en
Feedback
Wcu main campus

Wcu main campus

Open in Telegram

Show more
Ethiopia7 023The category is not specified
3 383
Subscribers
-124 hours
+147 days
+830 days
Posts Archive
በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ በ23/06/2015 ዓ.ም በሁለት ተማሪዎች መካከል በተፈጠረ አለመግባባት ለጉዳዩ መንስኤ የሆኑ ነገሮችና በዩኒቨርሲቲው የተሰጠ እልባት እንደሚከተለው ቀርቧል። በተማሪዎች መከካል ለተፈጠረው አለመግባባት መነሻ መንስኤው የካቲት 23/2015 ዓ.ም የተከበረው የ127ኛው የአድዋ ድል በዓል ነው በማለት አንዳንድ ሚዲያዎች ከእውነት ያፈነገጠ አሉባልታ ወሬዎችን በማናፈስ ላይ እንዳሉ ከተለያዩ የመረጃ ምንጮች ለመረዳት ተችሏል። በዕለቱ የተፈጠረውን አለመግባባት ምክንያት በማድረግ ጥቂት ተማሪዎች ጉዳዩን ሌላ መልክ ለማሳዝ ሙከራ ቢያደርጉም በፀጥታ ሀይልና በግቢው ማህበረሰብ የጋራ ቅንጅት መረጋጋት ተችሏል። ለተፈጠረው አለመግባበት መንስኤው በሁለት ተማሪዎች መካከል በተፈጠረ የግል ፀብ መነሻ ሲሆን በግጭቱ ላይ የተሳተፉ ተማሪዎች በጥፋታቸው ልክ ጉዳያቸው ተጣርቶ ለአንድ ዓመት ከትምህርት ገባታቸው እንዲታገዱ የዩኒቨርሲቲው ሴኔት የካቲት 24/2015 ዓ.ም ውሳኔ አስተላልፏል። በግጭቱ ጉዳት የደረሰበት አንድ ተማሪ በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የንግስት እሌኒ መሀመድ መታሰቢያ ኮምፕሬንስቪ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ህክምና እየተደረገለት ሲሆን ተማሪው በጥሩ ጤንነት ላይ ይገኛል። በአሁን ሰዓት የዩኒቨርስቲው መደበኛ የመማር ማስተማር ስራ በሰላማዊ ሁኔታ ተጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን ተማሪዎች የአንደኛ ሴሚስተር ማጠቃለያ ፈተና እየተፈተኑ ይገኛል። ነገረ ግን በውሸት ፕሮፓጋንዳ የተጠመዱ አንድንድ ሚድያዎች የበሬ ወለደ ሀሰተኛ መረጃ እያናፈሱ እንዳሉ ዩኒቨርስቲው ይገነዘባል። የእነዚህ አካላት ስውር ዓላማ በሁሉም የመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ሰላማዊ መማር ማስተማር ሂደት ሰላማዊ እንዳይሆን ለማሰናከል ታቅዶ የሚሠራ ስራ እንደሆነ አንዱ ማሳያ ነው። ስለዚህ ከላይ የተጠቀሱ አካላትና ጥቂት ሀሰተኛ ማህበራዊ ሚዲያዎች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡና ማህበረሰቡ ትክክለኛውን መረጃ ከዩኒቨርሲቲው ማህበራዊ ገጾች ማግኘት የሚችል መሆኑን ዩኒቨርሲቲው በአንክሮ ማሳሰብ ይወዳል። ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የካቲት 29/2015 ዓ.ም @wachemoo

photo content

ሰላም ዉድ የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ሐሙስ ዕለት ማለትም በቀን 23/06/2015 ዓ.ም በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን በድርቅ ምክንያት ለተጎዱ ወገኖቻችን የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃግብር ስለምንጀምር ሁላችሁም ከወዲሁ ዝግጅት እንድታደርጉ በታላቅ ትህትና እናሳውቃለን ። ሰዉን ለመርዳት ሰዉ መሆን በቂ ነዉ! @wachemoo

+1
remed fresh male dorm placement.pdf5.33 KB

photo content

photo content

photo content

photo content
+9

የትምህርት ጥራትን በማረጋገጥ ብቁና ተወዳዳሪ ዜጎችን ለማፍራትና ሰላማዊውን የመማር ማስተማር ሂደት ለማስቀጠል የተሟላ ዝግጅት መደረጉን የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ አስታወቀ ዩኒቨርሲቲው ከ1 ሺህ በላይ የ2015 ዓ.ም አዲስ ገቢ ተማሪዎችን በመቀበል ላይ ይገኛል። በቅበላ ፕሮግራሙ የተገኙት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር ሀብታሙ አበበ እንደተናገሩት በሀገራችን ትምህርት ላይ መንግስት የተለየ ለውጥ ለማምጣት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ በሚገኝበት በዚህ ወቅት የመማር ማስተማሩን ስራ መንግስት ባስቀመጠው ተልዕኮ መሰረት በብቃት ለመወጣት ሁሉአቀፍ ዝግጅት ሲያደርግ መቆየቱን አስረድተዋል። በ2015 ዓ.ም አዲስ ዩኒቨርሲቲውን ለሚቀለቀሉ ተማሪዎች ምቹ አከባቢ በማዘጋጀት የተሟላ ለማድረግ ሰፊ ስራ ሲሰራ መቆየቱን ፕሬዝዳንቱ ገልፀዋል። በዘንድሮው የአዲስ ተማሪዎች አቀባበል ፕሮግራም ላይ የአከባቢው ማህበረሰብ የተለመደውን ዝግጅት በማሰናዳት እንግዳ ተቀባይ ማህበረሰብ መሆኑን ያሳየበት ነው ያሉት ዶ/ር ሀብታሙ ዩኒቨርሲቲው የሚታወቅበትን የሰላም አምባሳደርነቱን ለማስቀጠል ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ጠንካራ ቅንጅት በመፍጠር እየሰራ ይገኛል ብለዋል። አዲስ ዩኒቨርሲቲውን የተቀላቀሉ ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ከአላአስፈላጊ ድርጊቶች በመቆጠብና የትምህርት ጊዜያቸውን በሚገባ በመጠቀም ብቁና ተወዳዳሪ ዜጎች ለመሆን በትጋት መስራት እንዳለባቸው ፕሬዝዳንቱ አሳስበዋል። የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲን ቀዳሚ ምርጫቸው በማድረግ አዲስ የተቀላቀሉ ተማሪዎችን በተሻለ ሁኔታ ለማስተናገድ ምቹ የመኝታ ቤት፣ ቀልጣፋ የምግብ አገልግሎት የሚያገኙበት ሁኔታ ማመቻቸትና በግቢ ውስጥ የሚገኘው የተማሪዎች ክሊኒክ በሚገባ መደራጀቱን የገለፁት ደግሞ በዩኒቨርሲቲው የአስተዳደርና ተማሪዎች አገልግሎት ምክትል ፕሬዚዳንት ዶ/ር ኑሪ ለፌቦ ናቸው። ተማሪዎችን ወደ ዩኒቨርሲቲው ለመሸኘት የመጡ የተማሪ ወላጆች በሰጡት አስተያየት በዩኒቨርሲቲው የተደረገው ዝግጅትና አቀባበል የሚበረታታ መሆኑን ተናግረው ዩኒቨርሲቲው እያሳየ ባለው ፈጣን ለውጥ መደነቃቸውን ገልፀዋል። ዩኒቨርሲቲውን አዲስ የተቀላቀሉ ተማሪዎችም ዩኒቨርሲቲው የሚፈልጉት ዓይነት ምቹ ሆኖ እንዳገኙት ገልፀው የመጡበትን ዓላማ ከግብ ለማድረስ ጊዜያቸውን በአግባቡ በመጠቀም ትኩረታቸውን ትምህርት ላይ ብቻ በማድረግ ውጤታማ ዜጋ ሆኖ ለመውጣት መዘጋጀታቸውን ገልፀዋል። አንድ ሆነን እንስራ ኢትዮጵያ ታሸንፍ ! @wachemoo

photo content

photo content

የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ መግቢያ በር እና አደባባይ! ****** በሩ እና አጥሩ የሀድያን ባህልንና እሴቶችን የያዘ ሲሆን በርካታ ትርጉሞች አሉት። ለምሳሌ አጥሩ የሚያሳየው የ"ቦያ ሴሌሜ" ጭፈራ ምልክት ነው። የቦያ ሴሌሜ ጭፈራ ትርጉም በሀዲያ ባህል አንድነትን (Mateeyyomma)፣ ህብረት እና ከፊት ለፊት ያለው መሪ ከኋላ ያሉትን ተከታይ ማየትና አብሮ ከአንድነትና ትብብር መንገድ እንዳይወጣ አድርጎ መምራት የሚየሳይ ነው። ይህም ሰፋ ተደርጎ ሲወሰድና ትርጉም ሲሰጥ ሰዎች ተያይዘን በመረዳዳት፣ በመተጋገዝ፣ ሰላምን በማስቀደም ስራን በትጋት ሰርቶ ብልጽግናን በማረጋገጥ ወደ ከፍታው ማማ መገስገስ ማለት ነው። "ሴሌሜ" ማለት በሀዲይሳ ቋንቋ ሴት ልጅን ለማሞገስ የሚጠቀሙት ቃል ሲሆን ትርጓሜውም ወደር የሌላት ቆንጆ፣ ውብ፣ አቻ የለሽ እና የምታማልል ማለት ነው። ዛሬ በጓደኝነትና በእጮኝነት ላሉ የነገ ባለትዳሮች ሰርግ የሚያደርጉበት፣ ወጣቶች ፎቶ የሚነሱበትና የሚዝናኑበት እጅግ ማራኪና ውብ አደባባይ ወደ መሆን ደረጃ ደርሷል። ሁላችሁም ለሰርግ፣ ለልደት እና ለሌሎችም መዝናኛዎች አደባባዩን በነጻ እንድትጠቀሙ የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ኑ ይላችኋል! Wachemo University's new entrance and square. ****** The gate and fence has several meanings that show an extensive culture of Hadiya people; for example the fence portrays the symbol of the "Boya Seleme" dance. The meaning of "Boya Seleme" dance in Hadiya culture demonstrs growing together (Maateyyomma), union and the leader in the front sees the follower behind and leader to a better path together. This name depicts the meaning of togetherness, helping each other, , and prioritizing peace, work, social life and development of the people. "Seleme" in derived from Hadiyya language that the people use so as to praise a girl’s beauty that means the most beautiful girl, and her beauty is incomparable with others. The new gate of Wachemo University is becoming an attractive and beautiful place where many people hold weddings and other events. Therefore, Wachemo University invites you all to use the square for weddings, birthdays, and other events without any cost. Let Your Light Shine in the Society! August 27, 2022

photo content
+3

photo content
+3

ዋቸሞ ዩኒቨርስቲ የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ተማሪዎችን እያስመረቀ ይገኛል @wachemoo

photo content

ለስፖርት አፍቃሪያን በሙሉ አርሰናል Vs ክርስታል ፓላስ የሚያደርጉትን የ2022/2023 የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የመክፈቻ ጨዋታ በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ DSTV አዳራሽ በልዩ ሁኔታ የምናሳይ መሆኑን እንገልጻለን። የጨዋታ ሰዓት ምሽት 4:00 @wachemoo መልካም ጨዋታ! የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ህብረት

photo content

ዋቸሞ በምሽት
+9
ዋቸሞ በምሽት

photo content