የፍቅር ታሪክ (seenaa jalaala)
Open in Telegram
2 842
Subscribers
+224 hours
No data7 days
+230 days
Posts Archive
የምትከተለውና የምትተወው
“አንድን ነገር መቼ ትተህ መሄድ እንዳለብህ ማወቅ ጥበብ ነው፡፡ ያንን እርምጃ መውሰድ ደግሞ ቆራጥነት ነው፡፡ በጨዋነትና አንገትህን ሳትደፋ መሄድ ደግሞ
ማዕረግና ክብር ነው”
የሰው ጥበቡና ክብሩ የሚለካው በሚከታተላቸው ታላላቅ ነገሮች ብቻ ሳይሆን ትቶ ለመሄድ በወሰናቸው ነገሮችም ጭምር ነው፡፡ አንድ ሰው ወደፊት የሚደርስበት ከፍታ ከወዲሁ የሚታወቀው ምንም እንኳን መስዋእትነት ቢያስከፍለውም፣ ከአጠቃላይ የሕይወቱ መርህና የልህቀት ደረጃ ጋር ከማይመጥን ነገር ለመለየት ባለው ቆራጥነት ነው፡፡ አንድን የተሻለ ነገር በእጃችን ለመጨበጥ በመጀመሪያ የያዝነውን ነገር የመልቀቅ ጥያቄ ሊቀርብልን እንደሚችል መዘንጋት የለብንም፡፡
ለመክፈል ፈቃደኛ የሆንክለት መስዋእትነት ነገ የምትደርስበትንና በእጅህ የሚገባውን ነገር ጥራት ይወስነዋል፡፡ አንዳንድ ሰዎች ተራውንና ላላቸው ታላቅ የሕይወት ግብ የማይመጥነውን ላለመልቀቅ ሲሉ ከብዙ መልካም ነገር ይጎድላሉ፡፡ ለጊዜያዊው ሲሉ ዘላቂውን ይሰዋሉ፤ ለተራው ሲሉ የከበረውን ይጥላሉ፤ ላይ ላዩን ብቻ ለተብረቀረቀው ነገር ሲሉ ጥልቅና የውስጥ ውበት የተላበሰውን እውነተኛውን ችላ ይላሉ፡፡ እንደዚህ አይነት ሰዎች አንድን የላቀ ነገር ለማግኘት አናሳውን መስዋእት ማድረግ እንዳለባቸው የዘነጉ ጥበብ-የለሽ ሰዎች ናቸው፡፡
አገራችንን የሞሉትን የችግር ምንጮች ካየሃቸው ይህ አመለካከት የተጠናወታቸው ሰዎች ናቸው፡፡ የሚያስቡት፣ የሚናገሩትና የሚከተሉት ነገር ሁሉ ተራ የሆነባቸው ሰዎች በሕብረተሰቡ መካከል ለሚፈጠሩ ለአብዛኛዎቹ ቀውሶች መንስኤ ናቸው፡፡ እንደዚህ አይነት ሰዎች ለብዙሃኑ ጥቅም ሲሉ የራሳቸውን አጀንዳ መጣል የሚባለውን ሃሳብ በፍጹም የሚገነዘብ አእምሮ የላቸውም፡፡ ለአጠቃላይ ሃገራዊ ራእይ ሲሉ ጊዜያዊ ጥቅምንና መብተኝነት መልቀቅ የሚባለው ሃሳብ ፈጽሞ ሊታያቸው አይችልም፡፡
አንተ በምትወስደው እርምጃ ምክንያት ያለህበት ሕብረተሰብ ወደተሻለ ደረጃ እንደሚደርስ ብታውቅ ያንን ነገር ለማድረግ ዝግጁ ነህ? አንተ ለመተው ፈቃደኛ በሆንከው ነገር ምክንያት በሕብረተሰቡ መካከል ሰላም እንደሚሰፍን ብትገነዘብ ያንን ነገር ለመተው ምን ያህል ፈቃደኛ ነህ?
ሃሳቡን ስንደመድመው፣ የሕይወታችን ጥራት የሚለካው በምንተገብራቸው ነገሮች ብቻ ሳይሆን አንዳንዴም ለመተው በምንወስናቸውም ነገሮች እንደሆነም ማስታወስ ጥበብ ነው፡፡ የጥበባችን ልክ የሚመዘነው እከተለዋለሁ በምንለው ነገር ብቻ ሳይሆን እተወዋለሁ በምንለውም ነገር ጭምር ስለሆነ ማለት ነው፡፡ አስተዋይነታችን የሚለካው መያዝ-መጨበጥ አለብኝ በምንለው ነገር ብቻ ሳይሆን አንዳንድ ጊዜም ለመልቀቅ ፈቃደኛ በሆንነው ነገር እንደሆነ ለማስታወስ ይፈቀድልኝ፡፡ ብርታታችን የሚታየው ለመብቴ እቆማለሁ በሚለው ጠንካራ አቋማችን ብቻ ሳይሆን ለአጠቃላይ ሰላም ሲባል አንዳንዴ መብቴን እተዋለሁ በሚለውም አመለካከታችን እንደሆነ ይሰመርበት፡፡
ካነበብኩት
@libmalet
የፍቅር ታሪክ (seenaa jalaala):
ጓደኛን ስትመርጥ . . .
አመለካከትህ የምትመርጠውን ጓደኛ ይወስናል፤ አብረህ የምትከርመው ጓደኛ ደግሞ በተራው አመለካከትህን የመወሰን ጉልበት ስላለው ወደ ሕይወትህ ዘልቆ እንዲገባ የምትፈቅድለትን ሰው በጥንቃቄ ምረጥ፡፡
“ጓደኝነት እንደ ሊፍት (Lift / Elevator) ነው፡፡ ወይ ወደላይ ያወጣሃል ወይም ደግሞ ወደታች ያወርድሃል” የሚል አባባል አለ፡፡ ሌላ ረዘም ላለ ጊዜ የከረመ አባባል፣ “በአጠገብህ የሚገኙ የአምስቱ ቅርብ ጓደኞችህ ጭማቂ ነህ” ይላል፡፡ እነዚህ አባባሎች ልቦናን የሚያነቃ እውነት ይዘዋል፡፡ የቅርብ ጓደኞችህን የያዝክበት የራስህ የሆነ ምክንያት ቢኖርህም፣ ለውጥ ለማምጣት በምትፈልግበት ጊዜ በዙሪያህ የሚገኙት ሰዎች ምን አይነት ሰዎች አንደሆኑ ማሰብ መጀመርህ አይቀርም፡፡
ከዚህ በታች ጓደኛን ስትመርጥ ሊኖርህ ስለሚገባ የምርጫ መመዘኛ የሚያስተምሩ ነጥቦችን ታገኛለህ፡፡
1. “ወደ ላይ” ምረጥ፡- የማደግና የመሻሻል ፍላጎቱ ካለህ የምትይዛቸው ጓደኞች ከአንተ ከፍ ያሉ እንዲሆኑ ትመከራለህ፡፡ ከፍ ያሉ ሰዎች ከፍ ያደርጉሃል፡፡ የበሰሉ ሰዎች ብስለትን ያስተዋውቁሃል፡፡ ይህንኑ ተመሳሳይ መርህ በመከተል የአንተን ላቅ ያለ ደረጃ ፍለጋ አንተን የሚቀርቡህ ሰዎች የመኖራቸው ሁኔታ እንደተጠበቀ ሆኖ፣ አንተ ግን ወደ ላይ መመልከትህን መዘንጋት የለብህም፡፡
2. ተመሳሳይ መርህ ያለውን ምረጥ፡- በልዩነት ውስጥ ያለውን ውበት ሳንክድ፣ አመለካከትንና መርህን አስመልክቶ ግን ተመሳሳይነት ያላቸውን ሰዎች መቅረብ ስኬታማ ያደርግሃል፡፡ መርህን አስመልክቶ ልዩነታችሁ ከጎላ ሰዎች ጋር ጓደኝነት መያዝ፣ ወደፊት ከመራመድ ይልቅ ልዩነትን በማስታረቅ ዙሪያ የሚሽከረከር ግንኙነት ውስጥ እንድትቀር ያደርግሃል፡፡
3. ተመሳሳይ ግብ ያለውን ምረጥ፡- የዚህ ምርጫ ጥቅሙ የመደጋገፍና የመበረታታት ጉዳይ ነው፡፡ ለምሳሌ፣ አንተ ያለህ ግብ ሕብረተሰብህን የማገልገል ከሆነና የቀረብከው ጓደኛ ዋና ግቡ በገንዘብ የመበልጸግ ብቻ ከሆነ የጋራ የሆነን ሃሳብ በመወያየት የሞራልና የተግባር ድጋፍ መለዋወጥ ሊያስቸግራችሁ ይችላል፡፡
4. በስኬትህ ደስ የሚለውን ምረጥ፡- በተሳካልህ ቁጥር ከአንተ ጥቅምን እንደሚፈልግ የሚያሳይ፣ ስለስኬትህ ስትነግረው ብዙም ሃሳብ የማይሰጥ፣ ስኬትህን አስምልክቶ ከአንተ ጀርባ ለሌሎች የሚያወራና የመሳሰሉት ባህሪይ የሚያንጸባርቅን ሰው ጓደኛ ከማድረግህ በፊት ደግመህ ልታስብበት ይገባል፡፡
5. በውድቀትና በችግር የማይለይህን ምረጥ፡- ሁሉም ነገር በተሟላልህ ወቅት አብሮህ ሆኖ፣ ሁኔታዎች እንደ ቀድሞው አልሆን ሲሉህና ነገሮች ሲፈራርሱብህ ከአንተ ዘወር የሚል ባህሪይ ያለበት ሰው አይበጅህም፡፡ እንዲህ አይነት ሰዎች ከአንተ ከሚያገኙት ጥቅም አንጻር ብቻ የሚቀርቡህ ናቸውና ስሜትህን ጠብቅ፡፡
6. እውነቱን የሚነግርህን ምረጥ፡- እውነቱን የማይነግርህ ሰው ከምታይበት ባህሪ አንዱ አንተ ጋር ሲሆን አንተን ደስ የሚልህን ብቻ እየመረጠ የመንገር ሁኔታ ነው፡፡ እውነተኛ ወዳጅ ግን እየወደደህና እያከበረህ፣ ቢያምህም እውነቱን ይነግርሃል፡፡ ይህ አይነቱ ሰው ባለውለታህ እንጂ ጠላትህ አይደለም፡፡
7. ማንነትህን የሚቀበልን ምረጥ፡-- ስህተትህን ሳይደብቅ እውነቱን እየነገረህ፣ ነገር ግን ማንነትህን ከነስህተትህና ከነጉድለትህ የሚቀበልን ሰው ማግኘት ታላቅ እድል ነው፡፡ እንዲህ አይነቱን ሰው ካገኘህ ለጓደኝነት አትለፈው፡፡ እንዲህ አይነቱ ሰው ባወቀህ መጠን አይንቅህም፤ እንዲያውም በወዳጅነቱ እየተመቻቸ ይሄዳል፡፡ በተጨማሪ፣ እውነተኛ ወዳጅ ዘርህን፣ መልክና ቁመናህን፣ እንዲሁም ሁለንተናህን የሚቀበል ሰው መሆኑን አትዘንጋ፡፡
8. መስመርህን የሚያከብርን ምረጥ፡- ጨዋ ጓደኛ መሆንና ማድረግ የማትፈልገውን ያከብራል፤ የግል ሕይወትህን አስመልክቶ የፈቀድክለት ድረስ ነው የሚገባው፡፡ በአንተ ህይወት መብተኝነት አይሰማውም፡፡ የሚበጅህ ጓደኛ፣ ጓደኝነት ማለት በየቀኑ መገናኘት፣ አብሮ ውሎ አብሮ ማደር፣ አብሮ መላስና መቅመስ እንዳልሆነ በሚገባ ያውቃል፡፡ ሌላ ማሕበራዊና ግላዊ ህይወት እንዳለህም በማወቅ ለቀቅ ያደርግሃል፡፡ ልቡ ግን ሁል ጊዜ ከአንተ ጋር ነው፡፡
9. ድብቅ ያልሆነውን ምረጥ፡- ማን እንደሆነ፣ ምን እንደሚያደርግ፣ ከየት እንደሚመጣና ወደ የት እንደሚሄድ በቅጡ የማይታውቀውን ሰው ከመወዳጀት ቆጠብ ማለት ይበጅሃል፡፡ ጓደኛ ሊታይ፣ ሊደመጥ፣ ሊዳሰስ ይገባዋል፡፡ በተለያዩ የማሕበራዊ የመገናኛ መረቦች ላይ “በስም” እና “በፎቶ” ለተዋወከው ሰው ሁሉ ልቦናንና ስሜትን መክፈት ከመስመር ያወጣሃል፣ አልፎም የስሜት ቁስል መሆኑ አይቀርም፡፡
@libmalet
👉እሱ ነው ❤💙
በእይታ ብቻ የተሸነፈልኝ
ምንም ሳያቅማማ ከልቡ የወደደኝ
በማይሆኑ ቃላት ስገፋው ያልራቀኝ
ካጠገቤ ሆኖ ሁሌም የሚያግዘኝ
በጥላቻ ውስጥም ፍቅርን የሚፈልግ
ለኔ ደስታ ብቻ የሚተጋ እስከ ጥግ
ካለኝ ነገር ሁሉ አብልጬ የምወደው
ከኔ ጋራ ያለው የኔ አፍሪቃ እሱ ነው
አለም ቢለዋወጥ መቼም የማልጠላው
በቃ እስከዘላለሙ ህይወቴ እሱ ነው
ምንም ሣይጠብቅ ዝም ብሎ የሚያፈቅር
በነገሮች መክፋት ምንም ማይቀየር
የትም አይገኝም ብንዞርም ባገር
እድለኛዋ እኔ እኔ አግኝቼዋለው
ቃላት ሳልደረድር ረትቼዋለው
ከሄዋኖች መሀል እኔን ለመረጠኝ
ከልቡ ዙፋን ላይ እኔን ላስቀመጠኝ
የፍቅርን ሀይል ላስተማረኝ ለሱ
እስካሁን ያረኩት ለሱ በማነሱ
ፀፀት ቢሰማኝም ብናደድም በኔ
ልገዛለት ወሰንኩ እስካለው በእውኔ
💜❣ዛሬም
ነገም
እስከመጨረሻው
ምድር ላይ ያለው ነገር ሁሉም ቢቀየርም
እኔ አንተን ማፍቀሬን መቼም አላቆምም
የእውነት ቃሌ ነው መቼም አላጥፍም
@libmalet
✍ከባልታሰር ጋርሽያ የብልህነት ጥበብ (the art of wisdom) መፃሐፍ።
በ17ኛው መቶ ክፈለ ዘመን እስፔን ኑሮ የመረረባት ምድር ነበርች ህዝቦቿም ተስፍ ቆርጠው በፀለምተኛ ኑሮ ነበር የሚገፉት ታድያ ባልታሰር ጋርሽያ የሀገሩ ህዝብ ከዚህ ተስፍ መቁርጥ ይወጣ ዘንድ የብልህነት ጥበበ (the art of wisdom) የተሰኘውን እጅግ ድንቅ መፃፍ ለመፃፍ የበቃው አልፎ ተርፎ መፃሐፉ ከዛሬ 400 አመት በኃላም። በአለም ለይ እጅግ ተወዳጅ ለመሆን በቅቷል እኔም የዚህ መፃሐፍ አድናቂ ብቻም ሳልሆን ልክፍተኛ ሆኛለው።ባልታስር ጋርሽያ ከጥቂት ሰወች ጋር አስብ ከብዙኃኑ ጋር ግን አውራ በሚለው ምክሩ ይታወቃል። እኔም ለዛሬ የመርጥኳቸውን እንሆ ብያለው እናንተ ሙሉ መፃሐፉን ፈልጋቹ እንብቡት።
📖 ሰወች ካከበሩህ እራስን አክብር።
📖 እጅግ አብዝተን የምናስታውሳቸው ሊረሱ የሚገባቸው ናቸው።
📖 ጓደኝነት መልካምነትን ሲያባዛ ክፍትን ያከፋፍላል።
📖 ሞኝ ሰው ከወዳጁ ከሚማረው ይልቅ ብልህ ሰው ከጠላቱ ይማራል።
📖 ምንም የሚያጣው ከሌለው ሰው ጋር በፍፁም አትፎካከር።
📖 በተናደድክ ጌዜ ምንም አታድርግ ሁሉም ስህተት ነው እና።
📖 ታላቅ እውቀት የሚያድገው እና የሚታየው በያአንድ አንዱ አዲስ ስራ ውስጥ ነው።
📖 መናገር ካለብህ በሚስጥር አጅብ ግን ደግሞ ጥንቃቄ የተሞላበት ዝምተኝነት በአለም ከሉ ብልህነት ሁሉ ቅዱስ መሆኑን ተረዳ።
📖 አንተ ከማንኛውም ተፅዕኖ ነፃ መሆን አለብህ ከማንኛውም ሰው አስተሳሰብ ከየትኛውም ፋሽን ከየትኛውም ዘመን አመለካከት ነፃ ሁን።
📖 ከጥሙ የረካ ሰው ከውሀ ጉድጓድ ይርቃል።
@libmalet
ካነበብኩት የወደድኩት ድንቅ የህይወት ታሪክ
የደግነት ጥግ
ሁለት ሰዎች በአንድ ሆስፒታል ክፍል ውስጥ አልጋ ይዘው ተኝተዋል... ሁለቱም በጠና ታመው በአምላክ እጅ ተይዘዋል።
አንደኛው ሳንባው የቋጠረውን ውሀ ለማድረቅ ሲባል ለሰአታት ያህል አልጋው ላይ ቁጭ እንዲል ይደረጋል ...ከመስኮት አጠገብ ነው።ሌላኛው ህመምተኛ ደግሞ በተቃራኒው ለሰአታት በጀርባው እንዲተኛ ይደረጋል።
እነዚህ ህሙማን በቆይታቸው ብዙ ተጨዋውተዋል። ስለ ቤተሰቦቻቸው፣ ስለ ኑሯቸው፣ በወታደር ቤት ስለሰጡት አገልግሎት፣ የእረፍት ጊዜያቸውን የት
እንደሚያሳልፉ... ወዘተ አውርተዋል።
ከመስኮት አጠገብ ያለው ህመምተኛ ቁጭ በሚልበት ሰአት ወደ ውጭ እየተመለከተ ሁሉን ነገር በጀርባ ለተኛው ሰው ይገልጽለታል።
".....በሚያማምሩ ዛፎች የተከበበ ሀይቅ ይታየኛል ... በሀይቁላይ ዳኪዬዎች ይዋኛሉ...... ህጻናት ደግሞ ከወረቀት የሰሩትን መርከቦች በሀይቁ ዳርቻ በማስቀመጥ ይጫወታሉ... ፍቅረኛሞች በአንድ እጆቻቸው አበባ በሌላው ደግሞ ተቃቅፈው ሀይቁን ይዞራሉ .. ከሀይቁ ባሻገር ውብ የሆነ ከተማ ይታየኛል ህፃናቶችም በደስታ ይቦርቃሉ "
በማለት ዘወትር የሚያየውን ሁሉ በሚያምር አገላለፅ ይተርክለታል! ... በዚህ አይነት ሁኔታ ሳምንታት አለፉ።
አንድ ማለዳ ነርስዋ ገላቸውን ልታጥብ ውሀ ይዛ መጣች። ከመስኮት አጠገብ ያለው የተቀመጠው በሽተኛ ግን በህይወት አልነበረም። በጣም ደነገጠች። ጓደኛውም እንዲሁ አዘነ።
ነርስዋ አስከሬኑን በቶሎ እንዲያነሱ ሰዎች ሌሎች ነርሶችን ጠርታ አዘዘቻቸቸው ...
ያ ብቻውን የቀረው በጀርባው የተኛው በሽተኛ አልጋውን ከመስኮቱ አጠገብ እንዲወስዱለት ጠየቀ ወሰዱለት።
ሟች የነገርውን በሙሉ በመስኮት ለማየት በጣም ቸኩሏል። ቀና ብሎ ወደ ውጭ ተመለከተ። ከመስኮቱ ባሻገር ያለው ጥቁር ቀለም የተቀባ ግድግዳ ብቻ ነው። ደነገጠ!!!
"ምን ሆንክ?" አለቸው ነርሰዋ። "ሰዉዬው ብዙ አስደሳች
ነገሮችን በዚህ መስኮት አሻግሮ ይመለከት ነበር" አላት። "ኧረ ሰዉዬው ማየት የማይችል #አይነስውር ነበር
አለችው።"
ልብ የሚነካ ነገር.... ለካስ እሱን ለማስደሰትና የመኖር ተስፋ ለመስጠት ነበር ያን ሁሉ ነገር ፈጥሮ የሚያወራው።
**
አንዱን ለማጠንከር ወይም ለማበርታት የኛ ጥንካሬና ብርታት አስፈላጊ ነው።
ለሰው መድኃኒቱ ሰው ነው።ሁሌም ደግነትን እናድርግ።
@libmalet
#አስተሳሰብን__መቆጣጠር
#አስተሳሰብን_መቆጣጠር_ማለት፦ ወደ እኔ የሚመጣውን ወይም በውስጤ የሚፈጠረውን ሃሳብ በማጣራት ማስተናገድ ማለት ነው፡፡ አስተሳሰባችንን ሳንለውጥ ሕይወታችንንም ሆነ ሁኔታችንን መለወጥ አንችልም፡፡ ይህ የሚሆንበት ምክንያት የሁሉ ነገር መጀመሪያ አስተሳሰብ ስለሆነና አስተሳሰባችን የማንነታችን “ወፍጮ” በመሆኑ ነው፡፡ በመጀመሪያ አንድ ሃሳብ ወደ አእምሮአችን ይገባል፡፡ በመቀጠልም ይህ ሃሳብ በውስጣችን ይብላላና በንግግርና በተግባር መገለጥ ይጀምራል፡፡ ይህ ተግባር ወደ ልማድ ከተለወጠ በኋላ ፍጻሜአችንን የመለወጥና የመቅረጽ ጉልበት ይኖረዋል፡፡ ይህ ሃሳብ ጤናማም ሆነ ጤና ቢስ ሂደቱ ያው አንድ ነው፡፡
#ጤና_ቢስ_አመለካከቶችን_ለማስወጣት_መውሰድ_የምትችላቸው_እርምጃዎች፡-
1. በሕይወትህ የምታሰላስላቸውን ሃሳቦች ለይተህ እወቅ፡፡
ለማንነትህና ለሕይወትህ አላማ የሚመጥኑ ሃሳቦች ምን እንደሆኑ ለይተህ ማወቅ አለብህ፡፡ ይህንን ለይተህ ስታውቅ በሃሳቦች መካከል መለየትንና የትኛውን ማስተናገድ እንዳለብህ ጥርት ባለ መልኩ እንድታውቅ ይረዳሃል፡፡
2. ጤና ቢስ አስተሳሰቦችን አታስተናግዳቸው፡፡
የመጣ ሃሳብ ሁሉ በአእምሮህ ስፍራ ማግኘት የለበትም፡፡ ለጤናማ አመለካከትህና ላስቀመጥከው የሕይወት ከፍታና ደረጃ የማይመጥነውን ተራ ሃሳብ በመጣበት ፍጥነት እንዲወጣ ተቃወመው፡፡ ይህንንም ልምምድ የዘወትር አድረገው፡፡
3. ጤና ቢሱን አስተሳሰብ በጤናማ አስተሳሰብ ቀይር፡፡
#ከዚህ__በፊት በውስጥህ ያስተናገድካቸውን ጤና ቢስ ሃሳቦች መልካምና ስኬታማ በሆኑ ጤናማ ሃሳቦች መለወጥ መጀመር አለብህ፡፡ ከአእምሮህ ክፉውን ሃሳብ አስወጥተህ በጤናማው ካልተካኸው ሌላ ሃሳብ መሙላቱ አይቀርም፡፡
@libmalet
ጠዋት ጠዋት ትዳር ያምረኛል!
ይነበብ ወንዶች
ሁሌም ጠዋት ከእንቅልፌ ስነቃ ሚስት ማግባት ያምረኛል። በቃ አለ አይደል ልክ እንደ አማርኛ ፊልም ሚስቴ ቀድማኝ ተነስታ ሸሚዜን ለብሳ በዚያ ውብ እግሯ ቤት ውስጥ ሽር ጉድ ብላ ሚገርም ቁርስ ከጁስ ጋር ሰርታልኝ በልቼ ምናምን ቡናዬን ጠጥቼ። የተተኮሰ ልብስ ራሷ መርጣ አምጥታልኝ እሱን ለብሼ እስከበር ድረስ ሸኝታኝ ከንፈሯን ስሜ ቀኔን ረሃ ሆኜ ብጀምር ደስ ይለኝ ነበር።
But … life is not like z movie my brother!! ሁሉም ወንድ ሊያገባ ሲወስን የሚታየው ከላይ የገለፅኩት አይነት ህይወት ነው። በርግጥ እህቶችም የሚሰሩን ሿሿ ቀላል አይደለም
ብራዘር ድንገት ቺክህ የወንደላጤ ቤትህ ከመጣች በምቾት ታጨናንቅሃለች። ትንከባከብሃለች። በአንድ ድስት ሰባት አይነት ወጥ ስትሰራ “አረረረ ጆርዳና in the house” ምናምን ብለህ ትቀውጠዋለህ። እየተሽከረከረች ያቺኑ አንድ ክፍል ቤትህን ታፀዳለች። እንደስፓይደር ማን ግድግዳው ላይ ተራምዳ ሁሉ ኮርኒስህን ልትወለውል ትችላለች። አንተ እያወለቅክ አልጋህ ስር የጣልከውን ካልሲ ፈገግታ ከፊቷ ሳይጠፋ (በሆዷኮ ይሄ በስባሳ እያለችህ ነው) አውጥታ አጥባ እንደቋንጣ ታሰጣልሃለች።
በቃ ምን አለፋህ ከሷ ጋር መኖር ሰቨን ስታር ሆቴል አዘግቶ መዝናናት እንዲመስልህ ታደርግሃለች። ባራት እንቁላል አምስት አይነት ወጥ ሰርታ ስታበላህ እነዚህ አድሃሪና ቡርዧ የሆቴል ቤት ባለቤቶች ሲበዘብዙህ እንደኖሩ ይሰማሃል! እሷን ማግባት ትመኛለህ። ትዳር ማለትኮ …. እያልክ ለጓደኞችህ ማብራራት ትጀምራለህ። የሙሽራ መኪና ስታይ አይንህ ይንከራተታል። እንተዋወቃለን ወይ? የሚለው ፕሮግራም ቋሚ ደምበኛ ትሆናለህ። በቃ ፋይናሊ ሽማግሌ ትልካለህ። እናትና አባቷ በየቀኑ «አንቺ ልጅ አግብተሽ አትፋቺንም እንዴ?» ሲሏት እንዳልኖሩ እየተጀነኑ ምን አለው? ማን ነው? ምናምን ብለው በመከራ ይፈቅዱልሃል!
ከዛ መልአኳ እጮኛህ ስለሰርግ ትጀነጅንሃለች። እንደጀነጀነችህ ግን አትባንንባትም። በስታየል ነው ምታሰምጥህ። አለ አይደል «እኔኮ ሰርግ አሎድም ግን እነማሚ እንዳይከፋቸው አነስ ያለች አንድ መቶ ሰው ብቻ ጠርተን ቀለል አርገን እንደግስ .. ግን ካልተመቸህ ይቅር» ትልሃለች! አረ ጣጣ የለውም ምናምን ብለህ እድሜ ልክህን ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ተሰልፈህ የቆጠብካት ፍራንክህ ላይ ትፈርድባታለህ!
እናቱ ቀለል ያለ ያለችውን ሰርግ የአንድ ሺ ሰው ካርድ በማሰራት ትጀምረዋለች ቀለል አርጋ የሃያ ሺ ቬሎ፣ ቀለል አርጋ ሜካፕ ሰላሳ ሺ፣ ቀለል አርጋ ሊሞ ሃምሳ ሺ፣ ወዘተ ብላ በአንዴ ከአበዳሪ ሐገራት ተርታ አውጥታህ ኢኮኖሚህን በጠረባ ትጥለዋለች። የሰርግህ ቀን በሰው መኪና እንደታቦት አደባባይ ሲያዞሩህ ይውሉና አንተ የማታውቀውን አንድ ሺ ሰው ሆድ ሞልተህ እጅህን እያጠላለፍክ ኬክ ትጎራረስና በአደባባይ ሃብቴ ሃብትሽ ነው ብለህ ፈርመህ ኮትህን አንጠልጥለህ ወደቤት ይዘሃት ትገባለህ!!
የመጨረሻው መጀመሪያ! እንዲል የድሮ ደራሲ the tragic part of your life begins
ጠኋት ከእንቅልፍህ የሚገርም የጀነሬተር ድምፅ ያነቃሃል! ብንን ስትል እያንኮራፋች ነው ካሁን አሁን ተነስታ ምርጥ ቁርስ ሰራችልኝ ብለህ ብትጠባበቅ እናቱ ተኝታ ህልም እየቀያየረች ታያለች። ምርር ሲልህ ትቀሰቅሳታለህ። ጠላትህ ቅይር ይበል በዚያ ሻካራ ድምጿ አፍጥጣ «ሰው ከእንቅልፌ ሲቀሰቅሰኝ ደስ አይለኝም» ብላ ተመልሳ ትተኛለች። በሆድህ “እቺ ነገር ያቺ ነገር ነች?” እያልክ ፆምህን ወደስራ ስትወጣ በር ላይ ለሰርግ ብር ጎሎህ የተበደርከው ሰውዬ ከቦክሰኛ ልጁ ጋር ይጠብቅሃል ….. ምፅ እኔ አፈር ልብላ!
ማታ ቤት ስትገባ ካልሲዎችህ በር ላይ ተከምረው ይጠብቁሃል! እሱን አጥበህ ስትጨርስ ጨው እንደ Dead sea የበዛበት ሽሮ ወጥ ይቀርብልህና “ከበላህ ብላ ካልበላህ አፈር ብላ” ትባላለህ!
በዘጠኝ ወሯም አንድ ጩኸታም ፈልፈላ ትወልድልሃለች። በየደቂቃው ዋኣኣይ ነው። በየሰከንዱ ኡኡ ነው። አናትህን ያዞረዋል። በመስኮት አውጥተህ ወርውረው ወርውረው ይልሃል። ለሊት ይነሳና ይቀውጠዋል። እሷ ምርር ሲላት ላሽ ትለዋለች። ቢቸግርህ ተነስተህ ጡጦ ትሰጠውና ተመልሰህ ተኝተህ እንቅልፍ ሸለብ ሲያደርግህ ጡጦውን ሻት አርጎት እንደገና ዋኣኣይ ይላል። በቃ ትነቅላለህ! ይሄ ሰውዬ ለምን አይተወኝም ግን? ትላለህ። የሶስት ወሩን ልጅ “ና ልብ ካለህ ወጥተን እንነጋገር” ምናምን ሁሉ ልትለው ትችላለህ
በገባህ በወጣህ ቁጥር ያ በደጉ ግዜ ስንት ነገር ያሳየህ ጡቷ ላይ እንደአልቂት ተጣብቆ ሲመጠምጣት ደምህ ይፈላል። ዘመዶቿ አያልቁም ዛሬ አባቷ ፣ ነገ አጎቷ፣ ከነጎዲያ አክስቷ እየመጡ ጠብ እርግፍ ብለህ ታስተናግዳለህ። እሱ ሳይበቃቸው ምነው ጠቆርሽ? ምነው ከሳሽ? እያሉ ወፍራ ጆንሲናን ያከለችውን ሴትዮ ይጨቀጭቋታል። ፕራይቬት ላይፍ ብሎ ነገርህ ይናፍቅሃል! ብቸኝነትህ በአይንህ ውል ይልብሃል!
ለሊት አንተ የልጅህን ዳይፐር ለመቀየር ስትታገል ፍሬንዶችህ ክለብ ሆነው ይደውሉልህና ዘፈን ይጋብዙሃል! ሲኦል ሆነህ ከመንግስተሰማይ ሚደወልልህ ያህል ትቀናለህ! ከዚያ ህይወትህን መለስ ብለህ በትካዜ ታስታውሰዋለህ። ከዚያም ሴትየዋ ከትዳር በፊት የነበራት ማራኪ ባህሪ የምርጫ ቅስቀሳ መሆኑ ይገባህና “All women are politicians” ብለህ መፈላሰፍ ትጀምራለህ።
ካነበብኩት
@libmalet
@libmalet
♥♥♥የምድሯ ገነቴ✉✉✉
ናፍቆቴ እንደምነሽ እንዴት ነሽ ልበልሽ
እንደማህተም ታትመሽ ከልቤ ላይ ቀረሽ
እኔስ ባይተዋርነኝ ሰው የለኝ ባገሩ
እንደወጣሽ ቀረሽ ምንድነው ነገሩ
አብረን ያሳለፍነው በደስታም በሀዘኑ
ትዝታው ኗሪ ነው ወራት ቢርቅ ቀኑ
አንሶላው ትራሱ ያንተራሰሽ ክንዴ
ምንስ ግዜው ቢረዝም ይረሳሻል እንዴ
ድንገት ሳላስበው ከጎንሽ ብለይም
ይኖራል ከልቤ ፍቅርሽ ለዘልአለም
ገነቴ ልበልሽ አንቺ ትዝታዬ
ተበትኖ ቢቀር ውጥኑ ተስፋዬ
ገነቴ ልበልሽ አንቺ ትዝታዬ
አስታውስሽ እና ይፈሳል እንባዬ
ገነቴ ልበልሽ አንቺ ትዝታዬ
ፎቶሺን አይና ይፈሳል እንባዬ
ገነቴ ልበልሽ ❀❀❀የምድራ ገነቴ
አዘንኩኝ ተከዝኩኝ አንቺን በማጣቴ፡፡
ይድረስሽ ናፍቆቴ በደብዳቤ ትዝታ
የኔ ውሎ ማደር የልቤ ትርታ፡፡
@libmalet
#አትሂድ አልልህም
ከልብህ ጨክነህ መለየት ካማረህ
አትሂድ አልልህም መሄድ ትችላለህ
ግን ለምን ውድዬ ምንስ ባጠፋ ነው
ፍቅራችንን ረግጠህ ለመሄድ ያሰብከው
ስለአንተ መኖሬ ይህ ምን ክፋት አለው
ሁሉንም ረስቶ ልብህ የሸፈተው
ለኔ መኖር ትቼ ስለአንተ ስለኖርኩ
የኔን ደስታ ትቼ ያንተን ስላስቀደምኩ
ህልምህ እንዲሳካ ከልቤ ሰለጣርኩ
ከሁሉ አብልጬ አንተን ስለወደድኩ
እስከማውቀው ድረስ
አንተን የሚያስከፋ ምንም አላደረኩ
ይህንን ማድረጌ ጥፋት ከመሰለህ
ያሳለፍነው ጊዜ ከመሄድ ካልያዘህ
ምን ማረግ ይቻላል በግድ አላስቀርህ
አትሂድ አልልህም መሄድ ትችላለህ
እንዲህ አስጨክኖ መሄድ ያሰኘህን
ምን እንዳስቀየምኩህ ባላውቀውም ጥፋቴን
ግን አንዴ......
ሁሉንም ረስተህ መሄድን መርጠሀል
አካልህ ነው እንጂ ልብህ ርቆ ሄዷል
ስለዚህ ውድዬ.....
ከኔ ርቀህ ሄደህ ደስተኛ ከሆንክ
ከኔ ውጪ ሌላ ሌላ መልመድ ከቻልክ
ምንም አልልህም ደስታህ ደስታዬ ነው
ልቤ እየቆሰለም ስቄ እሸኝሀለው
የእውነት ውድዬ አልቀየምህም
አንተን ይቅናህ እንጂ አትሂድ አልልህም
እራስወዳድ ሆኜ እኔ አላስቀርህም
@libmalet
@AASH23
#ትመጫለሽ_ብዬ
ከማየት የዘለለ
መንካት ያልታደልኩኝ
ደመና ሆነሽም
አፍቃሪሽ ነበርኩኝ
#ያኔ
ስታጉረመርሚ
በኩርፊያ አይን አይታሽ
ወደ ቤቷ ገባች
ፀሀይ እንኳን ፈርታሽ
#መሆኔን #ስታውቂ
ችዬ ማላኖርሽ ችዬ ማላጠፋሽ
ልታበሰብሽኝ በድንገት አካፋሽ
* * *
የበሰበሰ ሰው አይፈራም እንዲሉ
ወጥቼ ደቀንኩሽ ባለኝ ነገር ሁሉ
* * *
አንዴ ወደ ሰማይ
አንዴ ወደመሬት
በስስት እያየሁ
ጠብታ ቆጥራለሁ
የደቀንኩት ልቤ
በካፊያሽ ላይሞላ
እጠባበቃለሁ
* * *
#እናም #ባክሽ #ውዴ
መዳመኑን ትተሽ
ዝናብ ሆነሽ ምቺኝ
ማጉረምረሙን ትተሽ
ዶፍ ሆነሽ ቀጥቅጪኝ
ጎርፍ ሆነሽ ውሰጂኝ
ደብድቢኝ በጣሙን
ማብቀልን ልወቀው
የመትረፍረፍ ጣእሙን
#ደሞ
አገላግሉኝ ብዬ
ደቦ አልጠራብሽም
ቀጥቅጪኝ ግዴለም
ባንቺ ተደብድቦ
ማያበቅል መሬት
‘ማያጭድ ሰው የለም
=== || ===
@libmalet
@libmalet
ጥላ ፍለጋ
የህይወትን ብርታት ሳውጠነጥን እነሆ ዘመናት ተቆጠሩ፡፡ በርግጥ የዛሬው
ስሜቴ ይለያል፡፡ ከምጎነጨው ድራፍት ጋር ተዋህዶ ወደ ውስጤ እየገባ
ያለውን የነገር ቋት መረዳት አለመቻሌ ነው፤ ክፋቱ፡፡ የሚለቀቀው ሙዚቃ
የራሱ የሆነ ሚና ቢኖረውም፤ ህመሜን የማናር እንጂ የመረጋጋት ሀይል
አላጎናፀፈኝም፡፡ የሰው ግርግርም፤ እንዲሁ:: የስሜት ንረት ጥጉን ቀድሜ
ስለምገነዘብ፣ ምልከታዬ ላይ እየተጨነቅሁ አስታምማለሁ፡፡
የሚገርመው፤ .. “መገፋት ደግ ነው!” ትል ነበር፤ አያቴ፡፡ እንዲያው... በዚህ
ሰሞን፣ ከያቅጣጫው የሚወረወረው በትር መብዛቱ:: አህያ አይደለሁ፤ በጅብ
ጩኸት የምፈርስ፡፡ እንዲያው ለመሆኑ ውስጥ ውስጡን እየተሹለከለከ፣ ነገር
የሚተበትበውን የሰው አውሬ፤ ማለቴ ነው፡፡
ነገርን ነገር ያነሳው የለ ፤ በደርግ ዘመን ነው አሉ!... ሁሉም ኢትዮጵያዊ፣
ኢህአፓ ሆኖ በተጠመቀበት ሰሞን፣ የፓርቲውንም ሆነ የአባላቱን ስም
በማጉደፍ ላይ የተጠመዱ የመንደር አለሌዎችና ጠንካራው የደህንነት
መዋቅር፣ በፅንፈኞች እጅ ወድቆ ባልተገባ ሁኔታ አገልግሎት ሰጡ፡፡ ይህንን
ስውር ደባ ለማምለጥ ሲሉ አባላቱ፣ ለህፃናት በየለቱ የጨርቅ ኳስ እየሰፉ
ይሰጧቸው ነበር፡፡ ታዲያ ቀን በቀን አዳዲስ ኳስ የሚያገኙ ህፃናት፣ የትም
ምንም ቢላኩ ደስተኞች ነበሩ... ይባላል፡፡ በርግጥ መልዕክቱም፣ የነገ
ኳሳችሁን የሚሰጧችሁ አቶ “እገሌ” ናቸው፤ እንደ ልባችሁ ተጫውታችሁ
ስትጨርሱ፣ ትሰጧቸውና፣ አዲስ ኳስ ሰፍተው ይሰጧችኋል...ይባላሉ...አሉ::
በፍቅር ያደርጉታል፤ ህፃናቱ፡፡ በዚህ መንገድ የኢህአፓ አባላት በኳሱ ውስጥ
ደብዳቤ ይለዋወጡ ነበር፡፡ ሀገር በቀል የመረጃ መረብ እንበለው?
እና’ማ ...ሀገር ለማቆም በስውር ሰሩ፡፡ ለእኔ ግን፤ ሀገር... የኢህአፓን ኳስ
ትመስላለች፡፡ ከአባት ለልጅ የምትበረከት ውድ ስጦታ፤ በስስትና በስጋት
የተሞሸረች፡፡ በውስጧ ህልውና የቋጠረች:: ስስቱ የሚመነጨው ከሁለቱም
ወገን ሲሆን ስጋቱ ግን የአቀባዩ ብቻ ይመስለኛል፡፡ እውን በትክክል ተጫውቶ
ለቀጣዩ ያስረክብ ይሆን!!? የሚል የተደበላለቀ ስጋት፡፡ ሀገሬ እንደዚያ ናት፡፡
ሳስበው ...ሳስበው ኳሱዋ ሀገሬ ናት፡፡ ልክ እንደ እንቁላል ውስጧ ህይወት
አለ፡፡ እንክብካቤ ትሻለች:: በርግጥ እንቁላሉ ከወደቀ ይሰበራል፤ ሀገርም
እንዲሁ፡፡ ኳሷ ግን በእርግጫ ብዛት የበከተች፣ የተበጣጠሰችና የነተበች
ብትሆንም፣ የሰው አሻራ ነውና ክብር አላት፤ ምንም ቢሆን:: እናም ሀገሬ ኳሷን
ትመስላለች፡፡ ትበክታለች፤ ትታደሳለች፡፡ ውስጧ ግን ሚስጥር አርግዟል፡፡
አንዳንዴ ሳስባት መንፈስ ትሆንብኛለች፡፡ ከውስጧ የተሸከመችውን እውነት፤
አደራ የቀረፀላት ማነው ?? ኳሷ የኢህአፓን መልዕክት ስትሰንቅ፣ ሀገሬስ
የማንን ህልም ይሆን የተሸከመችው???...እላለሁ፡፡
ይገርማል!! የሴራውና የተንኮሉ ብዛት ውስጤን ቢያሳሳውም፣ ኳሷን
እመስላለሁ፡፡ የውስጤን ሀቅ አዝያለሁ፡እራሴ እቋጥራለሁ፤ እራሴ
እፈታዋለሁ፡፡ ያው...የአለት ያክል ቢበረታም፣ የህልሜ ብርታት ያይላልና
አፈራርሰዋለሁ:: ለምን ቢባል፣ ህልም ህይወት ነውና -- ርዕይ፡፡ ህልም፤ ሀገር
ነውና -- ሠላም፡፡ ህልም፤ ጉዞ ነውና -- ስንቅ፡፡ ህልም፤ ባህል ነውና ---
ውህደት:: ብቻ ሀገር ህልም ናት፤ የህልምም ህልም፡፡
የተደበላለቀ ስሜቴን ለመረዳት ያደረግሁት ጥረት፣ ጠንካራ ተብሰልስሎት
ውስጥ ዶለኝ፡፡
@libmalet
* * *NEW YEAR* * *
Going To Be Started . . .
& I Wanna Be The 1st Person
Who'll Wish U
12 Months Of Happiness. . .
52 Weeks Of Fun . . .
365 Days Of Success. . .
8,760 Hours Of Good Health . . .
525,600 Minutes Of Good Luck . . .
3,153,600 Seconds Of Smiling . . .
Happy New Year...@2012@
True love finds you in the most unexpected places, makes you go through hurdles that you never think you'll overcome. But saves you when you need it the most, and shows you just show beautiful the world can be on the other side.
📷 © Diogo Vieira
If I date you I want to know you. I don't mean your favorite color, food, and your middle name. I want to know those, too, but I mean, tell me about the time you broke your arm learning to ride a bike. Tell me the nightmares you have, the struggles you've dealt with, if you ever feel alone. Tell me if there's a voice in your head that tells you "you're not good enough". Tell me your secrets, your thoughts, about your childhood, how you got that scar on your knee, if you sucked your thumb. Tell me about your first love and heartbreak. I want to know everything and I won't settle for less. Because if I date you, I want it to last. If I date you, I'm dating you for a reason. ❤️💛
📷 © Lucy Litman
🍀2🍀🍀🍀0🍀🍀🍀1🍀🍀2🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀እንኳን አደረሳችሁ🍀🍀🍀🍀🍀🍀
🍀🍀🍀🍀🍀🍀በዚህ አዲስ አመት🍀🍀🍀
የተጣሉ የሚታረቁበት
የተራራቁ የሚገናኙበት
የተፋቀሩ የሚጋቡበት
የተጋቡ የሚያፈሩበት
የወለዱ የሚያሳድጉበት
ያደጉት የሚጦሩበት
የሰሩ የሚያተርፉበት
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
የሰረቁ የሚቀጡበት!
የተማሩ የሚያውቁበት
የተመረቁ የሚሰሩበት 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
ለመሪዎች ጥበብን
ለሕዝቡ ማስተዋልን
ለአክቲቪስቶች እዉቀትን!
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
የታመመ የሚድንበት
የዳነ የሚያመሰግንበት
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻
የኢትዮጵያን ብልጽግና የምናይበት
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼👍🌼
ከብሔርተኝነት....☠
ከጎጠኝነት..........✊
ከጥላቻ ............🗣 የምንድንበት
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
የፍቅር🌿
የሰላም🌱
የብልጽግና🍀
የፍሰሃ 🌷 🌷🌷🌷🌷 አመት ይሁንልን!!!
💘 አ🌺🌺🌺🌺🌺
🌹ሜ🌺🌺🌺🌺🌺
🌻 ን💐💐💐💐💐
እንኳን ለ 2012 ዓ.ም አደረሰን!!!
@libmalet
@libmalet
@AASH23
አስተማሪ ስለሆነ ሁሉም ያንብበው
ከእለታት አንድ ቀን አንድ ወጣት ወደ አንድ ሀገር ለመሄድ በጉዞ ላይ ሳለ ይመሽበትና በጅብ ከምበላት ብሎ ወደ አንዲት አነስተኛ መንደር ያመራል። ከመንደሩም ደርሶ <<የመሸብኝ እንግዳ ነኝ አሳድሩኝ>> ሲል ይማፀናል።
የቤቱም ባለቤት ምንም ቤቱ ጠባብ ብትሆንም ሰው አክባሪ እንግዳ ተቀባይ ነበርና <<ይግቡ>> ሲል ወጣቱን ወደ ቤቱ ይጋብዘዋል። እሱም ገብቶ ትንሽ እንዳረፈ ለእግሩ ውሀ ተሰጥቶት ከታጠበ በኃላ እራት ይቀርብለትና ይበላል። የቤቱ ባለቤት ለወጣቱ ልጅ መኝታ ሲያስብ የመኝታ ቦታ ስለሌለ ጥቂት ሲያስብ ቆየና ሌላ አማራጭ ስለሌለው ወጣቱ ከልጃገረድ ልጁ ጋር እንዲተኛ ይወስናል።
<<እንግዳው ልጄ እዚህ አልጋ ላይ ከልጄ ጋር ተኛ>> ብሎ አልጋውን ለሁለት ቦታ በትራስ ይከፋፍልና ያስተኛዋል።
ወጣቱ ልጅም በታዘዘለት ቦታ ላይ አንዴም እንኳን ገልበጥ ሳይል በሰላም ተኝቶ ለሊቱ ነጋ
ጠዋት ቁርስ በልቶ አመስግኖ ተሰናብቶ መንገዱን ይጀምራል።
ማታ ላይ አብራው የተኛችው ልጃገረድ እርሻ ላይ ድንች ስትኮተኩት በአጥር ተንጠራርቶ ይመለከታትና
<<እህት መሄዴ ስለሆነ በአጥር ዘልዬ ልሰናበትሽ?>> አላት ልጅቱም በአግራሞት ፈገግ ብላ
<<አንተ ማታ ትራስ መዝለል ያልቻልክ ሰውዬ አሁን እንዴት አጥር ልዝለል ትላለህ?>> አለችው። ልጁም ትንሽ ፈገግ ብሎ.......
<<የኔ እህት መተው አለመቻል አይደለም። ሰው የቻለውን ሁሉ አያደርግም ያ እንግዳ አክባሪው አባትሽ ያሰመረው ትራስ የእምነት መስመር ነው የመታመን አጥር ነው። አጥሩ ይርዘምም ይጠርም ብቻ ታጥሯል። ያንን አጥር ማክበር የእምነት ወሰንን አለማለፍ እንጂ አለመቻል አይደለም።
ስለዚህ እኔም መዝለል ስላልቻልኩ አይደለም መስመር ማለፍ ስላልፈለኩ ነው።>> አላት
ይህ ታሪክ እያንዳንዳችን እራሳችንን የምንጠይቅየምገዛው
ተት ነው።
ስንቶቻችን ነን ፍላጎታችንን አሸንፈን ለቃላችን ወይም እምነቱን ለጣለብን ሰው የምገዛው
@libmalet
🔆ጠቃሚ ምክር ለወንዶች“🔆
"1- ሴት ልጅ ምቾትን ስለምትፈልግ ያለህን ነገር ሳትሰስት
አጋራት። 😎
2- ሴት ፍቅርህን እንድትገልጽላት ትሻለች። (ባገኘከው
አጋጣሚ) ፍቅርህን ከመግለጽ ወደኋላ አትበል።
3- ሴቶች ግትር ወንዶችን ይጠላሉ። ደካማ ወንዶችን ደግሞ
ይንቃሉ አንተ ጥንካሬ በሚያስፈልግበት ቦታ ጠንካራ ሌላ ጊዜ
ደግሞ ገር ለመሆን ሞክር።
4- ሴቶችን መልካም ንግግር፡ ውብ ገጽታ፡ ንጹህ ልብሶችና
ጥሩ መአዛ ስለሚማርካቸው ሁሌም እነዚህ ነገሮች
እንዲኖሩህ ጥረት አድርግ።
5- ለሴት ቤቷ የቤተ መንግስት ያህል ክብር የምትሰጠው
ስፍራ ነው። ቤቷ ስትሆን ዙፋኗ ላይ በክብር የተቀመጠች
ንግስት ያህል ክብር ይሰማታል። በምንም ተአምር ይህን ቤተ
መንግስቷን የሚያፈርስባትን ነገር እንዳትፈጽም። ከንግስና
ዙፋኗ ላይ ልታወርዳትም አትሞክር። ይህን ካደረክ ንግስናዋን
እንደመቃወም ይቆጠራል። ለንጉስ ንግስናውን ከመቀናቀን
የበለጠ ትልቅ ወንጀል የለምና ጥንቃቄ አድርግ።
6- ሴት የቱን ያህል ብትወድህም ቤተሰቧን ማጣት
አትፈልግም። አንተን ከቤተሰቦቿ በላይ እንድትወድህ
ለማድረግ አትጣር። ይህን ማድረግ ፍጻሜው የማያምር
ጠላትነትን ሊያመጣብህ ይችላል።
7- ሴት ከጎንህ (ጠማማ አጥንት) መፈጠሯን አትዘንጋ። ይህ
አፈጣጠሯ የውበቷ ሚስጥር መሆኑን እወቅ። ትንሽ ስህተት
ባየህ ቁጥር አቃናታለሁ እያልክ እንዳትሰብራት ተጠንቀቅ።
ስብራቷ ፍቺ ነው። ላቃናት ከሞከርኩ ትሰበራለች በማለትም
የባሰ እንድትጠም መንገድ አትክፈትላት። መካከለኛ ሰው
ሁንላት።
8- ሴት አንዳንዴ የዋልክላትን ውለታ ልትዘነጋ ትችላለች።
(ስትናደድ) ያደረክላትን ነገርም ልትክድ ትችል ይሆናል። ነገር
ግን እንዲህ አደረገች በማለት ብቻ እንዳትጠላት። ይህን
ባህሪዋን ባትወድላት ሌሎች የሚስቡህ ብዙ ባህሪዎች
እንዳሏት አትዘንጋ።
9- ሴት አካላዊ ድካምና ስነልቦናዊ ጫና ሊያርፍባት
ይችላል። so ትእዛዝ አታብዛባት።
10- ሴት አንተ ዘንድ ያለች (የፍቅር) ምርኮኛህ መሆኗን
አትዘንጋ። ምርኮኛህን በጥሩ ሁኔታ ያዛት፡ እዘንላት፡ በድክመቷ
(የምትፈጽመውን ስህተት) እለፋት። ምርጥ የሂዎት አጋርህ
ትሆናለች።"
@libmalet
ካነበብኩት እና የወደድኩት ታሪክ ነው ተጋበዙልኝ
💫💫💫💫
.............የጭንቅላት ጨዋታ...........
የሰው ልጅ እንዴት እንደሚያስብ ስታቅ ሰውን ማታለል በጣም ቀላል ነው ተከታዩን ታሪክ ጋበዝኳቹ...
የሳይኮሎጂ ፕሮፌሰሩ ወደ ክፍል ገብቶ የእለቱን ወሳኝ ትምርት ለመጀመር ወደ ቦርድ እንደዞረ ፉጨት ሰማ። ወደ ተማሪዎቹ ዞሮ ማን እንዳፏጨ ጠየቀቃቸው ፣ሁሉም ዝም አሉ።
ፕሮፊሰሩ ተረጋግቶ ፣ እስክሪቢቶውን ወደ ኪሱ እየከተተ ፣ የዛሬው ሌክቸር እዚ ላይ ያበቃል፣ አለና ፈገግ ብሎ ነገር ግን መጀመሪያ አንድ ታሪክ እነግራችኋለው አላቸው። ሁሉም በጉጉት መጠበቅ ጀመረ
" ትላንት ቤቴ እንቅልፍ ስላስቸገረኝ ፣ዝም ብዬ ተነስቼ ነዳጅ ሞልቼ በዛውም ልናፈስ ለዛሬም ጊዜ ለመቆጠብ ከመሽ ወጣሁ ነዳጅ ከሞላሁ በኋላ ከትራፌክ ነጻ የሆነው መንገድ ላይ እየተንሸራሸርኩ ከሆነ ድግስ ቦታ የወጣች የምትመስል ቆንጂዬ ወጣት አየሁ።
መኪናዬን አዙሬ እርዳታ እንደምትፈልግ ጠየኳት "ታክሲ እንዳጣች እና ቤቷ እንዳደርሳት ጠየቀችኝ"
ጋቢና ገባች....ማውራት ጀመርን....ውበት ብቻ ሳይሆን ባወራነው ርእስ ሁሉ በጣም ስማርት ጭንቅላት እንዳላት ከምታወራው መገመት ቻልኩ።
ቤቷ እንደደረስን ፣በጣም ጥሩ ሰው እንደሆንኩ ነገረችኝ ፣እኔም ጥሩ አስተሳሰብ እንዳላት ነግሬያት በሌላ ጊዜ ተገናኝተን ሻይ ቡና እንድንል ጠየኳት በሀሳቤም ተስማማች ፣ዩኒቨርስቲ ፕሮፌሰር እንደሆንኩ አውርተን ፣ስልክ ተለዋወጥን።
ልንለያይ ስንል አንድ ነገር ላስቸግርህ ስትለኝ ፣ምንም ችግር የለውም አልኳት ።"ወንድሜ አንተ የምታስተምርበት ዩኒቨርስቲ ውስጥ ተማሪ ነው፣ በኛ ግንኙነት እንዳይጎዳ ቃል ግባልኝ" አለችኝ ....ችግር የለም ብዬ ስሙን ጠየኳት ስሙንም ነገረችኝ።
ምናልባት ብዙ ተማሪዎች በዩኒቨርስቲው ውስጥ ስለሚማሩና ተመሳሳይ ስም ሊኖራቸው ስለሚችል ወንድምሽን እንዴት ልለየው እችላለሁ ? ስል ጠየኳት።
እሷም :- ወንድሜ አንድ መለያ ባህሪ አለው በሱ ታውቀዋለህ፣ ፉጨት ማፏጨት ያዘወትራል። አለችኝ
ከዛ ሁሉም ተማሪ ወደ አፏጨው ልጅ ዞሮ ማየት ጀመረ
ፕሮፌሰሩም :- "የሳይኮሎጂ PHDዬን ተምሬ እንጂ ገዝቼ አይደለም ያገኘውት ና ውጣ ብሎ ጆሮውን ይዞ ከክፍል አስወጣው
@libmalet
