የኦርቶዶክስ ተዋህዶ መዝሙሮችና ትምህርቶች
Open in Telegram
✞ በዚህ Channel ላይ የኦርቶዶክስ የመምህራን ትምህርቶችና ትክክለኛ መዝሙሮች ይተላለፉበታል ኑ በአንድነት እንዘምር እናመስግን። አንደበት ያላችሁ ለእግዚአብሔር ዘምሩ የተከበረ ነው በሰማይ በምድሩ! "ድምፁ መልካም በሆነ ፀናፅል አመስግኑት እልልታ ባለው ፀናፅል አመስግኑት"ሃሄ ሉያ፨ መዝ ፻፶፥፭ (150፥5) ●●◎◉••••••• ✞ •••••••◉◎●● ፍቅር ይኑረን @ZebbeneLEMA
Show moreThe country is not specifiedThe category is not specified
2 096
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
፧
ከዓርብ የቀጠለ
7 ታላላቅ ተአምራት ከ6-9:00 ታየ
1. ጸሐይ ጨለመች
2. ጨረቃ ደም መሰለች
3. ከዋክብት ረገፉ
4. አለቶች ተሰነጣጠቁ
5. መቃብራት ተከፈቱ
6. ሙታን ተነስተው ታዩ
7. የቤተመቅደስ መጋረጃ ተቀደደ
ከሁሉም ትልቁ ተአምር የማይሞተው መሞቱ ነው እስካሁንም በአህዛብ ዘንድ መታመን ያልቻለ ሀቅ።
በነገራችን ላይ ጎኑን የወጋው ሌንጊኖስ ከጎኑ በፈሰሰው ደምና ውሀ እውር የነበረው 1 አይኑ ተፈውሶለት በጌታ አምኖ በሰማእትነት ሞቷል። ከመጀመሪያውም ጀምሮ ለጌታ ሲቆምለት የነበረው ለስልጣኑ ሲል ብቻ ጌታን አሳልፎ ሳያምንበት አለፍቃዱ የሰጣቸው ጰንጠናዊው ጲላጦስም ከትንሳኤው በሁዋላ ሊቃነ ካህናትና የመቃብሩ ጠባቂ የነበሩት ወታደሮች ትንሳኤውን መደባበቃቸውንና ሐዋርያት እንደሰረቁ ማስወራታቸውን ጌታ ግን የእውነት መነሳቱን ሲሰማ እርሱም አምኖ ተገድሏል
በዚህ እለት በቤተክርስቲያን በየሰአቱ የሚሰበኩ ምስባኮች
💠 1:00 መዝ 35÷1
💠 3:00 መዝ 22÷16
💠 6:00 መዝ 69÷21
💠 9:00 መዝ 143÷6
💠 11:00 መዝ 143÷3
በዚ እለት ቤተክርስቲያን ሙሉ ቀን አይቀርም።ጥብጣብ እንዳያመልጦ በተለይ "ይሁዳ ወልዱ ይደምሰስ "ሥርአት እጅግ ተወዳጅ ነው። የማታውቁ ሄዳችሁ ተመልከቱ። መሄድ የግድ ነው!!!
ቅዳሜ ይቀጥላል
https://t.me/Ortodox_Tewaahdo
፧
፧
ከዓርብ የቀጠለ
13. ቀይ ልብስ አልብሰው: የእሾህ አክሊል ደፍተው ዘንግ አሲዘው ዘበቱበት
14. መንገድ ላይ ደበደቡት:ገፍትረው ጣሉት: ወደቀ ተደፋ:ተነሳ: ምራቃቸውን ተፉበት: እናቶች አለቀሱ: ከቀሬና የመጣ ስምኦን የተባለ መስቀሉን በመሸከም አገዘው: አንዲት ሴት ደሙን ከፊቱ በነጭ ጨርቅ ጠረገች።ፊቱን የጠረገችበት ጨርቅም የጌታን የፊቱን ስእል ያዘ።(አውሮቅላ የጲላጦስ ሚስት ናት(ቬሮኒካም እንደሆነች ይነገራል)
15.በስድስት ሰአት በመስቀል ቸንክረው ከሁለት ወንበዴዎች መሀል ሰቀሉት
16. ልብሱን እጣ ተጣጥለው ወሰዱት
17. በመስቀል ላይ ሳለ ተሳለቁበት: ሆምጣጤ አጠጡት: ጎኑንም በጦር ወጉት
18. በመስቀል ሆኖ 7 ታላቅ ቃላትን ተናገረ: 7 ታላላቅ ተአምራትም ተፈጠሩ
19. በመስቀል ላይም ከ6-9 ሰአት ብዙ ከተሰቃየ በዋላ ነፍሱን በፈቃዱ ሰጠ
20. ዮሴፍ ዘአርማትያስና ኒቆዲሞስ በ11:00 ላይ አውርደው ገንዘው በአዲስ መቃብር ቀበሩት
(ማቴ 26፥57 ሜቴ 27፥61 ማር 14÷53 ማር 15÷45 ሉቃ 22÷54 ሉቃ 23÷56 ዮሐ 19÷32...)
13ቱ ሕማማተ ደረሱበት
1. ተኮርተ ርእስ/ራሲን መመታቱ
2. አክሊለ ሶክ/የሾህ አክሊል መድፋቱ
3. ተአስሮ ድህሪት/የዋሊት መታሰሩ
4. ሰትየ ሐሞት/ሐሞት መጠጣቱ
5. ወሪቀ ምራቅ/ምራቅ መትፋታቸው
6. ተቀስፎ ዘባን/ጀርባውን መገረፉ
7. ጸዊረ መስቀል/መስቀል መሸከሙ
8. ተጸፍኦ መልታህት/በጥፊ መመታቱ
9. በሳዶር ቀኝ እጁን መቸንከሩ
10. በአላዶር ግራ እጁን መቸንከሩ
11. በዳናት 2 እግሩን ከመስቀል ጋር ቸነከሩት
12. በአዴራ መሐል ልቡን ቸነከሩት
13. በሮዳስ ደረቱን ቸነከሩት
https://t.me/Ortodox_Tewaahdo
💠 አርብ 💠
ትልቁና ድንቁ ቀን እለተ አርብ።በሕማማት ሳምንት ውስጥ ያለው አርብ "ስቅለት "ተብሎ ይጠራል።ኢየሱስ ክርስቶስ በወታደሮች ከተያዘ ጀምሮ ነፍሱን እስከሰጠበትና ወደመቃብር እስከወረደበት ድረስ በዚህ እለት የተፈጸሙት ድርጊቶች ይታሰባሉ። በአራቱም ወንጌላትም ተጽፎ ይገኛል።
1. ጌታችንን ሐሙስ ማታ 3:00 ከተያዘበት ጀምሮ ወደ ካህናቱ አለቃ ግቢ ወስደው እስኪነጋ ደበደቡት
2. ንጋት 12 ሰአት ላይ ወደ ሸንጓቸው አቅርበውት በሐሰት ከሰሱት
3. ጠዋት 3:00 ላይ በጲላጦስ የፍርድ ወንበር ፊት ገትረውት የሐሰት መአት ክስ አወረዱበት
4. ጲላጦስ ምንም አላገኘበትምና ወደ ገሊላ ሐገረ ገዥ ሔሮድስ ዘንድ ላከው
5. ሔሮድስም በንቀት አናገረው የንግስና ካባውንም አልብሶ አፌዘበት።መልሶም ወደ ጲላጦስ ላከው
6. ወታደርች በአራት መአዘን አንገቱን አስረው እያንገላቱ አመላለሱት።እጅግ ብዙ ጊዜ እየወደቀ ተነሳ
7. ጲላጦስ ድጋሚ አገኘውና ምንም ስላልተገኘበት ገርፌ ልልቀቀው ብሎ በአደባባይ አስገረፈው
8. ወታደሮች እጃቸው እስኪዝል ጅራፍ የያዙበት እጃቸው እስኪቆስል ደበደቡት
9. በተራ በተራ እያረፉ ገበጣ እየተጫወቱ ከ6666 በላይ ጊዜ ገረፉት: ደሙ ጎረፈ ስጋው እየተቆረሰ ወደቀ: አጥንቱ ሁሉ ታየ ነጭ ስጋው ታየ: ደም ግባቱ መለየት እስካይቻል ጠፋ "እንወደው ዘንድ ደምግባት የለውም "የተባለው ትንቢት ተፈጸመ
10. አይሁድ አልረኩምና ሕዝቡን በጌታ ላይ አሳመጹ: "ክርስቶስ ስቀለው በርባንን ፍታልን "እያሉ ጮሁ
https://t.me/Ortodox_Tewaahdo
💠 አርብ 💠
ትልቁና ድንቁ ቀን እለተ አርብ።በሕማማት ሳምንት ውስጥ ያለው አርብ "ስቅለት "ተብሎ ይጠራል።ኢየሱስ ክርስቶስ በወታደሮች ከተያዘ ጀምሮ ነፍሱን እስከሰጠበትና ወደመቃብር እስከወረደበት ድረስ በዚህ እለት የተፈጸሙት ድርጊቶች ይታሰባሉ። በአራቱም ወንጌላትም ተጽፎ ይገኛል።
1. ጌታችንን ሐሙስ ማታ 3:00 ከተያዘበት ጀምሮ ወደ ካህናቱ አለቃ ግቢ ወስደው እስኪነጋ ደበደቡት
2. ንጋት 12 ሰአት ላይ ወደ ሸንጓቸው አቅርበውት በሐሰት ከሰሱት
3. ጠዋት 3:00 ላይ በጲላጦስ የፍርድ ወንበር ፊት ገትረውት የሐሰት መአት ክስ አወረዱበት
4. ጲላጦስ ምንም አላገኘበትምና ወደ ገሊላ ሐገረ ገዥ ሔሮድስ ዘንድ ላከው
5. ሔሮድስም በንቀት አናገረው የንግስና ካባውንም አልብሶ አፌዘበት።መልሶም ወደ ጲላጦስ ላከው
6. ወታደርች በአራት መአዘን አንገቱን አስረው እያንገላቱ አመላለሱት።እጅግ ብዙ ጊዜ እየወደቀ ተነሳ
7. ጲላጦስ ድጋሚ አገኘውና ምንም ስላልተገኘበት ገርፌ ልልቀቀው ብሎ በአደባባይ አስገረፈው
8. ወታደሮች እጃቸው እስኪዝል ጅራፍ የያዙበት እጃቸው እስኪቆስል ደበደቡት
9. በተራ በተራ እያረፉ ገበጣ እየተጫወቱ ከ6666 በላይ ጊዜ ገረፉት: ደሙ ጎረፈ ስጋው እየተቆረሰ ወደቀ: አጥንቱ ሁሉ ታየ ነጭ ስጋው ታየ: ደም ግባቱ መለየት እስካይቻል ጠፋ "እንወደው ዘንድ ደምግባት የለውም "የተባለው ትንቢት ተፈጸመ
10. አይሁድ አልረኩምና ሕዝቡን በጌታ ላይ አሳመጹ: "ክርስቶስ ስቀለው በርባንን ፍታልን "እያሉ ጮሁ
https://t.me/Ortodox_Tewaahdo
ሕጽበተ እግር
የዮሐንስ ወንጌል 13
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹² እግራቸውንም አጥቦ ልብሱንም አንሥቶ ዳግመኛ ተቀመጠ፥ እንዲህም አላቸው፦ ያደረግሁላችሁን ታስተውላላችሁን?
¹³ እናንተ መምህርና ጌታ ትሉኛላችሁ፤ እንዲሁ ነኝና መልካም ትላላችሁ።
¹⁴ እንግዲህ እኔ ጌታና መምህር ስሆን እግራችሁን ካጠብሁ፥ እናንተ ደግሞ እርስ በርሳችሁ እግራችሁን ትተጣጠቡ ዘንድ ይገባችኋል።
¹⁵ እኔ ለእናንተ እንዳደረግሁ እናንተ ደግሞ ታደርጉ ዘንድ ምሳሌ ሰጥቻችኋለሁና።
¹⁶ እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ባሪያ ከጌታው አይበልጥም። መልእክተኛም ከላከው አይበልጥም።
¹⁷ ይህን ብታውቁ፥ ብታደርጉትም ብፁዓን ናችሁ።
“ቀንበሬን በላያችሁ ተሸከሙ ከእኔም ተማሩ፥ እኔ የዋህ በልቤም ትሑት ነኝና፥ ለነፍሳችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ፤”
የማቴዎስ ወንጌል 11፥29
ኦ_የማይሞተው_ሞተ_O_Yemaymotew_Mote_በኩረ_መዘመራን_ኪነጥበብ_ዝማሬ_መላእክት_low.mp34.15 MB
📌 📌 📌
✝️፭ሐዋርያቲሁ✝️
ጌታመሐላቸው ተገኝቷል
የሐዋርያትን እግርአጥቧል
አባትና እናት ሆናቸው
ጥበብንም አስተማራቸው
ሃሌ ሉያ
የወደዳቸውን እነሱን ወደዳቸው
በትህትና ሆኖ ይኸው አጠባቸው
ሰጣቸው ለሕይወት ስጋውና ደሙን
እንዲመሰክሩ እስከሞት ስሙን
አዝ...
ሥላሴን በቤቱ አስተናግዶ ነበር
እግራቸውን አጥቦ አብርሃም በፍቅር
ዛሬ መለሰለት ይህንን ውለታ
ዝቅ ብሎ አጠበ አማኑኤል ጌታ::
አዝ...
ይሁዳም ታጠበ ሳይከራከረው
አካሉ ከጌታ ልቡ ከአይሁድ ነው
አሳልፎ ሰጠ ደግ መምህሩን
ታሪኩን ቀይሮ ሰው ያረገውን::
ሥላሴን በቤቱ
አዝ...
ራሱን ዝቅ አረገ አምላካቸው ሲሆን
ምሳሌውን ተወ እንዲመስሉ እርሱን
ከእናንተ የሚሻ ታላቅ መሆንን
በመካከላችሁ ታናሽ ሰው ይሁን
ሥላሴን በቤቱ
አዝ...
አለምን የያዘ ፍጥረቱን የፈጠረ
አሳልፎ የሚኖር ያለ የነበረ
ተገልጦ አየነው ልዑሉ ትሁት
ረቂቁ ገዘፈ ሊያድነን ከሞት
ሥላሴን በቤቱ
✝️/ ❖ / ❖ / ❖ / ❖ /❖ /✝️
Join✥✥👇🏽✝️👇🏽✥✥ተቀላቀሉ
...◉❖◉●••┈👇🏽✞✟👇🏽✞✟┈••●◉❖◉...
Mezmur
https://t.me/Ethiopianmezmur12
Sebket
https://t.me/ETO_Orthodox_Tewahedo_sebket
Nisha
https://t.me/EtoOrtodoxNishaMezmur
...◉❖◉●••┈✝️✞✟✝️✞✟┈••●◉❖◉...
📌Share
አኑሮኛል ቸርነትህ
ያቺ ፈዋሽ አዳኝ እጅህ ዛሬም ለኔ ተዘርግታ
በሐጢያት ርቄ እንዳልጓዝ አስረኸኛል በውለታ
ደግሞስ ህይወት ምርጫ ቢሆን ካንተ ወደማን ይኬዳል
አባቴ ፍቅርህ እኮ ጌታዬ ፍቅርህ እኮ አለምን ያስክዳል
ሞቼ ነበር ተቀብሬ ጌታ ወደ እኔ ባትመጣ
አንተ ሞቴን ባትሞትልኝ ወዴት ነበር የእኔ እጣ
ከንቱ ነበር ማንነቴ ተሸናፊ ለዚች ዓለም
ግን አንተ የያዝከው አባቴ የያዝከው ይኖራል ዘላለም
መቅደስህን ተጠግቼ አይቻለሁ ብዙ ነገር
በልቤ ውስጥ ያስቀመጥኩት እንዲህ ለሰው ማይነገር
ግን የሆነው ሁሉም ሆኖ የለም ዛሬ ያላረፈ
የመከራው እሳት የፈተናው እሳት ባንተ እየታለፈ
አይጠፋኝም ያ ፈገግታ ልጅ ብለህ ያሳየህኝ
አመፀኛ መጥፎም ሆኜ በትክሻህ ላይ ያኖርከኝ
እንዲህም አይነት ወዳጅ አለ እየጠሉት የሚያፈቅር
ስሙም ኢየሱስ ነው 2 የፅድቃችን ሚስጥር
ስነፈርቅ ሳለቅስብህ እሺ እያልከኝ ሁሉም ሆነ
ማይሆንለት ነገር የለም ለካስ ባንተ የታመነ
መቸኮሌ መጣደፌ አምላኬ ሆይ በከንቱ ነው
መፈፅሙ ላይቀር 2 ጌታዬ አንተ ያልከው
https://t.me/Ortodox_Tewaahdo
ተወዳጅ ሆይ! ክርስቶስ ኢየሱስ እንዲህ ይልሃል፦
"አንተ ግን ለድኾች ምጽዋትን ትሰጣለህ፤ እኔም እጄን ዘርግቼ ካንተ እቀበላለሁ፡፡ የታረዙትን በምታለብሳቸው ጊዜ እኔን ታለብሰኛለህ፡፡ ...የታሰሩትን በምታረጋጋቸው ጊዜ በመካከላቸው ኾኜ በዚያ ታገኘኛለህ፡፡ በሽተኛውንም በምትጎበኘው ጊዜ ከእርሱ ጋር በአልጋው ላይ ኾኜ ዳግመኛ ታገኘኛለህ፡፡
በቦታው ኹሉ የራቅሁ አይደለሁም፡፡ ትእዛዜን በምትፈጽምበት ዘንድ እኔ ከአንተ ጋር እኖራለሁና ችግረኞችን የምረዳቸው እኔ ነኝና፤ ለድኾች የምታደርገው ኹሉ ለእኔ ማድረግህ ነው፡፡ እኔም በእርሱ ፈንታ በጎ ዋጋ እከፍልሃለሁና፡፡
በቤትህ ውስጥ እንግዳ በአሳደርክ ጊዜ እነሆ ከእንግዳው ጋር በማደሪያህ አስገባኸኝ፡፡ እንደዚህ ለሚያደርግ ቁጣዬ ከእርሱ ይርቃል፤ ወደ ሕይወት ወደብም አደርሰዋለሁ፡፡ ከክፉ ነገር ኹሉ እጠብቀዋለሁ፡፡ እባርከዋለሁ፡፡ ዘሩንም አበዛለሁ፡፡ ዋጋውንም በሰማይ ባለው በአባቴ ዘንድ ከፍ ከፍ አደርገዋለሁ፡፡ ዘለዓለማዊ ዕረፍትንም እሰጠዋለሁ፡፡"
(#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ)
ቅዱስ ሲኖዶስ በጠራው አስቸኳይ ጉባኤ የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ ስርአተ ቀብር እሁድ የካቲት 27/06/2014 በመንበረ ፀባኦት ቅድስት ስላሴ ካቴድራል እንዲፈፀም ወስኗል።
✨✨✨✨🙏🙏🙏🙏✨✨✨✨
እንኳን ለጾመ ሑዳድ አደረሰን አደረሳችሁ
በዚህ ጾም ክርስቲያን ሊጾም የሚገባውን ሰዓት አስመልክቶ የቤተክርስቲያናችን መጽሐፈ ሕግ የኾነው ፍትሐነገሥት እንዲህ ይለናል።
👉“በዐቢይ ጾም መጀመሪያ ሱባኤ ፀሐይ እስኪገባ ይጹሙ፣ ሌሎቹን ሳምንታት እስከ 11 ሰዓት ይጹሙ፥ በሰሙነ ሕማማት ግን ኮከብ እስኪወጣ ይጹሙ” ብለዋል። (ፍት.ነገ.አን 15፥595)
👉“ዓርብንና ቅዳሜን (ሥቅለትን እና ቀዳም ሽዑርን) ግን ሁለቱንም በአንድነት ይጹሟቸው፣ የሚችል እስከ ሌሊት ዶሮ ጩኸት ድረስ ምንም ምን አይቅመስባቸው፣ ሁለቱን በአንድነት መጾም የማይቻለው ግን ቅዳሜን ይጹም”
(ፍት.ነገ.አን 15፥578)
👉እንግዲህ ስንጾም በዚህ መልኩ እንዲሆን እንጣር። ሊቁ ቅዱስ ያሬድ ደግሞ ጾሙን ከምግብ ከመጠጥ በመቆጠብ ብቻ ሳይኾን መጾም ያለብን
ከነዚህም ነው ይለናል።
👉 የስሜት ሕዋሳቶቻችን ጭምር መጾም አለባቸው በማለት "ይጹም ዓይን፥ ወእዝንኒ ይጹም፥ ወአፍኒ ከማሁ።" "ዓይን ይጹም (ክፉ ነገሮችን ከመመልከት)፥ ጆሮም ይጹም (ደግ ያልኾኑ ጸያፍ ነገሮችን ሥጋዊ ቃላቶችን ከመስማት)፥ አንደበትም እንዲሁ (ሰውን የሚያሳፍሩ እግዚአብሔርን የሚያሳዝኑ ንግግሮችን ከመናገር)።" ይለናል።
👉 ጾሙን ከጸሎት፥ ከሥግደት እና ከምጽዋት ጋር አጣምረን ለመጾምም እንጣር።🤲🤲🕯🕯🕯🙇♀🙇🙇♂
https://t.me/Ortodox_Tewaahdo
መልካም የጾም ወራት ይኹንልን
✝ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። 🙏
🙏 እንኳን ለዐቢይ ጾም ለመጀመርያ ሳምንት ለዘወረደ (ለጾመ ሕርቃል) በሰላም አደረሰን።
+ + +
✝የዘወረደ መዝሙር፦ ሃሌ ሉያ "ተቀነዩ ለእግዚአብሔር በፍርሃት ወተሐሠዩ ሎቱ በረዓድ እስመ ለዓለም ምሕረቱ ለትውልደ ትውልድ ጽድቁ ንሕነሰ ሕዝቡ ባኡ ቅድሜሁ በተጋንዮ ወውስተ አዕፃዲሁ በስብሐት እመንዎ፤ እ፣ ንጹም ጾም ወናፍቅር ቢጸነ ወንትፋቀር በበይናቲነ፤ እ፣ አክብሩ ሰንበተ ተገበሩ ጽድቀ እስመ ሰንበትሰ በእንተ ሰብእ ተፈጥረት፤ እ፣ ምሕረተ ወፍትሐ አሐሊ ለከ እዜምር ወእሌቡ ፍኖተ ንጹሐ እስመ ለዓለም ምሕረቱ ለትውልደ ትውልድ ጽድቁ ንሕነሰ ሕዝቡ አባግዐ መርዔቱ። ትርጉም፦ ለእግዚአብሔር በፍርሃት ተገዙ፣ ለእርሱም መገዛት ደስ ይበላችሁ። እግዚአብሔር ቸር ምሕረቱም ለዘላለም፣ እውነቱም ለልጅ ልጅ ነውና። እኛስ ሕዝቡ የማሰማሪያው በጎች ነን፤ ወደ ደጁ በመገዛት፣ ወደ አደባባዮችም በምስጋና ግቡ፤ ጾምን እንጹም፤ ጓደኞቻችንን እናፍቅር፤ እርስ በርሳችንም እንፋቀር። ሰንበት ስለሰው ተሠርታለችና ሰንበትን እናክብር። እውነትንም እንሥራ፤ አቤቱ ምሕረትንና ፍርድን እቀኝልሃለሁ፤ እዘምራለሁ፤ ንጹሕ መንገድንም አስተውላለሁ። ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በጾመ ድጓው ላይ።
+ + +
✝ ዘወረደ፦ የ0ቢይ ጾም የመጀመሪያው እሁድ (ሳምንት) ዘወረደ ይባላል።
✝ ጌታችን እኛን ለማዳን ከሰማይ መውረዱን የሚነገርበት ሳምንት በመሆኑ ዘወረደ ተብሏል።
✝ ከሰማይ ወረደ ማለት እርሱ የሌለበት ኖሮ ካለበት ወደዚህ መጣ ማለት አይደለም እርሱስ ጽርሐ አርያም ምጥቀቱ በርባኖስ ጥልቀቱ ፥ አድማስ ናጌብ ስፋቱ ተብሎ የማይነገርበት በዓለም ሙሉዕ ነውና ዓለማትን ቢወስን እንጂ ዓለማት እርሱን አይወስኑትም ።
✝ የፀሐይ ብርሃን ከክበቡ ሳይለይ ከ0ይናችን ብሌን ጋር እንደሚዋሓድ ወልደም ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ሳይለይ በምልዓቱ መወሰን ሳይኖርበት በሥጋ ማርያም መገለጹን ሰው መሆኑን ያስረዳል ::
✝ ከሰማይ ወረደ ሲባል ስንሰማ "ሰማይ" ያለው ዕበዩን፣ ክብሩን ፣ ልዕልናውን ፣ ጌትነቱን፣ መንግሥቱን ፣ ርቀቱን .... ነው :: ስለዚህ ከሰማይ ወረደ ማለት የባሪያውን መልክ ይዞ ሰው መሆኑን ለመግለጽ ነው። ፊል 2፥6-8
✝ ሰው ሆኖ መፈጠር ታላቅ ክብር ነው ለአምላክ ግን ሰው መሆኑ ተዋርዶ ነውና ይልቁንም እኛን ለማዳን በለበሰው ሥጋ መራብ መጠማቱ ፣ መገረፍ መታመሙ ... እንኳን ከአብ እና ከመንፈስ ቅዱስ ይቅርና ከመላእክት እንኳን ያነሰበት ነው መላእክት በባህሪያቸው መራብ መጠማት፣ መታመም የለባቸውምና " ከመላእክት እንኳን አሳነስከው" ያለውም ስለዚህ ነው ። መዝ 8፥5፣ ዕብ 2፥7
✝ ይህ ማለት ግን ወልድ ሰው መሆኑ አምላክነቱን አጥቶ በዚህም ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ አነሰ ማለት አይደለም ጌታችንም "አብ ይበልጠኛል" ያለው በለበሰው ሥጋ ባገኘው መራብ መጠማት አነሰ ለማለት ነው አብ እና መንፈስ ቅዱስ ሰው ሆነው መራብ መጠማት ... ያላገኛቸው መሆኑን ለመግለጽ ነው። ዮሐ.14፥28
✝ ቅዱስ ያሬድ ጾመ ድጓውን ሲጀምር ሃሌ ሃሌ ሉያ "ዘወረደ እም ላዕሉ አይሁድ ሰቀሉ ወሚመ ኢያእመሩ እግዚአ ኩሉ ዘየሃዩ በቃሉ"። ትርጉም፦ ከሰማየ ሰማያት የወረደ አይሁድ የሰቀሉት ሁሉን በቃሉ እንደሚያድን አይሁድ ያላወቁት ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። በማለት ሰው ሆኖ በአይሁድ ተዋርዶ ያገኘው መሆኑን የዚህን ሳምንት ጠቅላላ ሀሣብ ይገልጻል። ምንጭ፦ ከአምኃ ሥላሴ (መኩሪያ ተስፋዬ) ፔጅ የተወሰደ።
+ + +
✝ የዐቢይ ጾም የመጀመሪያው ሌላ ስሙ ጾመ ሕርቃል፦ ሕርቃል ማን ነው? ለምንስ በስሙ ተሰየመ? በ614 ዓ.ም ኪርዮስ የተባለ የፋርስ ንጉሥ ኢየሩሳሌምን በመውረር ጥቃት አደረሰ፡፡ በዚህ ወቅት በኢየሩሳሌም ንግሥት ዕሌኒ በሠራችው ቤተመቅደስ ውስጥ ሲገባ ንግሥቷ በክብር አስቀምጣው የነበረው የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል እንደ ፀሐይ ሲያበራ አገኘው፡፡
✝ ቢነካው አቃጠለው ዲያቆናቱን አሸክሞ ሌላውን ንዋየ ቅድሳት ዘርፎ 60ሺ የሚደርሱትን አቁስሎ ገድሎ 3ሺ የሚሆኑትን ማርኮ ከተማዋንም አቃጥሎ ወደ ፋርስ ባቢሎን ይመለሳል፡፡ በዚህ ጊዜ ከጦርነቱ ያመለጡ በየዋሻው በየጉራንጉሩ ገብተው የተሸሸጉ ተሰብስበው ከ14 ዓመት በኋላ በ628 ጩኸታቸውንና የደረሰባቸውን በደል ለክርስቲየኑ የሮም ንጉሥ ሕርቃል ይነግሩታል፡፡
✝ እርሱም "ሐዋርያት ሰውን የገደለ ዕድሜውን በሙሉ ይጹም ስላሉ እንዴት ላድርገው?" አላቸው እኛ "የአንተን ዕድሜ ተከፋፍለን እንጾማለን" ብለው አንድ አንድ ሳምንት ደርሷቸው ጾሙን በሚገባ ጾመውታል፡፡ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ መስቀልና የተማረኩ ክርስቲያኖችን ለመመለስ ሕርቃል ጦር መዝዞ በኪርዮስ ላይ ተነሳበት ድል ለሕርቃል ሆነና መስቀሉን ያለበትን አጥቶ ሲቸገር መስቀሉን ሲቀብርና ዲያቆናቱን ሲያስገድል በመስኮት ሆና ያየችው ከኢየሩሳሌም የተማረከች አንዲት ብላቴና አሳይታው አውጥቶ በልብሰ መንግሥቱ ጠቅልሎ ወደ ቊስጥንጥንያ ተመለሰ፡፡
✝ የተማረኩት በሙሉ ነጻ ወጡ ይህን ለማሰብ ለማስታወስ በተጨማሪም በኃጢአት ላይ ድል እንድናገኝ መንፈሳዊ ጦር በውስጣችን እንዲበዛልን መስቀልህ ከምርኮ እንደተመለሰ እኛንም ከኃጢአት ምርኮ መልሰን ለሕርቃል ድል መንሳትንና በጠላቶቹ ላይ ኃይልን እንደሰጠኸው ለእኛም በኃጢአት ላይ ድል መንሳት መንፈሳዊ ኃይልን ስጠን እያልን እንጾመዋለን፡፡
✝ በጌታ ጾም ላይ እንዲጾም የሆነበት ምክንያት ጾሙ የጌታ ጾም በሚጾምበት ወቅት ላይ ስለተጾመ ቤተክርስቲያናችን አብራ ደንግጋዋለች፡፡ እዚህ ላይ በዚያን ጊዜ ለሕርቃል ሕዝቡ ሱባኤ ይዞለታል፡፡
✝ ዛሬም እኛ ለቤተክርስቲያን ያደረግነውን በማሰብ እግዚአብሔር አምላክ ለሕርቃል የሰጠውን በጠላቶቹ ላይ ድል መንሳትን ለእኛም እንዲሰጠን የምንጠይቅበት ስለሆነ የመጀመሪያውን ሳምንት በሕርቃል ሰይመን ጾሙን እንጾማለን፡፡
✝ የእኛ ጠላት የጨለማ ገዥ የሆነው ዲያቢሎስ ነውና እሱን ደግሞ በጾም እንደምናሸንፈው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አስተምሮናል፡፡ ምንጭ፦ የመጋቢት 10 ስንክሳር እና ከፌስቡክ ከማኅበረ ጎዶልያስ ዘ ዑራኤል የተወሰደ።
+ + +
✝ የዘወረደ አራራይ ዜማ፦ ሃሌሉያ "መሐረነ ንጉሠ ስብሐት ተሣሀለነ እግዚአ ለሰንበት አቡሃ ለምሕረት ወሀበነ ጾመ ለንስሐ በዘይሰረይ ኃጢአት። ትርጉም፦ የምስጋና አምላክ ማረን የምሕረት አባት የሰንበት ጌታ ይቅር በለን ጾምን ለንስሐ ስጠን ኃጢአታችን ይሰረይ ዘንድ፡፡ ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በጾመ ድጓው ላይ።
+ + +
✝ የዕለቱ ምስባክ፦ "ተቀነዩ ለእግዚአብሔር በፍርሃት። ወተኀሠዩ ሎቱ በረዓድ። አጽንዕዋ ለጥበብ ከመ ኢይትመዐዕ እግዚአብሔር"። መዝ 2፥11-12። የሚነበቡት መልዕክታት ዕብ 13፥7-16፣ ያዕ 4፥6-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 25፥13-ፍ.ም። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 3፥10-25። የሚቀደሰው ቅዳሴ ቅዳሴ እግዚእነ ቅዳሴ ነው። መልካም የቅበላ በዓል። ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ከታች ያለውን ሊንክ ተጭነው ይቀላቀሉ።
https://t.me/Ortodox_Tewaahdo
https://t.me/Ortodox_Tewaahdo
✝ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። 🙏
+ + +
✝ "ሰላም ለከ መዓንዝር ፊልሞን። ዘፈጸምከ ገድለ ምስለ አስቃሎን። እንዘ ትብል ዘንተ ቅድመ መኰንን። አልቦ ሐይው በሠዊዕ ለጣዖት፡ ምኑን። እንበለ መዊት በክርስቶስ መድኅን"። ትርጉም፦ በመድኅን ክርስቶስ ስም ከመሞት በቀር ለተናቀው ጣዖት በመሠዋት መዳን የለም፤ ይኽነን ቃል በመኰንኑ ፊት እየተናገርኽ ከአስቃሎን ጋር ገድልን የፈጸመምኽ በገና ደርዳሪ የኾንኽ ፊልሞን ሆይ ሰላምታ ይገባኻል። ሊቁ አርከ ሥሉስ (አርኬ) የየካቲት 20።
https://t.me/Ortodox_Tewaahdo
እንኳን ለጾመ ነነዌ በሰላም አደረሳችሁ!
የቤተክርስቲያን አባቶች ይህን ፆም የወሰኑት ልትጠፋ የነበረች ነነዌን በፆም ምክንያት እግዚአብሔር ይቅር ስላላት ይህን አምላካዊ ይቅርታውን ለዘለዓለም ለማሰብና ዛሬም በዚህ ዓለም ከነነዌ የከፋ ርኩሰትንና ኃጢያትን ስላለ የነነዌ ሕዝብ ይቅር ያልክ አምላክ ዛሬን ይቅር በለን ለማለት ነው።
የነነዌ ህዝብን በምህረት የጎበኛ ቸር አባት ለሀገራችንም ለህዝባችንም ምህረትና ቸርነቱን ያብዛልን ፆሙን የበረከት ፆም ያድርግልን እግዚአብሔር ጾማችንን ጾመ ድህነት ጾመ
ስርየት ሰይጣንን ድል መንሻ የኃጢአት መደምሰሻ መንግስተ ሰማያት መውረሻ ያድርግልን አሜን!
ጾመ ሰብአ ነነዌ !
ጾመ ነነዌ ከሰባቱ የአዋጅ አጽዋማት አንዷ ስትኾን የምትጾመውም ለሦስት ቀናት ነው፡፡ ይህቺ ጾም የምትጀመርበት ዕለትም ልክ እንደ ዐቢይ ጾም ሰኞን አይለቅም፡፡ ጾሟ የምትጀመርበት ቀን ሲወርድ ወይም ወደ ኋላ ሲመጣ እስከ ጥር ፲፯ ቀን ድረስ ነው፡፡ ቀኑ ሲወጣ ወይም ወደ ፊት ሲገፋ ደግሞ እስከ የካቲት ፳፩ ቀን ይረዝማል፡፡ ጾመ ነነዌ በእነዚህ ፴፭ ቀናት ውስጥ ስትመላለስ (ከፍ እና ዝቅ ስትል) ትኖራለች፤ ከተጠቀሱት ዕለታት አትወርድም፤ አትወጣም፡፡ በዚህ ዓመትም (፳፻፲፪ ዓ.ም) የካቲት ፪ ቀን ትጀመራለች፡፡
‹‹ጾመ ሰብአ ነነዌ፤ የነነዌ ሰዎች ጾም›› የሚለው የጽሑፋችን ርእስ እንደሚያስረዳው ይህቺን የሦስት ቀን ጾም የጾሟት በነነዌ ይኖሩ የነበሩ ሰዎች ናቸው፡፡ ከተማዋም (ነነዌ) በጤግሮስ ወንዝ ዳርቻ የምትገኝ ስትኾን መሥራቿም ናምሩድ ነው /ዘፍ.፲፥፲፩-፲፪/፡፡ ጥንታዊቷ የነነዌ ከተማ ለአሦር መነሻ የኾነች፤ እጅግ ሰፊና ያማረች፤ የቅጥሯ ርዝመትም ፲፪ ኪሎ ሜትር የሚሸፈን ነበር፡፡ በከተማዋ ንጉሡ ሰናክሬም ብዙ ሕንጻዎችን ገንብቶባት ነበር /ዮናስ ፬፥፲፩/፡፡ በዚያ ዘመን የነበሩ የነነዌ ሰዎች ኀጢአታቸው በዝቶ እግዚአብሔር ሊያጠፋቸው ሲል ቸርነትና ምሕረቱ የማያልቅበት እግዚአብሔር መክሮ፣ ዘክሮ እንዲመልሳቸውና ንስሐ እንዲገቡ ነቢዩ ዮናስን ወደ ነነዌ ሕዝብ ላከው /ሉቃ.፲፩፥፴/፡፡
ዮናስ የስሙ ትርጕም ‹ርግብ› ማለት ነው፡፡ በዳግማዊ ኢዮርብዓም ዘመነ መንግሥት የነበረ ነቢይ ነው፡፡ ይህ ነቢይ መኖሪያው በገሊላ በጋትሔፌር ድንበር ከተማ ነበረ፡፡ አባቱም አማቴ ይባላል፡፡ ኢዮርብዓም ሶርያውያንን አባሮ የእስራኤልን ድንበር እንዲመልስ ነቢዩ ዮናስ ትንቢትን ተናግሯል /፪ኛነገ.፲፬፥፳፭፤ ዮናስ ፩፥፩/፡፡ ነቢዩ ኤልያስ ያስነሣው የሰራጵታዋ መበለት ሕፃን ነቢዩ ዮናስ እንደ ኾነ የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ያስረዳል /፩ኛነገ.፲፯፥፲፱/፡፡ መድኀኒታችን ክርስቶስም የዮናስን ከዓሣ ኾድ መውጣት የራሱ ትንሣኤ ምሳሌ አድርጎ ነግሮናል /ማቴ.፲፪፥፲፱-፵፪፤ ሉቃ.፲፩፥፴-፴፪/፡፡
እግዚአብሔር ‹‹ሔደህ በነነዌ ላይ ስበክ›› ባለው ጊዜ ነቢዩ ዮናስ ‹‹አንተ መሐሪ ነህ፤ ልትጠፉ ነው ብዬ ተናግሬ ብትምራቸው ሐሰተኛ ነቢይ እባላለሁ›› ብሎ ላለመታዘዝ እስራኤልን ለቆ በመርከብ ወደ ተርሴስ ሸሸ፡፡ እግዚአብሔርም ታላቅ ነፋስን አስነሥቶ መርከቧ በማዕበል እንድትመታ አደረገ፡፡ ከዮናስ ጋር በመርከቧ ተሳፍረው የነበሩ ነጋድያንም ያላቸውን ሀብት ወደ ባሕሩ መጣል ሲጀምሩ ነቢዩ ዮናስ ጥፋቱን ተገንዝቦ ‹‹ማዕበሉ በእኔ ምክንያት የመጣ ስለ ኾነ ንብረታችሁን ሳይኾን እኔን ወደ ባሕር ጣሉኝ›› ብሎ ተማጸናቸው፡፡ እነርሱም ‹‹ስለዚህ ሰው ነፍስ እንዳንጠፋ፣ ንጹሕም ደም በእኛ ላይ እንዳይደረግብን አይኾንም›› አሉ፡፡
ወደ ባሕሩ ለመጣል ዕጣ በተጣጣሉ ጊዜም ዕጣው በዮናስ ላይ ስለ ወጣ ነጋድያኑ ዮናስን ወደ ባሕሩ ጣሉት፡፡ ወዲያውኑ ከእግዚአብሔር ዘንድ የታዘዘ ታላቅ ዓሣ አንበሪ ዮናስን በአፉ ተቀብሎ ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት አሳድሮ ወደ ነነዌ አደረሰው፡፡ እግዚአብሔር የቅል ተክልን ምሳሌ በማድረግ ቅጠሉ በመድረቁ ዮናስ ባዘነ ጊዜ ‹‹አንተ ላልደከምክበት እና በአንድ ቀን በቅሎ ላደገ ቅል ስታዝን እነሆ በታላቂቱ ነነዌ ከተማ ያሉ ከአንድ መቶ ሃያ ሺሕ በላይ ሕዝብና እንስሳቱ የእጄ ፍጥረቶች ስለ ኾኑ ያሳዝኑኛል›› በማለት ነቢዩ ዮናስም ውሸታም ላለመባል መኮብለሉ ስሕተት መኾኑን አስረድቶታል፡፡
ዮናስም ነነዌ መሬት ላይ መድረሱን ባወቀ ጊዜ ከእግዚአብሔር መሸሽ አለመቻሉን ተረዳ፤ የነነዌ ሰዎችንም ‹‹ንስሐ ግቡ›› እያለ መስበክ ጀመረ፡፡ የነነዌ ሰዎችም ንስሐ በገቡ ጊዜ እግዚአብሔር ይቅር ብሎ ከጥፋት አድኗቸዋል፡፡ ሐሰት እንዳይባልም እሳቱ እንደ ደመና ኾኖ ከላይ ታይቶአል፡፡ የታላላቁ ዛፍ ቅጠል እስኪጠወልግ ድረስ አድርቆ ለሕዝቡ አሳይቷቸዋል፡፡ ንስሐቸው በከንቱ እንዳልቀረ አስረድቷቸዋል /ትንቢተ ዮናስን በሙሉ ይመልከቱ/፡፡ ታኅሣሥ ፭ ቀን የሚነበበው የመጽሐፈ ስንክሳር ክፍል ‹‹ወበልዐ አሐደ ኀምለ›› በማለት ንስሐ ያልገቡ አንድ አገር ያህል ሰዎች በእሳቱ እንደ ጠፉ ይነግረናል፡፡
ጾመ ነነዌ የሦስት ቀን ሱባኤ ናት፤ በሦስት ቀናት ጾምና ጸሎት ንስሐ የገቡ የነነዌ ሰዎች ከጥፋት እንደ ዳኑ ዅሉ፣ በብሉይ ኪዳን አስቴር ሦስት ቀን ጾማ፣ ጸልያ በእስራኤል ላይ የመጣውን መቅሠፍት እንዲመለስ አድርጋለች /አስ.፬፥፲፭-፲፮/፡፡ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም ከበዓል ስትመለስ ሕፃኑ ልጇ ኢየሱስ ክርስቶስ መንገድ ላይ ጠፍቶአት ከሦስት ቀን ፍለጋ በኋላ በቤተ መቅደስ አግኝታዋለች /ሉቃ.፪፥፵፮/፡፡ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ለሄሮድስ በሰጠው ምላሽ መልስ ሦስት ቀን የሱባኤ ፍጻሜ መኾኑን ገልጿል /ሉቃ.፲፫፥፴፪/፡፡
ጾመ ነነዌ የእግዚአብሔርን ቸርነትና መሐሪነት የምናስታውስበት ጾም ነው፡፡ ይኸውም እኛ ፍጡራኑ በበደልን ጊዜ ፈጽሞ ከማጥፋት ይልቅ ምክንያት ፈልጎ እንድንድን ያደርገናል፡፡ ዮናስ ለስብከት ፈቃደኛ ባይኾን እንኳን እግዚአብሔር በተለየ ጥበቡ እንዲሔድ አድርጎታል፡፡ በእርግጥ እግዚአብሔር ሌላ የሚልከው ነቢይ አጥቶም አይደለም፤ እርሱንም ጭምር ሊያስተምረው ስለ ፈለገ እንጂ፡፡ የነነዌ ሰዎች የተነሳሕያን ምሳሌ ናቸው፡፡ ይህም ማለት ሰው ጥፋቱን አምኖ ንስሐ ከገባ እግዚአብሔር ይቅር ማለቱን አይተውም፡፡ ለዚህም ነው ዮናስን ‹‹አንተ ላልደከምክበት እና በአንድ ቀን በቅሎ ላደገ ቅል ስታዝን እነሆ በታላቂቱ ነነዌ ከተማ ያሉ ከአንድ መቶ ሃያ ሺሕ በላይ ሕዝብና እንስሳቱ የእጄ ፍጥረቶች ስለ ኾኑ ያሳዝኑኛል›› ያለው፡፡
ቀደምት የቤተ ክርስቲያን አባቶቻችን ይህን እና ሌሎች አጽዋማትን እንድንጾም የወሰኑልን ያለ ምክንያት አይደለም፡፡ ሕጉ የተዘጋጀልን እንደ ነነዌ ሰዎች እኛም ጾመን፣ ጸልየን ከኀጢአታችን እንነጻ ዘንድ ነው፡፡ ዛሬ ዓለማችን በኀጢአት ማዕበል እየተናወጠች ባለችበት ወቅት እኛም እንደ ነነዌ ሰዎች ከበደላችን ብንመለስ እና ንስሐ ብንገባ ቸሩ ፈጣሪያችን እግዚአብሔር ይቅርታና ምሕረት የባሕርይ ገንዘቡ ስለ ኾነ ‹‹ወደ እኔ ተመለሱ፤ እኔም ይቅር እላችኋለሁ፤›› ይለናል፡፡
ስለኾነም በነቢዩ ዮናስ ላይ የተደረጉ ተአምራትንና ካለመታዘዝ የሚመጣ ቅጣት ቀላል አለመኾኑን በማስተዋል፣ ለነነዌ ሰዎች የወረደውን ምሕረት በመገንዘብ ለእግዚአብሔርም ኾነ ለሃይማኖት አባቶች እና ለወላጆቻችን መታዘዝ ይገባናል፡፡ ስንጾምም እግዚአብሔር አምላካችን መዓቱን በምሕረት፣ ቍጣውን በትዕግሥት መልሶ በኀጢአት ለጠፋው ዓለም ይቅርታውን ይልካል፡፡ በመጾማችን ራሳችን ከመዓትና ከመቅሠፍት ከመዳናችን ባሻገር በእኛ በደል ምክንያት አገራችን፣ ዕፀዋቱና እንስሳቱም ሳይቀር ከድርቅና ከቸነፈር ይተርፋሉና፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡
ምንጭ፡- (ማህበረ ቅዱሳን)
የነነዌ ሰዎችና እኛ
ከነነዌ ሰዎች በላይ ማን ክፉ ነበር? ከእነርሱ በላይ አላዋቂስ ማን ነበር? ("ቀኛቸውንና ግራቸውን የማይለዩ" ተብለው ተጠርተዋልና፡፡) ነገር ግን እነዚህ አሕዛብ፣ እነዚህ አላዋቂ፣ እነዚህ አንድ ሰውስ እንኳን የጥበብን ነገር አስተምሮአቸው የማያውቁ፣ እነዚህ ከማንም ይኹን ከማን እንደዚህ ዓይነት ትእዛዝን ያልተቀበሉ ሰዎች ነቢዩ፡- “በሦስት ቀን ውስጥ ነነዌ ትገለበጣለች” ሲል በሰሙት ጊዜ ክፉ ልማዳቸውን ኹሉ በሦስት ቀናት ውስጥ አስወግደዋል (ዮና.3፥4)፡፡
ዘማዊው ንጹህ፣ ደፋሩ ትሑት፣ ስስታሙና ጨቋኙ ራሱን የሚገዛና ደገኛ፣ ሐኬተኛውም ትጉህ ኾነ፡፡ እነዚህ ሰዎች በርግጥ ያሻሻሉት ክፋታቸውን ኹሉ እንጂ አንዱን ወይም ኹለቱን ወይም ሦስቱን ወይም አራቱን አይደለም፡፡ “እንዲህ የሚልስ የት አለ?” ብሎ የሚጠይቅ ሰው ሊኖር ይችላል፡፡ እኔም እንዲህ ብዬ እመልስለታለሁ፡- እነርሱን ሲወቅሳቸው የነበረውና፣ “የክፋታቸውም ጩኸት እስከ አርያም ድረስ ወጥቷል” ብሎ የተናገረው ነቢይ መልሶ ደግሞ የዚሁ ፍጹም ተቃራኒ የኾነን ምስክርነት አስቀምጧልና፤ እንዲህ ሲል፡- “እግዚአብሔርም ከክፉ መንገዳቸው እንደ ተመለሱ ሥራቸውን አየ” (ዮና.1፡5፣ 3፡10)፡፡ ተመልከት! ከዝሙት ወይም ከአመንዝራነት ወይም ከሌብነት ራቁ አላለም፤ “ከክፉ መንገዳቸው” እንጂ፡፡ እንዴትስ ከዚያ ሊርቁ ቻሉ? ይህን እግዚአብሔር ያውቋል እንጂ ሰው ሊመረምረው አይችልም፡፡
እንግዲህ አሕዛብ በሦስት ቀናት ውስጥ ብቻ ክፋታቸውን ኹሉ ማስወገድ ከቻሉ፥ ለአያሌ ቀናት የተመከርንና የተዘከርን እኛ ግን አንዲት ክፉ ልማድን [ለምሳሌ መሐላን] ሳናስወግድ ስንቀር ልናፍር አይገባንምን? ከዚህም በላይ እነዚህ ሰዎች ቀድሞ ክፋታቸው ጣሪያ ደርሶ ነበር፤ “የክፋታቸውም ጩኸት እስከ አርያም ድረስ ወጥቷል” የሚለውን ስትሰማ ከክፋታቸው ብዛት በቀር ሌላ ምንም ልትገነዘብ አትችልምና፡፡ ነገር ግን በሦስት ቀናት ውስጥ ወደ መልካም ምግባር ፍጽምና መድረስ ተችሏቸዋል፡፡ ፈሪሐ እግዚአብሔር ባለበት ቀናት ወይም የጊዜ ብዛት አያስፈልግምና፡፡ በተቃራኒው ይህ ፍርሐት በሌለበት ደግሞ የጊዜ ብዛት ምንም ጥቅም የለውም፡፡
የዛጉ ብረቶችን በውኃ ብቻ የሚያጥባቸው ሰው ምንም ያህል ጊዜ እነርሱን በማጠብ ቢያሳልፍም እነዚያን ዝገቶች ኹሉ ማስለቀቅ አይቻለውም፡፡ ወደ እሳት ጨምሮ የሚያወጣቸው ሰው ግን አዲስ ከተሠሩ ብረቶችም ጭምር ሳይቀር እጅግ ጽሩያን ያደርጋቸዋል፡፡ በኃጢአት የዛገ ልብም እንዲሁ በትንሽ በትንሹና በግድየለሽነት ኾኖ ዕለት ዕለት ንስሐ ቢገባም ምንም ጥቅም አያገኝም፡፡ ራሱን ወደ እቶን - ይኸውም ወደ ፈሪሐ እግዚአብሔር የሚጥል ከኾነ ግን በአጭር ጊዜ ውስጥ ኹሉንም ማስወገድ ይቻለዋል፡፡
(በእንተ ምክንያተ ሐውልታት፥ ፳:፳፩ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዳስተማረው)
"⚜️⚜️ሴተኛ_አዳሪ ስለሆንኩ ጧፉን ልነካ አልችልም!"
..............⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️.................
⚜️⚜️⚜️እኛስ ከእህታችን ምን እንማራለን ??⚜️⚜️⚜️
⚜️⚜️.................⚜️⚜️
ምን ቢመሻሽም ጻድቁ አባታችን ተክለ ሃይማኖትን ተሳልሜ ልምጣ ብዬ ወደ ደብረ አሚን ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን ሄድኩኝ፤ ወርሃዊ በዓላቸው እንደመሆኑ መጠን መግቢያው በር ላይ ግርግር አለ፤ አንዲት ተሽከርካሪ ወንበር ላይ ቁጭ ብላ ጧፍ የምትሸጥ ነጋዴ ጋር አንዲት ነጠላ የተከናነበች ወጣት ጧፍ ለመግዛት ቆማለች፤ እኔም አጠገባቸው ነኝ “ወንድም ይቅርታ አለችኝ’’ ወጣቷ፤ “አቤት” አልኳት “እኔ ስለማልገባ ነው ይህንን ጧፍ ስጥልኝ” አለችኝ፤ “እኔም ተሳልሜ ነው የምመለሰው ለሚገባ ሰው ስጪው” አልኳት፤ እሺ ለሚገባ ሰው አንተ ስጥልኝ አለችኝ፤ እኛ ስንነጋገር ተሽከርካሪ... ወንበሩ ላይ ያለችው ጧፍ ነ...ጋዴ ጧፉን እንደያዘች እጇን ዘርግታለች፤ እሺ ችግር የለውም እሰጥልሻለሁ ግን ለምን አንቺ አትሰጪም አልኳት፤ እኔ ሴተኛ አዳሪ ነኝ እንዴት በእጄ እነካዋለሁ ፤ ቤተክርስቲያን ውስጥ ገብቶ ሲቀደስ የሚበራ አይደለም ? አረክሰዋለሁ ብዬ ነው አለቺኝ፤ ደነገጥኩኝ ፤ አንዳች የሆነ ፍርሃት ሰውነቴን ወረረኝ፤ከዚህ በኃላ መልስ አልሰጠዋትም፡፡
እሺ ብቻ ብዬ ጧፉን ከጧፍ ነጋዴዋ ተቀበልኩላት፤ ብሩን ስትከፍላት እግዚአብሔር ይስጥልኝ ብላ ስትመርቀኝ አስታውሳለሁ፤ አንገቴን አቀረቀርኩኝ እኔ ግን ንጹህ ሆኜ ነው ? ይህንን ጧፍ የያዝኩት እንዴት ያለሁ ደፋር ነኝ ፤ ለምን እኔም ካንቺ የባስኩኝ ኃጢያተኛ ነኝ ፤ እኔም አልነካውም አላልኳትም? ስል ራሴን ሞገትኩት፤ ‹‹አንተ ውሸታም ጧፍ አይደለም ከታቦቱ ጋር ስትጋፋ አላውቅህም›› ሲል ጭንቅላቴ ወቀሰኝ፤ እኔ ዞርም ብዬ አላየዋትም ምናልባት እሷ ግን እየተመለከተችኝ ከሆነ ብዬ ወትሮ አድርጌው የማላውቀውን ወደ ቤተክርስቲያኑ ቅጥር ስገባ ተንበርክኬ መሬቱን ሳምኩኝ ፤ አረማመዴንም አስተካከልኩኝ ፤ ምናልባት ንጽህናዬን ካረጋገጠሊኝ ብዬ፤ ወይ አምላኬ በስንቱ ታስተምረኛለህ? አቤት ይህን ጊዜ ዮሐንስ ሐጺር በኖረ ስል ተመኘሁ፤‹‹የጥበብ መጀመሪያ እግዚያብሔርን መፍራት ነው›› የሚባለው ትርጉሙ ለካስ ይህ ነው፤ በወንጌል ላይ ያለው ቀራጭ ትዝ አለኝ ፤ ጌታ ያመሰገነው፤ከዛ ቀራጭ ግን ይህቺ ሴት ትበልጣለች ፤ እርሱስ ወደ ምኩራብ ገብቶ ነው፤ ይህች ሴት ግን ደጀ ሰላሙ ጋር እንኳን አለቀረበችም፤ እንዲህ ያለ ትህትና እንደምን ያለ ትህትና ነው፤ እንደዚህስ ያለ እግዚአብሔርን መፍራት እንደምን ያለ ፍርሃት ነው፤ በዚህ ዘመን አይቼውም ሰምቼውም የማላውቀው፤ወይ ግሩም።
🙏እስቲ በዚህ ፁሑፍ ራሳችንን እንመርምር !!!
ጌታ ሆይ ትሁት ልብን አድለን!
