነፍስያዬ ጠርታሽ ካላሽበት ቦታ ምክንያት ሳታበዢ ቀን ሳትይ ወይ ማታ በናፍቆት ጠርቼሽ፤ ተራራውን ምሰሽ በፍቅር ተራምደሽ ፤ቁልቁለቱን ወርደሽ እምነቴን አልብሼሽ ፤ዳገቱን ፊት ነስተሽ በፅናት መሰላል ወንዞቹን አቋርጠሽ ፡ ፡ ነይ ...ፎቶሽን ቀይሪ በአካል ተገኝተሽ። ለምወድሽ @libmalet @libmalet

​​እናትዬ 🤰🤰🤰🤰🤰🤰🤰🤰🤰🤰 ምሳሳላት አለች አይቼ ማልጠግባት አኑርልኝ እያልኩ ዘውትር ማነባላት ከዕድሜ ግማሹን ተችሎ ብሰጣት ቢያንስባት እንጂ እሷስ አይበዛባት ደስታዋን እያየሁ ደስታን እንዳገኝበት ጌታ ሆይ አኑራት... በመኖሯ ስላለ ..የኔ ሕይወት እናቴ የኔ እናት..... የሚገባሽ ነገር ምን ይሆን እላለሁ? ላረግሽልኝ ሁሉ ልመልስ እሻለሁ ከ9ወር ጀምሬ ማብቂያውን አጣለው ውለታሽ ተቆጥሮ ከቃላት በላይ ነው ፍቅርሽ እንዳይወዳደር ወደር እንኳ የለው እና እናትዬ .....እስኪ ምን ላርግልሽ? እኔ ፈልጌ አጣሁ.. ላንቺ ሚመጥንሽ፣ ወድሻለሁ ማለት መሰለኝ ሚያንስብሽ፣ መውደዴን በምን ..ልግለፅልሽ? እናትዬ.....እስኪ ምን ላርግልሽ? ውብ ቃላቶች ብደረድር...፣ አይችሉም ሊገልፁ ለሆንሽልኝ ነገር፣ እናቴ ምን ልናገር...፣ አጣሁ ቃል ፈልጌ ስላንቺ ልዘረዝር፣ ግን ወድሻለሁ ማለት ከገለፀ ፍቅር፣ ወድሻለሁ ብዬ በቃል ብቻ አልቅር፣ የሚገባሽን ሁሉ ላሳይሽ በተግባር። እናትዬ ..እስኪ ምን ላርግልሽ? የሚመጥን ካለ.. ለውለታሽ ምላሽ @libmalet @libmalet

እንደምነህ እግዜር ሰማይ ቤት እንዴት ነው እመጣለሁ ብለህ ቆየህሳ ምነው ? እኛማ ..... ለእልፍ አላፍ አለቃ ማመልከቻ ፅፈን ለወፈ ሰማይ ህዝብ መድረክ ላይ ለፍፈን ፆለት ቤታችንን እኛው ላይ ቆልፈን የምድር አተካራ ህግጋቱን አልፈን ደብዳቤ ላክንልህ፤ አይንህን ካየነው ሁለት ሽ ዘመን እንደቀልድ አለፈ የመምጣትህ ተስፋ እየኮሰመነ መቅረትህ ገዘፈ ... እንደውም እንደውም ... ‹‹በእመጣለሁ ተስፋ ሁለት ሽ ዘመን ቀጥሮን ከጠፋ በቀጠሮው ሰአት መምጣት ከተሳነው እግዜር አበሻ ነው›› እያሉ ያሙሃል እኔ ምን አውቃለሁ ... አመስግነው ሲሉ እልልታ የማቀልጥ ቃሉን ስማ ሲሉኝ ...ሰባኪው እግር ስር በደስታ እምቀመጥ እግዚኦ በሉ ሲባል ...እንባየን የማፈስ ሃሌ ሉያ ሲሉኝ ...በሳቅ ልቤ እሚፈርስ ምናምኒት እውቀት ውስጤ ያልፀደቀ እንበረከክበት ጉልበቴ ያለቀ እኔ ምን አውቃለሁ ... ግን አንተ ደህና ነህ ? ከምር እንደሚያሙት ምፅአት ቀረ እንዴ ? የሰናፍጭ ቅንጣት ታክል ጥርጣሬ አትከፋም አንዳንዴ ! ከሆነስ ሆነና ሰማይ ቤት እንዴት ነው አብረሃም ሰላም ነው ... እዛስ ቤት ገነባ ዛሬም በድንኳን ነው ? እኛማ ይሄውልህ ... በቤት ኪራይ ችንካር እየተሰቀልን ‹‹ኤሎሄ›› እንላለን ጎጆ እንድጥልልን .... ወደላይ ገነባን ወደጎን አሰፋን ወደላይም ከላይ ወደጎንም ከጎን እንደጉድ ተገፋን ቤት ለእንግዳ ማለት ጭራሹኑ ጠፋን !! አባታችን ሙሴ እነዴት ነው ለክብሩ ውቂያኖስ መክፈያው ደህናናት ብትሩ ? እኛማ ይሄውልህ .... እንጀራ ፍለጋ ባህር ስናቋርጥ የተስፋዋን ምድር አሸዋ ሳንረግጥ የትም ውሃ በላን የትም አሳ ላሰን ን ገ ር ል ን ና ብትሩን ያውሰን .... እናልህ እግዜር ሆይ .... ከተስፋዋ ምድር ወደሌላ ተስፋ አለን እየኳተን መሄጃው ሲገርመን መመለሻ መንገድ መቆሚያ ቦታ አጥተን ...! ላባታችን ሙሴ እንደምትልልን ... ‹‹የመሄድ ዘመን ነው ባህር የመሻገር ‹‹ዱላህን ላክልን›› ብሎሃል በልልኝ ... ሰማይ ቤት እንዴት ነው ? ....ዳዊትስ ደህና ነው ? ዛሬም ይዘምራል ...ዛሬም ይፎክራል ? ሰላም ነው ጠጠሩ .... ሰላም ናት ወንጭፉ ? እዛስ አቅል ገዛ ጎሊያድ ተራራው ጎሊያድ ግዙፉ ? እልፍ አላፍ ጎሊያድ ከቦን ሲደነፋ ወንጭፉን ጠቅልሎ ምነው ዳዊት ጠፋ ? ብሎሃል በልልኝ !! ለረከሰ ጠጠር ለሞላ ወርዋሪ ‹‹ወንጭፍህን ስጠው ለዚህ ታሪክ አውሪ›› ብለህ እዘዝልን !! እንዴት ነህ ጌታ ሆይ ... ሰማይ ቤት እንዴት ነው ? የሙሴ አልጋ ወራሽ እያሱ ሰላም ነው .... ያቆማትን ፀሃይ ግቢ ቢላት ምነው ... ያው እንደምታውቀው አስራ ሶስት ወራት ነው ፀሃይ የምንሞቀው ... ኧረ ፀሃይ በዛ ኧረ ፀሃይ በዛ ኧረ ፀሃይ በዛ የመጣው ወር ሀሉ ፀሃይ እያዘለ የተሸመው ሁሉ ‹ፀሃይ ነኝ› እያለ የአስራ ሶስት ወር የግዜር ፀሃይ የአስራ ሶስት ወር የሰው ጀምበር ባቃጠላት ምድጃ አገር ምን ታምር ሊኖር ይችላል ፀሃይ ሁኖ እንደመፈጠር .... ኧረ እግዜር በናትህ .... ኧረ እግዜር በናትህ ...በጭንቅ አማላጇ ባዘለህ ጀርባዋ ባቀፉህ እጆቿ ወይ ዝናብ ላክልን ወይ ዝናብ ሁነህ ና ሙቀት ገደለና ! እናልህ እግዜር ሆይ ማጣፊያው አጥሮናል ስም ያለው ሞኝ ነው ሁሉም ይጠራናል ... ጳውሎስ ሲሉን ...አቤት ጴጥሮስ ሲሉን ...ወይየ ይሁዳ ሲሉንም አቤት እንላለን ስማችንን ሸጠን ...ሰላሳ ጭብጨባ እንቀበላለን ተወው የኛን ነገር ...ሰማይ ቤት እንዴት ነው .... ሂዋንስ ደህና ናት ? ያው የልጅ ልጆቿ በእግሯ ተተክተው የፍሬው ሲገርምህ ግንዱንም አንክተው ለፍጥረተ አዳም ባይኑ ያገምጡታል ሰይጣንም ደህና ነው ኑሮ ተስማምቶታል .... ሰውን ለማሳሳት ላይ ታች ማለት ትቷል ሳይጠራው የሚጎርፍ ህዝብ በዝቶለታል ...! ኧረ እግዜር በናትህ በጭንቅ አማላጇ ባዘለህ ጀርባዋ ባቀፉህ እጆቿ ወይ ዝናብ ላክልን ወይ ዝናብ ሁነህ ና ሙቀት ገደለና !! @libmalet @libmalet

*አፍቅሬ ያጣሁሽ* ፡ አፍቅሬ ያጣሁሽ ያልሰመረው ህልሜ፡ ብመኝሽ ያልመጣሽ ደግሜ ደግሜ፡ ዞረሽ ያላየሽኝ ተሰባብሮ ቅስሜ፡ መጥተሽ ያላደሽው ባንቺ ታምቶ ስሜ፡ ፡ ልቤን አሳጥተሽ የፍቅርን ምላሽ፡ በባዶ ሸኘሽው ላይ ታች አንከራተሽ፡ እኔ ነኝ ምስኪኑ አፍቅሬ ያጣሁሽ፡ ፡ አይኖቼ አልቦዘኑም አልደከሙም ለ እንባ፡ ሙሾ አወርዳለው እጄ ላትገባ፡ ቀኑ አልነጋ አለኝ ቀትር ጨልሞብኝ፡ ምሽቱም ከሲኦል እኩያ ሆኖብኝ፡ መኖር ልክ እንደ ሞት መስሎ እየታየኝ ፡ ከላዬ ላይ ይውረድ ጨርቄ ምን ያረጋል፡ አልግባ ከቤቴ ካደባባይ ልዋል፡ ሰንደል በፀጉሬ ኮተቱን በእጆቼ፡ ቆሻሻን ወድጄ ንፁውን ጠልቼ፡ ፡ በዛጋ እንዳትሄጂ ተይ እብድ አለ ካሉሽ፡ ስለማንም አይደል ላንቺ የነገሩሽ፡ እስካሁንም ድረስ በእብደት የማፈቅርሽ፡ እኔው ነኝ፡ እኔው ነኝ ውዴ ሆይ አፍቅሬ ያጣሁሽ፡ ስለማንም አይደል ላንቺ የነገሩሽ፡፡ @libmalet @libmalet

I like it when you smile. But I love it when I'm the reason.
I like it when you smile. But I love it when I'm the reason.

ለጠቅላላ ዕውቀት... 1- የአለማችን ትልቋ ሀገር ሩስያ ስትሆን 17.09 ሚሊየን km2 የሆነ የቆዳ ስፋት አላት:: 2- በአለማችን ላይ በርሀማዋ ሀገር ሊቢያ ስትሆን ከአጠቃላይ የቆዳ ስፋቷ 99% የሚሆነው በረሀማነት የሚፈረጅ ነው:: 3- በአለማችን ላይ ምንም አይነት ወንዝ የሌላት ሀገር ሳውድ አረቢያ ነች:: 4- ለሴቶች የመምረጥ መብትን ቀድማ የሰጠች ሀገር ኒውዝላድ ነች:: 5- አሜሪካ በአለማችን ላይ ብዙ ክርሰቲያኖች የሚኖሩባት ሀገር ስትሆን ከአጠቃላይ የህዝብ ብዛቷ 245.9 ሚሊየን የሚሆኑት ክርሰቲያኖች ናቸው: 6- ብዙ የሆነ የእስልምና ሐይማኖት ተከታይ ህዝብ ያላት ሀገር ኢንዶኔዢያ ስትሆን ከ209 ሚሊየን በላይ የሚሆነው ህዝቧ ሙስሊሞች ናቸው:: 7- በአለማችን ላይ ከፍተኛ የሆነ የሀይቅ ብዛት ያላት ሀገር ካናዳ ስትሆን ወደ 3 ሚሊየን የሚጠጉ ሀይቆች ሲኖራት ይህም በአለማችን ላይ ካሉት የሀይቆች ብዛት 60% ይሸፍናል:: 8- በአለማችን ላይ ከፍተኛ የሆነ የግድያ ወንጀል የሚፈፀምባት ሀገር ኤል ሳልቫዶር ስትሆን በአማካኝ ከ100,000 ሰዎች ውስጥ 55.5% የሚሆኑት ግድያ ይፈፀምባቸዋል:: 9- በሀገሯ ፓርላማ ውስጥ ከፍተኛ የሆነ የሴቶች ቁጥር ያላት ሀገር ሩዋንዳ ስትሆን በፓርላማዋ ካሉት ጠቅላላ መቀመጫዎ ውስጥ 56.3% (50/80) የሚሆነው የተያዘው በሴቶች ነው:: 10- ዴንማርክ በአለማችን ላይ አነስተኛ የሆነ የሙስና ወንጀል የሚፈፀምባት ሀገር ናት:: @libmalet @libmalet

❖ # ሀብታም_ሁን_ብለሺኝ ❖❖ ''''''''➲➲ ➲➲ ➲➲''''''''' ...•••••••••••••••••••••••.... ፡ አንቺ አመለኛ ሲያቀብጥሽ አዘሽኝ፣ “ፍቅር ሀብት አይሆንም ሀብታም ሁን” ብለሽኝ ልብሽን ለማግኘት ግድ ሆኖብኝ ጥሪት፣ ባፈቀረሽ ልቤ ሀጥያት ሰራሁበት፡፡ አለኝ ያልኩዋት ሀብቴ ልሰጥሽ ያሰብኳት ንፁህ ድንግል ነብሴን ሳላውቅ አሳደፍኳት ለወከባ ኑሮ ለቁስ ውበት ሸጥኳት ያልሽኝን ለመሆን ስሮጥ የትም ጣልኳት፡፡ . . ምኞትሽን አሳምሬ ምኞቴ ከሸፈ ሀብት በሩን ሲከፍት ፍቅር ግን ቆለፈ፡፡ በዓመታት ስፍር አዱኛ ቀረበኝ የተመኘሽው ሀብት ይኸው ከጄ ገባ፡፡ ፊቴ ፈክቶ ታየ ደረቅ ወዜም ሰባ፡፡ ግና ምን ያደርጋል…. ግና ምን ያደርጋል… ግና ምን ያደርጋል… “ፍቅር ሀብት አይሆንም ሀብታም ሁን” እንዳልሽኝ በፍቀር አስምለሽ ቃል እንዳስገባሽኝ፣ ሀብታም ሆኜ ሳይሽ ገንዘብ ይዤ ሳይሽ፣ ያ የደማሁለት ያ የቆሰልኩለት ውብ ወጣትነቴን እንደ መስዕዋት በግ አጋድሜ አርጄ እልፍ የገበርኩለት፣ ውበትሽ ሊስበኝ ገላሽ ሊያማልለኝ ሳቅሽ ሊማርከኝ ጫወታሽ ሊገዛኝ፣ ቃናሽ ሊናፍቀኝ ፈፅሞ አልችል አለ፡፡ አዱኛ ሲቀርበኝ ሀብት ደጄን ሲረግጥ ልብሽ ልቤን ጥሎ ጠፋ ኮበለለ፡፡ ዜማዬ ተለየ ድምፄም ተቀየረ ምንሽም ከምኔ አልገጥምልህ አለ፡፡ . . ባልጠፋ ውለታ ውለታ ላይሆንሽ ከውለታ ቆጥረሽ ቃል አስገብተሽኝ፣ ፍቅር ሀብት አይሆንም ሀብታም ሁን ብለሽኝ ያልሽውን ለመሆን አይሆኑትን ስሆን የህልምሽን ሆኜ ላገኝሽ ስባክን፣ መልክሽ ተሰወረኝ አጣሁሽ አጣሽኝ፡፡ እናም ጎዳናችን ላይገጥም ጠመመ ፍቅራችን ገረጣ ተስፋችን ታመመ፡፡ ህልምሽ ህልሜን ራቀ ሀቁ ተከፈነ ፈቅደን ተጠፋፋን ዕድሜያችን ባከነ፡፡ ትናንት ለሚወድሽ ለዚያ ምስኪን ወጣት ትናንት ለሚያፈቅርሽ ለዚያ ብኩን ወጣት፣ “ፍቅር ነው ሀብታችን አምነን ከለበስነው ጥሪት ቢያስፈልግም ካልቀደምክ አንበለው፡፡” ብሎ ለሞገተሽ ሞግቶ ላልረታሽ ፍቅር አስቀድሞ ወዶ ለታዘዘሽ፣ ለዚያ ንፁህ ወጣት ይቅርታሽን አርጊ፣ ቁስ ተራ ተቀብሯል ለሀውልቱ አትስጊ፡፡ እርሜን አውጥቻለሁ በይ እርምሽን አውጪ፡፡ የሳቅ ዕድሜሽ ይጠር ላዘን እጅ ስጪ፡፡ @libmalet @libmalet

We fall in love by chance. We stay in love by choice.
We fall in love by chance. We stay in love by choice.

ባሌ ብለሽ ጥሪኝ . . ያኔ ትንሽ ነበርኩ አንቺ ግን ኮረዳ ውበትሽ የሚያጓጓ እንቡጥ ጽጌረዳ እኔ ለጋ ነበርኩ ጨቅላ አንድ ፍሬ መንደሩን ማካልል በማይዝለው እግሬ አንቺ ወጣት ነበርሽ የማለዳ ፀሀይ ጎበዝ ሚፈዝልሽ ፍል ውበትሽን ሲያይ እኔ ጮርቃ ነበርኩ ጭቃ የማቦካ ህፃን ትንሽ ፍጥረት ውበት የማለካ አቧራ ለብሼ መሬቱን ስቆፍር ከመሰሎቼ ጋር ስዘምር ስጨፍር መንደሩን ሳካልል በሽቦ መኪና ድንገት ብቅ ያልሽ እንደው ፊትሽ ይፈካና ባሌ እንዴት ነህ ብለሽ አቅፈሽ ስትስሚኝ በትኩስ ከንፈርሽ አንገቴን ስትበይኝ ልብሴ እንኳ ቆሽሾ በጭቃ በአቧራ ብድግ አርገሽ አቅፈሽ ስትስሚኝ ስፈራ አንቺን ያየሁ እንደው እንዲያ ስርበተበት ትቼሽ የምሸሸው ጠፍቶኝ ምገባበት ደግሞም ስናፍቅሽ እናቴን ፈልገሽ ደህና ነው? ስትያት ባሌ ጠፋ ብለሽ በእናቴ ቀሚስ ስር እኔ ተከልዬ ጥላሽ እስኪርቀኝ ድምፅሽ ከጆሮዬ ውስጥ ልብስዋን ይዤ ትንፋሼን አምቄ ሳሳልፍሽ ያኔ በእማ ተደብቄ። ትዝ ይልሽ እንደሆን ልጅ እያለው እኔ ውለሽ የማታድሪው ሳትስሚኝ ያኔ አብሮሽ ላለ ሁሉ ስታስተዋውቂኝ ባሌ አደገ ብለሽ በስስት ስታይኝ ላንቺ ሱስሽ ሆኜ እኔ አንቺን ስፈራ ሚስትህ ባልሽ ብሎ ሰፈሩ ሲያወራ በዘመን ሀዲድ ላይ አመታት ነጎዱ በአካልሽ በአካሌ ብዙ ለውጦች ሄዱ ሰውነቴ ሞላ አበበ ጎመራ በአንቺ ውብ ገላ ላይ የእድሜ ድር ተሰራ ሙቅ ገላሽ በረደ ማምሻሽ ጀማመረ በጉንጭ እና አይንሽ ስር መስመር ተሰመረ ጡቶችሽ ወደቁ ጥቁር ፀጉርሽ ነጣ የሚያፈዘው ገፅሽ በእድሜ እሳት ተቀጣ ዘመን ጨክኖብሽ ይሄ ሁሉ ሆኖ የእድሜ እሳት ቢፈጅሽ ትላንትናሽ በኖ ዛሬም በልቤ ላይ ትዝታሽ ታትሞ ማለዳሽ በውስጤ በአንጀቴ ተቀልሞ ያኔ በጠዋቱ ድምፅሽ በጆሮዬ ከነፍሴ መሽጎ የፍቅርሽ ምርኮኛ እስረኛሽ አድርጎ የንጋት ውበትሽ በአይኔ ስር ተስሎ ካንቺ በቀር ሌላ እንዳላይ ከልሎ ታማሚ አርጎኛል ምስኪን መፃተኛ ስላንቺ ሳላስብ ፍፁም የማልተኛ የት እንዳለሽ ሳላውቅ አንቺን የምጠብቅ ዘመኔን የፈጀው ስላንቺ ስጠይቅ ሁሌም የምራብሽ ከጎኔ ሳትኖሪ የአመታት ህልሜ ነሽ ለአንድ ቀን ማትቀሪ ውዴ... መቼም ስለማልድን ድምፅሽን ሳልሰማ ባሌ ብለሽ ጥሪኝ ብትሆኚም እማማ። @libmalet @libmalet

እውነተኛ ፍቅር መሆኑን እንዴት አውቃለሁ? የሚከተሉትን ጥያቄዎች መልስ፦ 1. “እውነተኛ ፍቅርን” እንዴት ትገልጸዋለህ? ․․․․․ 2. “የወረት ፍቅርን” እንዴት ትገልጸዋለህ? 3. በሁለቱ መካከል ያለው ልዩነት ምን ይመስልሃል? ከላይ ያሉትን ጥያቄዎች ለመመለስ ያን ያህል አልተቸገርክ ይሆናል። ጉዳዩ አንተን የሚመለከት እስካልሆነ ድረስ በእውነተኛ ፍቅርና በወረት ፍቅር መካከል ያለውን ልዩነት መናገሩ ብዙ አይከብድህም። የምትፈልጋት ዓይነት ሴት ስታገኝ ግን ሁሉ ነገር ይለወጣል። በፍቅር ክንፍ ስለምትል ሌላ ነገር አይታይህም። ልብህ እስኪጠፋ ትወዳታለህ። ሆኖም እስቲ ቆም ብለህ አስብ፦ የያዘህ እውነተኛ ፍቅር ነው ወይስ የወረት ፍቅር? ይህን ማወቅ የምትችለው እንዴት ነው? መልሱን ለማወቅ እስቲ በቅድሚያ ለተቃራኒ ፆታ ያለህ አመለካከት ልጅ ከነበርክበት ጊዜ ጋር ሲነጻጸር ምን ያህል እንደተለወጠ እንመልከት። ለምሳሌ ያህል፣ ለሚከተሉት ጥያቄዎች ምን መልስ ትሰጣለህ? ● የአምስት ዓመት ልጅ እያለህ ስለ ተቃራኒ ፆታ ምን ይሰማህ ነበር? ● አሁንስ ስለ ተቃራኒ ፆታ ምን ይሰማሃል? ለእነዚህ ጥያቄዎች የሰጠኸው መልስ፣ የጉርምስና ዕድሜ ላይ ስትደርስ ለተቃራኒ ፆታ ያለህ አመለካከት እንደተለወጠ የሚጠቁም መሆኑ አይቀርም። የ12 ዓመቱ ብራያን “አሁን አሁን ሴቶች ልጆች ቆንጆ ሆነው ይታዩኝ ጀምሯል” ብሏል። የ16 ዓመቷ ኢሌይንም ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ለተቃራኒ ፆታ ያላት አመለካከት እንደተለወጠ ተሰምቷታል። እንዲህ ብላለች፦ “ጓደኞቼ በሙሉ ወሬያቸው ስለ ወንዶች ሆነ። እኔም ያየሁት ወንድ ሁሉ ይማርከኝ ጀመር።” ታዲያ አንተስ በዚህ ለውጥ የተነሳ በውስጥህ የሚፈጠረውን ኃይለኛ ስሜት መቋቋም የምትችለው እንዴት ነው? እንዲህ ያለውን ስሜት እንደሌለ አድርገህ መቁጠሩ ስሜቱ እንዲያይል ከማድረግ በቀር የሚፈይደው ነገር የለም፤ በሌላ በኩል ግን ይህን ሁኔታ በተቃራኒ ፆታ ስለ መማረክ፣ ስለ ወረት ፍቅር እንዲሁም ስለ እውነተኛ ፍቅር ለማወቅ እንደሚያስችል ግሩም አጋጣሚ አድርገህ ልትመለከተው ትችላለህ። ከፍቅር ጋር በተያያዘ እነዚህን ሦስት ነገሮች መረዳትህ ከብዙ ሥቃይ የሚጠብቅህ ከመሆኑም ሌላ ውሎ አድሮ እውነተኛ ፍቅር ለማግኘት ይረዳሃል። መማረክ → መልክ “እኔና ጓደኞቼ ሁልጊዜ የምናወራው ስለ ሴቶች ነው። ስለ ሌሎች ጉዳዮች እያወራንም እንኳ አንዲት ቆንጆ ልጅ በአጠገባችን ስታልፍ ወሬያችንን ሁሉ ረስተን ስለ እሷ ማውራት እንጀምራለን!”—አሊክስ “ዓይን ዓይኔን እያየ የሚያናግረኝ፣ ደስ የሚል ፈገግታ ያለውና ኮራ ብሎ የሚራመድ ወንድ ቀልቤን ይስበዋል።”—ሎሪ ቆንጆ ሴት ወይም መልከ ቀና ወንድ ሲያዩ መማረክ ያለ ነገር ነው። ችግሩ ግን የአንድ ሰው ውስጣዊ ማንነት እንደ መልኩ ላይሆን ይችላል። እንዲህ የምንለው ለምንድን ነው? ምክንያቱም መልክ አሳሳች ሊሆን ይችላል። መጽሐፍ ቅዱስ “በእርያ አፍንጫ ላይ እንደተሰካ የወርቅ ቀለበት፣ ማስተዋል የጐደላት ቆንጆ ሴት እንዲሁ ናት” ይላል። (ምሳሌ 11:22) ይህ አባባል ለወንዶችም እንደሚሠራ ጥርጥር የለውም። የወረት ፍቅር → ስሜት “በ12 ዓመቴ ከአንድ ልጅ ጋር ፍቅር ይዞኝ ነበር፤ ልጁን ለምን እንደወደድኩት የገባኝ የያዘኝ የወረት ፍቅር ሲለቀኝ ነው። ጓደኞቼ በሙሉ የሚያስቡት ስለ ወንዶች ነበር፤ እኔም ልጁን ወንድ ስለሆነ ብቻ ወደድኩት። በቃ ምክንያቴ ይኸው ነበር!”—ኢሌይን “ከተለያዩ ሴቶች ጋር የወረት ፍቅር ይዞኝ ያውቃል፤ በአብዛኛው የተማረክሁት መልካቸውን አይቼ ነው። ባሕርያቸውን ስመለከት ግን ያሰብኩትን ያህል እንደማንጣጣም ገባኝ።”—ማርክ የወረት ፍቅር ሲይዝህ እውነተኛ ፍቅር የያዘህ ሊመስልህ ይችላል። ለነገሩ እውነተኛ ፍቅር የያዘው ሰውም ቢሆን ለሚወደው ሰው የተለየ ስሜት እንደሚኖረው የታወቀ ነው። ይሁንና ለእውነተኛ ፍቅር እና ለወረት ፍቅር መፈጠር ምክንያት የሚሆነው ነገር ይለያያል። አንድ ሰው የወረት ፍቅር የሚይዘው በመልክና በቁመና ተማርኮ ነው። በተጨማሪም የወረት ፍቅር የያዘው ሰው የወደዳት ሴት ድክመት ፈጽሞ የማይታየው ከመሆኑም ሌላ ጠንካራ ጎኖቿን አጋንኖ ይመለከታል። በመሆኑም የወረት ፍቅር የባሕር ዳርቻ ላይ በአሸዋ ቁልል እንደተሠራ ቤት ነው፤ ብዙም ሳይቆይ ውኃ አጥቦ ይወስደዋል። ፊዮና የተባለች ወጣት እንዲህ ብላለች፦ “እንዲህ ያለው ፍቅር አይዘልቅም፤ ዛሬ ከአንዱ የዛሬ ወር ደግሞ ከሌላው ጋር እንዲህ ዓይነት ፍቅር ሊይዛችሁ ይችላል!” እውነተኛ ፍቅር → እውቀት “እውነተኛ ፍቅር ሲይዝህ አንድን ሰው የምትወደው በቂ ምክንያት ስላለህ እንጂ ስለ ራስህ ብቻ ስለምታስብ አይደለም።”—ዴቪድ “እውነተኛ ፍቅር ቀስ በቀስ እያደገ የሚመጣ ነገር እንደሆነ ይሰማኛል። መጀመሪያ ላይ ከአንድ ሰው ጋር እንዲሁ ጥሩ ጓደኛሞች ልትሆኑ ትችላላችሁ። እያደር ግለሰቡን እያወቃችሁት ስትሄዱ ባሕርዩን ትወዱለታላችሁ፤ ከዚያም ቀደም ሲል ለዚያ ሰው ያልነበራችሁ ዓይነት ስሜት በውስጣችሁ ይፈጠራል።”—ጁዲት እውነተኛ ፍቅር የሚመጣው ስለ አንድ ሰው ጥንካሬና ድክመት በሚገባ ስታውቅ ነው። መጽሐፍ ቅዱስ ፍቅርን ከስሜት ጋር ብቻ አያይዞ የማይጠቅሰው ለዚህ ነው። መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይላል፦ “ፍቅር ታጋሽና ደግ ነው። . . . ሁሉን ችሎ ያልፋል፣ ሁሉን ያምናል፣ ሁሉን ተስፋ ያደርጋል፣ ሁሉን ነገር በጽናት ይቋቋማል። ፍቅር ፈጽሞ አይከስምም።” (1 ቆሮንቶስ 13:4, 7, 8) እውነተኛ ፍቅር የያዘው ሰው እነዚህን ነገሮች የሚያደርገው ጭፍን ስለሆነ ወይም ስለሚወደው ሰው ምንም ስለማያውቅ አይደለም፤ ከዚህ ይልቅ ስለ ግለሰቡ ማንነት የተሟላ እውቀት ስላለው ነው። የእውነተኛ ፍቅር ምሳሌ በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ የሚገኘው የያዕቆብ እና የራሔል ታሪክ እውነተኛ ፍቅር ምን እንደሆነ የሚያሳይ ግሩም ምሳሌ ነው። ያዕቆብ እና ራሔል መጀመሪያ የተገናኙት ራሔል የአባቷን በጎች ውኃ ልታጠጣ ወደ ውኃ ጉድጓድ በመጣችበት ወቅት ነበር። ብዙም ሳይቆይ ያዕቆብ በራሔል ተማረከ። የማረከው ምንድን ነው? ራሔል “ቁመናዋ ያማረ መልኳም የተዋበ” መሆኗ ነው።—ዘፍጥረት 29:17 ይሁንና ለእውነተኛ ፍቅር መሠረት የሚሆነው ነገር መልክና ቁመና ብቻ እንዳልሆነ አስታውስ። ያዕቆብ ከራሔል ውጫዊ ውበት ባሻገር ያየው ነገር አለ። መጀመሪያ ላይ በውበቷ ተማርኮ ነበር፤ ብዙም ሳይቆይ ግን ራሔልን ‘እጅግ እንደወደዳት’ መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራል።—ዘፍጥረት 29:18 የ1980 ትርጉም ታዲያ ታሪኩ በዚህ አበቃ ማለት ነው? በፍጹም! ያዕቆብ ራሔልን ለማግባት ሰባት ዓመት መጠበቅ እንዳለበት አባቷ ነገረው። የአባቷ ጥያቄ ተገቢ ሆነም አልሆነ፣ ይህ አጋጣሚ ያዕቆብ ለራሔል ያለውን ፍቅር የሚፈትን ነበር። ያዕቆብ የያዘው የወረት ፍቅር ከሆነ ይህን ያህል ጊዜ መጠበቅ አይችልም። በጊዜ ርዝመት ፈጽሞ የማይለወጠው እውነተኛ ፍቅር ብቻ ነው። ታዲያ ያዕቆብ ምን አደረገ? መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይላል፦ “ያዕቆብም ራሔልን ለማግኘት ሲል ሰባት ዓመት አገለገለ፤ አጥብቆ ይወዳትም ስለ ነበረ፣ ሰባት ዓመት እንደ ጥቂት ቀን ሆኖ ታየው።”—ዘፍጥረት 29:20 ከያዕቆብ እና ከራሔል ምሳሌ ምን ትምህርት ማግኘት ትችላለህ? እውነተኛ ፍቅር በጊዜ መርዘም አይቀዘቅዝም። በመልክና ቁመና ላይ ብቻ የተመሠረተም አይደለም። እንዲያውም ጥሩ የትዳር ጓደኛ የምትሆንህ ምናልባ... @libmalet @libmalet

🙏ይቅርታ🙏 *አርፋጅ* የኔታ ፍቄ(ግጥም እና ፍቅር) ፡ ለይቅርታ ቆየው ለበደል ቸኩዬ፣ ድንገት ገሸሽ አልኩኝ ልብሽን አቁስዬ፣ ፡ እንባሽ ተንከባሎ ፈሶ በጉንጭሽ ላይ፣ አገጭና እጅሽ ሆኖ ማይለያይ፣ ትካዜ በርትቶ መከፋት ባንቺ ላይ፣ አይንሽ ሲርገበገብ ካ'ንድ ቦታ ተክሎ አንድ ነገር ሳያይ፣ ከንፈርሽ ሲያወጋ ከሰው እንዲወያይ፣ ተዝ ይለኛል ዛሬም ያኔ ያየሽው ስቃይ፣ ፡ ማቅ ጨርቅሽን ቀደሽ ሆነሽ እንዳበደ፣ ሰው ሁሉ ባንቺ ላይ ስለኔ ፈረደ፣ ያላወቀው ጉዴን እኔን አፀደቀ፣ አላፊዋን አንቺን በፍርድ አስወደቀ፣ ፡ ከነሱ ሆታ ጋር ልቤ ተሰደደ፣ ጥፋቱን ሸሽጎ ባንቺ ላይ ፈረደ፣ ፅድቅን ተከናንቦ ሊኮንን ወደደ፣ ፡ እንደ ቅዱስ ካህን ሀጥእ እንደሌለው፣ ሌት ተቀን በእግዜር ፊት እንዳሸበሸበው፣ እውነተኛ ባሪያ የሆነ መሰለው፣ ፡ ግን እውነት ቆይታ ስታበራ ውስጤ፣ በሌለብሽ በደል አንቺን መኮነኔ፣ ፡ ሲገባኝ እውነታሽ ሆንኩኝ እንዳበደ፣ ውዴ ባክሽ ማሪኝ፣መጣው ከረፈደ፡፡ @libmalet @libmalet

ግጥም እና ፍቅር-የኔታ ፍቄ: *ኔጋን**(ልዑል ሀይሌ) ጥርስሽን ደብቂው ለማንም አትሳቂ የማንም አላፊ ቀኑን አታድምቂ . አፍሽንም ዝጊው አንድም ቃል አያውራ ካላፊ ካግዳሚው አንድም ስም አይጥራ . .. ፀጉርሽን ሸፍኚው አንድም ሰው አይየው ከዞማነት ይልቅ መላጣሽ ይታየው . ሰፊ ቀሚስ ልበሽ ዳሌሽን ደብቂው የጎረምሳ መዓት አንገት አይሰበር አይኖቹን አርቂው .. የጋን መብራት ሁኚ . ህዝብ አዳሙን ተይው ጋኑ ብቻ አብሪለት ፀሐይ ለማይደርሰው ለጠቆረው ቤቱ ብርሃንን ሙይለት .. ብዬ ስማፀንሽ ቃሌን አክብረሻል የብቻዬ መብራት ፀሐዬ ሆነሻል .. ተመስገን! . . ፈጣሪ ፈቅዶልኝ ለኔ ፀሐይ ምትሆን አንድ መብራት ቢያገኝ አንቺ እንድትኖሪበት እኔን ጋን አረገኝ፡፡ ግጥምዎን ለመላክ @AASH23 @libmalet @libmalet

"if you ever fell in love... Fell in love with someone who wants to know your favourite colour and just how you like your cof
"if you ever fell in love... Fell in love with someone who wants to know your favourite colour and just how you like your coffee. Fell in love with someone who love the way you Laugh and would do absolutely anything to hear it. Fell in love with someone who put their head on your chest just to hear your heartbeat, fell in love with someone who kisses you in public and is proud to show you off to anyone they know. Fell in love with someone who makes you a question why you where afraid to fell in love in the first place. Fell in love with someone who who falls in love with your flaws and think youre perfect just the way you are. Fell in love with someone who thinks that you're the one they love to wake up to each day."

ቆንጆ ነኝ (በላይ በቀለ ቀያ) . ስላንቺ ቁንጅና ስላንቺ ቁመና ከንፈር እና ዳሌ ጥርስና ተረከዝ ፣ ፀጉር ገለመሌ ለጡት ለወገብሽ ፣ ለፀባይሽ ጭምር በግጥም በዝርው ፣ ባድናቆት ስዘምር እስከዛሬ ድረስ... ውበትሽን አግንኜ ፣ ሰርክ መለፈፌ እኔ ስለራሴ ... አንዳች ቀን እንኳን ፣ ግጥም አለመፃፌ ሲትጠዪኝ ቆጨኝ ቢሆንም ቆንጆ ነኝ፡፡ ፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡ እርግጥ ነው ብዙዎች... ስለኔ ሳወራ ፣ ድንገት ያኮርፉኛል ያንተን ሌሎች ያውሩ ፣ ብለው ይነግሩኛል እኔን ከኔ በላይ... እርግጠኛ ሆኖ ፣ ሌላ እንዴት ያውቀኛል?! ።።።።፣፣ እናም እኔ ማለት... ቁመቴ ከአክሱም ፣ በእጥፍ ይረዝማል ጣፋጭ አንደበቴ... መስማት ለተሳነው ፣ ለስልሶ ይሰማል ውብ አረማመዴ... እንኳን መንገደኛን ፣ መንገድን ያቆማል፡፡ ፡፡፡፡፡፡ የከንፈሬ ወዙ ፣ ጥፍጥናው አያልቅም ጥርሴ ሺ ገዳይ ነው! ሺ ሟች ላለማየት ፣ ኗሪ ፊት አልስቅም፡፡ ከአይኔ ብሌን ውስጥ ፣ ብርሐን ይፈልቃል አይኔን ያየ ሁሉ ልቡን አሳውሮ ፣ በፍቅር ይወድቃል፡፡ ፡፡፡፡፡ የገላዬ ጠረን ፣ ከሽቱ እጥፍ ነው መልካም ጠረን ሁሉ... አለ ባሉት ስፍራ ፣ እኔ አለሁ ማለት ነው፡፡ ፀባየ ትሁት ነኝ ፣ ምጡቅ ነው እውቀቴ ግርማ ሞገሳም ነው ፣ ተክለ ሰውነቴ ያየኝ ይወደኛል የወደየኝ ሁሉ ፣ መቼም አይጠላኝም ከዚ በላይ እንኳን... ብዙም ስለራሴ ፣ የማውቀው የለኝም፡፡ እንደውም እንደውም... አልጎርርም እንጂ ፣ ያፈር ሰውነቴን ፣ በቁንጅና አብየው ቆንጆ ማየት ሲያምረኝ ፣ ራሴን ነው ማየው፡፡ ብቻ ግን ቆንጆ ነኝ!!! @libmalet @libmalet

❤️❤️እረ ልስቅ ነው❤️❤️ ተማሪ👧 እና አስተማሪ👨‍🏫 አንድ ቀን አስተማሪው በማስተማር ላይ እያለ ጥያቄ ይጠይቃል 👨‍🏫፦ ጫጩት እና ዶሮ ከ30ኛ ፎቅ ላይ ይወድቃሉ፡፡ ዶሮዋ ትሞትና ጫጩቷ ትተርፋለች ፡፡ይሄ እንዴት ሊሆን ቻለ ተማሪዎች? 🙋:-እኔ ቲቸር እኔ እኔ 👨‍🏫፦እሺ 🙋፦ ጫጩቷ በራ ነው 👨‍🏫፦አይ 🙋፦ጫጩቷ እስፖንጅ ላይ ነው የወደቀችው 👨‍🏫፦ተሳስተሻል 🙋፦ ታዲያ መልሱ ምንድነው? . . . . . . . . . . . . . . 👨‍🏫፦ ጫጩቷ አክተር ሰነሆነች ነው 😂? @libmalet @libmalet

# ጥፋተኛው_ፍቅር " ያኔ ነው መጃጃል፤ያኔ ነው ሞኝነት፤ በፍቅርሽ ታውሬ፤አንቺን ያመንኩኝ 'ለት። ያኔ ነው የሞትኩት፤አፈር የከበደኝ፤ ፍቅርሽ በልቤ ውስጥ፤ያለቦታው ሲገኝ "'ወድሀለው"አልሽኝ፤ቃላትን መራርጠሽ፤ ማመን ማይታክተው፤ልቤም ተቀበለሽ፤ ከንፈሬን ስትስሚው፤ከንፈርሽን ስስመው፤ "ፍቅር ማለት እኮ የኔና የ'ሷ ነው"፤ እያልኩ አወራለው የፍቅርሽን ጥቅም፤ ጥሩነትሽን እንጂ ክፋትሽን አላቅም ፡ ዛሬ ግን አየሁኝ........ ........ ዛሬ ግን አየሁኝ፤የፍቅርን አይነት፤ አንዱን ማግኘት ሲሹ፤ያኛውን መሰዋት። ከኔ በፊት ኑሮሽ፤የፍቅርሽ አጋር፤ እሱን ለማስቀናት፤ጀመርሽ ከኔ ጋር፤ እኔ ግን አመንኩሽ፤መሰለኝ የእውነት፤ ከ'ሱ ያጣሽውን እኔ ለመስጠት፤ ግን....ውዴ ለምን ?? ሂይወት ሲሳካልሽ፤ሀሳብሽ ሲሞላ፤ የቀድሞ ፍቅረኛሽ፤በንዴት ሲፈላ፤ ይቅር በይኝ ሲልሽ፤ስላየሽ ከሌላ፤ እኔን ጥለሽኝ ሔድሽ፤ከለመድሽው ገላ እንዳይድን አድርገሽ አረድሽው በቢላ ውበትሽ ሊስበኝ ገላሽ ሊያማልለኝ ሳቅሽ ሊማርከኝ ጫወታሽ ሊገዛኝ፣ ቃናሽ ሊናፍቀኝ ፈፅሞ አልችል አለ፡፡ ልብሽ ልቤን ጥሎ ጠፋ ኮበለለ፡፡ ዜማዬ ተለየ ድምፄም ተቀየረ ምንሽም ከምኔ አልገጥምልህ አለ፡ @libmalet @libmalet

ማራ ኪዬ: ይነበብ ይነበብ ኸረ ከ 21+🔞 አንዲት የ 19 አመት ልጅ በተደጋጋሚ ሲያስመልሳት አናትየው ታይና በመጠራጠር ሆስፒታል 🚑 ይወስዷታል እንደፈሩትም ልጅቷ የ1ወር እርጉዝ ናት 🙀 👴አባት ይህንን በሰሙ ጊዜ በጣም ይናደዱና 😡 ልጅቷን ጠርተው የዲቃላሽን አባት ማግኘት እፈልጋለሁ ደውለሽ በቶሎ ጥሪው 📞 ይሏታል ብዙም ሳይቆይ ከቤታቸው በረፋ ላይ ደማቅ ቀይ ፌራሪ መኪና ፓርክ አረገች 🚗 ከውስጧ አንድ መልከመልካም ዝንጥ ያለ ወጣት 👲ይወጣና ወደ አባትየው ቤት አንኳክቶ ይገባል! የተቆጡት አባት 😡 ከአስረጋዥ ተብዬ 😏 ጋር ተቀመጡና ማውራት ጀመሩ አባት👴፡ ልጄን ለምንድነው በዚች እድሜዋ አብረኻት የተኛኸው 😡? ወጣት፡ ይቅርታ አባባ ይሄ ይሆናል ብዬ አልጠበኩም ነበር 😔 አባት፡ እሺ ልጄን ማስተዳደር ትችላለህ 😳? ወጣት👲፡ ይቅርታ ልጆትን አሁን ማግባት አልችልም😔 አባት👴 ይሆን ጊዜ በንዴት ቱግ ብለው 😡 "አንተ ወሮበላ ባለጌ ውጣ ከቤ....." ብለው ሳይጨርሱ✋ ወጠት ረጋ ብሎ እንዲህ ይላል ወጣት👲፡ ግን ልጆት ሴት ልጅ ከወለደች ለመተዳደሪያ እንዲሆናት 20 ሚልዮን ብር💸 እሰጣታለሁ ወንድ ከሆነ ደሞ 20 ሚልዮን ብርና 💶 አንዱን ድርጅቴን እሰጣታለሁ!!!!! 🏗 ይሄን ሲል በቁጣ የጨሱት አባት ፊታቸው በደስታ ፍክት😁ይለና አባት👴፡ እሺ መንታ ቢሆኑስ? 😎😎😎😎😎 ወጣት፡ መንታ ከሆኑ ደግሞ ለያንዳንዳቸው 30ሚሊየን💸 ብርና አንዱን ድርጅቴን እሰጣለሁ አለ!😱 ? ያን ጊዜ አባት ከልክ በላይ ተደስቱ😃 ከዛ ወጣቱ በመሀል ምን ይላል👇 ወጣት👲፡ "ግን ልጁ ቢጨናገፋ ወይም ቢሞት ግን ምንም ነገር ከኔ አታገኙም "ሲል አባትየው ምን ቢሉ ጥሩ ነው . . . . . አባት፡ እሱ አያሳስብም ልጄ 😉 ልጁ ከተጨናገፈ ድጋሜ ትበ*ታለክ! ብለውት እርፍ 😂 @libmalet @libmalet

ለበደለህ ሰው ቅያሜህን ግለጥለት ፤ ቂመኝነት በክፉ መሸነፍ እንጂ ጀግንነት አይምሰልህ ። ፡ ከህሊናህና ከመንፈሳዊ አማካሪህ ሳትመክር ምንም ነገር አትወስን ፤ አጥርተህ ሳትሰማ ቃል አትግባ ። መከራ ካልደረሰ በቀር ባል በሌለበት ቤት ውስጥ ከሚስቲቱ ጋር ብቻህን አትቀመጥ ። : የሚበልጥህ ልኩራብህ እንዳይልህ ፣ ያነሰህ ልድረስብህ ብሎ እንዳያጠፋህ የሀብትህን ልክ እንዳታወራ ፤ በገዛ አፍህ ባንዱ ትከብራለህ ባንዱ ትቀላለህና። ፡ በጣም በማክበርህ እንዳታመልከው ፤ በጣም በመናቅህ እንዳታዋርደው ሠው እንዳንተ መሆኑን እወቀው ። ፡ የእኔ መናገር ምን ይለውጣል? ብለህም ስህተትን አትለፍ ፤ የእኔ አስተዋፅኦ ምን ይጠቅማል ? ብለህም ስጦታህን አትጠፍ ። ፡ መልካም ቃል ከስጦታ ይበልጣልና መልካም ቃል ተናገር ፤ ማንኛውም ስጦታ ከልመና ወንበር አያስነሣም ። የተስፋ ቃል ግን እንደሚያስነሣ አውቀህ ለሰዎች የተስፋ ቃል ስጣቸው ። ፡ ትምህርት ለዕውቀት ያዘጋጃል እንጂ ዕውቀትን አይጨርስም ። ዕውቀትህን የምትይዝበትን ሥነ-ሥርዓት ግን ያሳይሃል ። አእምሮህን ለማረቅ ትምህርት ፣ ሰውነትህን ለመግዛት ትዕግስት ፣ ከማንም ጋር ለመኖር ሥነ-ሥርዓት ያስፈልግሃል ። ለህሊናህ እረፍት ግን እምነት ያሻሃል ። ተከታይ ለማበጀት ደግሞ ግልጽ መሆንና ታማኝነት ግድ ይልሃል ። ፡ አንተው እውነትን ጠልተሃት ዘመኑ እውነትን ጠልቷል አትበል ። ዘመን እኔና አንተ ነን ፤ በራሱ ክፉና ደግ የሆነ ዘመን የለም። ፡ መልካም ምክር ብትሰማ ሕይወት ቀላል ይሆንልሃል ። ትክክለኛም ውሳኔ ከመልካም ምክር ነውና..!! አንብበው ለወዳጅዎ ካላካፈሉት እንዲሁም የተሰማዎትን ካልፃፉ ሲበዛ እራሥ ወዳድ ነዎት ማለት ነው!!!! @libmalet @libmalet