en
Feedback
የፍቅር ታሪክ (seenaa jalaala)

የፍቅር ታሪክ (seenaa jalaala)

Open in Telegram

ማስተዋል(mastewal) Fikirr @AASH23

Show more
The country is not specifiedThe category is not specified
2 842
Subscribers
+224 hours
No data7 days
+230 days
Posts Archive
1⃣፦ ሰዎች ምክንያት እየፈለጉ ጥፋተኛ ካደረጉህ ሊርቁህ እንደፈለጉ እየነገሩህ ነውና ከአንደበትህ አልፎ ውስጥህን የሚያዳምጥ አምላክ መቼም የትም እንዴትም ካንተ ጋር ነው። 2⃣፦ በህይወት ውስጥ ፈተና ከበዛብህ አትዘን ታገስ...የጨረቃ ውበት የሚጨምረው ጨለማ በዙሪያዋ በጨመረ ቁጥር ነውና። 3⃣፦ ጨለማን ጨለማ አያጠፋውም ጨለማን ማጥፋት የሚችለው ብርሀን ብቻ ነው፣ጥላቻን ጥላቻ አያጠፋውም፣ ጥላቻን ማጥፋት የሚችለው ፍቅር ብቻ ነው። @libmalet

*አፍቅሬ ያጣሁሽ* ፡ አፍቅሬ ያጣሁሽ ያልሰመረው ህልሜ፡ ብመኝሽ ያልመጣሽ ደግሜ ደግሜ፡ ዞረሽ ያላየሽኝ ተሰባብሮ ቅስሜ፡ መጥተሽ ያላደሽው ባንቺ ታምቶ ስሜ፡ ፡ ልቤን አሳጥተሽ የፍቅርን ምላሽ፡ በባዶ ሸኘሽው ላይ ታች አንከራተሽ፡ እኔ ነኝ ምስኪኑ አፍቅሬ ያጣሁሽ፡ ፡ አይኖቼ አልቦዘኑም አልደከሙም ለ እንባ፡ ሙሾ አወርዳለው እጄ ላትገባ፡ ቀኑ አልነጋ አለኝ ቀትር ጨልሞብኝ፡ ምሽቱም ከሲኦል እኩያ ሆኖብኝ፡ መኖር ልክ እንደ ሞት መስሎ እየታየኝ ፡ ከላዬ ላይ ይውረድ ጨርቄ ምን ያረጋል፡ አልግባ ከቤቴ ካደባባይ ልዋል፡ ሰንደል በፀጉሬ ኮተቱን በእጆቼ፡ ቆሻሻን ወድጄ ንፁውን ጠልቼ፡ ፡ በዛጋ እንዳትሄጂ ተይ እብድ አለ ካሉሽ፡ ስለማንም አይደል ላንቺ የነገሩሽ፡ እስካሁንም ድረስ በእብደት የማፈቅርሽ፡ እኔው ነኝ፡ እኔው ነኝ ውዴ ሆይ አፍቅሬ ያጣሁሽ፡ ስለማንም አይደል ላንቺ የነገሩሽ፡፡ @libmalet

በዝናብ ቅጠሪኝ አማልዱኝ ባልልም አስታራቂ ልኬ ባልማፀንሽም ፊትሽ ተንበርክኬ እንባዬ እንዳይታይ ከአንቺ ተደብቄ አነባለው ዛሬም ዝናብን ጠብቄ ልቤ በስቃይ ጣር ብሶቱን ሲያሰማ ሀዘኔ ተሰምቶሽ ልብሽ እንዳይደማ ቀኑ ጨላልሞብኝ ክረምቱ እስኪገባ መተሽ አጠይቂኝ ሆድሽም አይባባ ዝናብ የእኔን ብሶት ሀዘኔን ባያጥበው ሳለቅስ እንዳታይኝ እንባዬን ይጋርደው በጉንጭ የሚፈሰው ዝናብ እንዲመስልሽ ሁሌ ክረምት ይሁን ጉዳቴ አይታይሽ ውዴ ጥፋቴ ሲገባኝ ዛሬ ተመልሼ ነይልኝ አልልም ፊትሽ አልቅሼ አዲሱ ኑሮሽን ልረብሽ በእንባዬ በበጋ አልጣራም ናፍቀሺኛል ብዬ ሳለቅስ እንዳታይኝ ሁሌ በየአመቱ በክረምት ነይልኝ የናፈኩሽ እንደሆን ጉርምርምታው ሲብስ በዝናብ ጠይቂኝ አንቺን ያገኘው ዕለት ከንፈሬ ተላቆ ስስቅ እንዳታይኝ ቀን እየጨለመ ዕለት ዶፍ እየወረደ ዝናብ ውስጥ ጠብቂኝ ምንም እንኳ ፅኑ ብታይው እንባዬን @libmalet

፨፨፨ስለ ቤርሙዳ ትሪያንግል ፨፨፨ በምድር ላይ ካሉት ሚስጥራዊ ሥፍራዎች አንዱ የቤርሙዳ ትሪያንግል ነው፡፡ ቤርሙዳ ትሪያንግል በአንተርቲክ ውቅያኖሶች ውስጥ ይገኛል፡፡ ከአሜሪካ ፍሎሪዳ ግዛት ዝቅ ብሎ የሚገኝ ሲሆን በስተደቡብ በኩል የካሪቢያን ደሴት ያዋስነዋል፡፡ ይሄንን ጉደኛ ምስጥራዊ ስፍራ ለመጀመሪያ ያገኘው ክርስቶፈር ኮለምቦስ በ1449 እ.ኢ.አ አገኘ፡፡ ቤርሙዳ ትሪያንግል ባልታወቀ ሚስጥር በርካታ መርከቦች ፣ አውሮፕላኖች እና የሰውን ልጅ ህይወት እና ሀብት እንደያዙ ላንዴና ለመጨረሻ ግዜ ጠፍተዋል፡፡ ይህ ቦታ ዴቪልስ ትሪያንግል በሚል ቅፅል ስያሜ ይታወቃል፡፡ የቤርሙዳ ትርያንግል ሚስጥር ብዙ መላምቶች ተሰጥተዋል፡፡ ከዝህ በመቀጠል ከብዙ መላምቶች ውስጥ የተወሰኑትን ለማየት እንሞክር... 1⃣ከፍተኛ የሆነ የማግኔት መጠን በውቅያኖስ ውስጥ ሊኖር ይችላል 2⃣በውቅያኖሱ ውስጥ በከፍተኛ ፍጥነት የሚጓዝ ወንዝ ስላለ መርከቦችን ጠራርጎ ይወስዳቿል 3⃣ሁሪካን የተባለ አደገኛ አውሎ ነፋስ በአካባቢው ሊኖር ይችላል 4⃣ሚቴን ሃይድሬት የተባለ ንጥረ ነገር በባህር ውስጥ በከፍተኛ መጠን ስላለ የውሃውን እፍጋት (ዴንሲቲ) ይ ይቀንሰዋል፡፡ የውሃው ዴንሲቲ በሚቀንስበት ወቅት ውሃው መርከቦችን የመሸከም አቅሙ ስለሚወርድ መርከቦች በቀላሉ ይሰምጣሉ 5⃣ያልታወቁ በራሪ ፍጥረታት (UFO) በአከባቢው ሰፍረዋል 6⃣ሴጥያናዊ ቦታ ነው 7⃣ከፍተኛ የሆነ የማግኔትና ኤሌክትሮኒክስ ኃይል ያለው ዳመና በአከባቢው ሰማይ ላይ መኖር የመርከቦችንና የአውሮፕላኖችን እንቅስቃሴ ያግዳል 8⃣ከፍተኛ የማእከላዊ መሬት ስበት ያለበት ቦታ ሊሆን ይችላል የሚሉት ከመላምቶች ውስጥ ጥቂቶቹ ናቸው፡፡ ማጠቃለያ፡- አዲስ ጥናቶች እንደምያመላክቱ ደግሞ ቤርሙዳ የሚባልበት ቦታ ውሃ ውስጥ ራሱን የቻለ ተራራ ስላለ መርከቦች ከዛ ተራራ ጋር እየተጋጩ ይገለበጣሉ እንጂ ምንም አይነት የተለየ ሀይል እንደሌለ ቢናገሩም፡፡ እንደ እኔ እዝህ ላይ አንድ የሎጂክ ጥያቄ ማንሳቱ አግባብነት ያለው ይመስለኛል፡፡ እሱም ጥያቅዬ "መርከቦች በውሃ ላይ ተንሳፈው ስለሚጓዙ ሰመጡ እንበል ታድያ ለምንድነው አውሮፕላኖች የሚሰምጡት?" ብሎ መጠየቅ አግባብነት ያለው ይመስለኛል፡፡ ለዝህም ጥያቄ በአጭሩ ምላሽ "አውሮፕላኖች ሲሰምጡ መቼ እና እንዴት አየህ?" ከተባለ የእኔ ጥያቄ የሚሆነው ደግሞ "መርከቦች ሲሰምጡ ያየ አለ እንዴ?" በማለት የዛሬውን ፅሁፌን ልቋጨው፡፡ እውን ለመሆኑ እርሶ ስለቤርሙዳ ትርያንግል ምን ይሰማዎታል? @libmalet

ከልምዶች ሁሉ ጎጂ = ጭንቀት የሚያኮራ ስራ = ሰወችን መርዳት አስቀያሚ ባህሪ = ራስ ወዳድነት መጥፎ ልማድ = መስረቅ ትልቅ የተፈጥሮ ሀብት=ወጣትነት ትልቅ መሳሪያ = ብርታት መጥፎ ፀባይ = ይሉኝታ ቆንጆ ጌጥ =ፈገግታ አደገኛ ስብከት = አሉባልታ ትልቅ ስጦታ = ምክር የሰዉ ልጅ እንቆቅልሽ = ኑሮ አደገኛ መሳርያ = ምላስ ራስን የመጉዳት ዘዴ = ማልቀስ በሀይል የተሞላ ቃል = እችላለሁ ታላቅ ተስፋ = እኖራለሁ ዉድ ሀብት = እምነት ሀይለኛ የመገናኛ መሳርያ = ፀሎት ልንፈታዉ የሚገባን ችግር = ፍርሀት ዉጤታማ የእንቅልፍ ክኒን = የአእምሮ እረፍት መጥፎ የዉድቀት በሽታ = ከስህተት ይቅርታን አለመጠየቅ የህይወት ሀይለኛ ጉልበት = አእምሮ ከህይወት ልምዶች = የምድር ታላቅ ደስታ መስጠት … «ወዳጀ ሆይ» ትላንት ታሪክ ነዉና ተርከዉ!!! ዛሬ ቁምነገር ነዉና ተጠቀምበት!!! ነገ ምስጢር ነዉና ድረስበት!!! @libmalet @libmalet

#ቀለበት ምንድነው?? ምን ያደርግልሻል ቀለበት ማሠሩ፣ ልብሽ ላይ ከሌለ መውደድና ፍቅሩ፣ የመውደድ ማህተም ልብ ላይ ከሌለ፣ የፍቅር ሰው ሆኖ ፍቅር ካላደለ፣ ፍቅርን ተቀብሎ ፍቅሩን ካላጋራ፣ ከልብ ውስጥ ገብቶ ፍቅር ቤት ካልሰራ፣ ጣትሽን ስላሰርሽ ቀለበት አጥልቀሽ፣ ፍቅሬን አገኜሁት ብለሽ ታወሪያለሽ፣ የፍቅር ቀለበት ልብ ላይ ነው ቦታው፣ ለነገር ለወሬ ቦታ የማይሰጠው፣ ምቀኛ ሸረኛ መቼም የማይረታው፣ የልብ ቀለበት ፍቅር በእውነተኛ፣ ተቀብሎ እሚሰጥ ይህ ነው እድለኛ፣ የጣት ላይ ቀለበት ቢያወልቁት ለሚወልቅ፣ ላይኖር ለዘላለም ከእጅሽ ላይጣበቅ፣ ከልብሽ ግን ያለው እውነታው ቀለበት፣ መቼም የማይጠፋ የፍቅር ተምሳሌት፣ ምን ያደርግልሻል ቀለበት በጣትሽ፣ እውነተኛ ፍቅር ከልብሽ ከሌለሽ፣ ፍቅርን ተቀብለሽ ፍቅርሽን ካልሰጠሽ፣ እምነት መተሳሰብ በአንች ላይ ካልታየ፣ በጣትሽ ቀለበት እያልሽው ውድዬ፣ አንተ ትብስ አንች መባባል ከጠፋ፣ ቀለበት ምንድነው ወድቆ ለሚጠፋ፣ የፍቅር ቦታው ልብና ተግባር ነው፣ የጣትስ ቀለበት ቢያወልቁት ጠፊ ነው፣ ፍቅር ቤቱን ሰርቶ ከልብ ካልኖረ፣ የመውደድ ቀለበት በልብ ካልታሰረ፣ ያወለቁት ለታ እንደወጣ ቀረ፣ ግን .... የመውደድ ሚስጥሩ የፍቅር ምስጥሩ ፣ የፍቅር ጣዕሙ የፍቅር ምግባሩ፣ የፍቅር ሰው ይዞ ለፍቅር ማደሩ ማሳሰቢያነቱ ቀለበትን ማሰር ፍቅርን እንደመግለፅ አድርገው ለሚያስቡ ይሁን!#እግዚአብሔር ልብና ልብን ይሰር @libmalet @libmalet

ወታደር ወታደርን ሲያፈቅር የሚፅፈው ግጥም የገላሽ መአዛ የባሩዱ ሽታ አይንሽ እስናይፐር ነው ከሩቅ የሚመታ እኔን ነጥሎኛል ከምወደው ጋንታ ምክኒያቷ አንቺ ነሽ ትጥቄን እንድፈታ

ውድ የፍቅር ታሪክ ቤተሰቦች ባለፉት ለተወሰኑ ሳምንታት ፕሮግራማችን በመቋረጡ ከልብ ይቅርታ እየጠየቅን ከዛሬ ጀምሮ ፕሮግራማችን ሙሉ በሙሉ የሚቀጥል ስለሆነ እንድትከታተሉን በአክብሮት እንጋብዛቿለን።

የዚች ሰበበኛ ምላሳችን እውነታዎች ===================== ✅ ምላስ ወሳኝ ነገር ነው መቅመሱን ተወውና መዋጡን ያለ ምላስ ከባድ ነው! ስለምላስ ትንሽ እውነታዎችን ልንገራችሁ። 👉🏼ያለ ምላስ ማውራት፣ ማጣጣም እና መዋጥ አይቻልም። 👉🏼በአፋችን ውስጥ ከሚኖሩት ባክቴሪያዎች ግማሽ ያህሉ የሚኖሩት ምላሳችን ላይ ነው። 👉🏼ከሴቶች ምላስ ይልቅ የወንዶች ምላስ እርዝመት ይበልጣል። 👉🏼የምላስ ጡንቻ በሰውነታችን ውስጥ: ከሚገኙት ጡንቻዎች ሁሉ ጠንካራው ነው። 👉🏼መደበኛው የሰው ልጅ ምላስ ቀለም ወደሮዝ ያደላ ቀይ ሲሆን፤ የምላስን ቀለም በማየት የዚያን ሰው የጤንነት ሁኔታ መገመት ይቻላል። 👉🏼ምላስ ለማጣጣም እርጥበት ሊኖረው ይገባል። ደረቅ ምላስ የጣዕሙን አይነት መለየት አይችልም። 👉🏼ልክ እንደጣት አሻራ ሁሉ የእያንዳንዳችን የምላስ አሻራ የተለያየ ነው። 👉🏼የዓለማችን ረጅሙ ምላስ ተብሎ የተመዘገበው ከጫፍ እስከጫፍ የ3 ነጥብ 86 ኢንች እርእመት ያለው ምላስ ነው። 👉🏼የዓለማችን ሰፊው ምላስ ደግሞ የ3 ነጥብ 1 ኢንች ስፋት ያለው ነው። 👉🏼ምላስ በጥርሳችን ላይ የሚቀሩ ምግቦችን ማፅዳት በመቻሉ የተፈጥሮ ንፅህና መጠበቂያ ይባላል @libmalet @libmalet

"Here's to all the places we went, and here's to all the places we will go. And here's to me, whispering again and again and
"Here's to all the places we went, and here's to all the places we will go. And here's to me, whispering again and again and again. I love you"💞

​​Love hard. Get your heart broken. Laugh. Cry. Suffer. Explore. Wear your scars with pride. Allow life to teach you in it mysterious ways. Risk it all. Put your heart on the line. Fall down. Get up no matter what. The only guarantee we have in life is that everything is going to change. So knowing that, you really should take that chance and got for it. ✨

sticker.webp0.25 KB

" ቆም ብለን እናስብ!" የሚለው ማሰብ ማቆም ትንሽ ጓደኝነት ላይ ዝርክርክ ስለሆንኩ እኔን የሚረዳኝ ሰው  እያጣሁ ተችግሬ አንድ ቀን " ቆሜ ማሰብ" ጀመርኩ ። ቆሜ የጠየቅኩት ጥያቄ እየሄደ " ከአንግዲህ ሰው በቃኝ" የሚል የቆመ መልስ ሰጠኝ። በመልሱ መቆም ስላልቻልኩ እየሄድኩ ማሰብ ስጀምር እኔን የሚረዳ  ሰው አገኘሁ።  ቆሜ ባሰብኩት የቆመ መፍትሄ "ሰው በቃኝ!" ብዬ ከሰው ጋር መኖር ማቆም ለኔ መፍትሄ አይደለም። ሰው ነኝ ከሰው ጋር መኖር አላቆምም። በአጋጣሚ በጓደኛዬ ፅሁፍ ላይ ስንወያይ ይሄ አሳብ መጣልኝ። ለማሰብ መቆም ያስፈለገው እየሄዱ ማሰብ አይቻልም? ሀ) ማሰብን አለማሰብ ህይወታችን ሁሉ የኩሬ ነው። የለውጥ ጅረት አይፈልግም። ሁሉም ተቋጥሮ መቆም አለበት። ራሳችን ችግር ስለሆንን በኩሬ ካልሆነ የሚፈታ ችግር የለንም። "የረጋ ወተት ቅቤ ይወጣዋል" ቅቤው ግን የእርጋታ ኩሬ  ሳይሆን የለውጥ መናጥ ነው። "የቆዬ ሰው ከሚስቱ ይወልዳል" ኢንቫሊድ! ከሚስቱ የሚወልደው በወሲብ የለውጥ ሂደት ነው። ይኼ ሁሉ "ከኩሬው ቆመን እናስብ" ለማለት ነው። ቆሞ ማሰብ ፣ ማሰብ ማቆም ነው። ለውጥ እየሄዱ በማሰብ መቆምን ከመሄድ ጋር  በማወዳደር ነው። ማሰብን ማሰብ። እነሱ ግን  ከቆምክበት ኩሬው እንዳትወጣ " ከድጡ ወደ ማጡ" ብለው ያስፈራሩሀል። ይሄ ካልሰራ ደግሞ " የማያውቁት አገር አይናፍቅም" ብለው እየሄድክ እንዳታስብ ያባብሉሀል። የማያውቀት አገር ካልናፈቀ፣ እኔም ካልሄድኩ የማውቀው አገር አይኖርም ማለት ነው። ካልሄድኩ አላውቀውም። ካላወቅኩት አልናፍቅም። ስለዚህ ለማሰብ የማሰብ ሂደት አስፈላጊ በመሆኑ ለማሰብ መራመድ እንጂ መቆም ግዴታ አይደለም። ለ)  ኢምፕሊኬሽኑ የአንድ አሳብ ጥንካሬ በነባራዊው ህይወት ተግባራዊ የመሆን አቅሙ ይል ነበር እንግሊዛዊው ፈላስፋ።  አውቄ ነው ራሴው ነኝ ያልኩት። ፈረንጅ ካልጠራሁ አታምኑኝም ብዬ ነው። ቆሞ የማሰብ መርሀችን ችግር እያመጣ ነው። እንደ ማህበረሰብ በተረጋጋ ሰላም ውስጥ ሆነን የብሔርና የሀይማኖት ክፍፍል ውስጥ ሆነን በክላሽ የምንጠበቅበት ምክንያት  ቆመንም ማሰብ አለመቻላችንን የሚያሳይ እውነታ ነው። ቆመን የምናስበው አለማሰብን በመሆኑ በቆምንበት የአገር ችግር እንሆናለን። አንደኛው የለውጥ መንገዱን በድንጋይና በግንድ ይዘጋል። ሌላው ቆሞ እየነገደ ዋጋ ይጨምርና አገሩ ላይ ይቆማል። ባለፈው ረሀብ ሲያሯሩጠኝ የሆነ ግሮሰሪ የምትመስል ቤት ገብቼ ምሳ እንዳለ  ጠየቅኩ። መቼም የአቅሜን የሚመጣጠን ቤት አይቼ በመግባቴ ብዙ ሳልጨነቅ ዱለት አዘዝኩ። ዱለቷ ስትመጣ በባትሪ እየፈለግሁ፣ በዱለት ፍሬ እየቆጠርኩ በላሁና ሂሳብ ስል "አምሳ ብር!" ክው ልል አልኩና ተውኩት። መጨረሻ እንዲቀንሱልኝ ተከራክሬ እምቢ ሲሉኝ አንድ ጥያቄ ጠየቅኩኝ። " ቆይ!  25 ፍሬ ያላት ዱለት አምጥተህ አምሳ ብር የምከፍለው በአንድ የዱለት ፍሬ ሁለት ብር ነው እንዴ?" አበሻ የሚያሰበው ቆሞ ስለሆነ በራሱ በአገሩ ላይ የቆመ ችግር ነው። ነጋዴው ቆሞ ሲያስብ ዋጋ ይጨምርና ሸማች ይንጫጫል። ሌላው ቆሞ ባሰበው የመንግስት ሰራተኛ ቢቀጠር ሙሰኛ ይሆናል። አበሻ ቆሞ ሲያስብ በብሔርና በሀይማኖት ይከፋፈልና ይናቆራል። ተቃዋሚው ቆሞ ያስብና ትዝ የሚለው የአገር ጉዳይ ሳይሆን አብዮት ማስነሳት ነው። አንድ አበሻ ተቃዋሚ ለአገራዊ ችግር መፍትሄ ከአብዮት ውጪ ማሰብ ከቻለ ምክንያቱ ሁለት ነው። ወይ ተቃዋሚው አበሻ አይደለም። ወይ አበሻው ተቃዋሚ ሳይሆን የገዥው ፓርቲ አባል ነው።  በኩሬ ውስጥ ሆነን ማሰባችን የሚፈጥረው ችግር የቆምንበት ኩሬ ላይ ችግር መፍጠር ብቻ ሳይሆን በእንቅስቃሴያችንም ላይ ችግር መፍጠሩ ነው። አበሻ ከኩሬው ውጪ ሌላ ውቅያኖስ እንዳለ ብታስተምረው እዛም ሄጄ ልቁም ነው የሚለው።  "ደቡብ አፍሪካ የምትገኘው በአህጉሪቱ በደቡብ በኩል ነው " ተብሎ ጂኦግራፊ ሲያስተምሩት አበሻ የሚማረው ደቡብ አፍሪካ ስለመሄድ ነው። አረብ አገር የሚሄዱ ሴቶች መብዛታቸውን ያዬ አንድ ጂኦግራፊ ቲቸር  የሴቶቹን ረጅም ሰልፍ አየና በቁጭት ምን ቢል ጥሩ ነው!? " ሳይቸግረኝ ኳታርና ኩዌትን አስተምሬ ስደተኛ ላብዛ!?" እሱ አገሯ ሰርታ ኳታርን እንድትፈጥር እንጂ ወደ ኳታር እንድትሰደድ አልነበረም ያስተማረው።  አበሻ ኩሬው ውስጥ ሆኖ የሚማረው ያለበትን ኩሬ ውቅያኖስ ስለማድረግ ሳይሆን ውቅያኖሱንም ኩሬ ለማድረግ ብቻ ነው። አንድ ጊዜ የሀይስኩል አስተማሪያችን ስለ ስዊዲን ህዝብ ስልጣኔ እያስረዳን ነበር። " ስዊድን በሞራል፣ በፖለቲካ የሰለጠኑ ህዝቦች ናቸው። እዛ ሌባ የለም።መስረቅ የለም። ሁሉም ታማኝ ነው።  ሂሳብ የሚጠይቅ የለም። " ብሎ ሲናገር አንዱ " እዛ ነበር መሄድ?" ብሎ ጠየቀ። ሌላው ምን ቢለው ጥሩ ነው!" እዚህም ሆነህ እኮ ሌባ አለመሆን ትችላለህ"! ችግር ለመቅረፍ ችግሩ የሌለበት ቦታ መሄድ አስፈላጊ አለመሆኑ ላይ ተነቃቁ። አሁንኮ ለአበሻ ኩሬን ለቆ መሄድ ችግር የለውም። ችግሩ ኩሬውን ለቆ ወደ ውቅያኖስ ሲገባ ማሰብ ያቆምና የሄደበት በራሱ ችግር ሆኖ ይቆማል።  አበሻ ኩሬውን ለመልቀቅ የሚንቀሳቀሰው ቆሞ የሚያስብበትን አለማሰብ ፍለጋ እንጂ እየተራመዱ ለመሄድ አይደለም። ቦታ ብንቀይርም አስተሳሰብ የማሰብ ለውጥ የለም። ተራመድን ከተባለ ቆሞ ማሰብ የሚችልበት ኩሬ መቀየር ነው። ያው ቆሞ ማሰቢያ ኩሬ ፍለጋ እንደኛ ስደተኛ የለም። ዘፋኙ፣ አርቲስቱ፣ ፀሀፊው፣ ሰአሊው፣ ከኩሬ ወደ ሌላ ኩሬ ይሰደዳል። አንዳንዱ እዛ ያለበት ኩሬ ሆኖ የለቀቀውን ኩሬ በፖለቲካ ትግል ስም ያምሳል። ሌላው ደግሞ እዚህ ያለነውን በየፈረንጁ አስፓልት ላይ " ኑኑ!" ይላል። አንዱ የአማረኛ ክሊፕ አየቶ የተናገረው "ኢትዮጵያዊ የሚሰደደው ክሊፕ ለመስራትና ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ብቻ ነው እንዴ!?" እንዳለው። እየሄዱ ማሰብ ካስተማረ መሰደድ እኮ ችግር የለውም። ችግሩ ስደትን የማቆም ቆሞ ማሰብ መሆኑ ነው። አሁንማ ተዋናዩ፣ ዘፋኙ ፣ ፀሀፊው ብቻ ሳይሆን ፓስተሩ  ፣ ቄሱ፣ ዘማሪው፣ ዳቆኑም  ሁሉም ወደ አሜሪካ መሰደድ ነው። እና አንዱ አዲስ አበባ የሚያውቃቸውን ፓስተሮች፣ አማሪዎች፣ ሰባኪዎች ጠቅላላ አሜሪካ ሲያገኛቸው በአግራሞት ምን ብሎ ቢጠይቅ ጥሩ ነው!?" ጀለሶች አገራችሁን ትታችሁ እዚህ የመጣችሁት እግዜር ሰፈር ቀየረ እንዴ?"  ከምር ዘፋኙ ጠቅላላ ወደዛ ሲሄድ ሙዚቃ ሰፈር የቀየረች ነው የሚመስለው። እዚህ ተዋናይና ዘፋኝ የምትጣራ ጥበብ እያለች ተዋናዩ ፣ ፀሀፊው ሲሰደድ  ጥበብ  ሰፈር የቀየረች ነው የሚመስለው። እግዜር የሚያስፈልገው ህዝብ ትቶ ፓስተርና ዘማሪ አሜሪካ ሲንጋጋ እግዜር ሰፈሩ ዲሲ ይመስላል። እና ቆመን ባሰብነው ልክ ቆመናል። ቆመን ብንቀሳቀስም ለለውጥ ሳይሆን ተመልሶ ለመቆም ነው። ማሰባችን አለማሰብ በመሆኑ ከ3ሺ አመታት በኋላ መድረስ የቻልነው ያኔም የቆምንበት ቦታ ነው። ቆመን ማሰባችን ያቆመው እኛ እንጂ እየሄደ የሚያስበውን ለውጥ አይደለም። የቀድሞ የኢትዮጵያ መሪ አሁን ስልጣን ላይ ቢሆኑ ኖሮ በብስጭት ሊናገሩት የሚችሉት ንግግር ይህን ይመስል ነበር።  " ብታምኑም ባታምኑም ቆመናል። እየሄድን ቆመናል" @libmalet @libmalet @libmalet Silatamachang

መራር_እውነታዎች • ምንም ነገር ለዘላም አይቆይም፡፡ ችግሮችህ፣ የከበቡህ ሰዎች፣ ስራህ፣ ትዳርህና ግንኙነቶችህ ሁሉ ለጊዜዉ ነዉ፡፡ የሁሉም ነገር ፍፃሜ የሆነ ቀን ላይ ሲሆን ታየዋለህ፡፡ በህይወቴ ሁሉ አብረዉኝ ይኖራሉ ያልካቸዉ ነገሮች እንኳን ሳይቀሩ ሲፈረካከሹ ታያቸዋለህ • ለሁሉም ነገር ተራ አለዉ፡፡ ሰዉን ብትጠቅም ጊዜዉን ጠብቆ አምላክህ ይከፍልሃል፡፡ ብትጎዳም እንዲሁ...በሰፈርከዉ ማንነት ጊዜዉ ሲደርስ ትሰፈራለህ • ማንም ሰዉ ስላንተ አይጨነቅም፡፡ 20 ፐርሰንቱ ብቻ ስላንተ ሲጨነቁ (እነሱም የቅርብ ጓደኞችህና ቤተሰቦችህ መሆናቸዉን አትዘንጋ) 80 ፐርሰንቱ ግን ኑር አትኑር አንዳች ቅንጣት ስላንተ አያስቡም፡፡ ችግሮችህን ለነዚህ ለ 80 ፐርሰንት መናገር እራስህን ማባከን ነዉ ምክንያቱም ችግርህ ለነሱ ምናቸዉም አይደለምና! የራሳቸዉ ጉዳይ ብቻ ያሳስባቸዋልና ቆጠብ በል • ሰዎች በህይወትህ ይመጣሉ ደግሞም ይሄዳሉ፡፡ አንድ ቀን ለብቻህ ሰዉ በሌለበት ልትሞት ትችላለህና ሰዎችን # አትደገፍ • ከ5-6 የልብ የምትላቸዉ ሰዎች በቀር ፌስቡክ ላይ ያሉት የጓደኛ ጋጋታ ምንም አይጠቅሙህም፡፡ ብትሞት እንኳ ቀብርህ ላይ የማይመጡ ብዙዎች መሆናቸዉን እወቅ • የስራ አለቃህ እንድታድግና የተሻለ ቦታ እንድትይዝ ሊመኝ ይችላል ግን መቼም እንድትበልጠዉ አይፈልግም፡፡ ምንም ሽልማትና ጭብጨባ ቢበዛልህ ከሱ እንደምትበልጥ ካሰበ አንተን ለመገፍተር ወደኋላ አይልም • 98 ፐርሰንቱ ሰዉ መቼ እንደተወለድክ እንኳን አያዉቅም(2 ፐርሰንቱ መቼም እነማን እንደሆኑ መገመት አያቅትህም)፡፡ ካላመንከኝ ሞክረህ እየዉ! • የዉሸት ጓደኞችህ የተሻለ ህይወት እንድትመራ በፍጹም አይፈልጉም፡፡ ነገሮች መልካም ሲሆኑ የሚሰበሰቡ ሰዎች ሊያስገርምህ አይገባም! አንድ ቀን ህልምህ 'ወለም' ብሎ ካዩ እጃቸዉን ቀስረዉ ይስቁብሃል፡፡ የዛኔ ያልሳቁብህን የልብ ጓደኞችህ አድርጋቸዉ • ገንዘብ ያለዉና ፀዳ ብሎ የሚመላስን ሰዉ ብዙዎች ሲያከብሩት ትመለከታለህ ፡፡ የማያዉቅህ እንኳን ቢሆን ፀዳ ካልክበት ሊያከብርህ ሲዳዳዉ ታየዋለህ • ለሰዎች ምክር መስጠት በጣም ቀላል ነዉ ነገር ግን ምክርን ወደተግባር መቀየር ከባዱና አስቸጋሪዉ ነገር ነዉ፡፡ አንዳንዴ ሰዉን ካለበት ማጥ ለማዉጣት ካሰብክ ከምክር በላይ የሆነ ስብዕና ሊኖርህ ይገባል፡፡ • አንድ ዉሸታም ጓደኛህ ከ 100 ጠላትህ ጋር እኩል ጥፋት ያደርሳል፡፡ ጠላቶችህን ተከታተላቸዉ ጓደኞችህን ደግሞ በጣም ተከታተላቸዉ • ነገሮች መልካም እንዲሆኑና እንዲሳኩ ያለ የሌለ ጥረትህን አድርገህ ሳይሳካልህ ቀርቶ ይሆናል፡፡ ይሄ ያንተ ደካማነት ሳይሆን ህይወት እንዲህ አይነት ገፅታም ስላላት ነገሩን ተቀበለዉ፡፡ • ለመወደድ ልዩ ሰዉና ሁሉንም ሞካሪ መሆን አይጠበቅህም፡፡ እንዳንዴ ሰዉ ሁሉ ባይወድህ እንኳን ይሄ ምንም ማለት እንዳልሆነ ተረዳ፡፡ በሰዎች መጠላትንም ቀለል አድርገህ ዉሰደዉ ምክንያቱም እንዴት እራስህን ማሳደግ እንዳለብህ ማጤን ወሳኙ ነገር ሲሆን የሰዎችን ስሜት እያዳመጥክ ከፍና ዝቅ እያልክ መኖር አይጠበቅብህም፡፡ • የራስህ አስተሳስብ ይኖርሃል፡፡ ሌሎችም እንዲሁ...ሰዎች በሀሳብህ አለመስማማታቸዉ አንተነትህ ላይ የሚያመጣዉ ነገር የለም፡፡ ሃሳብህን ለማሳመን የሰዎችን አስተሳሰብ ረጋግጠህ አትዉጣ፡፡ የሰዎችን ሃሳብ አክብር ሰዎችም ሃሳብህን እንዲያከብሩ አድርግ • ይቺ አለም የምትፈልግህ ጠቃሚ ነገር አንተ ጋር እንዳለ ስታምን ብቻ ነዉ፡፡ ባጠቃላይ አለም እራስ ወዳድ ናት • ሰዎች ስለ ደስታ አጋነዉ ሲያወሩ ትሰማ ይሆናል፡፡ በኣጭሩ ደስታ ማለት ስሜትህ ሳይሆን አእምሮህ ያለበት ሁኔታ ነዉ፡፡ ደስተኛ ሆነህ በሰዎች ልትጎዳ ትችላለህ፡፡ • ህይወት እኩል አይደለችም፡፡በሆነ ነገር ጎበዝ ብትሆን ካንተ የበለጠ በጣም ጎበዝ ሰዉ አለ...እኩልነት ዉሸት ነዉ፡ ስለዚህ በመኖርህ ብቻ ተደሰት፡፡ አመሰግናለሁ @libmalet @libmalet

🔷ይቅርታ🔷 🔷ይቅርታ🔷 🔷ይቅርታ🔷 ይቅርታ በልጅነታቸን ከምንማራቸው እና በህይወት ዘመናችን ከምናዘወትራቸው ነገሮች አንዱ ነው፤ ሆኖም አንዳንድ ሰዎች ካጠፉ በኋላ ይቅርታን ለመጠየቅ ያመነታሉ ወይም ከነጭራሹኑ አይጠይቁም ይለናል ዶ/ር ጋይ ዊንች፡፡ ይቅርታ መንገድ ላይ ስንሄድ ሳናየው ለምንገፋው ሰው ከምንላት sorry እስከ የልብ ወዳጃችንን ላይ ከባድ ጥፋት አጥፍተን እስከምንጠይቀው ልባዊ ይቅርታ ድረስ ይዘልቃል፤ ያም ሆኖ ግን በብዙ ዓይነት ሰበቦች ሰዎች ይቅርታ መጠየቅ አይፈልጉም ይህንንም በተለያዩ ሳይኮሎጂካዊ ምክንያቶች ሲያስረዳ ፡- 1🦋 ይቅርታን መጠየቅ እና አጥፍቻለው ማለት ለአንድንድ ሰዎች እጅግ በጣም አስቸጋሪ ነው፤ ይህም የሚሆንበት ምክንያት እነዚህ ሰዎች ጸባያቸውን ከድርጊታቸው (ባህርያቸው) መለየት የሚያስቸግራቸው ስለሆነ ነው፡፡ የሆነ መጥፎ ነገር ከሰሩ እራሳቸውን እንደ መጥፎ ሰው ይቆጥራሉ፤ አልያም ከተሳሳቱ እራሳቸውን አንደ አላዋቂ መይም መሃይም ይቆጥራሉ፤ ስለዚህ ለእነዚህ ሰዎች ይቅርታ መጠየቅ ስለማንነታቸው እና ስለ እራስ ግምታቸው (self esteem) የሚደቀን አደጋ ነው ማለት ነው፡፡ 2🦋 ይቅርታ መጠየቅ ለእነዚህ (ለሚጠይቁ) ሰዎች የጸጸትን በር ይከፍታል፤ በአንፃሩ ደግሞ ይቅርታን ለማይጠይቁት ደግሞ የእፍረትን በር ይከፍታል፡፡ ጸጸት ጥሩ ስራን ካልሰራን ስለ ድርጊታችን መጥፎ ስሜት እንዲኖረን ሲያደርግ እፍረት ደግሞ ስለ እራሳችን እና ማንነታችን አሉታዊ የሆነ ስሜት እንዲሰማን ያደርጋል፤ ይህም እፍረትን እጅግ በጣም መርዛማ ያደርገዋል፡፡ 3🦋 ብዙዎቻችን ይቅርታን የወደ ፊት ግንኙነቶችን ለማጠናከር እንደ መልካም አጋጣሚ ስናየው ይቅርታ መጠየቅ የማይፈልጉ ሰዎች ጋር ደግሞ ይቅርታ ማለት ተጨማሪ ግጭቶችን እንደሚቀሰቅስ ችግር ነው የሚታየው፤ አንዴ ጥሩ ያልሆነ ስራቸውን ከተቀበሉ እና ይቅርታ ካሉ ሌላው ሰው ተጨማሪ ቅሬታዎችን እና ይቅርታ ጠያቂው ደካማ ነው የሚል ስሜትን ይፈጥራል ብለው ያስባሉ፡፡ 4🦋 ይቅርታ የማይጠይቁ ሰዎች ይቅርታ ከጠየቅን ሙሉውን ኃላፊነት እኛ እንወስዳለን በዚህም ሌላው አካል ከተጠያቂነት ይድናል ብለው ይገምታሉ፤ ለምሳሌ ከፍቅር አጋር ጋር በሚኖር ግጭት ይቅርታ ከጠየቅን ሌላው አካል የችግሩ መንስዔ በሙሉ ይቅርታ ጠያቂው ነው ብሎ ይወስዳል በማለት ሊገምቱ ይችላሉ፡፡ 5🦋 ይቅርታ ባለመጠየቅ ስሜታቸውን የተቆጣጠሩ ወይም ሌላው ሰው እንዳያውቀው ያደረጉ ሊመስላቸው ይችላል፤ ይቅርታ ሲጠይቁ ይህን የደበቁትን ወይም የተቆጣጠሩትን ስሜት ሁለተኛ አካል ያውቀዋል ብለው ስለሚገምቱ ይቅርታ ከመጠየቅ መቆጠብ ጥሩ አማራጭ ነው ብለው ያስባሉ፡፡ በተጨማሪም ይቅርታ መጠየቅ የማይፈልጉ ሰዎች እናዳሉም ይቅር የማይሉ ወይም ደግሞ ከአንገት በላይ ይቅር የሚሉ ሰዎችም እልፍ ናቸው፡፡ በሰው ልጅ መስተጋብር ውስጥ ይቅርታ መጠየቅ እና ይቅር ማለት የነበሩ፣ ያሉ እና የሚኖሩ ሁነቶች ናቸው፣ ምክንያቱም ዓለም የሁለት ተቃራኒ ሀይሎች ሙሌት ናት፡፡ፍቅር እና ጥላቻ፣ ደስታ እና ሀዘን፣ ማግኘት እና ማጣት፣ መውጣት እና መውረድ…. እንደ አንጓ እና መለልታ ከምናስበው በላይ ቅርብ ለቅርብ ሆነው የሚኖሩ ሁነቶች ናቸው ። ስለዚህም የሰው ልጅ በአንድ ላይ ሲኖር በሰላምና በፍቅር መወዳጀት እንዳለ ሁሉ በመጠላላትና በቂም መኖርም አለ፡፡ ሆኖም ግን ብዙዎቻችን የማንረዳው እውነታ ጥላቻ፣ ቁጣና ቂም አዕምሮአችንን እያደነዘዙ የሚያዳክሙ አደንዛዥ ዕፆች መሆናቸውን ነው፡፡ በጥላቻ የተሞላ አዕምሮ መልካም ነገሮችን ማሰብ አይችልም፤ በቁጣ የተሞላ አዕምሮ አዳዲስ ሐሳቦችን አያፈልቅም፤ በቂም የተሞላ አዕምሮ አካልን አምራች አያደርግም፡፡ በጠቃላይ አዕምሮአችን በጥላቻ ፣ በቁጣና በቂም ከተሞላ የተመደበበትን ስራ ማከናወን አይችልም፡፡ ለዚህ መፍትሔው ደግሞ በሂደት የሚመጣ ሰላም ነው፤ ይህም ልባዊ ሆነ ይቅርታ መጠየቅና ይቅር ማለት ነው፡፡ ባልንጀራ፣ ጓደኛ፣ የትዳር አጋር፣ የቤተሰብ አባል እንዲሁም ፍቅረኛ ሊበድሉንና ሊያስቀይሙን ይችላሉ ሆኖም ግን ቅያሜያችንን እና ቁጣችንን በውስጣችን ቋጥረን በጥላቻና በቂም የምንኖር ከሆነ ሰላማችንን እናጣለን፡፡ ከልብ ይቅር ስንል ግን በዳያችን እኛ ላይ ኃይል አይኖረውም፣ በደሉንም ትዝ ብሎን ባሰብነው ቁጥር አያመንም ፣ከልብ ይቅር ስንል በዳያችንን ጠቀምን ማለት ሳይሆን ለእራሳችን ውስጣዊ ሰላም በማግኘት፣ ለለአዕምሮአችን እረፍት በመስጠት ውለታ መስራት ነው፡፡ ሳይኮሎጂስቶቹ ሎረን እና ጓደኛቿም በጥናታቸው ያገኙት ይህን ነው ከልብ ይቅር ስንል በህይወታችን እርካታን እያገኘን እንኖራለን ፤ በተበደልነው በደል ምክንያት የሚመጣን ስነ-ልቦናዊ ጉዳቶችን ደግሞ የማስተናገድ ዕድላችን ጠባብ ነው ፡፡ ምክንያቱም ይቅርታ ማድረግ የአዕምሮም የአካልምፈውስ ነውና፣ ስለዚህ ይቅርታ መጠየቅም ሆነ ይቅር ማለት ለእራሳችን ነው፡፡ @libmalet @libmalet

*አልችልም* ፡ የፅጌን ማህሌት የዳዊቱን ደግም፣ ልሰማ ማልጄ ቤተስኪያን ብሄድም፣ አምላኬን ልወድስ እልፍ ብፈልግም፣ ፡ እኔ ግን አልችልም፣ ፡ ውርጩ ምን ቢወርጭ ነጠላ አጣፍቼ፣ ከመቅደሱ ቆሜ አይኖቼን ዘግቼ፣ ላመሰግን ብዬ ቃል ካፌ አውጥቼ፣ ስምሽን እንዳልጠራ ዝም አልኩኝ ፈርቼ፣ ፡ ፀሎቱ እንዲሰምር አሜን ሲል ምዕመን፣ በጉልበቱ ሲወድቅ ሲሰብር አንገቱን፣ በቃሉ ሲቀጣው ደንዳውን ልቡን፣ በምክር ሲጎሽም የምድር ስጋውን፣ ፡ እኔ ግን አልችልም፣ ካንቺ ሌላ እንዳስብ ሺ ምክንያት ባገኝም፣ አንቺን አለማሰብ ሀሳብ አይመስለኝም፣ ፡ ፈጣሪ ይመስገን ሲሉ መሪ ጌታ፣ ለኛ ይመስለኛል የህዝቡ ዕልልታ፣ በአንድ ልንኖር የተጋባን ለታ፣ ፡ አይ እኔ ምስኪኑ፣ ካንቺ ጋር ሆነና ልቤ ቃልኪዳኑ፣ በስምሽ ተሳስሮ ድምፄ ወ ልሳኑ፣ ከቤተስኪያን ቆሟል ስጋዬ በድኑ፣ ፡ ከአትሮኖሱ ቆሞ ቀሲሱን ባየውም፣ አይኔን ለአፍታ እንኳ ዳሩ ባልከድነውም፣ እውነት አልሻለሁ ምንም አላየሁም፣ ፡ እኔ ግን አልችልም፣ ፡ የቃሉን መገኛ ከያዝኩት ደብተሬ ላሰፍረው ፈልጌ፣ ስምሽን እፅፋለሁ ከመስመሩ ግርጌ፣ ፡ አሁን ምን ይለኛል የሰማና ያየ፣ የኔ አንቺን ማፍቀር ከፍቅር ተለየ፣ ፡ እኔ ግን አልችልም፣ ካንቺ ሌላ እንዳስብ ሺ ምክንያት ባገኝም፣ አንቺን አለማሰብ ሀሳብ አይመስለኝም፣ ፡ ፡ አልችልም፡፡ @libmalet @libmalet

" Take me to the places i have never been before. Let me see the sun raises and sun set in your eyes. I only want to be with
" Take me to the places i have never been before. Let me see the sun raises and sun set in your eyes. I only want to be with you luv🌷💞

Lakkii... Kophaatti Na Gattus Kophaa Ta'een Beekuu Waa'ee Kee Cinqamuun Sammuu Koo Hin Jeequu Ani Jedheef Mitii Inni Jennaan Ta'aa Yaada Keen Waaddamuun Maaltu Anaaf Bu'aa? Qarshiin Digdamaanii Lapheen Afurtamaa Ani Isheen Dhabee Mee Itti Naaf Himaa @libmalet @libmalet

ስቃይ ነጣቂ(ልዑል ሀይሌ) . የእባቡን ጉድ-ጓድ እንድትለኪበት ክንዴን ስዘረጋ፤ የእሳቱን ምድጃ እንድታነሺበት እጆቼን ሳስጠጋ፤ . ፀሐይ ጋርጄልሽ ራሴን ባጠቆርሁኝ፤ ዝናብ አስጠልዬሽ ውሃውን ባቆርሁኝ፤ . ሰውነቴን ሁሉ ስላንቺ እያሳደርሁ፤ ጥለሺኝ ስትሄጂ ከራሴ ገላ ላይ ያንቺን ገላ ቆጠርሁ፤ ያንቺን ሀሳብ ቆጠርሁ። . እንዴት ነው? ሸሽተሽኝ የሄድሽበት ሃገር፤ ያስተዳድራል ወይ እምነት ሸጦ ማደር፤ . እንዲያው ልጠይቅሽ... እምነትን መነገድ ያከስራል ያተርፋል?፤ ክንድን ቆርጦ መውሰድ ያከስራል ያተርፋል?፤ ልብ አድምቶ መሄድ ያከስራል ያተርፋል?፤ የኔማ ህመም ነው ከጊዜ ጋር መጥቶ ከጊዜ ጋር ያልፋል። . ያንቺ ግን ጨነቀኝ ህልሞቼን ነጥቀሺኝ እንደምን ልተኛ፤ ቅዠቴን ነጥቀሺኝ እንደምን ልተኛ፤ ሸክሜ ቀለለ ምን ሰርቼ ልብላ?፤ ሃሳቤን ወስደሽው የማስበው ጠፋ፤ ጭንቀቴን ሰርቀሽኝ አለመጨነቄ እያስጨነቀኝ ነው በነጋ በጠባ። . በነጋ በጠባ... እጆቼን ዘርግቼ ፊትሽን አጥባለሁ፤ እንጀራ ዳቦውን እየጠቀለልኩኝ አፌን እያጎረስኩ ቁርስ አበላሻለሁ፤ ጠግቤ እየዋልኩኝ ያጠገብኩሽ መስሎኝ ተመስገን እስክትዪ እጠብቅሻለሁ። . እንዴት ነው ክደሽኝ የሄድሽበት ሃገር፤ ያስተዳድራል ወይ ወዳጅ ሸጦ ማደር?። . ያስተዳድራል ወይ?... @libmalet @libmalet

Mee Itti Himaa Maaloo "Eessattuu hin argamu kan anarra caalu kunoo miidhaga koo Hundumtuu haa laalu Dhiirri ana arge martuu ni rifata waan godhu wallaalee Naasuudhaan dhaabata Kan na bira darbe Garagalee na laala Rukuttaan Onneesaa Garmalee dabala! Nan Bareeda kan jettu Na maddii dhaabattee Maal ta'a yoo galtee Daawitii ilaalte"! Jechuudhan hundumaa Akkanaan tuffatti, Akkuma Jecha Ishee Dhuguma ni taatii? Ani gama Kiyyaan Hundumaa ilaalee Hubadhee Madaalee Waanan jedhu dhabnaan Barreessef Walaloo Akka isheen Fokkistu Mee Itti Himaa Maaloo! @libmalet @libmalet