ራዕይ ዮሐንስ 20 የንፅፅር ቻናል
Open in Telegram
ይህ ቻናል የተለያዩ በዓለም ላይ የተከሰቱ ክስተቶችን ከኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልዕክት ጋር የሚያነፃፅር ነው። ይህ የዋናው የራዕይ ዮሐንስ 20 ግሩፕ ቅርንጫፍ ቻናል ነው።
Show more8 747
Subscribers
+324 hours
-17 days
-1330 days
Posts Archive
+4
" በድርቁ ምክንያት በደረሰባቸው ከፍተኛ የኑሮ ጫና እና የተስፋ መቁረጥ ስሜት ሰባት ወንዶች በአንድ ቀን መርዝ ጠጥተው ራሳቸውን ለማጥፋት ሙከራ አድርገው የሁለቱ ህይወት አልፏል " - ጃን አሞራ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት
• ከ4 ሺህ በላይ ነፍሰጡርና አጥቢ እናቶች ለምግብ እጥረት ተጋልጠዋል።
• ከ3 ሺህ በላይ እንስሳት በመኖ እና በውሃ እጥረት ምክንያት ሞተዋል።
(ቲክቫህ ኢትዮጵያ)
በሰሜን ጎንደር ዞን በጃና ሞራ ወረዳ የተከሰተው አስከፊ ድርቅ በአካባቢው ማህበረሰብ ላይ መጠነ ሰፊ ሰብአዊ ቀውስ እያስከተለ እንደሚገኝ ተገልጿል።
በወረዳው ስር ከሚገኙ 38 ቀበሌዎች መካከል 18ቱ በድርቅ የተጎዱ ሲሆን፣ በዚህም ምክንያት ከ96 ሺህ በላይ ሰዎች ለከፋ የምግብ እና የውሃ እጥረት ተዳርገዋል
በአካባቢው የተከሰተው የዝናብ እጥረት ለችግሩ ዋነኛ መንስኤ መሆኑን ሃላፊው አመልክተዋል።
በተለምዶ በግንቦት ወር መጀመር የነበረበት ዝናብ እስከ ሃምሌ 19 ቀን ድረስ በመዘግየቱ አርሶ አደሩ ሰብሉን በወቅቱ ለመዝራት አልቻለም።
ተዘርቶ ከበቀለው ሰብልም 4 ሺ ሄክታር የሚሆነው የጠወለገ ነው ያሉ ሲሆን በአጠቃላይ ወረዳው ካለው 26 ሺ 659 ሄክታር የእርሻ መሬት ላይ የበቀለው 12 ሺ 126 ሄክታር የሚሆነው ማሳ የተጎዳ መሆኑን እና ምናልባት ለዘር እና ለመኖ ካልሆነ በቀር ለምግብነት በማይሆን ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።
በተጨማሪም ከ4 ሺህ በላይ ነፍሰጡርና አጥቢ እናቶች ለተመሳሳይ ችግር ተጋልጠዋል።
እስካሁን ባለው መረጃ ከ3 ሺህ በላይ እንስሳት በመኖ እና በውሃ እጥረት ምክንያት የሞቱ ሲሆን፣ ቁጥራቸው ወደ 4 ሺህ የሚጠጉ እንስሳት ደግሞ የተሻለ ሳርና ውሃ ፍለጋ ወደ ጎረቤት አካባቢዎች ተሰደዋል።
+3
በራያ ጨርጨር የተከሰተው ድርቅ‼️
በራያ ጨርጨር የተከሰተው ድርቅ አስከፊ ሆኗል።
ከላይ የሚታየው ምስል ዛሬ ነሐሴ 22/2018 ዓ.ም የተወሰደ ሲሆን የተዘራው ሰብል ሙሉ ለሙሉ እየደረቀ ነው።
ከብቶች በመኖ እጥረት እየሞቱ ይገኛሉ።
+1
" ከሀምሌ አንድ ጀምሮ ባሉት 50 ያህል ቀናት ውስጥ ብቻ 15 ሺ እንስሳት በድርቁ ምክንያት ሞተዋል " - የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት (ለቲክቫህ ኢትዮጵያ)
• በተከሰተው ከባድ የዝናብ እጥረትና ድርቅ ከ95 ሺህ በላይ ነዋሪዎች ለከፍተኛ ችግር ተጋልጠዋል ተብሏል።
በሰሜን ጎንደር ዞን በየዳ ወረዳ ባለፉት ጥቂት አመታት በየተወሰነ ጊዜ ይከሰት የነበረው የዝናብ እጥረት ዘንድሮ በከፋ ሁኔታ ማጋጠሙን ተከትሎ፣ በወረዳው ከሚገኙ 22 ቀበሌዎች መካከል በ18ቱ ላይ ከፍተኛ የድርቅ አደጋ መከሰቱ የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግሯል።
የወረዳው የግብርና ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ገ/ህይወት በላይነህ በተከሰተው ድርቅ ምክንያት በወረዳው ከሚኖሩ 122 ሺህ ነዋሪዎች መካከል ከ95 ሺህ 500 በላይ የሚሆኑት ለከፍተኛ ችግር መጋለጣቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ሃላፊው ገበተለይም በደጋማ አካባቢዎች ቀድሞ መጣል የነበረበት ዝናብ እስከ ሀምሌ 19 ቀን ድረስ በመዘግየቱና አሁንም በተቆራረጠ ሁኔታ በመጣሉ በአካባቢው ግብርና ላይ ከፍተኛ ጥፋት አድርሷል ብለውናል።
እንደ ጽህፈት ቤቱ መረጃ፣ በወረዳው በዘር ተሸፍኖ ከነበረው 17 ሺ 75 ሄክታር መሬት ውስጥ ከ14 ሺህ 375 ሄክታር በላይ የሚሆነው በድርቁ ምክንያት ተመቷል።
ከዚህ በተጨማሪም ከ450 ሄክታር በላይ መሬት ላይ የበቀለው ዘር በመድረቁ ምክንያት ተገልብጦ እንዲታረስ የተገደደ ሲሆን፣ 2 ሺህ 228 ሄክታር የሚሆነው ሰብል ደግሞ ድርቁን ተከትሎ በመጣ የተባይና የበሽታ ወረርሽኝ መውደሙ ታውቋል።
⚠️ GRAPHIC CONTENT - ይህ ቪድዮ አስደንጋጭ እና የሚረብሽ ይዘት ስላለው በጥንቃቄ ይመልከቱ።
በኔፓል እና በቲቤት ድንበር መንደሮችን ጠርጎ የወሰደ እንዲሁም መንገዶችን ያፈራረሰ ድንገተኛ ጎርፍ እና የመሬት ናዳ ምክንያት ቢያንስ 392 ሰዎች ሲሞቱ ከአደጋው ጋር በተያያዘ ከ1400 በላይ ሰዎች ደግሞ የደረሱበት አልታወቀም።
ቪድዮ ፦ ከማህበራዊ ሚዲያ
+2
በኢሮብ ወረዳ 35 ሺህ ህዝብ ለከባድ ድርቅ ተጋልጧል።
በትግራይ ክልል ምስራቃዊ ዞን የሚገኘው ኢሮብ ወረዳ ከባድ ድርቅ እየተጋፈጠ ሲሆን በአካባቢው የሚኖሩ 35 ሺህ የሚጠጉ ሰዎች ለድርቅ አደጋ መጋለጣቸው ተገልጿል።
በወረዳው የክረምት ዝናብ በበቂ ሁኔታ ባለመዝነቡ የውሃ ጉድጓዶች መድረቃቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ገልጸዋል። በውሃ እጥረቱም የቤት እንስሳት መሞት መጀመራቸውን አስረድተዋል።
በወረዳው የሚገኙ ስምንት ቀበሌዎች በከፍተኛ ተራራና ተዳፋት አካባቢዎች መሆናቸው የተጀመረውን የእርዳታ ማዳረስ ስራ ፈታኝ እንዳደረገው ተጠቁሟል።
የአካባቢው አርሶ አደሮች እንደሚሉት፣ ከዚህ በፊት እንደ ዘንድሮ ያለ ከባድ ድርቅ አጋጥሟቸው አያውቅም።
የዝናብ እጥረቱ በማሳ ላይ የተዘራው እህል እንዲደርቅ ከማድረጉም በላይ በክረምት ዝናብ ይሞሉ የነበሩ የውሃ ጉድጓዶች እንዲደርቁ አድርጓል።
