en
Feedback
Suleman Abdela ሱሌማን አብደላ

Suleman Abdela ሱሌማን አብደላ

Open in Telegram

Suleman works for peace

Show more
Ethiopia15 998The category is not specified
901
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Similar Channels
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
December '24
December '240
in 0 channels
November '240
in 0 channels
Get PRO
October '240
in 0 channels
Get PRO
September '240
in 0 channels
Get PRO
August '240
in 0 channels
Get PRO
July '240
in 0 channels
Get PRO
June '240
in 0 channels
Get PRO
May '240
in 0 channels
Get PRO
April '240
in 0 channels
Get PRO
March '240
in 0 channels
Get PRO
February '240
in 0 channels
Get PRO
January '240
in 0 channels
Get PRO
December '230
in 0 channels
Get PRO
November '230
in 0 channels
Get PRO
October '230
in 0 channels
Get PRO
September '23
+28
in 0 channels
Get PRO
August '23
+67
in 0 channels
Get PRO
July '23
+11
in 0 channels
Get PRO
June '23
+20
in 0 channels
Get PRO
May '23
+13
in 0 channels
Get PRO
April '23
+15
in 0 channels
Get PRO
March '23
+8
in 0 channels
Get PRO
February '23
+8
in 0 channels
Get PRO
January '23
+13
in 0 channels
Get PRO
December '22
+10
in 0 channels
Get PRO
November '22
+57
in 0 channels
Get PRO
October '22
+128
in 0 channels
Get PRO
September '22
+196
in 0 channels
Get PRO
August '22
+118
in 0 channels
Get PRO
July '22
+610
in 0 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
09 December0
08 December0
07 December0
Channel Posts
ይህ ሰው ከባድ ሰው ነው። ይህ ሰው አጋር ቢያገኝ ወሳኝ ምዕራፍ ከፋች ሰው ነው። ዳሩ ግን ወርቅና አልሙኒየም እየሰጡ ዶላር የሚበደሩ መሪዎች እስካሉ ድረስ አፍሪካ ባሪያ ከመሆን አትድንም ብሎ ነበር
ይህ ሰው ከባድ ሰው ነው። ይህ ሰው አጋር ቢያገኝ ወሳኝ ምዕራፍ ከፋች ሰው ነው። ዳሩ ግን ወርቅና አልሙኒየም እየሰጡ ዶላር የሚበደሩ መሪዎች እስካሉ ድረስ አፍሪካ ባሪያ ከመሆን አትድንም ብሎ ነበር ጋዳፊ። የዚህን የሰው ሀሳብ ወደተግባር ለመቀየር 50 ይፈጅብናል። እኛም አንድ ሰሞን ከምዕራባዊያን ጋር አንፈልጋችሁም ብለን ዘመቻ ከፍተን #nomore ስንል ኖረን በሉ ከዚህ ቡኋላ እንዳትሉ የሚል ቀጭን ትዕዛዝ የተሰጠን። አይሰሙትምና አይተገብሩት እንጅ ቢሆን ትልቅ ድልና የነፃነት ምልክት ነበር። ግን ምን ዋጋ አለው። ሱሌማን አብደላ

2
ከፍተኛው የእናትነት መስዋዕትነት🙌🏼❤️ በ Zemelak Endrias ሴቷ ኦክቶፐስ (ባለ ብዙ እግሮች የአሳ ዝርያ) ይህች የባህር ዝርያ በአምስት አመት የህይወት ቆይታዋ አንዴ ነው መራባት የምትችለው:: ነገር ግን ልጆቿን ለማየት አትታደልም🤗ነፍስ ሰጥታ ነፍሷን የምታጣ እናት ያደርጋታል !! በአንድ ጊዜ ከ50,000 እስከ 80,000 እንቁላሎችን የምትጥለዋ ኦክቶፐስ እንቁላሎቿን የምትጥለው ድንጋያማ የባህር ክፍል በመፈለግ ነው:: እንቁላሎቿ ተፈልፍለው ራሳቸውን እስኪችሉ ከ6 እስከ 10 ወራቶች ድረስ ይፈጃል:: በእነዚህ ጊዜያቶች ሁሉ ኦክቶፐሷ ምግብ አትበላም ምንም አትቀምስም - አንዳንዴ ለተከታታይ 53 ሳምንታቶች በሚዘልቀው የመራቢያ ጊዜያቶች ውስጥ አይኗን ከእንቁላሎቹ ላይ ሳትነቅል ተፈልፍለው እድገታቸውን እስኪጨርሱ አብራቸው ትቆያለች:: በእነዚህ ጊዜያት ውስጥ ምግብ አትበላም - ይልቅስ ለእንቁላሎቹ በውስጧ ያለውን ምግብ: ንጥረ ነገር እና ኦክስጅን አሟጣ ትሰጣቸዋለች:: ከእነዚህ እንቁላሎች ውስጥ የበረቱት ተፈልፍለው ያልተሳካላቸው ደግሞ በዚያው ይቀራሉ:: አሳዛኙ ነገር በስተመጨረሻ በረሃብ እና በድካም እስከወዲያኛው ታሸልባለች:: ከረሃቧ የተነሳ እና እንቁላሎቹ እድገታቸውን እንዲጨርሱ ለማድረግ ስትል በስተመጨረሻ የራሷን ስጋ መብላት እንደምትጀምር ሳይንቲስቶች ይናገራሉ - አለም ላይ ከፍተኛው የእናትነት መስዋዕትነት ይባላል!! ይህ ብቻ አይደለም ወንዱ ኦክቶፐስም ቢሆን ግንኙነት በፈፀመ በሳምንታቶች ወይም በወር ጊዜ ውስጥ ይሞታል:: ምክንያቱ ደግሞ ሴቷ ኦክቶፐስ በግንኙነት ወቅት ለረጅም ጊዜ ስለምታቆየው ከግኑኝነቱ በኃላ ጉልበት ያጣል:: በዚህም የተነሳ የሌሎች የባህር ፍጥረታት የእራት ሲሳይ ይሆናል🤗
379
3
ታጭታም ይሆናል ብሏል የኤንቢሲው ተንታኝ። ሌሎች ሰሜን ኮሪያን ከማንም በላይ ጠንቅቀን እናውቃለን የሚሉ ተንታኞች ግን፣ ይቺ ልጅ ለታላቅ ሥልጣን ታጭታለች ብሎ ለመናገር ጊዜው ገና ነው ሲሉ ያሳስባሉ። በሰሜን ኮሪያ ጉዳይ ላይ መጽሐፍ የጻፉት እና በቅርቡ ሮይተርስ ዘገባ ላይ የተጠቀሱት ቹን ሱ ጂን ደግሞ “በጭራሽ” ይላሉ። የፎቶው ባለመብት, KCNA VIA REUTERS የምስሉ መግለጫ, ኪም ከልጃቸው ጋር “በጭራሽ” ምን? “በጭራሽ ይቺ የኪም ልጅ ለሥልጣን የመታጨት ዕድሏ ዜሮ፣ ከዜሮም በታች ነው” ብለዋል። የእሳቸው መከራከሪያ ደግሞ የጾታ ጉዳይ ነው። በሰሜን ኮሪያ ሴት ልጅን ወደ ከፍተኛ ሥልጣን ለማብቃት ጊዜው ገና ባሕል አልሆነም። ታዲያ ለምን በቴሌቪዥን ታየች? ተብለው ሲጠየቁ “ኪም ሚሳኤል አስተኳሽ አምባገነን መሪ ብቻ ሆነው መታየት አይልጉማ” ብለዋል። “ልጃቸውን የሚወዱ አፍቃሪ አባት እንደሆኑ ለሕዝብ ማሳየት ስለፈለጉ ብቻ ነው” ይላሉ። ይቺ ልጅ ለሥልጣን ታጨችም አልታጨች በሰሜን ኮሪያ ከኪም ቀጥሎ የሚጠራው ስም የሴት ነው። ምክንያቱም የኪም እህት አሁንም ቢሆን አድራጊ ፈጣሪ ናት። ስሟም ኪም ዮ ጁንግ ይባላል። ከሁለት ዓመት በፊት ኪም ጆንግ ኡን “ታሟል፤ ከዚህ ወዲህ አበቃለት” ሲባል፤ “ውፍረቱ ገደለው” ተብሎ በምዕራብ ሚዲያ ሲሟረትበት በቴሌቪዥን ብቅ ብላ አገሩን ልክ ያስገባች የኪም እህት ዮ ጆንግ አይደለችምን? እህት ኪም ዮ ጆንግ በቅርቡ ጎረቤት ደቡብ ኮሪያን ከፍ ዝቅ አድርጋ አስጠንቅቃለች። ማንም ምንም አላላትም። በተደጋጋሚ በደቡብ ኮሪያ ላይ ዛቻ እና ማስፈራሪያ በመሰንዘር ማን ይደርስባታል? ዛቻ ብቻ ሳይሆን ሠራዊት ድንበር ድረስ አስጠግታም ታውቃለች። አሁን የኪም እህት ሳትሆን የኪም ልጅ ናት መነጋገሪያዋ። የፎቶው ባለመብት, GETTY IMAGES የምስሉ መግለጫ, ኪም ጆንግ ኡን ከእህታቸው ኪም ዮ ጁንግ ጋር የኪም ልጅ ለምን መነጋገሪያ ሆነች? የቢቢሲዋ የሴዑል ዘጋቢ ጂን ማኬንዚ አንድ ነገር ትጠረጥራለች። ምናልባት ኪም ጤናቸው እምብዛም አስተማማኝ አይደለም። አልፎ አልፎ አመም ያደርጋቸዋል። ለኪም ሰሜን ኮሪያ አገራቸው ብቻ ሳትሆን ርስታቸው ናት። ርስትን ደግሞ ለልጅ እንጂ ለሌላ አያወርሱም። ምናልባት ያ ለግማሽ ክፍለ ዘመን ሰላም የራቀው የኮሪያ ልሳነ ምድር በሴት ቢመራ ሰላም ይወርድ ይሆናል። በሴት ቢሞከርስ? የኪም ሴት ልጅ ለአቅመ ሥልጣን ደርሳ፣ ከኃይለኛዋ አክስቷ ይልቅ የመሪነት መንበሩን ትረከብ ይሆን?
467
4
ኪም ከልጃቸው ጋር ከወታደሮቻቸው ጋር ከ 2 ሰአት በፊት ሰሜን ኮሪያ የምሥጢር ሙዳይ የሆነች አገር ናት። ከሚታወቁት ነገሮች የማይታወቁት ይበልጣሉ። ለምሳሌ ሕዝቡ ምን በልቶ እንደሚያድር እምብዛምም አይታወቅም። ለምሳሌ መንግሥት ምን ነግዶ ምንዛሪ እንደሚያመጣ እምብዛምም አይታወቅም። ለምሳሌ የኮቪድ-19 ተህዋሲ ምን ያህል ሕዝብ እንደገደለ በጭራሽ አይታወቅም። ለምሳሌ የኪም ጆንግ ኡን ሴት ልጅ በትክክል ማን እንደሆነች የታወቀው በቅርብ ነው። እንደ ሰሜን ኮሪያ ምሥጢራዊ የሆነ አገር የለም የሚባለው በምክንያት ነው። ከሰሞኑ ትልቅ መነጋገሪያ የሆነቸው የኪም ሴት ልጅ ናት። ስሟ አይጠቀስም። የአገሬው ሚዲያ ‘ዕጹብ’ ወይም ‘ተወዳጇ’ እያለ ያሞካሻታል እንጂ ስሟን ግልጥ አድርጎ ቢጠራው ችግር ሊገጥመው ይችላል። ‘ዕጹብዬ ከታላቁ መሪያችን ጋር ታየች’ እያለ ነው ለጊዜው ዘገባ የሚሠራው። ስሟን ማንም መጥራት አይችልማ፤ ወይም አይደፍርማ። የሰሜን ኮሪያው ኪም ጆንግ ኡን በአዲሱ የፈረንጆች ዓመት ምን አስበዋል? 3 ጥር 2023 የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን ከሴት ልጃቸው ጋር ለመጀመሪያ ጊዜ በአደባባይ ታዩ 19 ህዳር 2022 የሰሜን ኮሪያዋ ኃያል ሴት ማን ናት? 18 መጋቢት 2021 ለመሆኑ የኪም ልጅ ማን ናት? አሁን ይቺ ልጅ የኪም ተተኪ እንደምትሆን ብዙዎች ትንቢት መናገር ጀምረዋል። ምክንያቱም ኪም ያለ ምክንያት ለስንት ዘመን ከሚዲያ አይደብቋትም ነበር። ከዚህ ሁሉ ጊዜ በኋላ ሴት ልጃቸውን ወደ አደባባይ እንዲያወጧት ያደረጋቸው አንዳች ቁም ነገር ቢኖር ነው ይላሉ ጠርጣሪዎች። ይቺ የኪም ሴት ልጅ በአገሬው ሚዲያ ስሟ ብቻ አይደለም ያልተጠቀሰው፤ ዕድሜዋም ተጠቅሶ አያውቅም። የሰሜን ኮሪያ ብሔራዊ ዜና አገልግሎት (ኬሲኤንኤ) በቅርቡ እንደዘገበው ታላቁ መሪ ኪም እና ሴት ልጁ ‘ዕጹብ’ የአገራቸውን ጀግና ወታደሮችን እና ጀግና ሳይንቲስቶችን አግኝተዋል። ገናናውን ህዋሶንግ ሚሳኤልንም አብረው ጎብኝተዋል፤ ዳሰውታልም። የሰሜን ኮሪያ ብሔራዊ ዜና አገልግሎት በለቀቀው በዚህ የአባትና ልጅ ፎቶ ብዙዎች ተገርመዋል። ነገር ግን ዜናው ፎቶው በትክክል መቼ እንደተነሳ አይጠቅስም። ወታደሮች እና ሳይንቲስቶች በኪም እና በሴት ልጃቸው በመጎብኘታቸው ታላቅ ክብር፣ የትየለሌ ኩራት ተሰምቷቸዋል። “ነፍሳቸው እስክትወጣ ድረስም በደስታ ሰክረዋል” ይላል ዘገባው። በዚህ አያበቃም ታዲያ። “በኪም እና በልጃቸው መጎብኘት እንዴት ያለ ታላቅ ጸጋ ነው” ሲሉ ተጎብኚዎቹ ገልጸዋል ብሏል ዜናው። የፎቶው ባለመብት, KCNA VIA REUTERS የምስሉ መግለጫ, ኪም ከልጃቸው ጋር በሚሳኤል ሙከራ ስፍራ ተደብቃ የቆየችው የኪም ሴት ልጅ የኪም ሴት ልጅ ለመጀመርያ ጊዜ መኖሯ የታወቀው በፈረንጆቹ 2013 ነበር። እንኳንስ ስለ እርሷ ስለ አባቷም የሚታወቀው በጥቂቱ ነበር። የያኔው ጎረምሳ አባቷ ኪም ሲለው ከሚዲያ ይሰወራል። የአገር መሪ በመሆኑ ብቻ “አንቱ የሚሰኙት” ኪም ሰሜን ኮሪያን በጎርምስና መምራት የጀመሩ ሰው ናቸው፤ በነጠላ የመጠራታቸው ምሥጢርም ይኸው ነው። ኪም ቁጣቸው ከመሬት ያደባያል። የገዛ ጄኔራሎቻቸውን፣ የገዛ አጎታቸውን አስቀልተዋል። በአገራቸው ለመጣ ቀልድ አያውቁም። ኩ-ር-ት ያሉ አምባገነን እንደሆኑ ነው የሚነገረው። በሐምሌ 2012 (እአአ) የሰሜን ኮሪያ መገናኛ ብዙኃን የኪም ባለቤት ማን እንደሆኑ ገለጹ፤ ለመጀመሪያ ጊዜ ሰሜን ኮሪያ ቀዳማዊት እመቤት ሪ ሶለ ጁ እንደሚባሉ አገሬው ተነገረው። ይህ የሆነው ታዲያ ኪም በአደባባይ ከሚስታቸው ጋር በታዩ በወሩ ነው። ከሚስታቸው ጋር በታዩበት የመጀመሪያዎቹ አራት ሳምንታት ማንም እመቤቲቱን የኪም ባለቤት ብሎ ለመጥራት የደፈረ አልነበረም። ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ታዲያ ባል እና ሚስቱ፣ ማለትም ኪም እና ሪ ልጅ አላቸው ወይስ የላቸውም? የተከበሩ ወ/ሮ ሪ ጸንሰዋል ወይስ? ሁለት ነፍስ ይሆኑ? ወይስ. . . በሚለው ጉዳይ ትንፍሽ ያለ አልነበረም። ቆየት ብሎ ወ/ሮ ሪ እና ኪም ሦስት ልጆች እንዳሏቸው በሚዲያ ተነገረ። ያው ሕዝቡ ይነገረው ተብሎ ተፈቅዶ መሆን አለበት። የፎቶው ባለመብት, KCNA VIA REUTERS የምስሉ መግለጫ, ኪም ከልጃቸው ጋር በሚሳኤል ሙከራ ስፍራ ከዓመት በኋላ በመስከረም 2013 (እአአ) የቀድሞው ዕውቅ አሜሪካዊ የቅርጫት ኳስ ተጫዋች ዴኒስ ሮድማን ለ‘ዘ ጋርዲያን’ ጋዜጣ አንድ አዲስ መረጃ ሰጠ። መረጃው ኪም ሴት ልጅ እንዳላቸው የሚያረጋግጥ ነበር። መታደል ወይም አለመታደል ሆኖ ይህ ጫማውን የሰቀለ ጡረተኛ አሜሪካዊ የቅርጫት ኳስ ጥበበኛ፣ በኪም የሚወደድ ብቸኛ አሜሪካዊ ሳይሆን አይቀርም። ከአንዴም ሁለት ሦስቴ ወደ ሰሜን ኮሪያ፣ ፒዮንግያንግ ተጋብዟል። ፊልም ሁሉ ተሠርቶበታል፤ በኪም እና በቅርጫት ኳስ ተጫዋቹ ወለፈንዲ ወዳጅነት። ሮድማን ታዲያ ያኔ ለዘ ጋርዲያን በሰጠው ቃል፤ “ወዳጄ ኪም ሴት ልጁን አብልጦ የሚወድ ሰው ነው” ሲል አባትነቱን መሰከረ። የኪምን ሴት ልጅ እንደተወለደች፤ እሱ ራሱ ከእናቷ ወ/ሮ ሪ ተቀብሎ እቅፍ አድርጎ መሳሙንም አረጋገጠ። ቅርጫት ኳስ ተጫዋቹ ሮድማን ያን ካለ በኋላ ነው የዓለም ሚዲያ “ኪም እኮ ሴት ልጅ አለቻቸው” ብሎ በድፍረት መዘገብ የጀመረው። ለመጀመሪያ ጊዜ መቼ ታየች? በዚህ ዓመት ኅዳር ወር መጀመሪያ ላይ የሰሜን ኮሪያ ዜና አገልግሎት አከታትሎ በርከት ያሉ ፎቶዎችን ለቀቀ። ፎቶዎቹ ኪም እና ሴት ልጃቸውን ያሳያል። ያን ጊዜ ነው በሕይወት እንዳለች የተረጋገጠው። አባት እና ልጅ ታዲያ ሚሳኤል ሲዳብሱ፣ ወታደር ሲያንቆጳጵሱ፣ ቀጭን ትዕዛዝ ሲያወርዱ ተወንጫፊ ሚሳኤል ሲመርቁ ነበር የዋሉት። አባት እና ልጅ የመረቁት ሚሳኤል አገር ብቻ ሳይሆን አህጉር አቋራጭ ነበር። ደቡብ ኮሪያ ሴዑል የምትገኘው የቢቢሲ ዘጋቢ ጂን ማኔንዚ የምዕራብ ሚዲያም ሆነ የአገሬው ሚዲያ ከሚሳኤሉ ይልቅ በአባት እና ልጅ አብሮ መታየት ዜና ተጠምደው ነበር ብላለች። በተለይ የአገሬው ሚዲያ የኪምን ሴት ልጅ በማንቆለጳጰስ መጠመዱ ምናልባት ይቺ ልጅ ታላቁ ኪም ለመሪነት እያጯት ይሆን? የሚል ጥርጣሬን ጭሯል። የፎቶው ባለመብት, KCNA VIA REUTERS የምስሉ መግለጫ, ኪም ከልጃቸው ጋር ለሁለተኛ ጊዜ መቼ ታየች? የመጀሪያ ፎቶዋ በተለቀቀ በሳምንቱ ሌላ ፎቶ ተደገመ። ዓለም ጉድ አለ። “ይሄማ አንድ ነገር ታስቦ መሆን አለበት” ተባለ። ይህ የሆነውም በቅርቡ ነበር። በዚህ ጊዜም ቢሆን ስለ ስሟም ይሁን ዕድሜዋ ትንፍሽ ያለ አልነበረም። ይሁንና ከመጠሪያ ስሟ ይልቅ “ተዋዳጅዋ” እና “ዕጹብ” የሚለው ቅጽል በዜና አንባቢዎች ዘንድ ጥቅም ላይ ውሏል። መጠሪያ ስሟን የሚያውቀውስ ይኖር ይሆን? አስተማሪዋስ ቢሆን በስሟ ይጠራት ይሆን? የብዙዎች ጥያቄ ነው። የአሜሪካው ቴሌቪዥን ኤንቢሲ ኔትዎርክ አንድ የአካባቢውን ጉዳዮች አዋቂን ጠቅሶ እንደዘገበው፣ ኪም ከልጃቸው ጋር እጅግ ወሳኝ በሚባል የሚሳኤል ሳይንቲስቶች ጉብኝት ወቅት መገኘት በፍጹም እንደዋዛ የሚታይ አይደለም። ምናልባት አንድ የተደገሰላት ነገር ይኖር ይሆናል። ለአንድ ታላቅ ተግባር
376
5
No text...
346
6
+2
No text...
557
7
አጭር የሕይወት ታሪክ አርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ (ባባ) ከአባቱ አቶ ብርሃኑ አምባው ከእናቱ ወ/ሮ አባይነሽ ክብረት በአዲስ አበባ ፣ በተለምዶ ተክለሃይማኖት ጅምናዚየም ተብሎ በሚጠራው ሠፈር በ1977 ዓ.ም ተወለደ ። ዕድሜው ለትምህርት እንደደረሰ የአንደኛ ደረጃ ትምህርቱን በባልቻ አባነፍሶ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ፣ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በአዲስ ከተማ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማረ :: በመቀጠል ወደ ቆዳ እና የቆዳ ውጤቶች ተክኖሎጂ ኢንስትቲዩት (ሌዘር ኤንድ ሌዘር ቴክኖሎጂ ኢንስትቲዩት) በማምራት በሌዘር ቴክኖሎጂ ዲፕሎማውን አግኝቷል። በትምህርት በነበረበት ወቅት በኢንስትቲዩት አስተማሪዎች ተወዳጅ ተማሪ እንደነበረ የተቋሙ መምህራኖች እና ባለሙያዎች የሚመሠክሩለት ተማሪ ነበረ ። አርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ የጥበብ ህይወት ጉዞ የጀመረው በአበቦች የትያትር ክበብ የነበረ ሲሆን ይህን ጅማሬውን እንዲያብብ እና ከፍታ ያወጣለት ዘንድ በአርቲስት ዶ/ር ተስፋዬ አበበ (ፋዘር) እግር ስር ቁጭ ብሎ የቴአትርን ሀ..ሁ የቆጠረ ሲሆን ለስኬቱ ይረዳውም ዘንድ በተለያዮ ጊዜያት የፊልም እና የቲአትር ኮርሶችን ወስዷል ። አርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ /ባባ/ በፀርሀ ፅዮን ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ሰንበት ትምህርት ቤት አባል ሆኖ ባገለገለበት ጊዜ ዋዜማ ፣መንገደኛው እና የይቅርታ ዘመን የተሠኙ የሙሉ ጊዜ መንፈሳዊ ፊልሞችን ሰርቷል ። በአበቦች የቴአትር ክበብ ባይተዋር የተሰኘ ቴአትር ሰርቷል እንዲሁም በቀንዲል ቤተ ተውኔት በተለያዮ የጥበብ ዝግጅቶች አቅሙን አሳይቷል። ከነዚህ በኋላም ወደ ስኬት ጉዞ የወሰደውን የፊልም ህይወት በዋና ገፀባህሪ የተሣተፈበትን ላውንደሪ ቦይ የተሠኘውን ፊልም አበረከተ። በላውንደሪ ቦይ የጀመረው የፊልም ጉዞ ባላገሩ ሕይወትና ሣቅ ወንድሜ ያዕቆብ የፍቅር ABCD እና በተለያዩ የሀገራችን ፊልሞች ላይ በድንቅ ብቃት በመተወን በተለይ ደግሞ በወጣቶች ዘንድ እጅግ የሚወደዱ ከስልሣ በላይ ፊልሞች ላይ የተወነ ሲሆን ከስራዎቹም ጥቂቶቹ እነዚህ ይገኙበታል :: ወጣት በ97፣ ላውንድሪ ቦይ፣ ማርትሬዛ፣ ይመችሽ-የአራዳ ልጅ 2 ፣ሞኙ የአራዳ ልጅ 4፣ አንድ ሁለት ፣ብር ፣ ወደው አይሰርቁ፣ ወፌ ቆመች፣ እንደ ቀልድ ወቶ አደር ፣አባት ሀገር የሞግዚቷ ልጆች፣ ይዋጣልን ፣ዋሻው፣ ወሬ ነጋሪ እና ሌሎችም ፊልሞች ላይ ተውኗል። በነዚህ ስራዎች እያበራ የደመቀው አርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ /ባባ/ የጥበብ ህይወቱ በተለያዮ ሽልማቶች የደመቀ ነበር ከነዚህ ውስጥ አዲስ ሚውዚክ አዋርድ እና በሸገር ኤፍ ኤም 102.1 የለዛ የዓመቱ ምርጥ ተዋናይ ሆኖ የተሸለመበት እና በጉማ አዋርድ ኢንተርናሽናል የፊልም ፌስቲቫል ለእጩነት እና ለሽልማት የበቃበት የሚጠቀሱ ስኬቶቹ ነበሩ ። ከጥበብ ህይወቱ ባሻገር በተለያዮ የማህበራዊ ሕይወት በትህትናው እና በለጋስነቱ የሚታወቀው አርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ /ባባ/ የአንድ ወንድ ልጅ አባት ነበረ ። አርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ /ባባ/ በህይወት በነበረበት ዘመን በሀገራችን አሉ ከሚባሉ ውድ ተከፋይ የጥበብ ሰዎች ተርታ ይመደብ የነበረ ቢሆንም ከነብሱ ጋር የተጣበቀው ደግነት እና ፍፁም ቸርነት ለኔ ይድላኝ እንዳይል አድርጎት በክፍያ ያገኘውን ገንዘቦች እንኳን በበጎነት ለአካባቢው ሰዎች እየለገሠ የኖረባትን ጥቂት ዘመን በምርቃት እና በመልካም ምግባር አሳልፎ የግል ህይወቱን ለሌሎች የሠጠ ድንቅ ባህሪ የነበረው ወጣት ነበረ ። አርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ በየእለት ውሎው በተገኘበት ቦታ ሁሉ ህፃን አዋቂ ሳይል በፍቅር እና በመረዳዳት ሲያሳልፍ ኖሯል። ለጓደኞቹ እና ለሰፈሩ ሰዎች ሁሉ በችግራቸው ቀድሞ በመድረስ ይታወቃል በተጨማሪም በአካባቢው ከሚገኙ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች እንደ CBCDO ሲደርታ እና ሰዋዊ የጎ አድራጎት ማህበር ወዘተ የመሣሠሉት ላይ በበጎ ፍቃድ በመሣተፍ በነበረው እውቅና እንደ አምባሳደር በማገልገል ለላይብረሪ ከ500 በላይ መፃህፍትን በማሠባሠብ ወላጆቻቸውን ያጡ ህፃናትን አቅመ ደካሞችን በመደገፍ በጎ ተግባሮች ላይ በፊት አውራሪነት ተሣትፎ ነበረው ። በተጨማሪም አርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ /ባባ/ በጎ ስራውን የጀመረው ከእውቅናው በፊት ሲሆን በ2000 ዓም በ 23 አመቱ ለኢትዮጵያ የዓይን ባንክ በሰጠው ኑዛዜ መሠረት ህይወቴ ከዚህች ዓለም ድካም ሲያርፍ ሁለቱን ዓይኖቼን በህይወት ኖረው ማየት እክል ላጋጠማቸው ወገኖቼ በነፃ እንዲወስዱ ብሎ ለግሧል። አርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ ባጋጠመው የጤና እክል በተለያዮ ጊዜያት በህክምና እና በፀበል እራሡን ሲያሳይ የነበረ ቢሆንም በ ታህሳስ 02 2015ዓም ከዚህ ዓለም ድካም አርፏል ።
314
8
ጀርመን ስደተኞችን በመጠቀም የህዝብ ብዛቷን ማሳደግ እንደምትፈልግ ገለጸች ጀርመን የህዝብ ብዛቷን ወደ 90 ሚሊዮን ከፍ የማድረግ እቅድ እንዳላት አስታውቃለች። ጀርመን በተለይም የሰራተኞችን ቁጥር ለማሳደግ ስደተኞችን እንደ አማራጭ እንደምትጠቀም ገልጻለች።
386
9
ሁመራ‼️ ሁመራ ማከፋፈያ ጣቢያ ከሁለት ዓመት በኋላ ኤሌክትሪክ አገኘ። ከሁለት ዓመት በላይ ኤሌክትሪክ ተቋርጦበት የቆየው ሁመራ ማከፋፈያ ጣቢያ ዳግም የኤሌክትሪክ ኃይል አገኘ። አካባቢው ከሽሬ ማከፋፈያ ጣቢያ ኃይል ያገኝ የነበረ በመሆኑ አስቸጋሪ መልክዐምድርና የአየር ሁኔታ ያለው የሁመራ -  ሽሬ  230 ኪሎ ሜትር ባለ 230 ኪሎ ቮልት መስመር ሲጠገን ቆይቷል። ይሁንና ጥገናው ተጠናቆ ከሽሬ ማከፋፈያ ጣቢያ ለማገናኘት ሲሞከር ከተከዜ ወደ ሽሬ የሚመጣው መስመር ላይ ችግሮች በማጋጠሙ ኃይል ሽሬ ከተማ ማድረስ አለመቻሉን መገለጹ ይታወሳል። አስቸጋሪ የነበረው የተከዜ መስመር ጥገና ከተጠናቀቀ በኋላ ሁመራ ማከፋፈያ ጣቢያ ኃይል ማድረስ ተችሏል። በመሆኑም ከሁመራ ማከፋፈያ ጣቢያ ኃይል ያገኙ የነበሩ ከተሞች በሙሉ  ኃይል የሚያገኙበት ሁኔታ ተፈጥሯል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ እና የተቋሙ ከፍተኛ የሥራ አመራር ቡድን በተከናወነው ሥራ የተገኘው ውጤት እንዳስደሰታቸው ገልፀዋል። በቀጣይም ኃይል ያላገኙ አካባቢዎችን መልሶ ለማገናኘት በትኩረት እንደሚሰራ ማስታውቁን ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል የተላከልን መግለጫ ያመለክታል። =============
389
10
ልጅ፣፣፣፣😪😪😪ሚስት ፣፣ ታሪኩ /ባባ ለዚህ ነው "መኖርን" የማላምናት #ያስፈራል ለዚህ ነው "ህይወት" "የሰው ስም ብቻ ነው" የምለው:: ለዚህ ነው "አለሁ" ማለት ነውር የሚመስለኝ:: ለዚህ ነው "ሳለን እንከባበር" እና " ሞትን እንቅደመው" የምለው:: እሳት ነው "ሞት" ያገኘውን ይበላል:: ጨለማ ነው "ሞት" ወደ-አለመተያየት ያስገባል:: "ሳይጨልምብን እንተያይ"
402
11
+2
No text...
398
12
የኢትዮጵያ እና የጅቡቲ ሰላም አስከባሪ ኃይል አባላት የጥምር ውጊያ ልምምድ አደረጉ ****** በአትሚስ ሴክተር አራት 7ኛ ዙር ሰላም አስከባሪ ኃይል ከጅቡቲ ሰላም አስከባሪ ኃይል ጋር ግዳጅን መሰረት ያደረገ የጥምር ውጊያ ልምምድ አድርገዋል። የሁለቱም አገራት የሰላም አስከባሪ ኃይሎች የጋራ ጥምር ውጊያ ልምምድ ማድረጋቸው ቀጣይ የሚያጋጥሙ ግዳጆችን በተገቢው መንገድ ተናቦ ለመፈጸም ሚናው የጎላ ነው ሲሉ የሴክተሩ ምክትል አዛዥ ኮሎኔል ሹመት ጠለለው ተናግረዋል። የጥምር ውጊያ ልምምዱ ከመጀመሩ በፊት ለአባላቱ የግዳጅ መመሪያ ገለፃ የሰጡት ኮሎኔል ሹመት ጠለለው፤ ልምምዱ አልሸባብ አልፎ አልፎ የሚፈፅማቸውን ትንኮሳዎች በመመከት መደምሰስ እንዲቻል የሚረዳ ከመሆኑም በተጨማሪ የኢትዮጵያን እና የጅቡቲን ወታደሮች አንድነት የሚያጠናክር መሆኑን ገልፀዋል። ከልምምዱ በኋላ ሰላም አስከባሪ አባላቱ በሰጡት አስተያየት የመስክ ልምምዱ በታሰበው ልክ መፈጸሙን ገልፀው፤ ይህ ዓይነቱ በተግባር የተደገፈ ልምምድ ወታደራዊ ቁመናን ከመፈተሸ ባለፈ ከጅቡቲ ኃይል ጋር ጥምረት በመመስረት የሽብር ቡድኑ አልሸባብን ለመደምሰስ የሚያግዝ ነው ማለታቸውን ከኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት የማበራዊ ትስስር ገፅ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። =====================
526
13
ሰበር ዜና‼️ በስብሰባ ላይ ያሉ ባለስልጣናት ተከበቡ "ከባድ ተኩስ ተጀምሯል" ሳይጠበቅ አልሻባብ በስብሰባ ላይ ያሉ ባለስልጣናትን በመክበብ ከባድ ተኩስ ከፈተ‼️ በሶማሊያ ሞቃድሾ በዚህ ሰዓት ባለስልጣናቱ በተሰበሰቡበት ከቤተመንግስቱ በቅርብ ርቀት የሚገኘው ቪላሮዝ ሆቴል ከየት መጣ ያልተባለ የአልሻባብ የሽብር ቡድን ቦታውን በመክበብ ከባድ የተኩስ ሩምታ መክፈቱን አልጄዚራን ጨምሮ አለም አቀፍ ሚዲያ በሰበር ዜና ዘግበዋል። በጉዳዩ ላይ ከዚህ በላይ ዝርዝር መረጃ ለመስጠትም አስቸጋሪ ነገር መፈጠሩን ዘገባው ጠቁሟል።
522
14
ካይሮ ነገ ለመንግስት ተቃውሞ ሰልፍ ጠርታለች። የስንዴ አቅርቦት ችግር፣ የዋጋ ግሽበት፣ ኑሮ ውድነት እና የሰብዓዊ መብት ጥሰት ከልክ ማለፍ ግብፃዊያንን ለነገው ዕለት ማለትም ለ11/11/2022 ለተቃውሞ ወደ አደባባይ ጠርቷል:: የሲሲ መንግስት "የስንዴ አቅርቦት እጥረት፣ የዋጋ ግሽበት፣ የኑሮ ውድነት መንስኤው በሩሲያ እና ዩክሬን መካከል የተፈጠረው ጦርነት ዓለምም እየተፈተነበት ያለው ችግር ነው እንጂ የኔ የአስተዳደር ችግር አይደለም" እያለ በአክቲቭስቶቹ በኩል እየለፈለፈ ውሏል:: ሱሌማን አብደላ
643
15
+1
No text...
839
16
ሰላም👋 - እንኳን ወደ Telegram ቻናሌ  👥 በደና መጡ🙏🙏🙏 አላማው እውነተኛ መረጃዎችን በማጋራት ኢትዮጵያን እና የኢተዮጵያዊያንን አንድነት፣ክብር፣ሉአላዊነት መስጠበቅ ነው፡፡ ⚠️ለግሩፑ  እድገት ሲባል አዲስ ገቢ ከሆኑ 20+.... (ሃያ)ሰው ወደ ግሩፑ ☑️ #Add #Share  ወደ ግሩፖች፡በማረግ የኢትዮጵን  እወነት ለአለሙ መህበረሰብ እናሳዉቅ። ❗️እስካሁን 0 ሰው ወደ ግሩፑ ጋብዘዋል። ®🇪🇹 🇪🇹®
1
17
ሰበር መረጃ ከፕሪቶሪያ በደቡብ አፍሪካ በተካሄደው የሰላም ውይይት የህወሓት መዋቅር ፈርሶ የፌደራል መንግሥት የሚመራው ጊዜያዊ አስተዳደር እንዲቋቋም እና ቡድኑ ሙሉ በሙሉ ትጥቅ እንዲፈታ ስምምነት ላይ ተደረሰ በደቡብ አፍሪካ ለስምንት ተከታታይ ቀናት ሲካሄድ የነበረው የሰላም ድርድር የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት፣ የግዛት አንድነት እና ዘላቂ ሰላም በሚያረጋግጥ መልኩ በስምምነት መቋጨቱን ከውስጥ ምንጮች የተገኙ መረጃዎች ይጠቁማሉ። ለሁለት አመታት የዘለቀው የሰሜኑ ጦርነት መቋጫ እንደሚሆን የተገመተ የሰላም ስምንነት ፊርማ በዛሬው እለት በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ በኢትዮጵያና በህወሓት ተደራዳሪዎች መፈረሙን ያስታወቁት ምንጮች ፤ ውይይቱ የሀገራችንን ብሔራዊ ጥቅም ባስጠበቀ፣ የሕግ የበላይነትን ባረጋገጠ እና ለውጭ ጣልቃ ገብነት እድል በማይሰጥ መልኩ በስኬት መጠናቀቁን ገልጸዋል። ቁልፍ የስምምነት አጀንዳዎች፦ 1. ህወሓት ሙሉ በሙሉ ትጥቅ ለመፍታት መስማማቱን፦ በስምምነቱ መሰረት ከዛሬ ጀምሮ በሰላሳ ቀናት ውስጥ ቡድኑ ሙሉ በሙሉ ትጥቅ እንደሚፈታ፤ ይህንን ውሳኔ ተግባራዊ ለማድረግ የሁለቱ ወገን ከፍተኛ ወታደራዊ አመራሮች በ24 ሰዓት ውስጥ አመቺ ቦታ መርጠው ንግግር ያደርጋሉ፤ 2. ስምምነቱ በተፈረመ አምስት ቀናት ውስጥ የሁለቱ ወገን ወታደራዊ አመራሮች የትጥቅ ማስፈታት ሂደቱ የሚመራበትን ዝርዝር አፈጻጻም በጋራ በማውጣት ተግባራዊ ሥራዎችን መሥራት ይጀምራሉ፤ 3. የሁለቱ ወገን ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖች በተገናኙ አስር ቀናት ውስጥ ህወሓት ያሉትን ሁሉንም የቡድን እና ከባድ መሣሪያዎች ለመከላከያ ሠራዊት ያስረክባል፤ 4. ስምምነቱ በተፈረመ ሰባት ቀናት ውስጥ የፌደራል መንግሥት መቀሌን ተረክቦ በከተማው ውስጥ እና ዙሪያ ሁሉንም አይነት የጦር መሣሪያ ያስፈታል፤ 5. በአጭር ቀናት ውስጥ አሁን ያለው የህወሓት መዋቅር ፈርሶ የፌደራል መንግሥት የሚመራው የጊዜያዊ አስተዳደር ይቋቋማል። በሚዋቀረው ጊዜያዊ አስተዳደር ውስጥም የትግራይን ሕዝብ የሚወክል አካል ይሳተፋል፤ 6. የሀገር መከላከያ ሠራዊት ከጎረቤት ሀገራት የሚያዋስኑ የድንበር አካባቢዎችን ደኅንነትና ሰላም የሚያረጋግጥ ስምሪት የሚያደርግ ይሆናል። መከላከያ ሠራዊቱ በማንኛውም የትግራይ አካባቢዎች ተንቀሳቅሶ ሕግ የማስከበር ስልጣኑን ከህወሓት ሙሉ በሙሉ ይቀበላል። ህወሓት ለተግበራዊነቱ ምንም አይነት እንቅፋት እንደማይፈጥር ተስማምቷል። 7. የሚመሰረተው ጊዜያዊ አስተዳደር በሁሉም የትግራይ አካባቢዎች የማኅበራዊ አገልግሎቶች በፍጥነት እንዲጀመሩ ሁኔታዎች ያመቻቻል፤ ተግባራዊነታቸውን ያረጋግጣል፤ 8. ህወሓት ያለ ፌደራል መንግሥት እውቅና ከማንኛውም የውጭ አካል ጋር ግንኙነት ማድረግ ያቆማል። እንዲህ አይነት ተግባር የሚፈጹ ግለሰቦች ካሉ በሀገሪቱ ሕግ የሚጠየቁ ይሆናል።
866
18
+1
No text...
728
19
‹‹ዋሽንግተን አደብ ብትገዛ ይሻላል›› ሰሜን ኮሪያ የዋሽንግተን እና የደቡብ ኮሪያ የጋራ የጦር ልምምድ ሰሜን ኮሪያን ወደ ኒኩሌር የጦር መሳሪያ ሙከራ ሊወስዳት ይችላል ተባለ፡፡ ሰሜን ኮሪያ ከ2017 ወዲህ ምንም አይነት የኒኩሌር ጦር መሳሪያ ሙከራ አላደረገችም፡፡ ሁለቱ ሀገራት ሰኞ የጋራ የአየር ላይ የጦር ልምምድ መጀመራቸው ታውቋል፡፡ ፔዮንግያንግ በቅርብ ሳምንታት ውስጥም በርካታ ሚሳኤሎችን ምላሻሼ ይሁን በማለት ወደ ጎረቤቷ ደቡብ ኮሪያ አስወንጭፋለች፡፡ እንዲህ አይነቱ አካሄድ ሰሜን ኮሪያን ከጥቂት አመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ  ወደ ኒኩሌር ጦር መሳሪያ ሙከራ ያመራታል የሚል ሀሳብ እየተሰጠ ነው፡፡ ዩናይትድ ስቴትስ ከደቡብ ኮሪያ ጋር የምታደርገውን ወታደራዊ ልምምድ የምትገፋበት ከሆነ እኛን ለጠነከራ አጸፋ ምላሽ ያዘጋጀን ይሆን እንጂ በፍጹም ሊገታን አይችልም ሲሉ የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በመግለጫቸው እወቅልን ብለዋል፡፡ አክለውም ዋሽንግተን ምንም ጠቀሜታ ከማይኖረው እንዲህ አይነቱ ድርጊት እንድትታቀብ እንዲሁም ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ጥቅም አልባውን የጦር ልምምድ እንድታቆመው ሲሉም ጠይቀዋል፡፡ የአሁኑ የሁለቱ አገራት የአየር የጋራ የጦር ልምምድ በመቶዎች የሚቆጠሩ አውሮፕላኖች የሚሳተፉበት ሲሆን እነዚህም በአንድ ጀንበር ውስጥ ብዙ ጥቃቶችን ማድረስ የሚችሉ ናቸው ተብሏል፡፡ ፔዮንግያንግ ከ2006 እስከ 2017 ባለው ጊዜ ውስጥ ስድስት የኒኩሌር ጦር መሳሪያን ሙከራ ማድረጓም ይታወሳል። በአብርሃም መኳንንት
750
20
መንግስት ስም የሚያጠፉ ምእራባውያንን አልታገስም” ማለቱን ተከትሎ አሜሪካ ምን አለች? November 1, 2022 ኔድ ፕራይስ፤ “የድርድሩ መራዘም ተደራዳሪዎች የተራራቀ አቋም ይዘው ለመቀመጣቸው አመላካች ነው” ብለዋል “መንግስት ስም የሚያጠፉ ምእራባውያንን አልታገስም” ማለቱን ተከትሎ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ኔድ ፕራይስ ምለሽ ሰጥተዋል። የኢትዮጲያ መንግስት ምእራባውያን አካላት በኢትዮጲያ መንግስት ላይ የሚያደርሱትን በሀሰት ሰም የማጥፋት ዘመቻ እንደማይታገስ መግለጹ ይታወሳል። የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ኔድ ፕራይስ በትናትናው እለት መግለጫ በሰጡበት ወቅት ከዚሁ ጋር በተያያዘ ጥያቄ ቀርቦላቸው ነበር። መንግስት የኢትዮጵያን ስም የሚያጠፉ ምእራባውያንን እንደማይታገስ አስታወቀ ኔድ ፕራይስ በምለሻቸው፤ የኢትዮጵያን መንግስት መግለጫ መመልከታቸውን ገልጸው፤ “በመግለጫው ውስጥ ክሱ ትክክልኛ ነው በሚለው ላይ በዚህ ሰዓት ምንም መናገር አልችልም፤ የቀረበውን መረጃ እና አላማውን መጀመሪያ መረዳት አለብን” ሲሉ ተናግረዋል። “ሆኖም ግን የአሜሪካ ዋነኛ ዓላማ በአፍሪካ ህብረት የሚመራው የሰላም ሂደት ከግብ እንዲደርስ ነው፤ ይህ በጣም ግልጽ ነው ሌላ ድብቅ የፖለቲካ አላማ የለውም” ሲሉም ገልጸዋል። የአሜሪካ አለማ በጣም ግልጽ ነው ያሉት ቃል አቀባዩ፤ እነዚህም ጦርነቱ በአስቸኳይ እንዲቆም ማድረግ፣ ለተቸገሩ ኢትዮጵያውያን ሁሉ ሰብአዊ ርዳታ ለማድረስ፣ ሲቪሎችን ለመጠበቅ እርምጃዎችን መውሰድ እና ኤርትራ ከሰሜን ኢትዮጵያ መውጣቷን ማየት ነው ሰሉም ተናግረዋል። “ጦርነት በሚካሄድባቸው አካባቢዎች አሳሳቢ የሰብአዊ መብት ረገጣዎች እንዳሉመረጃዎች የደርሱናል፤ ከሚደርሱን መረጃዎች ውስጥ የተወሰኑት አሳማኝ ናቸው” ያሉት ቃል አቀባዩ “ይህ አሜሪካ ህ እንደሚያሳስባት በግዳሚ ትገልጻለች፤ ግጭቱ ተዋናይ የሆኑ ሁሉም ሀይሎች ከዚህ ተግባር ሊታቀቡ ይገባል” ብለዋል። የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ኔድ ፕራይስ ስምንተኛ ከሳምንት በፊት በመንግስት እና የህወሓት መካከል እየተደረገ ስላለው ድርድር በተመለከተ ከጋዜጠኞች ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ ሰጥተዋል። ቃል አቀባዩ በመግለጫቸው በአፍሪካ ቀንድ የአሜሪካ ልዩ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ማይክ ሐመር በድርድሩ ላይ በ“ተሳታፊነት እና በታዛቢነት” እየተካፈሉ መሆኑን ገልጸው፤ ድርድር እስከሚጠናቀቅ ድረስ በደቡብ አፍሪካ እንደሚቆዩ ተናግረዋል። ይጠናቀቃል ተብሎ ከተያዘለት ቀነ ገደብ ያለፈው የኢትዮጵያ መንግስት እና የህወሓት ድርድር መራዘም፤ ተደራዳሪዎቹ የተራራቀ አቋም ይዘው ወደ ድርድር ለመግባታቸው አመላካች ነው” ብለዋል። ቃል አቀባዩ ኔድ ፕራይስ የድርድሩ መራዘም መንግስትና ህወሓት አብረው ለመቀመጥ ፈቃደኛ ሆነው እንደቀጠሉ ያመለክታል ያሉ ሲሆን፤ ተደራዳሪዎች በመካከላቸው ያለውን እንደሚያጠቡ ተስፋ እናደርጋለን ሲሉም ተናግረዋል። በአፍሪካ ህብረት መሪነት በፌደራል መንግስት እና በህወሓት መካከል ባለፈው ሳምንት ሰኞ በደቡብ አፍሪካ የተጀመረው ድርድር እንቀጠለ ነው። የሰላም ንግግር ሂደቱ “ብዙ ጣልቃገብነት” እንዳጋጠመው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ገለጹ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ከሲጂቲኤን ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ግጭቱን በሰላም የመፍታቱ ሂደት “ብዙ ጣልቃገብነት” እንዳጋጠመው ተናግረዋል። በኢትዮጵያ ጉዳይ “በግራ በቀኝ ብዙ ጣልቃገብነት” መኖሩን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ “ኢትዮጵያውያን መረዳት ያለባቸው የራሳችንን ጉዳይ በራሳችን መፍታት አንደምንችል” ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ መንግሰት አና በህወሓት መካከል የሰላም ንግግሩ ቢጀመርም ጦርነቱ አሁንም እየቀጠለ ነው። በድጋሚ ነሀሴ አጋማሽ ላይ በተቀሰቀሰው ጦርነት የህወሓት ሃይሎች እስከ ቆቦ ድርስ መግባት እና የተወሰኑ ቦታዎች መቆጣጠር ችለው የነበረ ቢሆን የኢትዮጵያ መንግስት መልሶ መቆጣጠር ችሏል። ጦርነቱ አሁን የቀጠለ ሲሆን የኢትዮጵያ መንግስት ሽሬ፣አላማጣ እና ኮረምን እና ሌሎች ቁልፍ የትግራይ ከተሞችን መቆጣጠር መቻሉን ማስታወቁ ይታወሳል።
532