cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

UMMI/ኡሚ

"ለበጎነት መስፈርት የለውም" ንግድ ባንክ 1000278180388 አዋሽ 01425797253900 አቢሲኒያ 64642227 ኡሚ የልማትና የየቲሞች መረዳጃ ያላችሁን ሀሳብ ጥያቄ 0980482001 መገኛችን #ቤተል አልመሻን #አዳማ #ሻሸመኔ #ወልቂጤ #ደሴ ስልክ ቁጥር 0980482001 0912927557

Show more
Advertising posts
2 347
Subscribers
-224 hours
No data7 days
-3030 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

ብርሃናማ ቀን የአይን ብርሃናቸውን ካጡት ጋር እንሆ በሰበታ ምድር የቂረአት ቦታ በማጣት ሲንከራተቱ የነበሩ አይነ በስሮችን ከአብደላህ ኢብኑ ኡሙ መክቱም ጋር በጋራ በመሆን የቂርዓት ቦታ አመቻችተን እንዲሁም ለደስታቸው ሰደቃ ሰድቀን ተመራርቀን 1 ብለናል አላህ ያበርታን ብዙም እንሰራለን ኢንሻአላህ ኡሚ የየትሞች የልማትና መረዳጃ ተቋም ለበጎነት መስፈርት የለውም
Show all...
16👍 1🎉 1
አስጀምሮ ላስጨረሰን አላህ ምስጋና ይገባው። አልሐምዱ ሊላህ! ሕዝበ ሙስሊም ሆይ! እንኳን ለዚህች ቀን ደረሳችሁ። ዒዱኩም ሰዒድ ኩሉ ዓሚን ወአንቱም ቢኸይር!
Show all...
🥰 31👍 4 4🔥 2🎉 2
ረመዷን -30 ኢማናችንን ያነቃቁ ዉቦቹና መልካም የረመዷን ቀናት በዚህ መልኩ አለፉ። አግቶ ማስቀረት ቢቻል እነርሱን ነበር ማስቀረት። ግና የአላህ ሱንና ነውና ማስቀረት አልተቻለም። ሁሉም የዱንያ ቀናት የጊዜ ቆይታ አላቸዉና ረመዷንም ሊሰናበተን ጫፍ ደረሰ። ዛሬን አድረን ነገን ፆመን ዒድ ነው። በርግጥ ትናንት ልዩ ቀን ነበር። ጥሩ መንፈስ ላይ ሆነን ዒዳችንን እናከብራለን። በአላህ ፈቃድ 29 የረመዷን መልዕክቶቼ ተጠናቀቁ። መጀመርያ ሰላም ጤና አቆይቶን አብሮ ያዘለቀንን አምላኬን አመሰግናለሁ፣ እናንተንም በትዕግሥት የተከታተላችሁኝን ሁሉ ጀዛኩሙሏሁ ኸይረን እላለሁ።
Show all...
14🫡 7👍 5👏 1
ረመዷን -29 የራህመቱን ወር በመሸኘት ላይ ነን ወላሂ አይናችንም አነባ ልባችንም ባዶነት ተሰማት አንተው ሙላን ረመዷን አለቀብን የአንተ እዝነት መቼም አያልቅም ያአላህ ጠግነን ያአላህ መልሰን ያአላህ ስማን ያአላህ ተቀበለን ያአላህ ጀነትን ሸልመን ያአላህ ቀልብ ስጠን ያአላህ ምረጠን ያአላህ ውደደን ያአላህ አዋደን ያአላህ ሰላም አርገን ያአላህ ፆማችንን ተቀበለን ያአላህ አፅዳን ያአላህ በራህመትህ እየን ያአላህ ያሰብነውን አሳካልን ያአላህ ከቀብር ቅጣት ጠብቀን አሚን
Show all...
👍 42🫡 6 3
ረመዷን - 28 ረመዷን ተጠንቅቆ ለፆመው ድርብርብ ትርፍ እንዳለው ሁሉ ትኩረት ለነፈገው ደግሞ ከባድ ኪሳራ አለው። ቀኑን ሙሉ ፆሞ እንዳልፆመ የሚቆጠር አለ። ቅጥፈትንና ዉሽትን ያልተወ ሰው አላህ ስለ ፆሙ ግድ የለዉም። ዞር ብሎ አያየዉም። ስለዚህ ፆሙ ኪሳራ ነው ዋጋ አይኖረዉም፣ ዝምብሎ ነው የሚደክመው ማለት ነው። ሀሜት በቁሙ እያለ የወንድም እህትን ሥጋ መብላት ነው። ቡጨቃ ላይ የሚዉሉ ሰዎች በሰው ሥጋ አፍጥረዋልና ፆማቸው ብላሽ ነው። በረመዷን ከፆሙ ድካም፣ ርሃብና ጥም ብቻ የሚተርፈው ኸልቅ እጅግ ብዙ ነው። ረመዷን መጥቶ ሲሄድ አላህ የማይታረቀው በርካታ ነው። ይህም ለከባድ ኪሣራ ብቻ ሳይሆን ለእርግማንም የተጋለጠ ነው። ረመዷን የለውጥ ወር ነው። ከዚህ የሥልጠና ወር በኢማን ዳብሮ፣ በመንፈስ በልጽጎና ተሻሽሎ አለመውጣት የወር ብክነት፣ አጉል ድካም ነው። ረመዷንን ትርጉም ማሳጣት ነው። እናም መፆማችን ካልቀረ፣ መራብ መጠማታችን ግድ ከሆነ ለፆማችን እንጠንቀቅለት። ሙሉ በሙሉ ከሚያበላሹትም ሆነ ምንዳዉን ከሚያጎድሉብን ነገሮች እንጠንቀቅ። አላህ በሚሻው መልኩ እንፁም። ሠርቶ ዉጤት ከማጣት፣ ደክሞ ለዕረፍት ካለመብቃት አላህ ይጠብቀን።
Show all...
9👍 4🫡 1
ረመዷን - 27 21ም፣ 23ም፣ 25ም ምሽት አለፈ፡፡ 27 ላይ ደረስን ፡፡ ከመጨረሻዎች አሥር የረመዷን ምሽቶች ዉስጥ እጅግ ወሳኟ ሌሊት ዉስጥ ነን፡፡ ረመዷን 27 ምሽት፡፡ በዚህ ምሽት ዉስጥ የመካዉን ታላቁን ሐረም ጨምሮ በርካታ የዓለማችን መሳጂዶች በሰጋጆች ይጨናነቃሉ፡፡ ምክንያቱም ብዙ ዑለሞች ይህች ምሽት ዋናዋ ተጠባቂ የለይለቱል ቀድር ምሽት መሆኗን ተናግረዋል፤ አንዳንዶች ደግሞ በርግጠኝነት ምሽቷ ይህች ምሽት ናት ብለዋል፡፡ ለሁሉም በዱዓችን እንበርታ፡፡ ለለይለቱል ቀድር ትልቁ ዱዓ “አልላሁምመ ኢንነከ ዐፉዉን ተሒቡል ዐፍወ ፈዕፉ ዐንኒ” የሚለው መሆኑንም አንርሳ፡፡ አላህ ይግጠመን፡፡ 
Show all...
👍 18
ረመዷን 26 ዘካተል ፊጥር ዘካተል - ፊጥር ፡- ‹‹ዘካተል ፊጥር›› የረመዷን ወር ፆም መጠናቀቅያ ላይ የሚሰጥ የምጽዋት ዓይነት ነው፡፡ ‹‹ሶደቀተል ፊጥር›› በመባልም ይታወቃል፡፡ የሚሠጥበት ጊዜ ፡- መሠጠት ያለበት እንደ ነገ ዒድ ሲል ፀሐይ ከጠለቀችበት ጊዜ ጀምሮ የዒድ ሶላት እስኪሰገድ ድረስ ባለው ጊዜ ዉስጥ ነው፡፡ ከዒድ በፊት ሁለትና ሦስት ቀን አስቀድሞ ማስጠትም ይቻላል፡፡ ዓላማው ፡- የዘካተ-ልፊጥር ዓላማውም ድሆች የሆኑ ሙስሊሞች በዒድ ዕለት ተደስተው እንዲውሉ፣ ተርበዉና ተከፍተው እንዳይውሉ ለማድረግ ነው፡፡ እንዲሁም ስለዋለለልን ዉለታ ሁሉ አምላካችን አላህን (ሱ.ወ.) ፀጋ የምናመሰግንበት ነው፡፡ ዘካተል- ፊጥር የፆመኛን ነፍስ ታጠራለች፣ በፆሙ ወቅት  በመጥፎ ሥራዎችና ቸልተኝነት ምክንያት በፆሙ ላይ የደረሱ የተለያዩ ጉድለቶችን ትጠግንለታለች፣ አማኝንም ወደ አምላኩ ታቃርባለች፡፡ ዘካተል ፊጥር ግዴታነቱ በነማን ላይ ነው? ዘካተል ፊጥር ሴት፣ ወንድ፣ ባል፣ ሚስት፣ ትንሽ ትልቅ… ሳይል በእያንዳንዱ ሙስሊም ላይ ግዴታ ነው፡፡ አንዳንድ ዑለሞች ሆድ ውስጥ ላለ ጽንስ ጭምር ዘካተል ፊጥር ማውጣት ግዴታ ነው ብለዋል፡፡ አባወራ ለሚያስተዳድራቸዉና ለሚቀልባቸው ሁሉ አስልቶ ዘካዉን መስጠት ይኖርበታል፡፡ አንድ ሰው ዘካተል ፊጥር ማውጣት ግዴታ ይሆንበት ዘንድ ቤተሰቦቹ ለአንድ ቀን ያክል መሠረታዊ ፍላጎታቸውን ማሟላት የሚችሉበት ገንዘብ ሊኖራቸው ይገባል፡፡ ለዘካተል ፊጥር የሚወጡ የእህል ዓይነቶችና መጠኑ፡- ዘካተል ፊጥር ከስንዴ፣ ከገብስ ከተምር፣ ከዘቢብ፣ ከሩዝና ሌሎችም ቀለብ ሊሆኑ ከሚችሉ ነገሮች አንድ ‹‹ሷዕ›› ይወጣል፡፡ አንድ ሰው ሀገሩ ላይ አብዛኛው ሰው ከሚመገበው ምግብ ለዘካተል ፊጥር መስጠት ይችላል፡፡ አንድ ‹‹ሷዕ/ቁና›› 3 ኪሎ ግራም አካባቢ ይሆናል ተብሏል፡፡ ሚዛን ወይም መስፈሪያ የሌላቸው ሰዎች በመካከለኛ ሰው እጆች አራት እፍሶች ማውጣት ይችላሉ፡፡ አንድ ‹‹ሷዕ›› ይሆንላቸዋል፡፡ ለዚህ ጥቂት ቢያክሉም መልካም ነው፡፡ አላህ ነፍስን ከችሎታዋ በላይ አያስገድዳትም፡፡ የአወጣጡ ስልት፡- ሰውየው ራሱን ጨምሮ ከሥሩ ያሉ የሚቀልባቸው ቤተሰቦቹን አባላት ቁጥር ያሰላል፡፡ ቁጥራቸዉን በ3 ኪ.ግ ያባዘዋል፡፡ አባዝቶ የሚያገኘውን ቁጥር ያክል ኪሎ ግራም እህል ወይም ተመኑን በገንዘብ ለ‹‹ዘካተል ፊጥር›› ይሰጣል፡፡ ለምሳሌ ሰውየው በሥሩ 9 የቤተሰብ አባላት አሉት፡፡ ከራሱ ጋር ቁጥራቸው 10 ይሆናል፡፡ እናም፡- 10 x 3 ኪ.ግ = 30 ኪ.ግራም እህል ዋጋውን ለዘካተል ፊጥር ይሰጣል፡፡ የቤት ሠራተኞች፣ ዘበኞችና ሌሎች ቤት ውስጥ የሚያገለግሉ ሰዎች ከቤተሰብ አባላት ጋር አብረው ይቆጠራሉ፡፡ የዘካተል ፊጥር ዋና ዓላማው ድሆችን በዒድ ቀን ማስደሰት እስከሆነ ድረስ ለዕለቱ እንዲደርስላቸው ገንዘብ ይሁን እህል ለነርሱ የሚሻለዉን መስጠቱ መልካም ነው፡፡ ዘካተል ፈጥር የሚሰጣቸው ወገኖች፡- ዘካተል ፊጥር የሚሰጣቸው ሰዎች ዘካ እንዲሰጣቸው የተደነገገላቸው የኀብረተሰብ ክፍሎች ናቸው፡፡ ግና ለድሆች ቅድሚያ ሊሰጥ እንደሚገባ ዑለሞች ያፀድቃሉ፡፡ የዘካ ድርሻ ለሌላቸው ሰዎች ዘካተል ፊጥርን መስጠት አይፈቀድም፡፡ ዘካተል ፊጥርን ሲሰጡ ለአካባቢ ድሆች ቅድሚያ መስጠት ይገባል፡፡   1 እና 2. ድሆች (ፉቀራእ)ና ሚስኪኖች የዘካ ዓይነተኛ ዓላማ ድህነትን ማስወገድ ነው፡፡ ኢብን ጀሪር እንዳሉት፡- ‹‹ድሃ (ፈቂር) ሰዎችን የማይጠይቅ ቁጥብ (ሙተዐፊፍ) ችግረኛ ሲሆን÷ ሚስኪን ደግሞ ሰዎችን የሚለምን ችግረኛ ነው፡፡ ለሀብታሞች ወይም ሠርተው የራሳቸውንና የቤተሰባቸውን መሠረታዊ ፍላጎት የማሟላት አቅሙ ላላቸው ሰዎች ከድሆች ድርሻ መስጠት አይፈቀድም፡፡ 3.  የዘካ አስተባባሪ ቡድን ከድሆችና ሚስኪኖች ቀጥሎ ዘካ የሚሰጣቸው ወገኖች የዘካን ገንዘብ በመሰብሰብ፣ በማስላትና በመሳሰሉት ተግባራት የተሰማሩ ወገኖች (የዘካ አስተባባሪ ቡድን ሠራተኞች) ናቸው፡፡ 4.  ‹‹ሙአልለፈህ ቁሉቡሁም›› (ኢስላምን እንዲላመዱ የሚከጀሉ ወገኖች) አዲስ ወደ ኢስላም የገቡ ሰዎች ከዘካ ድርሻ አላቸው፡፡ ኢስላም ላይ እንዲፀኑና እንዲላመዱ፡፡   5. ሰዎችን ከባርነት ነፃ ለማውጣት የዘካ ገንዘብ ሰዎችን ከባርነት ነፃ ለማውጣት ሲባልም ወጭ ይደረጋል፡፡ ኢስላም ባርነትን ከምድር ላይ ለማስወገድ ከተጠቀማቸው በርካታ ስልቶች ይህ አንዱ ነው፡፡ 6. ዕዳ ያለባቸው ሰዎች በዕዳ የተያዙና ለመክፈል የተቸገሩ ሰዎችም የዘካ ገንዘብ ባለመብቶች ናቸው፡፡  ዕዳቸውን መሸፈን የሚያስችላቸውን ያህል የዘካ ገንዘብ ሊቀበሉ ይችላሉ፡፡ 7. በአላህ መንገድ (ፊ ሰቢሊልላህ) ‹‹ፊ ሰቢሊልላህ›› ወደ አላህ ሊያደርስ፤ የአላህን እርካታ ለመጎናፀፍ የሚያስችል ማንኛውም መልካም ተግባር ሊሆን ይችላል፡፡ ለምሳሌ የኢስላምን መልዕክት ለሰዎች ማድረስ የሚያስችሉ የዳዕዋ ተቋማትንና ድርጅቶችን ማቋቋም፣ ሙስሊሞችን በትክክለኛ ኢስላማዊና ስብዕና መቅረጽ የሚያስችሉ፣ የተለያዩ ተያያዥ ተቋማትን መገንባትና መዶገም የመሣሠለው ሊሆን ችላል፡፡ 8.     በጉዞ ላይ እክል የገጠመው መንገደኛ (ኢብኑ ሰቢል) ወደ ሀገሩ ለመግባት እክል ያጋጠመው መንገደኛ ገንዘብ የሚያገኝበት ሁኔታ የማይመቻችለት ከሆነ ሀገሩ ላይ ባለንብረት ቢሆንም እንኳ ዘካ ይሰጠዋል፡፡
Show all...
👍 8🙏 1
በዛሬው እለት መጪውን የዒድ-አል ፊጥር በዐልን በማስመልከት #ኒዛምፋሽን ኑ የቲሞችን እናልብስ በሚል መሪ ቃል በተቋማችን ለሚገኙ ህፃናት ዒድን አምረው እና ተደስተው እንዲውሉ በማሰብ 30 ለሚሆኑ ልጆቻችን ውብ የሆኑ ጀለቢያዎችን በነፃ በመስራት አስረክቧል። እኛም ልጆቹን አልፎም ተቋሙን ስላስደሰተልን የምስጋና የምስክር ወረቀት አበርክተናል። ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000278180388 አዋሽ ባንክ 01425797253900 ስልክ 0954834163/0912927557 INSTAGRAM https://instagram.com/ummiorphanscharity FACEBOOK [ https://www.facebook.com/ummicharityinstitute ] TELEGRAM [ https://t.me/ummi_charity ] https://t.me/ummicharity tiktok https://vm.tiktok.com/ummicharity.orpha https://vm.tiktok.com/ummicharityinstitue YOUTUBE https://youtu.be/Ea-MhtYSy74
Show all...
19
ረመዷን - 25 “ሰሉላሀ አል-ዐፍወ ወል ዓፊያ” ይላሉ ሐቢባችን (ሶ.ዐ.ወ.)፡፡ “አላህን ምህረትና ጤና ለምኑት” ማለት ነው፡፡ 'ታምሜ ከመታገስ ይልቅ፣ ጤና ሆኜ አላህን ባመሰግን ይሻለኛል ' ይላሉ አቡበክር አስ ሲዲቅ (ረ.ዐ.)። መፈተን እና ጤና ማጣትን ማንም አይወድም። ከዓፊያ የበለጠ ነገር ይኖር ይሆን ! አላህ በችሮታው ረመዷንን በጤና አደረሰን፣ በጤናም ፆምን፡፡ ሳያመን፣ ራስምታት እንኳን ሳያገኘን፣ ሳይደክመን፣ ከባድ ሓጃ ሳይገጥመን፣ ሁሉንም ቀናት ፆመንና ቆመን እዚህ የደረስን በርግጥም የአላህ ችሮታ በኛ ላይ ብዙ ነው። ለዚህም ለአላህ የምናቀርበው ምስጋና የበዛ መሆን አለበት፡፡ አልሐምዱ ሊላህ፡፡ ጤና መሆን ቀላል ነገር አይምሰላችሁ፤ በረመዷን ለአንድ ቀን ጤና ማጣት ብዙ ዕድል ያሳጣል። የጤና እክል ስንቱን ከምኞቱ ገድቧል መሰላችሁ!፣ ስንቱን ከፕሮግራሙ አሰናክሏል፣ ስንቱ መስጊድ መሄድን እየተመኘ፣ ጀማዓ እየናፈቀው አልጋው ላይ ቀርቷል!። አላህ የተመሰገነ ይሁን። ለራሳችሁም ሆነ ለሌሎች አሁንም አላህን ሰላምን ጤና ለምኑት። የአካል ጤና፣ የመንፈስ ጤና፣ የአገር ጤና፣ የዉስጥ የዉጭ ጤና፣... አላህ ሰላም ጤና ያቆያችሁ። ጤና ሰላም ፤ ሰላም ጤና፡፡
Show all...
👍 17🥱 1
ረመዷን - 24 ዱንያ የዉድድር ሜዳ ናት። አሯሯጩ ሳይሆን የጨረሰው ነው ሚሽለመው። ያቋረጠው ሳይሆን በጽናት ያጠናቀቀው ነው ትልቅ ስኬት የሚጎናፀፈው። ከረጅም ሩጫ በኋላ ተወዳዳሪዎች ይዳከማሉ። ወደ መዳረሻው እየቀረቡ በመጡ ቁጥር በርካቶች ይንጠባጠባሉ። የሥራዎች ፍፃሜያቸው ነዉና ሚታየው ብልሆች ግን ስለ ፍፃሚያቸው ነው የሚጨነቁት። ከዛሬው ድካም ይልቅ የነገን እርካታ ነው አሻግረው የሚያዩት። ስለሆነም ጽኑ ናቸው፣ ብርቱ ናቸው፣ ጠንካሮች ናቸው፣ ትጉሃን ናቸው። ረመዷን አሁንም አለ። ከረመዷን በጥሩ ዉጤት ለመውጣት ማለቂያው አካባቢ መበርታት አስፈላጊ ነው። የዉድድር ፈረሶች ለማሽነፍ ያለየሌለ ሀይላቸዉን የሚጠቀሙት በመጨረሻ ዙር ላይ ነው። በዉድድሩ መጨረሻ አካባቢ ከሚሳነፉት እንዳንሆን እንጠንቀቅ። አላህ ረመዷናቸው ተቀባይነታቸው አግኝቶ፣ ኻቲማቸው አምሮ፣ ዉጤታቸው ሰምሮ ረመዷንን ከሚሰናበቱት ያድርገን። እስከመጨረሻው መስመር ድረስ በርቱ።
Show all...
👍 21 1